አቡ_ሉቅማን የሱና እና የተውሒድ ቻናል


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


ተውሒድና ሱና የአንድነት ምንጭ ሲሆኑ
ሺርክና ቢድዓ ደግሞ የልዩነት ምንጭ ናቸው።
ስለዚህ ተውሒድና ሱና አጥብቀህ ያዝ
ሺርክና ቢድዓ ደግሞ በእጅጉ ራቅ
አላህ ቁርኣንና ሐዲስን በደጋግ ቀደምቶች መንገድ
አረዳድ ተረድተው ከሚጓዙ ምርጥ ባሮቹ ያርገን

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


    የሱብሂ ሶላት ትሩፋት

أَقِمِ الصَّلَاةَ لِدُلُوكِ الشَّمْسِ إِلَىٰ غَسَقِ اللَّيْلِ وَقُرْآنَ الْفَجْرِ ۖ إِنَّ قُرْآنَ الْفَجْرِ كَانَ مَشْهُودًا

ሶላትን ከፀሐይ መዘንበል እስከ ሌሊት ጨለማ ድረስ ስገድ፡፡ የጎህንም ሶላት ስገድ፡፡ የጎህ ሶላት (መላእክት) የሚጣዱት ነውና፡፡
ሱረት አል ኢስራእ 78

ሱብሕን የሰገደ በአላህ ጥበቃ ስር ነው” ረሱል ﷺ
【ሙስሊም】


ሱብሕን በጀማዐህ የሰገደ ደግሞ ሌሊቱን በሙሉ እንደቆመ ነው”
ረሱል ﷺ 【ሙስሊም】


ሱብሕን ለሰገድ መላእክት ይመሰክሩለታል፡፡
ረሱል ﷺ  እንዲህ ብለዋል፡- በናንተ ውስጥ የሌሊት
መላእክትና የቀን መላእክት ይተካካሉ፡፡

በፈጅር ሶላት እና
በዐስር ሶላት ላይ ይሰባሰባሉ፡፡

ከዚያም እነዚያ በናንተ ዘንድ ያደሩት 
ወደ ሰማይ ይወጣሉ፡፡
ይህኔም ጌታቸው በነሱ
ሁኔታ አዋቂ ሆኖ ሳለ “ባሪያዎቼን በምን ሁኔታ ላይ
ተዋቸኋቸው?”
ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡ “እነሱ እየሰገዱ ነው
የተውናቸው፡፡ እየሰገዱም ነው የመጣናቸው” ይላሉ፡፡
ቡኻሪና ሙስሊም


ትሰግዳላችሁ ወይስ ለሸይጧን ትሸነ ፋላችሁ ⁉️⁉️






ከወሳኝ ነቢያዊ ዱአዎች ውስጥ

ከዘይድ ቢን አርቀም (رضيﷲ عنه)ተይዞ ረሱል (ﷺ) ይህን ዱዓ ያደርጉ ነበር፡‐

”اللهمَّ إنِّي أعوذُ بك من علْمٍ لا ينفعُ، ومن قلْبٍ لا يخشعُ، ومن نفسٍ لا تشبعُ، ومن دعوةٍ لا يُستجابُ لها“

“አላህ ሆይ! ከማይጠቅም ዕወቀት፥ ከማይፈራ ልብ፥ ከማትጠግብ ነፍስ፥ ተቀባይነት ከሌለው ዱዓም በአንተ
እጠበቃለሁ።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 2722


http://t.me/Ibnu_Teymya_Ye_Ewket_Maed


"ሒጃባችሁን ካላወለቃችሁ ፈተና ላይ አትቀመጡም!" - ዶክተር ዘላለም

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብት ትምህርት መምህር ነው :: በዛሬው እለት 2ኛ አመት ተማሪዎችን final exam ይፈትን ዘንድ በገባበት ሒጃቢስቶችን ወይ ሂጃባችሁን አውልቁ ወይ ደግሞ ክላሱን ለቃችሁ ውጡ በማለት በእብሪት ተናግሯል :: የአንዲት እህትንም ሒጃብ ለማውለቅ ሙከራ አድርጓል :: ልትወጣ ስትል ተመለሺ ብሎ ተመልሳ ብትፈተንም እሷ ላይና ሌሎች ሒጃቢስቶች ላይ በሙሉ ፈርሟል ::

ድፍረት ነው ! ጋጠ ወጥነት ነው ! ሙስሊም ጠልነት ነው ! ጉዳዩን ጀመዓው ይዞ እስከ ጥግ ድረስ ይሄዳል :: መድረስ እስካለብን እንደርሳለን :: ሁላችሁም በንቃት ተከታተሉ ::

