ሐሽማል ቤተ-መዘክር


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Books


👉Only for readers
👋መግቢያ👋
መግቢያ ለመግባቢያ
ገታ አርገነዋል የቃላትን ግልቢያ
እናም በዚህ ሀሳብ ከተስማማህበት
ያንኳኳኸዉን በር የገለፅከዉን ገፅ ፈቅደናል ግባበት
ምንጭ - ካልታወቀ ገጣሚ
Join the group
@amharicbooksforeadersgroup
አድሚኑን በ ቀጥታ ለማናገር ይህንን ቦት ተጠቀሙ @Digitallibraryofhashmal_bot

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Books
Statistics
Posts filter




አታምጣው ስለው አምጥቶ ቆለለው #2

"የገጨሃት ቦታ ውሰደኝ ምናልባት ሰፈሯ ሊሆን ይችላል። ምናልባት ስልኳን እዛ ጥላው ሊሆን ይችላል። የሚያውቃት ሰው ሊኖር ይችላል!"

በውስጤ ምናልባት ጎዳና ላይ ቢሆንስ የምትኖረው ብዬ አስቤያለሁ ጮክ ብዬ አላወራሁትም እንጂ ምናልባት ከነአካቴው ስልክም አልነበራት ይሆናል። መታወቂያዋ ላይ ያለውን ቀበሌና የቤት ቁጥር ተከትዬ ቀበሌ ሄጄ ቤቷን ፍለጋ አስቤዋለሁ። ቀላል እንደማይሆን ግልፅ ነው። ቀበሌ አልወድም!!

"በፍፁም እኔ አልነዳም። ህም ...በጭራሽ መሪ አልይዝም። ታክሲ .....ራይድ ይጠራ" ሲል አሳዘነኝ ማንም ትኩረት ሰጥቶ እሱን ያየው የለም እንጂ እሱም ከባድ ድንጋጤ ላይ ነው። አሁንም እጆቹ እየተንቀጠቀጡ ነው። ሲያወራ መሸሻ ያጣ አይነት ዓይኖቹ መሬቱን ይምሳሉ። ይሄን እያለኝ ድርብብ ያሉ የሴት ወይዘሮ የሚያነክስ እግራቸውን በጌጠኛ ከዘራ እያገዙ የሚራመዱ ሰውዬ አስከትለው ወደ ክፍሉ ገቡ።

"ኪያዬ ......ደስ አላለኝም ! በለሊት አትጓዝ እያልኩህ ...." እያሉ እያገላበጡ ሲስሙት እና ደህና መሆኑን ሲያረጋግጡ ልጃቸው ተገጭቶ እንጂ እሱ ገጭቶ አይመስልም። እሱም እናቱን ሲያይ የሆነው የልጅ መሆን ካቀፍኩት ህፃን አይለይም ነበር። በኋላ እሱም ገብቶት ነው መሰለኝ ከእናቱ እቅፍ ወጥቶ በማፈር ሲያየኝ ነው ገና ሰው እንኳን መኖሩን እናትየው ያዩት።

"እባክሽ ልጄ አንድ ልጄ ነው በሽምግልና እንጨርሰው? (ባጌጠ ልብሳቸው እግሬ ስር ሲንበረከኩ ክብራቸው አላሳሰባቸውም። እናት ናቸዋ! ደንግጬ ደነዘዝኩ። ካሰብኩት በላይ ውጥንቅጥ ውስጥ እንደተዘፈቅኩ ገባኝ። ከተንበረከኩበት ላነሳቸው እየሞከርኩ ከአፌ ግን ቃል አይወጣልኝም።) ካሱ የምንባለውን እንክሳለን። እናትየው እስኪሻላት ህፃኑንም ቢሆን ወስጄ እንከባከባለሁ። እባክሽ ልጄን አሳልፈሽ አትስጪብኝ?"

ለደቂቃ ህፃኑን ሰጥቻቸው ጭልጥ ብዬ መጥፋት ሁሉ አሰብኩ። ባባ ቀልቡ የነገረው ይመስል ጭምቅ አድርጎ አቀፈኝ። የተገጨችው እህቴ ብትሆን ምንድነበር የምወስነው? ብትሞት የእነሱ ካሳ የህይወት ካሳ ይሆናል? እሺ ጥፋቱ የሷስ ቢሆን? እንዳለው እሷ ብትሆንስ ዘው ብላ የገባችበት? ኸረ ምን አይነቷ ሴት ናት ግን እዚህ ጣጣ ውስጥ ዘፍቃኝ ማን እንደሆነች እንኳን የማላውቃት

"እባኮትን ይነሱ። እኔ ለራሴ ዞሮብኛል።"

የተፈጠረውን አስረዳኋቸው። አባትየው መታወቂያው ላይ ባለው አድራሻ ቤቱን ሊያፈላልጉ ሀላፊነት ወሰዱልኝ። ማን እንደሆነች እና ከእኔጋር የሚያዛምዳትን ነገር እስክደርስበት ባባ እኔጋ እንዲቆይ ወሰንኩ። እነርሱም የሚያስፈልገውን ሊያሟሉለት እና ሊጠይቁት ቃል ገቡልኝ። አንድ ላይ በእነርሱ መኪና እናትየው እየነዱ አደጋው የደረሰበት ቦታ ሄድን:: ምንም ነገር የለም። ከአልፎ አልፎ ሂያጅ መንገደኛ ውጪ በአካባቢው ማንም አይታይም። የመኖሪያ ሰፈርም አይደለም። ዓይኔ መሬቱ ላይ ካለ አንድ ብር ሳንቲም ላይ አረፈ። ደም ነክቶታል። ለምን እንዳነሳሁት አላውቅም ግን አነሳሁት። የሷ ይሆን? በእጇ ይዛው ነበር? ወድቆባት ልታነሳ ስትል ይሆን መኪናውን ያላየችው? ወይስ ሌላ ሰው የጣለው ሳንቲም ነው? ስልኬ ሲጠራ ባላወቅኩት ምክንያት ደንግጬ ዘለልኩ

"አይዞሽ አይዞሽ" አሉኝ እናትየው መደንበሬን ሲያዩ

"እማ በጠዋት የት ሄደሽ ነው? " ልጄ ናት። ቤቴን ረስቼዋለሁ። ሰዓቱን ረስቼዋለሁ። ዛሬ ቅዳሜ መሆኑንም እረስቼዋለሁ።

"መጣሁ እናቴ! ለባብሰሽ ጠብቂኝ" አልኳት ቅዳሜ ጠዋት ሁል ጊዜ እናትና አባቴ ጋር ነው ቁርስ የምንበላው።

እነርሱ ስልክ ተቀያይረን እቤት አድርሰውኝ ተመለሱ። የማልዋሸው በዛው ቢጠፉስ ብዬ አስቤያለሁ። ሰው ለማመን ቅርብ አይደለሁም። የመኪና ታርጋቸውን መዝግቤ መታወቂያቸውን ፎቶ ኮፒ አደረግኩ።

"እማ ትልቅ ሰው የሚበላውን ምግብ ይበላል ኸረ ጥርስኮ አለው" ትለኛለች ልጄ ለባባ ምግብ ምን ልስጠው ብዬ ስባዝን እየሳቀችብኝ። ልጄ 15 ዓመቷ ነው። በስንት ዓመቷ ምን እንደበላች ጠፍቶኛል። ለመጨረሻ ጊዜ ገላዋን መች እንዳጠብኳት ረስቼዋለሁ ..... ባባን አጣጥቤ እነእማዬጋ ተያይዘን ሄድን::

"እግዚአብሄር የሆነ ነገር ሊያስተምርሽ ነው ይሄን ህፃን ወደ ህይወትሽ ያመጣው" አለችኝ እናቴ የሆነውን ሁሉ ከነገርኳቸው በኋላ። ከቤተሰቡ አንድ ሰው እንኳን ድንገት ቢያውቃት ብዬ አስቤ ነበር:: ማንም አያውቃትም። (እናቴ ምን ማለቷ እንደሆነ አውቃለሁ። ማግባት አለብሽ ልጅ መድገም አለብሽ ነው ቅኔው። ወንድሜ በሚያስቀና ትዳር ሶስተኛ ልጁን ሰልሷል። የእኔ ያለባል መቅረት ያሳስባታል:: )

"እማ ደግሞ እግዚአብሄር እኔን ስለሚወደኝ እኔን ለማስተማር ይሄን ህፃን አይቀጣም! የሆነችን ሴት በመኪና አስገጭቶ ለኔ ትምህርት አይሰጥም። እነርሱምኮ ፍጡሮቹ ናቸው እኔን ለማስተማር ህይወታቸውን የሚያዘባርቅባቸው አሻንጉሊቶች አይደሉም!!" አልኳት። ወንድሜና አባቴ ተያይተው ጨዋታውን ቀየሩት። ከእማዬጋ እንዲህ አይነት ወሬ ከጀመርን ማባሪያ የሌለው ጭቅጭቅ እንደሆነ ያውቃሉ:: እዛው ቤተሰቦቼ ቤት ሆኜ ወደ ከሰዓት ስልኬ ጠራ ባባ ኩርምት ብሎ ከተኛ ሰዓታት አልፈውታል።

"አብርሃም ነኝ"

"አብረሃም? አብረሃም?"

"የግሩም አባት! ልጅቷን የገጫት ልጅ አባት... "
"እእ ....እሺ "

"የምትኖርበትን ቤት አግኝተነዋል። አከራዮችዋን አናግረን የእሷ ቤት መሆኑን አረጋግጠናል።"

"በዚህ ፍጥነት? እንዴት? ያውም በቅዳሜ?"

"ብዙም አስቸጋሪ አልነበረም:: የቤት ቁጥሩ የአከራዮችዋ ቤት ነው:: ደግሞስ የልጄ ጉዳይ አይደል? ይልቅ መምጣት ሳይኖርብሽ አይቀርም። ከባሏ ውጪ ማንም ዘመድም ሆነ የቅርብ ሰው እንደሌላት ነው የነገሩን።"

"ታዲያ ባሏ እያለ እኔን ምን ቤት ናት ብላ ነው የፃፈችኝ?"

"ባሏ ከታሰረ ሁለት ዓመት አልፎታል።"

"እሺ እኔ ምን ቤት ነኝ መታወቂያዋ ላይ የተገኘሁት? ወይ ፈጣሪ ! "

"እኔ ምን አውቄው ብለሽ? (እኔ አልፃፍኩሽ የሚል አንድምታ ባለው ለዛ) ምናልባት በባለቤትዋ? እስር ቤት ያለ የቅርብ ሰው ወይ ዘመድ የለሽም?"

"በፍፁም ኸረ እኔ ጭራሽ የታሰረ የሩቅም ሰው አላውቅም። "

"ምናልባት አከራዮችዋ ከሚነግሩሽ ነገር ፍንጭ ልታገኚ ስለምትችዪ ብትመጪ መልካም ይመስለኛል:: ብዙ አመት ኖራለች አብራቸው.... እ.... ባለቤቷ ... አሸናፊ ይባላል ነው ያሉኝ .......እንደው ካወቅሽው "

ከጀርባዬ የሆነ ነገር ማጅራቴን በሀይል የደለቀኝ ነገር መሰለኝ .........ጭው አለብኝ። አይሆንም። እሱማ አይሆንም! ሊሆን አይችልም።... ስም ተመሳስሎ ነው.... ማሰብ ተሳነኝ!!

"ምነው ሴትየዋ ሞተች እንዴ?" ትለኛለች የወንድሜ ሚስት ......

ይቀጥላል
#Meri Feleke
https://t.me/amharicbooksforeaders


አታምጣው ስለው .... አምጥቶ ቆለለው (ርዕስ ነው)

የስልኬ ጥሪ ነው ከእንቅልፌ የቀሰቀሰኝ። ከንጋቱ 12:10

"ከሆስፒታል ነው የምንደውለው!! ዶክተር ፈቃደ እባላለሁ።"

"በየሱስም! እናቴ ምን ሆነች?" ብድግ ብዬ ቁጭ አልኩ:: ማታ ስኳሬ ከፍ ብሏል ስትለኝ ነበር።

"ወይዘሮ ሄለን አበራ አደጋ ገጥሟቸው ...."

"ሄለን አበራ? በስመአብ! (ልቤ ጉሮሮዬጋ ደርሳ ነበር ምልስ ብላ አቃፊዋ ውስጥ ስትገባ ታወቀኝ) ምነው እያጣራችሁ ብትደውሉ? በዚህ ጠዋት ያልታመምኩትን ሴትዮ በድንጋጤ ልትገሉኝ ነው እንዴ? ተሳስታችኋል!! እኔ ሄለን አበራ የምትባል ሴት አላውቅም! "

"ወይዘሮ ፌቨን አዳነ አይደሉም?"

"ነኝ!" አሁን ግራ ገባኝ። ስልኬን ቢሳሳት ስሜን ግን አስተካክሎ ሊጠራ አይችልም።

"የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ተብለው የተመዘገቡት እርሶ ኖት!" ከአልጋዬ በደመነፍስ ወረድኩ

"እህ እኔ እንዲህ የምትባል ሴት አላውቅማ? ቆይ የሆነውን አስረዳኝ ምን አይነት ሴት ናት? ምን አይነት አደጋ ነው የገጠማት?"