በሒጃባችን ላይ የሚሰነዘርን ምንም ነገር አንታገስም ! በየክላሳችሁ በሀይማኖታችን ላይ የሚቀረሹ መምህራን ካሉ በአላህ ይሁንባችሁ አትታገሷቸው :: በሚገባቸው ቋንቋ አናግሯቸው ::

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች


ሱረቱል ከህፍ ተጋበዙ
በቃሪእ አሊ ጃቢር አላህ ይዘንለትና


t.me/audioquranmp3


Forward from: ተቅዋ የሱና ቻናል
የሞተዉ ሼኻቸዉ ጨረቃ ላይ ታዩ ሲሉ አሁን ደሞ በረራ ጀመሩ .... እ


=


Forward from: ተቅዋ የሱና ቻናል
ለሴት ልጅ እስፖርት መለማመዷ ብይኑ ምንድን ነዉ

በታላቁ ሸይኽ ሙቅቢል ኢብኑል ሃዲይ አልዋዲኢይ ረሂመሁሏህ

🛑👉ጥያቄ?
ቤት ዉስጥም ይሁን ወይም ከቤት ዉጭ ሴት ልጅ እስፖርትን መለማመዷ የሸሩዓ ብይኑ ምንድን ነዉ?

🛑👉 መልስ
ቤት ዉስጥ ከሆነ ችግር የለበትም እንደዉም በዚህ ላይ እንመክራለን ከርሷጋ ስራ ካላት ስራዋ ተቀዳሚ ነዉ የሚሆነዉ፣ ማለትም ቤቷ ስራ ካላት በስራዋ ልትጀምር ይገባል፣ ልክ እንደዚሄዉ ከሴቶች ጋር ከሆነች አጅነብይ ሰዉ የማያያቸዉ ከሆነ በአሏህ ፍቃድ በዚህ ላይ ምንም ችግር የለበትም፣ እንደዉም በዚህ ላይ እንመክራለን፣
📚( غارة الأشرطة 2 / 469 )
=
t.me/teqwasuna


🔍ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይምያ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ።

ወደ አላህ ኪታብ (ቁርአን) መመልከትና መቅራትን እንደማብዛት የአቅልና የሩህ ምግብ የሆነ፣ አካልን የሚጠብቅና ደስታን የሚሰጥ የሆነ ነገር ምንም አላየሁም።

📚[مجموع الفتاوى 493/7]
=
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru


🔆" فَسَبِّحْ بِحَمْدِ رَبِّكَ وَاسْتَغْفِرْهُ ۚ إِنَّهُ كَانَ تَوَّابًا"
Poll
  •   A. ሱረቱ ነስር
  •   B. ሱረቱል በቀራ
  •   C. ሱረቱ ዘልዘላህ
  •   D. ሱረቱል ኢስራእ
31 votes


ሰለፍይ ፤ መንሀጀ-ሰለፍ ምን ማለት ነው?

🎙በኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም ሐፊዘሁላህ

የቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ።
👉 t.me/AbuMeryemNeja 👈


Forward from: ተቅዋ የሱና ቻናል
👉  ወጣቶች: 
ልጃገረዶችን ያበላሹና ከዛም
ጥሩ የሆነች  ሚስት ይፈልጋሉ:


ወንድሜ እውነታው ግን እንደዛ አይሆንም ምክንያቱም ሁለተኛዋ ላይ የምታገኛት
ሚስትህ የአንተው አይነት ስነምግባር ያላት ነው ምትሆነው:: አብዛኘው ወጣት girlfriend  ብሎ የያዛትን የዝሙት ጓደኛ በፍፁም አላገባም ይላል:: 
የምልህ ነገር ቢኖር የዝሙት ጓደኛህን ባታገባትም አንተ የምታገባት ሚስትህ ግን የሌላ ሰው የዝሙት ጓደኛ ነበረች::

ኢተቂላህ ያኣኺ ሴቶችን አደራ!!!!


የድን እውቀት ቀስ በቀስ ነው እሚሰባሰበው ያሙስሊሙን

በትንሽ አመታቶች ብዙን ዒልም አልቀሰምን ብለን ተስፋ አንቁረጥ

መታገላችንን እስታልተውን ድረስ መጠራቀሙ አይቀርም ሁሉም የትግሉን ያገኛል እመኑኝ ሁሉም የትግሉን ያገኛል

ከኛ እሚጠበቀው

1 ለድን ትምህርት ውዴታ እና ጉጉት እልባችን ላይ መያዝና መቊጠር
በልባችን የድን ትምህርትን ከቋጠርን ስንማረውም እየጣመን ነው እምንማረው