"የመኪና አደጋ ነው። ለጊዜው conscious አይደለችም:: ቦርሳዋ ውስጥ ባገኘነው መታወቂያ ላይ የእርሶን ስልክና ስም ነው ያገኘነው።"

"እሺ መጣሁ!" አልኩኝ ነገሩ ምንም ስሜት ሳይሰጠኝ ..... አደጋ ደርሶ ነው እየተባልኩ ከዛ በላይ ጥያቄ ማብዛት ክፋት ነገር መሰለኝ። የእኔን ስም የአደጋ ጊዜ ተጠሪ ብሎ ሊመዘግብ የሚችል ዘመድ አሰብኩ ........ ምናልባት በቤት ስሟ የማውቃት ዘመድ ..... ጭንቅላቴ እዚህም እዛም እየረገጠ የተባልኩት ሆስፒታል ደረስኩ እና የተባለውን ዶክተር አገኘሁት። የተባለችው ሴት የተኛችበት ክፍል ወሰደኝ። ሰውነቷ በአብዛኛው በፋሻ ስለተጠቀለለ የማውቃት ሴት እንኳን ብትሆን መለየት አልችልም ነበር።

"የማውቃት አይመስለኝም!" አልኩት ግራ ገባቶኝ። ከጋውን ኪሱ መታወቂያዋን አውጥቶ ሰጠኝ። ሲገለባበጥ ሌላ ምስል ያሳየኝ ይመስል እያገለባበጥኩ አየሁት። በፍፁም አላውቃትም! ስሜና ስልክ ቁጥሬ ግን የመታወቂያው ጀርባ ላይ ቁልጭ ብሎ ተፅፏል። እድሜ 30 .... ቆንጅዬ ወጣት ናት። ፎቶዋ ላይ ጥርሷን ሳትገልጥ ፈገግ ብላለች። በወፋፍረሙ ተገምዶ ደረቷ ላይ የተዘናፈለ ፀጉር አላት ..... በፍፁም አይቻት አላውቅም።

"ማነው ሆስፒታል ያመጣት?" አልኩኝ ትክክለኛ ጥያቄ ይሁን ሳልረዳ

"አደጋ ያደረሰባት ሰው ነው ይዟት የመጣው። መጠበቂያ ክፍል ተቀምጧል ልታገኚው ከፈለግሽ? " ብሎ መልሴን ሳይጠብቅ በሩን ከፍቶ ወጣ ተከተልኩት የተባለው ሰው ከዶክተሩ ጋር ወደክፍሉ ስገባ ሲያየኝ ዘሎ ከመቀመጫው ተነሳ ..... አጠገቡ ተቀምጦ የነበረ በግምት የ4 ዓመት የሚሆን ህፃንም ተከትሎት ብድግ አለ።

"ቤተሰቧ ነሽ? ምን ማድረግ እንደነበረብኝ አላወቅኩም ነበር! እጄን ለፖሊስ ልስጥ? እሰጣለሁ በቃ! (መላ አካሉ ይንቀጠቀጣል።) ከየት መጣች ሳልላት ነው ዘው ብላ የገባችብኝ በቦታው የነበረ ሰውም አልነበረም። አልነጋምኮ .... የሞተች መስሎኝ ነበር !" ድንጋጤው እንዳለ ነው የለበሰው ጥቁር ሱፍና ነጭ ሸሚዝ በደም እንደተነከረ ነው። እጆቹ ላይ የቀረውን የደረቀ ደም ሊጠርገው ግድ ያለው አይመስልም ወይም ከነጭራሹ ደም እጁ ላይ መኖሩንም አላስተዋለውም። ግራ ገባኝ። ምንም በማላውቀው ክስተት ውስጥ የተነከርኩት እኔ ምን ልበል? አይኖቼ ህፃኑ ላይ መንቀዋለላቸውን ሲያይ

"ልጇ ነው። አብረው ነበሩ። እማ ብሎ ሲጮህ ነው ያየሁት እኔ እንጃ ምን እንደተፈጠረ። እሱ የእግረኛ መንገድ ላይ ነበረ። ቤተክርስቲያን እየሄዱ መሰለኝ ነጠላ ለብሳ ነበር። .... ቤተክርስትያን ለመሄድ ራሱ በቅጡ አልነጋም ነበር:: "

ምን እንደማደርግ ሳላውቅ ህፃኑጋ ተጠግቼ በርከክ አልኩ። ደነበረ። ትንንሽ እጆቹን ልይዛቸው እጄን ስዘረጋ ሰበሰባቸው።

"ስምህ ማነው?" አልኩት እናቱን መኪና ሲገጫት በአይኑ ካየ ሁለት ሰዓት ላልሞላው ህፃን የእኔ ጥያቄ ምኑ ነው? እኔስ ምኑ ነኝ? ዓለምስ ራሱ ምኑ ናት?

"ባባ" አለኝ የደረቁ ከንፈሮቹን እያላቀቀ

"ባባዬ እኔን ታውቀኛለህ?" አልኩት የማይጠየቅ ጥያቄ እንደሆነ እያወቅኩ። በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ።

"አባትህ የት እንደሆነ ታውቃለህ?" አሁንም በአሉታ ጭንቅላቱን ነቀነቀ። ግራ ገባኝ! ይህቺ ሴት ማናት? ለምንስ ነው የማላውቃት ሴት መታወቂያ ላይ የእኔ ስም የሰፈፈረው?

"ዶክተር እሷ ያለችበትን ሁኔታ ንገረኝ? ትድናለች አይደል? " እንድከተለው ምልክት ሰጥቶኝ ወደ ቢሮ ይዞኝ ሄደ። ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢ እንደሆነ ለመገመት አልተቸገርኩም።

"ተጨማሪ ምርመራዎች አዝዣለሁ። ውጤቶቹ እስኪመጡ እርግጠኛ የሆነ ምላሽ ልሰጥሽ አልችልም። ጭንቅላቷ በሃይል ተጋጭቷል። እንዳልኩሽ ሁሉም ውጤት ሳይመጣ ብዙም ማለት አልችልም።"

"የምትድን ይመስልሃል ግን? የምትነቃ ይመስልሃል?"

"ይቅርታ ይሄን አሁን መናገር አልችልም።"

"እሺ እኔ ምን ላድርግ? አላውቃትምኮ? ህፃኑንስ ምን ላድርገው? ምን ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት?"

"የማታውቂያት ከሆነ ሆስፒታሉ ለፖሊስ የማሳወቅ ግዴታ አለበት" አለኝ። አላውቃትም ያልኩትን ግን ያመነኝ አይመስልም።

"እሺ የገጫትስ ሰውዬ?"

"ቤተሰብ ቢገኝ ወይ በሽምግልና ያልቃል ወይ ይከሱታል። እንደምትዪው የማታውቂያት ከሆነ ጉዳዩን ለፖሊስ ማሳወቅ ግዴታችን ነው። ሰውየው የማምለጥ ሀሳብ የለውም። ሲገጫት ማንም አላየውም ጥሎ መሄድ ይችል ነበር። ይልቅስ ያላነሰ ብር ከፍሎ የግል ሆስፒታል ሊያሳክማት ፈቃደኛ ከሆነ በህግ ይዳኝ በሽምግልና ቤተሰብ ነው የሚወስነው።"

ሁሉንም ጥዬ መሄድ ፈለግኩ። ምን አገባኝ እና ነው እዚህ ጣጣ ውስጥ የምገባው ብዬ ..... ወደመጠበቂያው ክፍል ስመለስ ህፃኑ የምስራች የምነግረው ይመስል ከተቀመጠበት ዘሎ ተነስቶ በተስፋ አይን አይኖቼን ሲያየኝ እግሬ የሚቀጥለውን እርምጃ መራመድ አቃተው:: አጠገቤ ደርሶ ትንሽዬ ፊቱን ወደ ላይ አንጋጦ እያየኝ ሊያለቅስ ጉንጩ እየተንቀጠቀጠ

"እማዬስ?" አለኝ:: እንባው ከፊደሎቹጋ ከአይኑ እየወረደ..... ከሱ ብሼ እንደህፃን ማልቀስ አማረኝ:: አቅፌ ብድግ እያደረግኩት በዛች ቅፅበት አብሬው እማገዳለሁ እንጂ እሳት ውስጥ ጥዬው እንደማልሄድ አወቅኩ። ...

ይቀጥላል ........

#Meri Feleke

“ሼሪንግ ኢዝ ኬሪንግ” ይላሉ ፈረንጆች
❤️❤️ሼር ማድረግ እንዳይረሳ❤️❤️
https://t.me/amharicbooksforeaders




"እንኳን ነገር አበረድሽ ቢያንስ ተረጋግተሽ ተመረቂ! እኔማ በእልህ ከአሁን አሁን የሆነ ነገር አደረጋት ብዬ

ሌት ተቀን አምላኬን ስወተውት ነው የማድረው!" አለችኝ። እንደባልና ሚስት ሳይሆን እንደ ፍቅረኞች ነገር ሆንን ..... ያለፀብ አለቀ እና ልንመረቅ አንድ ቀን ሲቀረን አብረን አደርን!!

በነገታው እነማሚ መጡ ልጃችን ልታስመርቀን መጣች። ተመረቅን!! እንደማንኛውም ተመራቂ ተማሪ ፊታችን እስኪገረጣ ፎቶ ስንነሳ ዋልን!! እንዳሰብኩት በማእረግ ባልመረቅም በሚያኮራ ውጤት ተመረቅኩ። በምወዳቸው ሁሉ ተከብቤ ያ የናፈቅኩት ቀን ሆነ!! በሚቀጥለው ቀን ቤተሰቦቼን ሸኝቼ ዶርም ተመለስኩ። ለማንም ምንም ሳልል እቃዬን ሸካክፌ ወደአዲስ አበባ ......... ለማሚ ያለሁበትን ለማንም እንዳይናገሩ አስጠነቀቅኩ። ብዙም ሳልቆይ የግል ዩንቨርስቲ ማስተማር ስራ ጀመርኩ።

በወሩ ደወልኩለት።

"ማወቅ ስላለብህ ልንገርህ ብዬ ነው። ፍቅርን አርግዣለሁ!" አልኩት። ደስ አለው። እብድ ናት በሉኝ በማርገዜ ደስታዬን ብታዩት። ከእርሱ ውጪ ከሌላ ወንድ ልጅ መውለድ አልፈልግማ!!

"የት ነሽ?" ቦረቀ። "ላግኝሽ? We can fix this eko ልጆቻችንን አብረን እናሳድጋለን አይደል? "

"ልጆቻችንን እናሳድጋለን። እኔና አንተ ግን አንድ ላይ ሆነን አይደለም። ልጅህን መጥተህ እንድታይ ስወልድ አሳውቅሃለሁ። በልጆችህ ህይወት ውስጥ እንደፈለግክ ሁን አባታቸው ነህ። በእኔ ህይወት ውስጥ ግን አይደለም።" አልኩት።

happily divorced

እና ዛሬ ላይ ለልጆቼ ሳወራላቸው እንዲህ ነው የምላቸው

"እንዳባታችሁ ያፈቀረኝ ወንድ የለም! ወደፊትም አይኖርም። እንዳባታችሁም ደግሞ የጎዳኝ ወንድም የለም። ....... አባታችሁ ጣኦቴ ነበር። በምድር ላይ ትልቁን ስጦታዎቼን እናንተን ሰጥቶኛል። በእናንተ ደግሞ ደስተኛ ሴት አድርጎኛል። መልካም ነገር ብቻ ይግጠመው።"

................ጨርሰናል🤗 ........


#Meri feleke


ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!!
ክፍል 12
(የመጨረሻ ክፍል)

ጉንጬን ከነደሜ አንገቴን ይስመዋል። ከሰከንድ በፊት 'ምንዓይነቱ ነው?' ሲሉ የነበሩት 'ምፅ ምፅ ሲያሳዝን' አላሉም? በዚህ መሃል ማን መጣ ያ ያባለገኝ ልጅ ባልየው ልክ ሲያየው አወቀው መሰለኝ እኔን እንዳይለቅ እኔ ሆንኩበት ዝም እንዳይል እሱ ሆነበት። በቃ ቆንጆ ቲያትር ተፈጠረ።

"አንተ እናትህ ..... አገኝሃለሁ!!" ያኛው ለራሱ አንድ ሁለት ብሏል መደንፋት።

"ማነኝ ነው የምትለው?" የነበረው ተማሪ የተፈጠረው ሳይገባው ያኛውን ይይዛል ይመስለኛል። እኔ ለራሴ ምንም እንዳልል ልሳን ላይ ነኝ የባሌንና የልጁን ድምፅም መለየት እራሱ እየቸገረኝ ነበር። ፖሊስ መጥቶ እኔ ወደሆስፒታል እሱ ወደፖሊስ ጣቢያ ሄድን። አይኔ ስር ስቲች ተደረግኩ። (ይሄ ምልክት አሁንም ድረስ አይኔ ስር አለ። አዳሜ እየገባሽ ፎቶዬን ዙም አድርጊ አሉሽ!)

እና ከዚህ በኋላ ፍቅር ተወለደ ነው የምትዪው? አላችሁኣ? ግድ የላችሁም እንቀጥል። እኔኮ የብዙ ሰው ህይወት የኖርኩ ነው የሚመስለኝ የምላችሁ ለዚህ ነው።

በነገታው ማሚ እኔጋ ስትደውል ስልኬን አላነሳሁላትም አንድ ጓደኛዬጋ ስትደውል የተፈጠረውን ነገረቻት። እኔ መስማቷን እንኳን ከማወቄ ማሚ መጥታለች። ማታ አሳድረውት ፖሊሶቹ ለቀውት ነበር እሱን። ማሚ ቀወጠችው። ሴቶች ጉዳይም አይደለች? ደዋወለች። አሳሰረችው። እኔጋ ስትመጣ ግን ከፍቷት ነው የደረሰችው።

"ምነው?" ስላት

"ባልሽ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ? "

"ምን አለሽ?" (ምንም ቢል የምገረም ይመስል)

ልጄን ይገድላታል ብላ ስትቀውጠው። "ሞታም ቢሆን ዘግይተሽ ነው የደረስሽውኮ ታዲያ አንቺ አታስጥያትም ማሚ በሷና በኔ መሃከል አትግቢ!" ብሏት ነው የምትብሰከሰከው። ትምህርት ቤት በዶርሜም አካባቢ ሆነ በክላሴ አካባቢ ብቻ እኔ ባለሁበት አቅራቢያ እንዳይገኝ ታገደ እና ከቀንት በኋላ ተለቀቀ። ሁሉም እንደነበረ ቀጠለ። ማሚም ተመለሰች። እኔም ትምህርቴን ቀጠልኩ። ከዛ ልጅጋም እንደነበረ (ምን እንደነበረ መድሃንያለም ይወቀው ) የነበረውን ቀጠልን። የሆነ ቀን ስልክ ደወልኩለት ለልጁ

"ና በናትህ ወክ እናድርግ!" አልኩት ስልኩን እንዳነሳ

"ገምቺ የት እንደሆንኩ?"

"እኔንጃ የት ትሆናለህ? መሽቷልኮ!"

"እቤትሽ ከባልሽ ጋር !" ቀልድም መሰለኝ።

"አንተ በማይቀለድ ነገር አትቀልድ!"

"እግዚአብሄርን የምሬን ነው።" ጠላታችሁ ክው ይበል። (አሁንም እማጅኑልኝ ያባለግኩት ልጅና ባሌን አንድ ቤት።)

"ይገድልሃል!! እየቀለድኩ አይደለም ይገድልሃል!" አልኩት

"እየጠበቅኩት ነው!.... ተፋጠን ነው ዛሬ የምናድረው!! ነገ ጊቢ ስመጣ ደውልልሻለሁ።" ይለኛል እየሳቀ

"እኔ አንተን ብሆን እዛች ቤት አላድርም።"
ስልኩን ዘግቼው ምን ማሰብ እንዳለብኝ ግራ ገባኝ። ምንድነው ሁለቱን አንድ ቤት የሚያሳድራቸው? ወይ አንደኛው አጋች አንደኛው ታጋች ሆነው ካልሆነ በቀደም እኔ እየደማው እናቶቻቸውን በብልግና ሲቀባበሉ የነበሩ ሰዎች አንድ ቤት ማደር? ይሄ በዓለምም የትኛው ልብ ወለድ ውስጥም የለም። ይሄ የተከሰተው እኔ ቤት ብቻ ነው። እንደ ቅዠትም እንደዱካክም እንደመባነንም እንልክፍትም ሲያደርገኝ አደርኩ።

በነገታው እንዳለውም ደወለልኝ። የምናወራው ጉዳይ አለ ብሎኝ ተያይዘን ፀጥ ያለቦታ ሄድን። ከትናንት ወዲያ ነገር ይኸው ራሱ ጉድ ወድጄሻለሁ ብሎኝ ነበርኮ ዛሬ መጥቶ "ከባልሽ ጋር ታረቂ!" ብሎኝ እርፍ!! ለልብወለድነት ሁላ አይሆንም አላልኳችሁም? የእውነት ዞረብኝ! ተጋድለው እሁድ ፖሊስ ፕሮግራም ላይ ቀርቤ "ሁለቱንምኮ እወዳቸው ነበር .... ጌታ ለእኔ ባይላቸው ነው ..... ፎሊስ ምን ታደርገዋለህ? " ምናምን ብዬ ቃሌን ሰጠሁ ስል አጅሬዎቹ ፍቅር በፍቅር ሆነው አይዞህ ሲባባሉብኝ ነው ያደሩት!

"ማንም ሰው እንዲህ አይወድም ሜሪዬ ግፍ ነው። በስመአብ እኔ እንዲህ ዓይነት ፍቅር አይቼ አላውቅም!! የትኛውም ወንድ ወንድነቱን ውጦ ከሚስቱጋ ያለ ወንድ አስታርቀኝ አይልም። የመጨረሻ ይወድሻል።"

"ሚስቱ አይደለሁም! ሚስትህ አይደለችም ስትለው የነበርከው አንተ አይደለህ እንዴ?"

"ለሱ አሁንም የሚወዳት ሚስቱ ነሽ!! ሜዬ አሁን አንቺን አጥቶ መኖር ምን ማለት እንደሆነ በጣም ተምሯልኮ አንድ እድል ስጪው!" በአንድ ለሊት ሚኒ ባሌን ሆኖ ብቅ አለልኝ። ስለሌላ ሰውም እያወራ ወይም እሱም ሌላ ሰው ነው የመሰለኝ ሳቅኩኝ

"በቀደም መስሎኝ በቦክስ ያነጠፈኝ .....ይታይሃል ? ፊቴ ገና አልጎደለም። ተለውጧል? ቆይ ምን ቢልህ ነው?"

"እንዴ እሱማ በቃ ቀንቶ ነው። ደግሞ የዛን ቀን የመጣው እኔን ሊጣላ እንጂ ካንቺጋ ሊጣላ አልነበረም። ከወንድ ጋር ሲያይሽ ደሙ ፈልቶ ነው በዛ ላይ አንቺ አጋጋልሽ! " (ወንዶችኮ ግን አትስማሙ።)

"እ........ሺ?" ደንቆኝ ነው የማየው። "የምልህ ቆይ አንተ በቀደም ወድጄሻለሁ ስትለኝ አልነበር? "

"እግዚአብሄርን ነው የምልሽ እሱ የሚወድሽን እሩቡን አልወድሽም። ደሞ ሀጥያት ነው እንደዛ እየሆነልሽ እያወቅኩ ለራሴ አላዳላም።"

ነግሬአችኋለሁኮ ከኔጋ አብረው ሲያለቅሱ የቆዩ ጓደኞቼ እሱ መጥቶ "እሷ ማለት ለእኔ የህይወቴ ካስማ ብሎ ..." እትት ብትት ሲል በግልምጫ የሚያፈርጡኝ ሰው ነኝ። የሚገርመኝ ያጠፋው እሱ ከሆነ ጥፋቱን አያስተባብልም። የሚናገርበት መንገድ ግን በቃ ለመኮነን አይመችም። የተፈጠረውም እንደዛ ነው። በጉልበት የሚሆን ነገር እንደሌለ ሲገባው ቢያንስ የተሻለ ብሎ ያሰበው መንገድ ይመስለኛል ልጁን ጠርቶ ማናገር ነው። ከዛ ያው ጠርቶ አጥምቆ ላከልኝ። ከቺኩጋ ተጣልቶ ትታው ሄዳለች።

ብቻ ለሌቱን ሙሉ ሲባባሉ ያደሩትን ሲነግረኝ እኛም ልናድር ሆነ። የታሸገ ነገር ሰጥቶኝ ተለያየን። ገብቼ ስከፍተው ቀለበቴ ነበር።

እዚህጋ የተሰማኝን ወይም የሚቀጥለውን እርምጃ እንዴት እንደተራመድኩ ምክንያቴን ልፅፍላችሁ የምሬን አሰብኩትኮ። አላውቅም! ምናልባት እዚህኛው ጊዜ ላይ ቡረቃም ህመምም ስለሌለው ይሆናል ትዝ አይለኝም ምን አስቤ እንደነበር። ኤጭ በሉና ተዘጋጁ አንዴ .......

የሆነ ቀን ልንመረቅ አንድ ወር ሲቀረን ይመስለኛል። እሱም የተወሰነ ኮርስ እየቀረው አብሮኝ ተመራቂ ነበር። ብድግ ብዬ ብቻ ቀለበቴን አደረግኩት። ተነስቼ እቤት ሄድኩ። በቃ ሄድኩ አልኩኮ .......

ምንም እንዳልተፈጠረ...... ይቅርታ የለ ...... መወቃቀስ የለ ....... ልክ ትናንት ተገናኝተን እንደነበር ሁላ ጨዋታ ጀመርን:: ስገባ ሲያየኝ የነበረው ፈንጠዝያ እንዳለ ሆኖ ...... ወላ

"ቺኳ ጎበዝ ናት አንተ ቤቴን አሪፍ አድርጋ ነው የያዘችው!" ሁላ አይነት ወሬ ነበረው። የገዛነውን መሬት እንደሸጠው ነገረኝ ሚስት ሚስት አልሰራራኝም። ይመችህ አልኩት።

"አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው እሱን የወደድሽው ሎቲ የሚያደርግ ወንድ አትወጂም አልነበር?"
(ሲቆይ ጆሮዬን ልበሳልሽ ከወደድሽ ብሎኛልኮ)

"አንተ ግን በጣም ከሳህኮ እህል አታበላህም ነበር እንዴ?" (እኔምኮ ከስቻለሁ ከዛ በላይ የሚከሳ ቀሪ ስጋ ስላልነበረኝ እንጂ)

"በቃ እስክንመረቅ ለምን አብረን አንሆንም?"

"እንዲህኮ ደስ ስንል" ምናምን ተባብለን ወደ ዶርም ተመለስኩ።

ምንም ሳይጨመር ሳይቀነስ በቃ እንዲህ ነው የሆነው። ዶርም ስመለስ ሁሉም ሊበላኝ በጣም የገረመኝ ማሚ ታብዳለች ብዬ ስጠብቃት።


ሁለቱ ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው አንድ ክፍል ነው የቀረው ........ ምን የሚሆን ይመስላችኋል ?
Poll
  •   ይቅር ብላው ድጋሚ የሚታረቁ
  •   የሚለያዩ
  •   ለመገመት ይከብዳል
57 votes


በልብሱ ደሜን ከፊቴ ላይ ይሞዥቀዋል። በዛ ላይ እንባው ደግሞ እኔን መልሶ ያወራኛል። "እማ እኔኮ እንዲህ ላደርግ አይደለም የመጣሁት የነበረው ምዬ ነበርኮ አልነካትም ብዬ ምዬ ነበርኮ !" ደግሞ በዚህ ሁሉ መሃል መሳምም አለው። ጉንጬን

ከነደሜ አንገቴን ይስመዋል። ከሰከንድ በፊት 'ምንዓይነቱ ነው?' ሲሉ የነበሩት 'ምፅ ምፅ ሲያሳዝን' አላሉም?

........ አልጨረስንም ......

#Meri feleke


ሁለቱ ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል 11)

"እሺ እንለያይ!" አለኝ የምር ማመን አቃተኝ።

"ከምርህን ነው? ያ ማለት አትከታተለኝም? የፈለግኩትን እሆናለሁ ማለት ነውኣ? እንደመንፈስ ዙሪያዬ አታንዣብብም። አብሮኝ የታየ ወንድ አትደበድብም? "

"አዎ አጠገብሽ አልደርስም። እንደፈለገሽ ሁኚ ቃሌ ነው። ብቻ እንደማፈቅርሽ እወቂ!" አለኝ

"እንደምታፈቅረኝ ጠርጥሬ አላውቅም። ችግሩ ፍቅርህን የምትገልፅበት መንገድ ልክ አይደለም። 24 ሰዓት ሙሉ አይንህ ስር የምትሆን ከማንም የማትገጥም ሴት እኔ መሆን አልችልም። ስታገኘኝ ያቺን ሴት አልነበርኩም። ስትወደኝ ያቺን ሴት አልነበርኩም። ያንተ ካደረግከኝ በኋላ ሌላ ሴት አድርጌ ልስራሽ ብለህ ትግል ነው የያዝከው። አይሆንም!" አልኩት

"አውቃለሁ" አለኝ። ተለያየን። ተለያየን ስላችሁ መቶ ጊዜ መተቃቀፍ መቶ ጊዜ መሳሳም እንደነበረውም አልደብቃችሁም። ለቅሶም ነበረው ከፈለጋችሁ። ለተወሰኑ ቀናት ማመን አቅቶኝ በየሄድኩበት ድንገት ዱብ ይል እንደው ብዬ እፈልገዋለሁ። የለም። ማታ ትምህርት ቤት ሲገባ ድንገት ከሆነ ሰው ጋር ካየኝ ፈነዳ ብዬ ብጨነቅም የለም። አልከፋኝም። ይልቅስ ነፃነት ተሰማኝ። በቃ ተለያይተናል። የምጠቀመው እሱ የሚሰራበት ባንክ ስለሆነ የሆነ ቀን ስሄድ የለም። ጓደኞቹን ስጠይቃቸው ስራ መልቀቁን ሰማሁ። የሆነ ቀን የጋራ ጓደኛችን ትምህርቱን ለሴሚስተር ዊዝድሮ ሞልቶ አዲስ አበባ ለእረፍት መሄዱን ነገረኝ። ጣዖቴ እንደነበረው ባሌ ሳይሆን እንደሰው አዘንኩ። እንዴት ስራ ይለቃል? እንዴት ትምህርቱን ያራዝማል?

ከአንድ ሴሚስተር በኋላ ባሌን ከተማ አየሁት። በጣም ከስቶ ጠቁሮ አምስት ወር ሳይሆን 5 ዓመት ያልተያየን ነበር የመሰለኝ።

"በየሱስ ስም ደህና ነህ?" አልኩት ደንግጬ ሳየው

"ደህና ነኝ!" አለኝ። "እቤት ሄጄ ነበር። ከቤተሰቤጋ ከሀ ለመጀመር እየሞከርኩ ነው። ቢያንስ አሁን ጴንጤ ስላልሆንኩላቸው ደስተኛ ናቸው!" አለኝ። ደስ አለኝ ያ የህይወቱ ጉድለት እንደሆነ አውቅ ነበር።

"አሪፍ አደረግክ!" አልኩት። እኔም የማውቃትን ደብዳቤ ፅፋለት አጊንቼ የተጣላሁትን ሴት ስም ጠቅሶ (የድሮ ፍቅረኛው ነበረች። ቤተሰቦቹ የሚወዷት ፍቅረኛው ነበረች።) ከሷጋ እንደሆነ ነገረኝ። እውነት ነው በቃ ተለያይተናል። እርግጠኛ ሆንኩ። ከዛን ቀን በኋላ እሷም ተከትላው መጥታ ኖሮ አብረው ከተማ አየኋቸው። ያ ማለት እቤቴ ሌላ ሴት እየኖረች ነው። አልጋችን ላይ ከሌላ ሴት ጋር እየተኛበት ነው። ያ ማለት በይፋ ትዳራችን ፈርሷል ማለት ነው። አልተናደድኩም። ጭራሽም አልቀናሁም። በቃ ለሱ ያለኝን ነገር ጨርሻለሁ። ወይም መሰለኝ።

መመረቂያዬ እየደረሰ ባለበት ጊዜ ውስጥ በባለጌ አይን ያየኝ ከነበረ ልጅ ጋር ባለግኩ። ዌል የባለግኩ የመጀመሪያ ቀን ቁጭ ብዬ ሳለቅስ አደርኩ። ትዳሬ እንደፈረሰ እያወቅኩ እንኳን የሆነ ሀጢያት የሰራሁ የረከስኩ ዓይነት መሰለኝ። ለምን እንዳለቀስኩ እንኳን አላውቀውም። ብቻ የዛን ቀን ነው ቃሌን ያፈረስኩ የመሰለኝ:: ..... የካድኩት አይነት......... የሆነ ቀን ከልጁ ጋር ወክ እያደረግኩ ስልክ ተደወለለት።

"እገሌ ነህ?"