2 በየ አጋጣሚው ያለምንለትን የድን ትምህርት መቅሰም አለብን ያለ መሰላቸት

3 ሙራጃዓ ላይ ቦዘኔ መሆን የለብንም

4 ሀላፍትና ማብዛት የለብንም አላማችን ላይ እንደርስ ዘንድ ለሀላፍትናው እንደርስበታለን

እንትጋ እንማር 1 ቀን አላማችን አናት ላይ እንወጣለን

ደግሞስ ከ አመት አመት የሆነ ለውጥ አለን ሳህ እስኪ እናስታውስ የዛሬ አመት የት ነበርን ዛሬ የት ነን ለቀጣዩም አልፈን መገኘት አለብን በአላህ ፍቃድ

አብሽሩ


🛑👉በነገራችን ላይ ወሀብያ፣ ጃሚያ፣ መድኸልያ፣ ረስላንያ የሚባል መዝሀብ የለም። እነዚህ ለቀቦች የባጢል ሰዎች (በተለይ ሱፍዮች አህባሾችና ኢኽዋኖች) ለሀቅ ሰዎች የሚሰጧቸው የውሸት ስያሜዎች ናቸው።

📍ሸኽ መሀመድ አብዱል ወሀብ
📍ሸኽ መሀመድ አማን አልጃሚ
📍ሸኽ ረቢእ ቢን ሀዲ አልመድኸልይ
📍ሸኽ መሀመድ ሰኢድ ረስላን

ኡማውን የኻደሙ ዲንን የጠበቁ ባጠቃላይ ለሙስሊሞች በተለይ ደግሞ ለሰለፍዮች ትልቅ ውለታ የዋሉ እንደ አይናችን ብሌን የምንሳሳላቸው ውድና እንቁ ኡለማዎቻችን ናቸው።

የሞቱት አላህ ይዘንላቸው። በህይወት ያሉት ደግሞ እድሜያቸው ከመልካም ስራ ጋር ያርዝመው።

=
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru


🛑👉ቤተሰብን ስኬታማ  ከሚያደርጉ ምክኒያቶች፦
     

قوامة الرجل على أهله
🛑👉ባል በቤተሰቡ ላይ የበላይ ተቆጣጣሪ መሆን

ደስተኛ እና ስኬታማ ቤተሰብ ለመመስረት ከሚረዱ ምክኒያቶች መካከል አንዱ ባል በሚስቱ ላይ የበላይ እና ጠባቂ መሆኑ ነው ።

🛑👉ለዚህም አላህ በተከበረው መፅሐፉ እንዲህ ይላል፦

«ወንዶች በሴቶች ላይ ቋሚዎች (አሳዳሪዎች) ናቸው፡፡ አላህ ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ በማብለጡና (ወንዶች) ከገንዘቦቻቸው (ለሴቶች) በመስጠታቸው ነው፡፡»  ኒሳእ 34

🛑👉ይህ የበላይ አስተዳዳሪነት (ቀዋማ)፦

↝የኢስላም ውበት መገለጫ ነው።
↝የአላህ ፀጋ በኛ ላይ ሙሉ ለመሆኑም ማሳያ ነው ።
↝በውስጡ በጣም ብዙ መልካም ነገሮች አሉ።
↝ከወንድ አፈጣጠር  ጋር የሚሄድ ነው።

🛑→ይህ የበላይ ጠባቂነት ለባል የተሰጠው ሚስትን ለሚጠቅማት ነገር እንዲያስተካክላት  ነው ።

👉ሸይኽ ኢብን ሰዓዲ  አላህ ይዘንላቸዉና እንዲህ ብለዋል፦ "አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ወንዶች በሴቶች ላይ የበላይ (ቀዋም) ናቸው ብሎ ነግሮናል።

👉ይህም ማለት ፦ ወንዶች ሴቶችን የአላህን መብቶች እንዲሁም ግዴታ የሆነባቸውን ተግባራት እንዲፈፅሙ  እና ብልሹ ከሆኑ ተግባራቶች  እንዲታቀቡ ያደርጋሉ ማለት ሲሆን ፤  ወንዶች በዚህ ተግባር ላይ ሴቶችን ሊያስገድዱ ግድ ይላቸዋል ማለት ነው  ።

ከዚህም በተጨማሪ የወንዶች የበላይነት፦ ለሴቶች የቤት ወጪን በመስጠት ፤ልብስን በማልበስ እና የሚኖሩበትን ቤት በማመቻቸት ይገለፃል ። "
           ┈┈•••✿❒❒✿•••┈┈
{ أسباب سعادة الأسرة }
የሚለውን የሸይኽ ሱለይማን አሩሀይሊ መፅሐፍ ከገፅ 25 - 26 ይመልከቱ }