"አዎ ነኝ ማን ልበል?"

"የሜሪ ባል ነኝ (ባልሽ ነው አንቺ አለኝ ዞር ብሎ ጥጋበኛ ነው ለራሱ። ደነገጥኩ)

"እኔ ሜሪ ከባሏ መለያየቷን ነው የማውቀው!" አለው መልሱ ድምፁን ላውድ አድርጎት እሰማዋለሁ

"እገልሃለሁ እናትህ ሆድ ብትገባ የምታመልጠኝ እንዳይመስልህ እገድልሃለሁ።" ይለዋል። ወላ አጠገባችን ያለ መሰለኝ ተንቀጠቀጥኩ። እሱ ምንም አልመሰለውም።

"ስትገለኝ ዝም ብዬ እሞትልሃለሁ እንዴ?" ይለዋል። ሲያብድ ይሰማ

እንደዛ ከደነፋ ከቀናት በኋላ የተመራቂ ተማሪዎች ፓርቲ አዘጋጅተን ዝግጅቱ የነበረው ከተማ ነበር። ልንመረቅ ሁለት ወር ነበር የቀረን። እኔን ብሎ ደግሞኮ ተተራማሽ። መግቢያ ትኬት ምናምን እየሸጥኩ ስተራመስ ከርሜ የፓርቲው ቀን ጠዋት ከጓደኞቼጋ ጫማ ልንገዛ ከተማ ስንወጣ አገኘሁት። ምንም እንዳላደረገ ...... እንደዛ እንዳልደነፋ (ማለት ሁኔታውኮ የዛን ቀን ሳይገለው የሚያድር አይመስልም ነበር።)

"እንዴት ነሽ እማ?" አላለም?

"ደህና!" አልኩት ግራ ገብቶኝ። ሁኔታው የሰማሁትን እንድጠራጠር አደረገኝ።

"ዛሬ ፓርቲ አላችሁኣ??"አለኝ ደነገጥኩ። እየተከታተለኝ እንደሆነ ገባኝ ግን ዝግጅቱ የነበረው ማታ ከ2 ሰዓት ጀምሮ ስለነበር ቢያንስ ቺኩን ትቶ አይመጣም ብዬ ተረጋጋሁ።

"ይመችሽ ፈታ በይ!! ይገባሻል!!" ብሎኝ እንደሰላማዊ ሰው ቻው ብሎኝ ሄደ። የምር ግራ ተጋባሁ። ቀልቤ አልተመቸውም። ቢሆንም ሀገር ሰላም ብዬ ቀሽ ቋ ብዬ ፓርቲውጋ ሄድኳ!!

እስከሆነ ሰዓት ድረስ ድንገት ከመጣ ብዬ በር በሩን እያየሁ አልተረጋጋሁም። ልክ ማታ 5 ሰዓት ሲያልፍ ተነፈስኩ። የዳንስ ወለሉ ላይ ከኔ ሌላ ማን አለ አልኳ!! ከአንድ የክፍሌ ልጅ ጋር ቅንጥስ ውልቅ እያልኩ ስደንስ ልጁ ድንገት እንደጅብራ ግትር ቀጥ አለብኝ። ምን ሆኖ ነው ብዬ አይኑን ተከትዬ ያየውን ሳይ ባሌ እየገባ ነበር። (ልጁ ግን ባሌን ያየ ሳይሆን ይሄ ነጩ የበረዶ ድብ ፊቱ ቀጥ ብሎ የቆመበት ነበር የሚመስለው .....እኔ ክው ልበልለት።) እዛ መሃል ግርግር ከተነሳ የተማሪውን ቀልብ እንስብና የተማሪው ምላስ ላይ መክረሜ ነው ብዬ ፈራሁና ቀስ ብዬ እንዳማረብኝ ወደሱ ሶምሶማ (በሂል ሶምሶማ ግን ኢማጅኑልኝማ ) አጠገቡ ስደርስ እጄን ለቀም አድርጎ መራመድ ጀመረ ወደ ውጪ በሩን እስክናልፍ ዝም አልኩት። ምክንያቱም አዳራሽ ውስጥ ኮሽ ካለ ነገር ተበላሽ። ከዛ ልክ ስንወጣ እጄን መንጭቄ ፊን ፊን አልኩ ........ ተረስቶኝ ነበራ!!

"እኔን ለማስቀናት ሆነ ብለሽ ነው እንዲህ የምታደርጊው?" አላለም? የምር የምለው ጠፋኝ?

አንተ ማነኝ ብለህ ነው የምታስበው? ምን ልሁን ነው? አታፍርም ሴት እቤትህ አስተኝተህ ልታስቀኚኝ ስትል? እኔና አንተ ተለያይተኛል። ረስተህ ከሆነ ራስህን አስታውሰው? የትም ከመሄድ ምንም ከማድረግ አትከለክለኝም" እሪሪሪሪ አልኩ (ቆይ ለምስሉ በደንብ እንዲገለፅላችሁ ድመት ዝሆን ፊት ስትውረገረግ ማለት ነው ላየኝ )

አንዴ በቦክስ ሲጠጣኝ ብዙ እስካሁን ስያሜ ያላገኙ ሁላ ከለሮች ታዩኝ። በቃ የሆኑ የቀለሞች ድብልቅ .... ሀምራያዊ ..... ብርቱጓዴ .... ምናምን በስንት እጅ መጫን ቢባል በዘይት በፀሎት ያላወራሁትን ልሳን ሁላ ሳልናገር አልቀረሁም። ጥምልምል ብዬ መሬቱ ላይ ከመውደቄ በፊት ቀለበኝ። የመታኝ አይኔጋ ነበር!! ከዓይኔ ስር የቀለበቱ ፈርጥ ቀዶኝ ስለነበር ደሙ ወደላይ ተፈነጠቀ። አቅፎ ይዞኝ እሪሪሪሪ የፈራሁት አልቀረም አንዳንድ እያለ የተወሰነ ተማሪ ተሰበሰበ። ደግነቱ ያው ውስጥ ሙዚቃ ስለነበረ ሊያጨስ ... ሊሳሳም ... አየር ሊወስድ ... ዜድ ሪፖርት ሊያወጣ .... ምናምን ከወጣው ተማሪ ውጪ ውስጥ አይሰማም። የለበሰው ነጭ ቲሸርት ቀይ ጠቃጠቆ ሰራ 'እሺ ልቀቃት?' 'አልለቅም።' ዝም ሲሉት 'እርዱኝ እንጂ እየደማችኮ ነው።!' አልኮል ሲሰጡት በሁለቱም እጆቹ ወደላይ ተሸክሞኛል እንዴት ያድርግልኝ? ሊያደርጉልኝ ሲሉ 'አትንኳት እኔ ነኝ ያደማኋት ራሴ ነኝ የማደርግላት!' የሚያየው ሰው ግራ ገባው።


ከዚህ ቀጥሎ ምን የሚሆን ይመስላችኋል?
ሀሳባችሁን አጋሩን 👇👇


"ኸረ አርፈሽ

ቁጭ በይ እነሱ ነገ ታርቀው አልጋቸው ላይ ሆነው። 'ይህቺ ወሬኛ እንዲህ አላለች መሰለህ?' ሊባባሉብን ዝም በይ ነገ ይታረቃሉ" ይባባላሉ።

ደግሞ የምራቸውን ነውኮ 'ውይ በቃ ይሄማ የመጨረሻቸው ነው!' ሲባል በነገታው እኛ እፍፍፍፍፍፍ ብለን የሚሪንዳ ቆርኪ ለሁለት ሻወር ለመውሰጃ ይበቃናል። እንላለን። እዚህጋ ብጠየቅ ምን እዛ ትዳር ውስጥ እንዳቆየኝ አላውቅም። በየቀኑ አዲስ ነገር እንደማይፈጠር አውቃለሁኮ ግን በቃኝ አልልም። ምን እንደፈራሁም አላውቅም። ብቸኝነቱን ነው የምፈራው? ፍቺውን? እሱን ማጣቱን? አላውቅም ምናልባት እሱ ናት ያላትን ሜሪ እወዳታለሁ ይመስለኛል። ልዩ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ የሚያደርገኝን ........ ብቻ አላውቅም። ለስድቡ ለምቱ ለሌላው ለእያንዳንዱ ጥፋት የራሴን ምክንያትና ሰበብ እደረድራለሁ። ለውስልትናው ግን ምንም ሰበብ ብሰጠው ልክ አይደለም። ልክ እንዳልሆነ እያወቅኩም አልፈዋለሁ። እንደበፊቱ አያምም ........ እንደመጀመሪያው አይጠዘጥዝም። ግን አዙሪት አለው ተመሳሳይ ሂደት እዞራለሁ!!

ቸርቹን እሱም እርግፍ አድርጎ ተወው ጭራሽ ክለብ ይዞኝ ወጣ። ድሮ በመዝሙር እንዳልተባረክን ሙዚቃ መገባበዝ ያዝን .....በዛኛው ህይወቱ ዲጄ ሁላ ሆኖ የሚያውቅ ቀውጢ እንደመሆኑ ሙዚቃ ምርጫ ሲያውቅበት ..... ማሪንጌ ሬጌ ፖፕ ብለን ጨፈርን። (እነዚን ሁሉ ነገሮች አላውቅም ለምን ብሎ እንዳደረጋቸው። እሱ አንቺን ለማስደሰት ደስ የሚልሽ መስሎኝ ነው የሚለው። )

ከዓመት በኋላ ለክረምት ፀጊ እኛጋ መጣች በድጋሚ። እንደተለመደው ፈንጠዝያችን ተጀመረ። ይሄኛው ክረምት ግን ከአንድ ወር አላለፈም። አሁን ምክንያቱን በማላስታውሰው ምክንያት ንትርክ ጀመርን። ጸቡ እየተጋጋለ ሲሄድ ልጄ ስላለች ዝም አልኩ። አልቀረልኝም አንዴ በጥፊ ሲለኝ ልጄን ነው ያየኋት ፊቷ ላይ የነበረው መሳቀቅ ድንጋጤ ፊቷ አመድ መሰለ። የተመታሁ አልመስልም። የእጁ ምልክት የተሰመረበትን ፊቴን እያሸሁ ልጄን ማባበል ጀመርኩ። ምንም አልተናገርኩም። በቃ ምንም !!!

ጠዋት እሱ ስራ ሲሄድ ቀለበቴን አስቀምጬለት ልጄን ይዤ ሄድኩ። አላለቀስኩም። አልተገረምኩምም። ውስጤ ዝም ነው ያለው። በቃ እንዳከተመ ገባኝ!! ራሴን ስሰማው የገባኝ አሁን እሱ ከህይወቴ ቢጎድል አልጎዳም! ሳላየው ሳምንት ሲሆን የማብድ የሚመስለኝን ባሌን ስለመለየት ሳስብ እርፍት ነው የተሰማኝ። እቤት ስሄድ ለማሚ መፋታት ነው የምፈልገው አልኳት። ገባት! ዝም አለች አልመከረችኝም። ምንም ቢመጣ እቀበላለሁ። ተመርቄ ስራ እይዛለሁ። ልጄን አሳድጋለሁ።

ስመለስ መነጋገር አለብን ብሎ የቀጠረኝ እሱ ነው። ተገናኘኝ!! ምንም ቢፈጠር የቃልኪዳን ቀለበቴን እንደማላወልቅ ያውቃል። የእውነት የሚመስለኝ የነበረው ያ ማለት ቃሌ ነው። ያ ማለት ፍቅሬ ነው። ያ ማለት እኔና እሱ ብቻ ማንም ሳያየን በእግዜሩ ፊት እንደሚስት በህመም በድሎትም ብዬ የገባሁት ቃሌ ነው። (እርግጥ ከገባሁት በላይ ኖሪያለሁኮ ስጠለዝም ሲማግጥም ብዬ የገባሁት የለም)

"እሺ እንለያይ!" አለኝ የምር ማመን አቃተኝ።



....... ....... አልጨረስንም ........

#Meri feleke


ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል አስር)

ልታሸንፈኝ የምትችለው እሷ ብቻ እንደሆነች ያውቀዋል። እንዴት ብሎ እንደነገራት አላውቅም። ግን እንዳልኳችሁ ነው ..... ይሄን ታሪክ እንኳን እየነገራችሁ ያለው እሱ ቢሆን እንዴት አንጀት እንደሚበላ ያውቅበታል። 'አንቺ ልዩ ነሽ' ያልሽ ሁላ ክርብት ብለሽ 'ምን ልሁን ነው የምትዪው?' ማለትሽ አይቀርም ነበር። በእርግጥ እንደወሰለተ ነው እንጂ የነገራት ሌላ ጣጣችንን አልነገራትም።

መፅሃፍ ቅዱሱ እንኳን ፍቺን የሚፈቅድበት ብቸኛ ምክንያት ውስልትና መሆኑን እያወቀች። እሱን አልፋ ስለይቅርታ ስትሰብከ አመሸች።

"ውይ አንጀቴን በላው! ሌላ መሄጃ የለኝም .... ጉዴን ልንገርሽና እንደፈለግሽ አርጊኝ ብዬ ነው አንቺጋ የመጣሁት አንቺው አማልጂኝ! ያለእሷ መኖር አልችልም ብሎ እግሬ ላይ ሲወድቅ አንጀቴን በላው! በጣም ነው የሚወድሽ" ብላ ጭራሽ ልትቆጣኝ ሁላ ዳዳት።

ከዛ ግን ለብቻዬ እንዲህ አለችኝ

"ትዳር አንዴ ከገባሽበት በኋላ ያውም ልጅ ካመጣሽ በኋላ በሰበብ አስባቡ ብድግ እያልሽ ወጥቼበታለሁ የምትዪበት አይደለም።" (በሰበብ አስባቡ አይደለምኮ ብዬ የሆነውን ሁሉ ልነግራት እፈልግና እተወዋለሁ። ምናልባት 'መጀመሪያ እረፊ ብዬሽ ነበር' መባልን ፈርቼ? ወይም 'ልክ ነበርሽ እሱን ተከትዬ መምጣት አልነበረብኝም' ማለት ሽንፈት መስሎኝ ወይም አሁንም ለእሱ ያለኝ ፍቅር እርሱን እንዳትጠላብኝ እንድሰስት አድርጎኝ። ዝም ብዬ ሰማሁ ብቻ)

"አግብተሽ ያውም ከልጅ በኋላ ብቻሽን ህይወትን መግፋት ለሴት ልጅ ከባድ ነው። አንቺ ገና ህፃን ነሽ ለዛ አልተዘጋጀሽም! ቅስምሽ ይሰበራል። ምንም አድርጎሽ ውጪ ዝቅ ተደርገሽ የምትታዪው አንቺ ነሽ። ምንም በደል ደርሶብሽ ትዳርሽን ፍቺ ያው ፈት ነሽ! የምታገኚው ወንድ እንኳን ፈት መሆንሽን ሲያውቅ ያጎድልሻል።" አለችኝ (ይሄኛው ምን ማለት እንደሆነ የገባኝ ዘግይቶ ነው።)

ከምክሩ በኋላ በዘይትም በእጅ መጫንም ተፀልዮልን። "በጌታ ስም ትዳራችሁ ካሁን በኋላ የሰይጣን ሴራ መጠቀሚያ አይሆንም። ልጆቼን ልትዋጋ በአየር በባቡር በየብስ ...... የምታንዣብብ በየሱስ ስም የከሸፈ ይሁን" ተብለን ታረቅን።

እኔና እሱ መሃል ሶስተኛ ሰው ገባ! ያ ለእኔ የትዳራችን መፍረስ ጅማሬ ነበር። በዚህ ሁሉ መሃል እያለፍን ሌላ ሰው የማይረዳው የእኔና የእሱ ስሜት አለ። በቃ ለሌላ ሰው የማይገባው ያንን ድንበር አልፈን ተጣልተን እንዲያሸማግለን ሶስተኛ ሰው ስንጠራ መግባባት አቅቶናል።

ክረምቱን ፀጊ መጣች እኛጋ። ሁሉ ሞላልኝ። እሱም ቦረቀ። ሁለቱን ወር እራሱ ፈጣሪ ተገልጦ 'ምን ልስጥሽ?' ቢለኝ

'እያየኸኝ? ከዚህ በላይ ምን እፈልጋለሁ?' ነበር የምለው። ደስታ አልፈጅም ብያችሁ የለ? በቃ ምንም ነገር ከዚህ ደስታ አይበልጥም አልኳ!! የልጄና የአባቷን መፍለቅለቅ እያየሁ ይሄን ቤት ለማቆየት መክፈል ያለብኝን እከፍላለሁ አልኳ!

አልኩ ነው እንግዲህ ........ ትምህርት ሲጀመር ጸግዬን ወደነበረችበት ወሰድኳት። ንትርኩ የተጀመረው ይሄኔ ነው። "ልጄ አብራኝ ትሁን!" አለ። እኔም ልጄ አብራኝ ብትሆን ደስታዬ ልክ የለውም። ግን የሚያስከፍለኝን ደግሞ አውቀዋለሁ። ልጄን እቤት እየተውኩ ምን አይነት ትምህርት ነበር የምማረው? ከዛ ደግሞ እነማሚን በቃ ልጄን ወስጃለሁ ካልኳቸው በኋላ የሆነ ቀን ቢባርቅበት አይ በቃ ደግሞ ትመለስ ልላቸው ነው? በዛ ላይ እዛ የለመደችውን ድሎት በሰዓቱ እኔ አልሰጣትም። የነበረው አማራጭ ሁለት አመት ታግሼ ልጄን በሙሉ አቅሜና ትኩረት ማሳደግ ነበር።

"ለሁለተኛ ጊዜ ልጄን ቀማሽኝ!" የንትርክ ሁለት ነጥብ ሆነ። ይችልበታል! እናም በዚህ ጉዳይ ሁሌ ራሴን እንድወቅስ ..... ራስ ወዳድ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ አደረገኝ። እናም ይሄን ነጥብ አንስቶ ንትርክ ሲጀምር እንደጎዳሁት ስለሚሰማኝ ሁሌ ይቅርታ እጠይቀዋለሁ። እውነታውንኮ ልቤ አሳምሮ ያውቀዋል። ልጄን ባመጣት የሆነ ቀን ትምህርቴን አቆማለሁ። ግን ደግሞ እሱም ልክ ነው ልጁን ነው ከአጠገቡ ያጣው። እሱ እንደአባት ሃላፊነት ወስዶ ቀን ከሌት ልጁን ይንከባከባል ብዬ 100 % እሱን ማመን ልቤ ከበደው። ስለዚህ በራስ ወዳድነቴ ፀናሁ!!

ከዚህ በኋላ ያለው አንድ አመት አዙሪት ነው። እያንዳንዱን ዝርዝር ብፅፍላችሁ ምክንያቱና ሰዎቹ ይቀያየራሉ እንጂ ሂደቱ ያው ነው። አንድ ወር እፍፍፍፍ ብለን እንፋቀራለን ከዛ በሆነኛው ሰበብ እንጣላለን ወይ ይጠልዘኛል ወይ ሞልጬው ወደዶርሜ እመለሳለሁ። በነገታው ትምህርት ቤት ይመጣል እማ አይለመደኝም ይላል። ሁለት ቀን አኮርፋለሁ ከዛ ደግሞ እፍፍፍፍፍፍፍ .......

ደግሞ የሆነ ቀን እኔው ደሙን አፈላዋለሁ። እንፋታ በቃ መዝሙሬ ሆነች። ያብዳል። ይቅርታ እጠይቃለሁ ..... ደግሞ እንታረቃለን።
ለውጡ ምንድነው መሰላችሁ? ያቺ ምስኪኗ ሜሪ ድራሿ ጠፋ! ይህችኛዋ በራሷ የማትተማመን 'ሽቶ ሸተተኝ' ብላ ሀገር ይያዝ የምትል። (እርግጥ ሸቶኝ ነው። ፓንቱ ድረስ የሴት ሽቶ ምን ይሰራል? ) 'ደብዳቤ ሴት ፅፋልህ አልነገርከኝም' ብላ እሪሪሪሪ የምትል ........ ራሴን እያየሁት ሌላ ሰው ሆንኩ። በጣም የምጠላት እና ልሆን የማልፈልጋት መንቻካ ሴት ሆንኩ። በፊት እንዳይናደድ ሰማይ ከምድር የምገለብጥ ልጅ ሲናደድ እሳት ለኩሼለት ሄዳለሁ።

አሁን እንደበፊቱ ሰው ሰማ አልሰማ ችግሬ አይደለም። ይሄኔ ስንጣላም ስንታረቅ ጓደኞቼ ወይም ሰፈር ያውቃሉ። እርግጥ ዶርም ድረስ መጥቶ አንጥፎኝ ያውቃል እና ላያውቁ የሚችሉበት ሁኔታ አልነበረም። ብቻ አቡካካነው። ስንታረቅ ሁሉ እንደነበረ ቢመስለንም አልነበረም።

የሆነ ቀን ከአንዱ የፈረደበት ተማሪ ጋር የሙዝ ገበያ እያወራሁ እየገለፈጥኩ አምሽቼ ወደዶርሜ ገባሁ። መጥቶ ሲያስጠራኝ የነገር ዲዘርት ሊያበላኝ እንደሆነ ሳልጠረጥር ዊን ዊን እያልኩ ተንደርድሬ ወረድኩ። ሁለቱን እጆቼን ጭብጥ አድርጎ እያሳመመ አርገፈገፈኝ። የተፈጠረው ስላልገባኝ የያዘኝ እጁ ስለሚያም ለማስለቀቅ እታገላለሁ።

"ማነው?"

"ማነው ማን?"

"ቅድም አብሮሽ የነበረው? ከዛሬ ጋር ብዙ ጊዜ ነው አብረሽው የነበርሽው! ማነው?" ሲለኝ የፈረደበት ልጅ ትዝ አለኝ

"ኸረ ማንም አይደለም በጌታ ! ከሰው ሰው ጋር እንዳትጣላ?" ዘግይቻለሁ ልጁን ዘመዶቹን የሚያስረሳ ቡጢ ጠብቶት ነው እኔጋ የመጣው።
ልጁ ደግሞ ወሬ አማረልኝ ብሎ ከሰይጣን ጋር እንደተፋጠጠ ሳይገባው "ሜሪ ቀሽት ልጅ ናት" ምናምን ብሎ ዘላብዷል።እኔኮ ብድግ እያልኩ ባምፅም መጽሃፍ ቅዱስ ሳጠና እንደማደጌ እግዜሩን እፈራለሁ። መጀመሪያ የዘፈንኩ ቀን ዝናብ ሲዘንብ በኔ ምክንያት መብረቅ ሊዘንብ ነው ብዬ የፈራሁ ሴትዮ ነኝ። አንድ የሆነ ቆንጅዬ የክፍላችን ልጅ ቸኮሌት ገዝቶ ሰጥቶኝ ስለበላሁ በከፍተኛ የፀፀት መንፈስ የምናዘዝለት ካህን ባገኝ "አባ በድያለሁ በትዳሬ ላይ ማግጫለሁ" ልል ትንሽ የቀረኝ ሴትዮ ነኝ።

የዚን ቀን ዓይኖቹ ሲያስፈሩ
"የሌላ ሆነሽ ከማይ ገድዬሽ ሞታለሁ!" ያለኝን አመንኩት። የንዴት አይደለም። የምሩን እንደሚያደርገው ያስታውቅ ነበር።

የሚያውቀን ሁሉ "አንድ ቀን ይገላታል!" ይላል። የኔ ቤተሰቦች "የሆነ ነገር አድርጎባት!" ነው ብለው ወጥረው ይፀልያሉ። ጭራሽ ከጅምሩ ያልነበሩ የሱ ቤተሰቦች በተቃራኒው ባለቀ ሰዓት መጥተው "ልጃችንማ የሆነ ነገር ሆኖ ነው በሴት ፍቅር እንዲህ አይኮንም ፀበል ይግባ!" ይሉኛል ከነሱ ብሶ
ጓደኞቼ ቢሞቱ እሱን በእኔ ፊት አያሙትም።
ምንም ሆኜ ብመጣ


"እባክሽ አታውልቂው በናትሽ። የልጅሽ አባት ነው። ይቅርታ ልጠይቅሽ ነው የጠራሁሽ። በጉዳዩ መጠየቅ ካለብኝ እኔም ነኝ ጥፋተኛ! እኔም እሱም አስበን ያደረግነው ነገር አይደለም። እናቴ ትሙት ባለትዳር መሆኑን ግን አላውቅም ነበር።" እያለች ነገሩን ስታብራራልኝ

እኔ ያደረጉት ነገር በስዕል መልክ እየተከሰተብኝ ደሜ መንተክተኩን አልክድም። ብዙ መጠየቅ የምፈልገው ነገር ነበር ዲቴሉን ማወቅ ህመም እንጂ የሚሰጠኝ መልስ እንደሌለ ሳውቅ ተውኩት። ከእርሷ ጋር ያወራሁ ቀን ድብዝዝ ብሎ የነበረው ቁጣዬ ፈላ!! ማታ ላይ ሳየው ሀገር ሰላም ብሎ ሲያቅፈኝ። ለነገር ሲሊፐሬን አቀብሉኝ አልኩ። ... ሌላ የማላውቃት ሴትዮ ከውስጤ ወጣች .... እያለቀስኩም እየተሳደብኩም... እየተራገምኩም..... የሆነ የማልወዳት የመንደር ነገረኛ ሴት ነገር ሆንኩ:: ........ ... ዝም አለኝ። በሚቀጥለው ቀን አልመጣም። .......... ማለት ሲቀርብኝ ጠበቅኩትኮ። 'እንለያይ' ብዬው ነበርኮኣ? ምን ሆኖ ይሁን ብዬ ስጨነቅ አደርኩ። በሚቀጥለውም ቀን አልመጣም። ማታ ላይ ማሚ ደወለችልኝ።

"በይ ነይ እቤት እየጠበቅኩሽ ነው!"

"የት ቤት ነው?"

"እቤትሽ!"

"አርባምንጭ ነው?"

"አዎ!" ማሚ ከሀዋሳ ልትመጣ የምትችልበትን ምክንያት ማሰብ ቸገረኝ። .... የሆነ ነገር ሆኖ ቢሆን ግን ድምፅዋ እንዲህ አይረጋጋም::

....................... አልጨረስንም................

#Meri feleke


ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል ዘጠኝ)

ከሁሉም ከሁሉም ምኑ ያስጠላል መሰለሽ? ራስሽን ባልሽ ካባለጋት ሴት ጋር ማነፃፀር ...... መድቀቅ የምትጀምሪው እዚህጋ ነው ...... ራስሽን ከሆነ ሰው ጋር ማነፃፀር ስትጀምሪ በራስ መተማመንሽ እየተምዘገዘገ ይፈጠፈጣል። ከዛ በፊት ከማንም በልጣለሁ ወይም ከማንም አንሳለሁ ብዬ ራሴን ከማንም አወዳድሬ አላውቅም እራሴን እንዳለሁ እንደዛ በብዙ እወደዋለሁ። ደግሞ ምናለ ከሆነች ጥፍጥፍ ጋር እንኳን ቢያደርገው ......... ማለት ምንም ንፅፅር ሳያስፈልገው ቆርጥማ ትበላኛለች።

እንደው ለማረጋገጥ አለ አይደል ከወንዱም ከሴቱም 'እገሊት ግን ታምራለችኣ?' ብዬ ጠይቃለሁ? ሴቱ 'ልቅም ያለች ቆንጆ ናት!' ይለኛል። ወንዱ 'ፓ ቂጥዋ ይምጣብኝ!' ይለኛል። (ይኸው በሷ የለከፈኝ ....... ትልቅ ቂጥ ሳይ አንገቴ እስኪጠማዘዝ እየዞርኩ እሸኛለሁ። ሰርች ሳደርግ ራሱ ቂጥ ለማተለቅ የሚረዱ 10 የምግብ ዓይነቶች የሚል ነገር ዓይኔን ይጠልፈዋል።)

የዛን ቀን ማታ እቤት አላድርም ብዬ 6 ሰዓት ጊቢ በሚሄድ የሰራተኞች ሰርቪስ ዶርም ገባሁ። ደጋግሞ የሆነ ጥፋት ባጠፋ ቁጥር የማለቅሰው መጠን እየቀነሰ የህመሜ መጠን እየቀነሰ መጥቷል። ማሪኝ ባለ ቁጥር ይቅርታ ሳደርግለት እንደመጀመሪያው ሁሉ ነገር ይቀጥል ነበር። ሁለታችንም ያልገባን ቀስ በቀስ ፍቅራችንን እየገዘገዘው እንደሆነ ነው። መጀመሪያ ቢላ አንገቴ ላይ ያደረገ ቀን ለሳምንታት ነው ባሰብኩት ቁጥር ያለቀስኩት የዛን ቀን ማልቀስ ብፈልግ ራሱ አላለቀስኩም። ካደረገኝ ሁሉ የከፋ ነው ያልኩት እኮ ይሄንንን ነው። ግን እንባ እንቢ አለኝ። ይልቅስ ለመጀመሪያ ጊዜ እሱ የሌለበት ህይወቴ ምን ሊሆን እንደሚችል ከአሁኑ ጋር ማነፃፀር ጀመርኩ። እሱን መጥላት የምችልበት ጉልበት አይደለም የነበረኝ ራሴን መውደዴን መጨመር የምችልበት ጉልበት አገኝሁ። ..... ዳዴ ማለት ...... ያቺ እሱ ቢሆን የሚወዳት ሴት ብዬ የሆንኳትን ሜሪ አውጥቼ ጣልኳት። እሱ ስለሚሰማው ሳይሆን እኔ ስለምፈልገው ነገር መጨነቅ ጀመርኩ። የዛን ቀን እንቅልፍ በአይኔ ሳይዞር አደረ። ጠዋት ክላስ ቀርቼ ተኛሁ። ስነሳ መከፋቴ ልቤን ቢጫነውም ከሌላው ጊዜ በተለየ በማንም ላይ ያልተደገፈ መነቃቃት ውስጤ ነበር።

"ባልሽኮ ውጪ ተቀምጧል!" አለችኝ ጓደኛዬ ወደዶርም እየገባች

"ተይው ባክሽ ይቀመጥ!" ስል ራሴን ሰማሁት።

ለሳምንታት እንደዛ አደረገ። ሊያዋራኝ አይሞክርም። አይቶኝ ብቻ ይሄዳል። ሲበርድልኝ የሆነ ቀን 'እናውራ' ብዬ ጠራሁት እና ካፌ ተገናኝኝ። (እቤት ከሄድኩ እንደምቀልጥ አውቀዋለሁ።) አንድ ጥያቄ ብቻ ነው የነበረኝ።

"ለማያቅህ ሰው ሁሉ የሜሪ ባል ነኝ ብለህ ሳትጠየቅ የምታወራ ሰው ያውም እንደምታውቀኝ እያወቅክ ለሷ መንገሩ እንዴት አልመጣልህም?"

"አላውቅም እማ! ሁሉም ነገር በአጋጣሚ የተከሰተ ነው። የአንድ ቀን ስህተት ነው። እባክሽ ዲቴሉን እንዳወራ አታድርጊኝ። ላንቺ ማውራቱ ከሰራሁት በላይ ያማል።" አለኝ።

"እንለያይ?" አልኩት። የሰማውን ማመን አቃተው።

"እንለያይ! አባ እንዲህ እንዳፈቀርኩህ እንለያይ! አልጥላህ .... እውነቱን ልንገርህ በፊት እንደምወድህ አሁን አልወድህም! በዚህ ከቀጠልን ግን ጭራሽ ላልወድህ ነው። እኔ መኖር የምፈልገው ካሉን ጥሩ ትዝታዎች ጋር ነው። አንተን ሳስብ ካፈቀርከኝ ፍቅር በልጦ የጎዳኸኝ እንዲያመኝ አልፈልግም። ሳስብህ ፈገግ ማለት ነው የምፈልገው።" አልኩት

"አልችልም። እኔ አንቺን አጥቼ መኖር አልችልም። ቤተሰቤ እኮ አንቺ ነሽ! ማን አለኝ? እንለያይ? ከዛስ? ሰው አልሆንብሽምኮ! እማ እታመምብሻለሁ ተይ!" አለኝ (እሱ እውነት ነው ከኔ ውጪ ቤተሰቤ ብሎ የሚጠያየቀው የለም። ቤተሰቦቹም ከሁለቴ በላይ ደውለውልን አያውቁም። ዛሬም ድረስ የማይገባኝ የተወሳሰበ ግንኙነት ነው ያለው ከቤተሰቡ ጋር። ብቻ እንዲህ ሆንኩ የሚባባለው ቤተሰብ የለውም። ይሄም ሌላኛው ለራሴ ከምሰጣቸው ምክንያቶች አንዱ ነበር። ቤተሰቤ ለእኔ ምን ማለት እንደሆነ አውቃለሁና 'ከኔ ሌላ ማንም የለውም'

"እኔ ደግሞ እንዲህ መኖር አልችልም።"

"ልጃችንስ?"

"እኔ እየሞትኩ ለልጄ እንዴት ነው እናት የምሆናት?" (በዚህ ጉዳይ ያለኝን አቋም ያውቃል። እውነቱን ነው ልጄን ሳላስባት ቀርቼ አይደለም። ባሌ ለልጆቼ ጥሩ አባት ከሆነ መቻል አይከብደኝም ብዬ የማምን ዱዝ እንደሆንኩ ያውቃል።)

"እማ በፍፁም አይሆንም! እኔና አንቺ ገና ነጭ ፁጉር እስክናበቅል አብረን እንሆናለን። ፍቅርን እንወልዳለን (ፍቅር የሁለተኛ ልጃችን ስም ነው።) የፈለግሽውን ጊዜ ውሰጂ ብቻ ተመለሺልኝ .... አትተይኝ" አለኝ

ብዙ ነገር አውርተን። 'እንለያይ' ያልኩት ልጅ ከንፈሩን ስሜው የምለየውስ ነገር? ሸኝቶኝ ልንለያይ ስንል

"ካንተ ውጪ ከሌላ ወንድ ልጅ አልወልድም። ምናልባት ወደፊት ፍቅርን የመውለድ ሃሳብ ከመጣልኝ ትቸገርልኛለህ።" ብዬው ተሳስቀን ተለያየን። የእውነቴን ነበር ከሁለት አባት ልጅ አልወልድም።( እሱ ሌላ ታሪክ ነው ግን የራሴ ምክንያት አለኝ።) በዛ ላይ come on እሱኮ ጣኦቴ ነበር።

ወደ ዶርሜ ተመለስኩ። ከትምህርቴ በተጨማሪ ትምህርት ቤት ውስጥ የማልገባበት መድረክ ነገር የለም። እሱን የማስብበት ጊዜ እንዲኖረኝ አልፈልግም በተጨማሪ እሱ ደስ ስለማይለው ተውኩ እንጂ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ላይ መሳተፍ እወድ ነበር። ብሄር ብሄረሰቦች ቀን ....የሴቶች ቀን ....ኪነጥበብ ምሽት ....ብቻ ምንም ይሁን ...... እንደቀይ ወጥ መሃል ላይ ዱቅ ..... ግጥም ....አጭር ልብወለድ .... ዘፈን መዝፈን ..... መድረክ መምራት .... ብቻ ምንም አልኩ ......የአባቶች ቀንም መድረክ አስመሩኝ ብዬ ከልክለውኝ ነው።

"ትቼለታለሁ የኔን ጉዳይ ..." ያልኩትን ጌታ ራሴ ትቼ

"ይማርሽ ይሉኛል አሜን ይማረኝ
አንተ ልጅ ፍቅርህ እንዳልሄድ ይዞኝ " ማቀንቀኑን ያዝኩት (የምሬን ነውኮ ይሄንኑ ዘፈን ጊቢ ዝግጅት ላይ ዘፍኜዋለሁ)

እኔ መድረክ ዝግጅት ሲኖርብኝ ወፎቹ ይነግሩታል። ይመጣል። ያየኛል። "ዛሬ ታምሪ ነበር" ብሎኝ ይሄዳል። እርግጥ አንዳንዴ "ይሄ ነገር ትንሽ አላጠረም?" ይላል። በሱ እልህ የሃመሮቹን ቆዳ ብለብስ ራሱ ውስጤ ነበር። ወደቤቴ ሳልሄድ ወራት አለፈ። መጥቶ ያላየኝ አንድም ቀን የለም። እንለያይ ካልኩት በኋላ ግን ቢያንስ ሰላም እንባባላለን። 'ምንድነው አንተ እህል አትበላም እንዴ? ከሳህኮ?' 'ምንድነው ሸሚዝህን አትተኩሰውም እንዴ?' ዓይነት ንግግሮች አሉበት። በጠዋት አንድ ቀን አይኔን ስገልጥ ጊቢ ሳየው 'ለመሆኑ ቁርስህን በልተሃል?'ነው መጀመሪያ ከአፌ የወጣው።

ሀቁንኣ የምናወራው? በጣም ከመናፈቄ የተነሳ ብዙ ቀን "በቃ አባ ይቅር ብዬሃለሁ ወደ ቤት እንሂድ" ልለው አስቤ አውቃለሁ። ሰላም ስንባባል አለው አስተቃቀፍ ውስጡ ክትት የሚያደርገኝ ለቅጽበት የሆነውን ሁላ እርስት የሚያስደርገኝ። እልሄ ያንን ያልፍ ነበር።

የሆነ ቀን አስተማሪያችን ቢሮ አስጠራችኝ። ምንም የሚያገናኘን ኮርስ ስላልነበረ እየገረመኝ ሄድኩ። ገና እንደገባሁ ቀለበቴን እጄ ላይ ቼክ ስታደርግ አየኋት::

"አላወለቅኩትም" አልኳት


"አንቺ ብርቱ ሴት ነሽ ምንም ነገር እን

ዳይበግርሽ እሺ? ልብሽን ጠብቂው በናትሽ። አደራ በርቺ" አለችኝ። እንስ ስል ታወቀኝ..... በቃ ቅንስ ...... ኩምሽሽ ።

ስለሷ ያወራነውን ሁሉ ገጣጠምኩት። ብትን ብዬ የምፈነዳ ነገር መሰለኝ። ከምሽቱ 4 ሰዓት ወደከተማ የሚሄደውን የመጨረሻ ታክሲ ይዤ እቤት ደረስኩ። በሩን በርግጄ እንደገባሁ ፈነዳሁ።

"አንተ በእኔ ላይ? ያውም ከአስተማሪዬ ጋር (ያውም ከዛ ቂጥ ጋር ብለው ደስታዬ ነበር?) ወይኔ ሜሪ !!

አበድኩ ሊሰደቡ የሚችሉ ስድቦችን ሁላ ብልግና ስድቦች ሳይቀር ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳደብኩ። ብቻዬን እየተቀነጣጠስኩ ስውረገረግ ለመጀመሪያ ጊዜ ዝምምምምምም አለ።

     ...........አልጨረስንም ....

#Meri feleke


ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል ስምንት)

'ጊቢ ግቡ' እስኪባል ድረስ ምን መወሰን እንዳለብኝ ግራ ገባኝ። ማንም FBE በLAW እንደማይቀይረኝ እያወቅኩ ሞከርኩ። ላለመማርም አስቤያለሁ። ከዛ ልጄን ይዤ የሆነ ቦታ እልም ብዬ መጥፋት ....... ማንም የማያውቀኝ ቦታ ሄጄ ከዜሮ መጀመር። በእኔ እልህ ልጄን ማስከፈል የማይታሰብ ነው። እጅ መስጠትም ምርጫዬ አልሆነም። ልክ ጊቢ ግቡ ሲባል አሁንም አቧራዬን አራግፌ ተነሳሁ ....... እማራለሁ ........ ጥሩ ውጤት አመጣለሁ ..... ለሚጠብቀኝ ሁሉ ኩራት እሆናለሁ ...... ከማንም በላይ ራሴን እና ልጄን አኮራለሁ ........ ቀና ብላ የምትሄድ ሴት እሆናለሁ ....... ህይወቴን ሳሸንፍ የሆነ ቀን ህግ እማራለሁ። ራሴን ሳፅናና "ያውም ህግ መማር የምፈልገው ወንጀል ነክ መፅሃፎች ለመፃፍኣ? እደርስበታለሁ"

እሱን? ግራ ቂጡን ትወጋዋለች ብላችሁ ነው የምትጠብቁትኣ? አልገባችሁም ግራ ቂጤ እስኪጨስ እንደማፈቅረው።

"አምላክ ሆይ እባክህ ለሱ ያለኝን ፍቅር ውሰድልኝ አልችልም ብዙ ነው" ብዬ የምፀልይ ሰገጥ እንደሆንኩ አልገባችሁም። በዚህ ሁሉ ውስጥ እንዴት እንደምወደው ቢያውቅልኝና ድሮ እንደማውቀው 'እሱ' ፍቅራችንን ብንኖረው ስለቴ እንደሆነ አልገባችሁም። በዚህ ሁሉ ውስጥ ለነገ አብሮ ኑሮኣችን መሰረት ይሆነናል ብዬ ከወር ደሞዙ ላይ የሚከፈል መሬት በሊዝ እንደዳስገዛሁት አታውቁማ (ለዛዛ በሉኝ ስትፈልጉ።)

እናም ተውኩለት "ይቅር ብዬሃለሁ" አልኩት "ካንተ አይበልጥብኝም!" አልኩት በአዋቂ ደንብ ቁጭ ብለን አወራን (እኔ 20 ዓመቴ እሱ 25 ነበርን ይሄ ሲሆን ለሚያጠፋቸው ጥፋቶች ለራሴ ከምሰጠው ምክንያት አንዱ 'ስላልበሰለ ነው ወደፊት እንዲህ አይሆንም' የምለው ነገርስ? የሆነች አሮጊት ሴትዬማ ውስጤ ነበረች )

"ይሄን ማሪኝና ሁን ያልሽኝን ልሁን" አለኝ። ከዛም እሱም የማታ ኢኮኖሚክስ MA ሊማር ተመዘገበ።

ጊቢ የገባሁ ቀን አብሮኝ ሄደ። ከዘበኛው የጀመረ በጋሞኛ ሰላምታ እየሰጠ ሚስቱ መሆኔን አበክሮ እየነገረ። ፕሮክተር ነሽ ወጥ ቤት ያልዞረበት የለውም እጄን ይዞ ....... እንዴት እንደሚያወራ ያውቅበታል። ስቆ አያውቅም የሚባል ሰፊ ፊት ማስፈታት ያውቅበታል።

"ባልሽ ግን 'የሜሪ ባል ነኝ' እያለ ራሱን የሚያስተዋውቀው ማነሽ ብሎ ነው የሚያምነው ሴሌብሪቲ ነው እንዴ የምትመስዪው?" ብሎኛል አንዱ የአርክ ተማሪ 'ሚስቴ ናት' ሲል ኩራቱን አይቶት  .....

አብረን ዶርም ድረስ ሄድን:: አልጋዬን አንጥፎልኝ። ዶርሚተሪዎቼን ተዋውቆ ሲያስቀን ቆይቶ ወደቤት ተመለሰ።

"ወንድምሽ ነው?" ሲሉኝ የምበሳጨው መበሳጨት

"ባሌ ነው። የልጄ አባት እሺ" እላለሁ:: በነገታው አዳዲስ ልብሶች ገዝቶልኝ መጣ። ግራ ገባኝ ምክንያቱም ብር እንደሌለው አውቃለሁ። ከሁለት ቀን በኋላ እቤት ስሄድ ቴሌብዥኑን እንደሸጠው አየሁ። እኔ እንደሱ 'አልበላ አልጠጣ ብዬ የገዛሁትን ...... እንዴት አትነግረኝም' አላልኩም:: ዶርም የገባሁ ቀን ቱታ እንደለበስኩ ነው የሄድኩት ሴቶቹ ዘንጠው ሲያያቸው ሚስቴ ከነሱ አትነስብኝ ብሎ እንዳደረገው ገብቶኛል አቅፌው አለቀስኩ ብዙ እንደምወደው ነገርኩት.....

እኔ የሀብታም ልጅ አይደለሁም። ግን ቤተሰቦቼ ባላቸው አቅብጠውኝ ነው ያደግኩት። እሱን እስካገባሁበት ሰዓት ድረስ እግሬን ሰራተኛ ያጥበኝ ነበር። ሀብታሞች የሚማሩበት የግል ትምህርት ቤት ነው የተማርኩት። ይሄ ሁሉ ሆኖ ካነበብኳቸውም መፅሃፍት ሆነ መፅሃፍ ቅዱስ ከሚታየው የላይ ለውጥ ራሴን ውስጤን ስለመቀየር እንድጨነቅ ነው አብዝቼ የተማርኩት። ልብስና እህል በፍፁም ብርቄ አይደሉም። ስለእውነቱ ከእኩዮቼ በተሻለ የምፈልገውን በእድሜዬ አጊጫለሁ። እዛ እድሜዬ ላይ ቁሳቁስ የሚያሳስበኝ ሴት አልነበርኩም። ሀብት ካፈራሁ የምመኘው ከእርሱ ጋር ስለምናፈራው ሀብትና እኔና እሱ ከልጆቻችን ጋር ስለምንኖረው ድሎት እንጂ ጊቢ እገሊት የለበሰችው ቀሚስ ግድ የሚሰጠኝ ሴት አልነበርኩም።  ለእሱ ግን ለእኔ የሚያስፈልገኝን አለማሟላት ሞቱ ነበር። የቤተሰቤ ቤት የሚናፍቀኝ ...... የማያቸው ሰዎች የሚያስቀኑኝ ይመስለው ነበር ....... ላስረዳው ይቸግረኛል። 

ተማሪዎቹ ስልክ ስለነበራቸው የሱን ስልክ ለእኔ ሰጠኝ። 'ስትናፍቂኝ እኔ መጥቼ አይሻለሁ ስልክ እኔ ምንም አያደርግልኝም' አለኝ ስለእውነቱ ለእኔ ከሚያደርግልኝ በላይ ለእርሱ ያደርግለት ነበር።

አንደኛ ሴሚስተር አርባምንጭ ተማሪ በማባረር አንደኛ ነው ብለው አስፈራርተውኝ ስለነበር ድምፄን አጥፍቼ ትምህርት ላይ አደፈጥኩ። ያው በሳምንት ብዙውን ቀን ነው እሱጋ የማድረው ዶርም ያደርኩ ቀን ደግሞ ስለእርሱ እያወራሁ ሳደነቁራቸው አድራለሁ። እሱም በሳምንት ብዙውን ቀን ትምህርት ቤት ጊቢ ይመጣል። ማታ ከክላስ መልስ ጊቢ ውስጥ አቅፎኝ ሲንጎራደድ ትምህርት ቤቱን የገዛ ባለሃብት ነው የሚመስለው።  የሚያየን ሁላ ታድለሽ ባልሽ ደስ ሲል እንዲህ ዓይነት ባል ቢኖረኝ' የማይቀናብኝ የለም።

ነፃነቴን በሆነ መልኩ እንደያዘው ባውቅም አልጎረበጠኝም። ለምሳሌ ከጠዋት እስከማታ የለበስኩትን ያገሳሁትን የበላሁትን የሄድኩበትን የፈሳሁትን ፈስ ቁጥር ልክ የሚነግሩት ሰዎች አሉት። አውቃለሁ። ከእሱ ተደብቄ የማደርገው ነገር ስላልነበረ ግድ የለኝም። ቢበዛ 'ዛሬ ለብሰሽ የነበረው ቦዲ ግን አልሳሳም? ደረብ አታደርጊም?' ቢለኝ ነው። ወይም ከጓደኞቼጋ ሻይ ልንጠጣ ወደከተማ ስንወጣ ከየት መጣ ሳንለው ዱብ ብሎ ሰላም ብሎን ይሄዳል። ወይም ስንጨርስ 'ባልሽ ሂሳብ ከፍሎላችሁ ነው የሄደው' እንባላለን ሳናየው

"ይሄ መንፈስ የሆነ ባልሽ ትከሻዬ ላይ ዱብ እንዳይል" ይሉኛል ጓደኞቼ ሙድ ሲይዙ የሆነ ቦታ ስንሄድ

ደስተኛ ሆንኩ። ደሞኮ ብዙ የማልፈጀው ነገሬ ..... በቃ ደስተኛ አደረገኝ ...... የመጀመሪያ ሴሚስተር ውጤት መጣ። ሁሉንም ትምህርት A ሳመጣ ካልኩለስ B አመጣሁ። ካልኩለስ አስተማሪያችን ሴት ናት (ይሄን ፅሁፍ አታየውም ብዬ ተስፋ ላድርግ) ቂጧ ትልቅ የሚያምር ...... ስታስተምረን ፊቷን አዙራ አዳሜ ይቸክልና ልክ ስትዞር ሁሉም በልቡ ኤጭ የሚል አይነት ይመስለኛል። ያልሰራሁት ጥያቄ በጣም ቀላሉን ስለነበር በዛ ላይ ሴት መሆኔ በዛ ላይ ሌሎቹን በሙሉ A ማምጣቴ ይመስለኛል ቢሮ አስጠራችኝ።

"ከባዱን ሰርተሽ ቀላሉን ነው የሳትሽው" አለችኝ

"ካልኩለስ የመጨረሻ ቀን አልነበር? የልጄ ልደት ነበር ፈተናውን ቶሎ ሰርቼ ሀዋሳ መሳፈር ነበረብኝ ስቸኩል መሰለኝ የሳትኩት!" አልኳት

"ልጅ አለሽ?" አለችኝ

"አዎ ሁለት ዓመት ሆናት። ቤተሰቦቼጋ ነው ያለችው እኔና ባሌ እዚህ ነው የምንኖረው ብዬ " ያልተጠየቅኩትን መቀባጠር። ዝም ብልስ ኖሮ?
ደስ ብሏት ስታደንቀኝ ቆየችና ምንም ብፈልግ እንደምታግዘኝ ከጎኔ እንደሆነች እንደምታግዘኝ ምናምን ነገረችኝና

"ባልሽ እዚህ ከተማ ነዋሪ ነው?" አለችኝ ባትጠይቀኝስ እሷስ ቢቀርባት? እኔ ደግሞ ስለእሱ እንኳን ተጠይቄ ሳይጠይቁኝ የፍቅር እስከመቃብርን ትረካ ያህል ክፍሎች ያለመታከት እተርካለሁ።

"አዎ እገሌ ይባላል! እንዴ ታውቂዋለሽኮ የማታ ታስተምሪዋለሽኮ ስላንቺ እንደውም አውርቶልኛል .... ረዥም እንኳን .... ጠይም ቆንጆ ዓይኖቹ ትልልቅ ......" እኔ እለፈልፋለሁ እሷ ስሙን ከሰማች በኋላ ደንዝዛለች። በልፍለፋዬ መሃል አስተዋልኳት አሳዘንኳት ወይም ለራሷ አዘነች ወይም አላውቅም እጄን ጥብቅ አድርጋ ይዛኝ


"አባ በቃ ሙላልኝ እና አስገባ!" አልኩት ምክንያቱም የትና ምን እንደምፈልግ ያውቀዋል። እኔን

የሚያውቀኝ በሙሉ ያውቃል ህግ መማር እንደምፈልግ። ከተማ የመጀመሪያ ምርጫ ሀዋሳ ሁለተኛ አዲስ አበባ

ወደ እሱጋ ተመልሼ መጣሁ:: አቃቤ ህግ ነሽ ወንጀለኛ መቅጫ ብቻ ሊጠቅመኝ ይችላል ብዬ የማስበውን በሙሉ መፅሃፍ ከላይብረሪ እያወጣሁ ማንበብ ሆነ ስራዬ እዚህ ወቅት ላይ ምንም ተጨማሪ ፈጣሪዬን የምጠይቀው ነገር አልነበረኝም።

አዳራሽ ውስጥ ተቀምጠን በፕላዝማ ምድባችን ሲነገር ስሜ ብቅ አለ አርባምንጭ ዩንቨርስቲ FBE Faculty ...... ተማሪው አብሮኝ “WHAT?” አለ.... ዓይኔን ማመን አቃተኝ...

እግሬ እንዴት እየረገጠልኝ እቤት እንደደረስኩ አላውቅም። ለመጀመሪያ ጊዜ እሱ ከልቤ ግምስ ሲል ታወቀኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ ልለየው እንደምችል አሰብኩ። በቃ ለመጀመሪያ ጊዜ ሞልቶ ከጠበበው ልቤ ሲቀነስ ታወቀኝ።

"እንኳን ደስ ያለህ እዚሁ ነው የደረሰኝ" አልኩት ማታ ሲመጣ

"እማ እርቀሽኝ እንድትሄጂ ስላልፈለግኩ ነው። ....ስለማፈቅርሽ አንቺን ላለማጣት ......." እንባው ለመጀመሪያ ጊዜ የማንም ሰው እንባ ዓይነት ሆነብኝ።

"አላሳዝንህም? ቢያንስ ህግ እንደምማር አምኜ ያን ሁላ መፅሃፍ በፍቅር ሳነብ 'እማ ተይ የሞላሁልሽ ሌላ ነገር ነው እንዲህ አትልፊ አትለኝም?' ልቤ እንደሚሰበር መገመት ከባድ ነበር? አላሳዝንህም? የ5ተኛ ክፍል አስተማሪዬ እንኳንኮ ህግ መማር እንደምፈልግ ያውቃል። እንዴት አንተ ከአይንህ እንዳታጣኝ ህልሜን ትቀማኛለህ? እስቲ ራስህን ጠይቅ የእውነት ትወደኛለህ? እኔስ ራሴን ነጥቀኸኝ... ህልሜን ነጥቀኸኝ ... ከዛም ዝም ብዬ ማፍቀሬን ልቀጥል?"
......
.....
.....
................ አልጨረስንም.................

#Meri feleke


ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል ሰባት)

ይሄ ሁሉ ሲሆን በጌታ ነን 🤣🤣 በጌታ ፍቅር ጥላ ስር ሆነን ነው የምንፋቀረውም የምንቧቀሰውም። ቸርች እናስመልካለን። የምሬን የምፀልይለትስ “ጌታ ሆይ ቁጣውን እንዲገታ እርዳው” ብዬ እሱ በተቃራኒው “ጌታ ሆይ ዱላዬን የምትችልበት ፀጋ ስጣት!” እያለ እየፀለየ ይሁን እንጃ አይደለም ተመትቼ ጮክ አድርገው ተናግረውኝ ቤት የማምስ ልጅ ዝም አልኩ ......... ውርድ አልኩ.....

"ትቼለትለሁ የእኔን ጉዳይ ትቼለታለሁ የእኔን ታሪክ
መላ አለው እንዴት እንደሚያደርግ ያውቃል
ዘዴ አለው እንዴት እንደሚያደርግ ያውቃል"

የሚለው የሊሊ መዝሙር እየዘመርኩ ስነፋረቅ አመሻለሁ። ዛሬም ድረስ ስሰማት እንባዬ ይመጣልኮ

ጎበዝ ተማሪ ከመሆን ውጪ ለሌላ ምንም ምርጫ ጭንቅላቴ ዝግ ነው። ገና ትምህርት ቤት እንደገባ ህፃን ቦረቅኩ ሰው በማትስ ይወሰወሳል? በቃ በትምህርት ጠፋሁ ...... ከሱ ውጪ ጓደኞች ኖሩኝ። Bilen ቢዬ መጣች ...... ሳልነግራት ገባኋት። እሱን እንዴት እንደምወደው ማውራት ከጀመርኩ የሚሰማኝ ሁሉ ጤንነት አይመስለውም። ጓደኞቼን አስተዋወቅኩት ወደዱት። እያደር እየዋለ ግን በአጠገቤ ዝንብ ራሱ ብታልፍ ጾታዋን ማጣራት ጀመረ። እንዴት እንደምወደው እንዴት እንደማይገባው ይነደኛል። ወንድ አይደለም እኔ አይቼው እሱ አይቶኝ ነገር አከተመ። ችግሩ ትምህርት ቤት ውስጥ አንድ ነጠላ ማገር በህይወቷ ዝንፍ ያለባት የማልመስል ተጫዋች ነኝና ወንዱም ሴቱም ይቀርበኛል። እቤት ስመጣም ቆንጆ ነገር ይቀርብልኛል። "ቅድም አብሮሽ ሲገለፍጥ የነበረው ልጅ አስተያየቱን አልወደድኩትም ሁለተኛ አብረሽው እንዳላይሽ"

ቆዩኝማ መሆን የነበረበትኮ ተቃራኒው ነው። እኔ ነኝ መቅናት የነበረብኝ። ቁመቱ ሜትር ከ83 ሰውነቱ ገራሚ አይኖቹ ጥርሱ ከንፈሩ (ልጆቼን አይታችሁ መስክሩኣ?) የትም ቦታ ሄደን ሲያወራኮ ሴቶቹ አፉ ውስጥ ሊገቡ ትንሽ ነው የሚቀራቸው ሲቀልድ ሲያምርበት ሲኮሳተር ግርማ ሞገሱ ሲደመጥ (እየቀለድኩ አይደለም! አሁን ይሄንኑ ታሪክ እየነገራችሁ ያለው እሱ ቢሆን ተከርብታችሁ እንዲህ እየወደደሽ ቢቀጠቅጥሽ ምናለበት ቻዪው ነበር የምትሉኝ!! ፍቅርንማ እሱ ያውራት) የትም ብወስደውኮ ኩራቴ ነው:: ሁሉም ሰው ይወደዋል። እሺ በዚህ ላይ ፍቅር ችሎበት ..... በዚህ ላይ ስለምንም ርእስ ቢነሳ በሃሳብ መከራከር ችሎበት.... በዛ ላይ ጉዳዩ ላይ ጉድ አርጎኝ (ከዛኛው እሱ ውጪ ሌላው ነገሩ እኮ በምድር የሌለ ሰው ነው።)

የተለወጠው ነገር ልጄን ለማሚ ሰጥቻት ከመጣሁ በኋላ በጣም ተሰብሬ ስለነበር ድጋሚ እንዳይሰብረኝ ራሱን ይፈራው ነበር። ሲናደድ መማታቱን ትቶ ጥሎኝ ይወጣ ጀመር። እንደመፍትሄ የወሰድነው ያንን ነው። ከዛ ግን ትምህርት ቤት መዋሌ ለኔ ሳቅ ሲጨምርልኝ ለሱ ስጋት ሆነበት። አስተማሪዎቼን የክፍል ተማሪዎችን በሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ ያውቃቸዋል።

አንድ ቀን የሆነ ርእስ ተሰጥቶን በግሩፕ በተማሪ ፊት ከግሩፑ ሁለት ሰው ወጥቶ present ሊያደርግ አሳይመንት ተሰጠን። ከኛ ግሩፕ እኔና ሙሄ የሚባል ጓደኛዬ ተመረጥን። በደስታ ተቀብለን ተዘጋጀን!! የሚቀርብ ቀን 60 የማይሞላ ተማሪ ፊት ወጥቶ ለማቅረብ ፈራሁ። እኔ ሜሪ ሰው ፊት መቆም ፈራሁ ....... በ10 ዓመቴ በሺዎች ፊት ቆሜ ግጥም ያነበብኩ ልጅ ........ ማንንም ፈርቼ የማላውቅ ልጅ እጄን ሲያልበኝ አገኘሁት ........ የምወደው ነገርኮ በሰዎች ፊት ቆሞ ያን ሁሉ ጆሮ መያዝ ነበር .... የዛን ቀን ፍቅሬን ላለማጉደል ራሴ እየጎደልኩ እንደሆነ ገባኝ። "ደህና ነሽኣ?" ይለኛል ሙሄ መቶ ጊዜ ..... ይግባው አይግባው አላውቅም " ፈሪ ሆኛለሁ ማለት ነው!" አልኩት

"አንቺ? እኮ አንቺ ... በይ አትቀልጂ ..." ብሎኝ የሱን ፓርት ቀጠለ

የሆነው ሆነና ጨርሰን ስንወጣ አስተማሪያችን ለባሌ "ሚስትህ በራስ መተማመኗ ምናምን ...." ብሎ አዳንቆ ነግሮታል። ያለፉትን ዓመታት ምርጥ ከሚባሉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ በአንደኛው ስለተማርኩ ጥሩ መሰረት ነበረኝ። ...... እና ባልዬ ሊኮራብኝ ሲገባ (የትኛው ሰይጣን ሹክ እንዳለው መድሃንያለም ብቻ ነው የሚያውቀው) አቴንሽን ፍለጋ ሆነ ብዬ ሰበብ እየፈለግኩ ተማሪ ፊት እንደምቆም ነገረኝ። ከተፈጠረው ነገር ጋር ተደማምሮልኝ የዛን ቀን ፀቡን እኔው ጀመርኩት። ልክ ከሆነ ነገር እንደነቃ ሰው ሁሉም ነገር ዛሬ እንደተገለጠልኝ ነገር። ..... የተዋበች ቡጢዬን ቀምሼ ባበጠ ፊቴ ትምህርት ቤት ገባሁ። ወድቄ ነው አልኩ። ... ለመጀመሪያ ጊዜ ባሌ መታኝ ብዬ ለሰው ተናገርኩ። ለቢዬ !! ምሳ እየበላን ብቻችንን ቁጭ ብለን ነገርኳት። እቤት ስመጣ ግን ከፋኝ!! እሱን ማንም በዛ መንገድ እንዲያውቅብኝ አልፈልግማ!! ማንም እሱን ከዛ ማንም ከሚያውቀው ተወዳጅ ስብዕናው እንዲያወርደው አልፈልግም!!

አንዳንዴ ምልክት ኖሮኝ ትምህርት ቤት እገባለሁ:: ሙሄ "እሺ ዛሬስ ምንላይ ወድቀሽ ነው?" ይለኛል:: ቢዬ ታውቃለች:: .... የልጄ ናፍቆት ሊያስነቅለኝ ይደርሳል:: እንዲያም ሆኖ ዓመቱ አለቀ::

ማትሪክ ሰኞ ልፈተን ቅዳሜ እሱ ታመመ። ቅዳሜ ለሊት ሀኪም ቤት ሄድን። እጄ ላይ ያለው ገንዘብ 1000 ብር አይሞላም። ለሊት 6 ሰዓት ገደማ ነው። አሁኑኑ መተኛት አለበት ሰርጀሪ መደረግ አለበት ተባልኩ። የሆስፒታሉ በረንዳ ላይ በቂጤ ዘጭ ብዬ ተቀመጥኩ።

"ለምን? ምን አድርጊ ነው የምትለኝ? ለምንድነው አንዱን በአንዱ የምትጭንብኝ? እላይ ሆነህ ሙድ ነው የምትይዝብኝኣ? ለመሆኑ ትሰማኛለህ ግን?" ከሰው ጋር እንደሚያወራ ሰው ከእግዜሩ ጋር ጭቅጭቅ ጀመርኩ። ገንዘብ ልጠይቀው የምችለው ብቸኛ ሰው በዛ ሰዓት ቢዬ ብቻ ነበረች። ደወልኩላት!! ከእናቷ ጋር ሲመጡ ሳያቸው ላለማልቀስ ታገልኩ። ተኛ። ሆስፒታል እያደርኩ ፈተናዬን ተፈተንኩ።

ከሆስፒታል ሲወጣ ብር ስላልነበረኝ እናቴ ለሰርጌ የሰጠችኝን ወርቆች ሸጬ የሚደረገውን ሁሉ አደረግኩ። ሳድግ እንዳየሁት ሰው ከታመመ በግ ይታረዳል:: ወግ ነው ብዬ በግ ገዝቼ አሳረድኩ:: (እራሴው እንባባባባ ብል ይሻለኝ ነበር) ሲሻለው በቀረኝ ብር ለልጄ የሆነ የሆነ ነገር ገዝቼ ልጄጋ ሄድኩ። አንዳንዴ ምኑም አይገባኝም። ወርቆቼን እንደሸጥኳቸው ሲያውቅ እኔ ለሱ ብዬ የምሄደው ርቀት ሳይሆን የታየው "ለምን አልነገርሽኝም" ብሎ መቀወጥ ነበር። ደከመኝ። ልቤ ዛለ ...... የምር ደከመኝ። ..... ምን ባደርግ ደስተኛ እንደሚሆን አላውቅም:: ያስቆጣዋል ብዬ የማስበው ነገር ምንም ሳይመስለው ያልፋል:: ጭራሽ ያልጠበቅኩት ነገር እብድ ያደርገዋል:: ክረምቱን ልጄጋ ከሱ ተለይቼ አሳለፍኩ። እዛ እያለሁ ውጤት መጣ።

ውጤቴ መጣ። ከትምህርት ቤቱ ከፍተኛውን ውጤት አምጥቼ አለፍኩ። ቅብርር ያለ ውጤት አምጥቼ። ውጤቴን ያየልኝ እሱ ነበር። በስልክ እየነገረኝ አላስጨረስኩትም ሳቅና ለቅሶዬ ተደባለቀብኝ። ነፍስ ዘራሁ ነገር..... አለሁኝ አልኩ.... ለእናቴ ስነግራት እልልልልልልል አለች። አባቴ ውጤቴን ሲሰማ አቀፈኝ። በቃ ዝም ብሎ ለደቂቃዎች አቀፈኝ። ምንም ሳይናገር ሁሉንም አለኝ። .... ልጄ ይህቺ ናት ያለ መሰለኝ...... ኮራሁብሽ ያለ መሰለኝ..... ከዛ በኃላ ምንም ዳገት የሚወጣ አቅም እንዳለኝ አመንኩ:: .... ትችያለሽ አልኳት ራሴን!!!

የዛኔ ልክ ውጤት ሲመጣ ነበር የትምህርት ምርጫችንን የምንሞላው።


7 ሀይለኛ ትምህርቶች ከ "የጀመርከውን ሁሉ እንዴት መጨረስ እንደሚቻል" መጽሐፍ

1☀️. ያለ ርህራሄ ቅድሚያ ስጥ፡ ሁሉንም ነገር በአንድ ጊዜ ለማድረግ አትሞክር። ዋና እሴቶችዎን እና ግቦችዎን ይለዩ፣ ከዚያም ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ነገሮች ጋር የሚጣመሩ ስራዎችን በማጠናቀቅ ላይ ያተኩሩ። ቅድሚያ ለሚሰጡህ ቁርጠኝነት እምቢ ማለትን ተማር።

2. ⭐️ትላልቅ ስራዎችን ወደ ትናንሽ፣ እርምጃዎች ይሰብሩ: ከልክ በላይ ስራዎች ፓራላይዝድ ሊሆኑ ይችላሉ። ከትንሽ ጋር ስብራቸው፣ የበለጠ መተዳደር የሚችሉ ችንኮች። ይህ ያነሰ ያስመስላቸዋል እናም እድገትን እንደምታዩት ተነሳሽነት እንዲኖሮ ይረዳዎታል።

3. 🌈የማስተር ጊዜ አስተዳደር፡ ጊዜዎን በአግባቡ ለመጠቀም የሚያስችሉ ስልቶችን ይተግብሩ። እውነተኛ ቀነ-ገደቦችን ያስቀምጡ፣ ስራዎችን በስትራቴጂካዊ መንገድ ያስይዙ፣ እና ማዘናጊያዎችን ይቀንሱ። እንደ ጊዜ መከታተያ መተግበሪያዎች እና ተደራጅተው ለመቆየት ዝርዝሮች ያሉ መሳሪያዎችን ከግምት ያስገቡ።

4. ⚡️የእድገት አስተሳሰብን ይቀፍ፡ ፈተናዎችን ለመማር እና ለማደግ እድሎች ይመልከቱ። መሳሳትን አትፍራ በስኬትህ መንገድ ላይ መረገጫ ድንጋይ ሆነህ ተመልከታቸው። ምንም ያህል ትንሽም ቢሆን እድገትዎን ያክብሩ እና ከጓሮዎች ይማሩ።

5. 💥ራስን መንከባከብ አሳድጉ፡ ለደንነታችሁ ቅድሚያ ስጡ፡፡ በቂ እንቅልፍ ይውሰዱ፣ ጤናማ ምግቦችን ይመገቡ፣ አዘውትረው የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ያድርጉ፣ እና የሚዝናኑባቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ይሳተፉ። እራስህን መንከባከብ የጀመርከውን ለመጨረስ የሚያስፈልግህን ጉልበትና ትኩረት ይሰጥሃል።

6. 👥ተባበሩና ተባበሩ፡ እርዳታ ለመጠየቅ አትፍሩ። ስራዎችን ሲቻል ይሰርዙ እና የሌሎችን ባለሙያነት ይመርዙ። መተባበር የስራ ጫናዎን ማቅለል ብቻ ሳይሆን ትኩስ እይታዎችን ማምጣት እና እድገትን ማፋጠን ይችላል።

7.✨ ያንጸባርቁ እና ያስተካክሉ: በመደበኛነት ሂደትዎን ይገምግሙ እና አቀራረብዎን እንደ አስፈላጊነቱ ያስተካክሉ። ከተሞክሮዎችዎ ይማሩ እና ማሻሻል የሚችሉባቸውን ቦታዎች ይለዩ። እቅዶችህን በውጤታማነት የማያገለግሉህ ከሆነ ለመቀየር አትፍራ።



20 last posts shown.