አላህ! ሀላፊነታቸውን አውቀው ከሚተገብሩ ባሮችህ አድርገን።


ወሳኝ የጥቢ፞ ህግጋት
~
በሃገራችን ወላጆች ልጆቻቸውን ጎረቤት ወይም ጓደኛ ዘንድ ጥለው ሲሄዱ የተተወባት እናት ልጁን ማጥባት የተለመደ ነው። ነገር ግን የሚከተለው ሸሪዐዊ ህግጋት እንዳለ ስለማያውቁ ለጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት አይሰጡትም። ይሄ ትልቅ ርእስ ስለሆነ እናቶች ተገቢውን ጥንቃቄና ክትትል ሊያደርጉ ይገባል።

በኢስላም ጥቢ፞ ከተራና አላፊ እለታዊ ክስተት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ ማለትም አጥቢና ጠቢን ያማከሉ ሰፋ ያሉ ሸሪዐዊ ህጎች ስላሉ ሙስሊሞች ተያያዥ ብይኖችን ማወቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ይህንን ከሚያረጋግጡ ማስረጃዎች ውስጥ አንዱ እናታችን ዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ ያስተላለፈችው ሐዲሥ ነው፡፡ በዚህ ሐዲሥ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
"الرَّضَاعَةُ تُحَرِّمُ مَا تُحَرِّمُ الْوِلَادَةُ".
“ጥቢ፞ መዋለድ (ከመጋባት) የሚከለክለውን ይከለክላል፡፡” [ቡኻሪ፡ 2646] [ሙስሊም፡ 1444]

ስለዚህ ጥቢ፞ ከስጋዊ ዝምድና ጋር የሚጋራቸው ነገሮች አሉ ማለት ነው። እነዚህም አራት ናቸው፡-

① ጋብቻ:–
በስጋ እናት ሰበብ ለመጋባት ክልክል የሆነ ሁሉ በተመሳሳይ በጥቢ፞ እናት ሰበብም ክልክል ይሆናል። ዝርዝሩ ወደፊት ይመጣል።

② እይታ (ነዞር):–
በስጋ እናት ሰበብ መመልከት የሚፈቀድ ሁሉ በተመሳሳይ በጥቢ፞ እናት ሰበብም የተፈቀደ ይሆናል። ስለዚህ እናቱን፣ እህቱን፣ አክስቱን፣… ማየት፣ መጨበጥ፣ መሳም እንደሚፈቀደው ሁሉ በጥቢ፞ ሰበብ ተመሳሳይ ብይን የሚይዙንም መመልከት፣ በሰላምታ መጨበጥና መሳም ይፈቀዳል። ስጋት እስከሌለ ድረስ።

③ ተገልሎ መቆየት:–
እንደሚታወቀው ለአንድ ወንድ ከአጅነቢያ ሴት ጋር ከሰው እይታ ተገልሎ መቀመጥ አይፈቀድም። ነገር ግን ከስጋ እናት፣ እህት፣… ጋር ተገልሎ መቀመጥ እንደማይከለከለው ከጥቢ፞ እናት፣ እህት፣ አክስትም፣… ጋርም ተገልሎ መቀመጥ አይከለከልም።

④ የጉዞ ጓደኛ መሆን:–
አንድ ወንድ ለወላጅ እናቱ፣ ለእህቱ፣ ለአክስቱ፣… የጉዞ ጓደኛ እንደሚሆነው ሁሉ ለጥቢ፞ እናቱ፣ እህቱ፣ አክስቱም መሆን ይችላል።

መጠነኛ ትንታኔ
~
1. አንድ ሰው ልጅ እያለ አንዲት ወላጅ እናቱ ያልሆነች ሴት ብታጠባው ያቺ አጥቢ እንደ እናቱ ትታሰባለች፡፡ ሴቶች ልጆቿ እንደ እህቶቹ፣ ወላጆቿ እንደ አያቶቹ፣ እህቶቿ እንደ የሹማዎቹ፣ ስታጠባው ጊዜ ያለው ባሏ እንደ አባቱ፣ የባሏ ወላጆች እንደ አያቶቹ፣ የባሏ እህቶች እንደ አክስቶቹ፣ የባሏ ሌሎች ሚስቶች እንደ አባቱ ሚስቶች፣ ባሏ ከሌላ ሚስት የወለዳቸው ልጆች ልክ እንደ እህትና ወንድሞቹ ይቆጠራሉ፡፡
የጠባችው ሴት ከሆነችም ተመሳሳይ ንፅፅር እንሰራለን፡፡ ባጭሩ የአጥቢዋ ወንዶች ልጆች ለጠቢዋ ወንድሞቿ፣ የአጥቢዋ ወንድሞች ለጠቢዋ አጎቶች፣ … ይሆናሉ፡፡ አጅነቢዮች አይሆኑም።
2. ልክ በመዋለድ (በስጋዊ ዝምድና) የተነሳ ለማግባት እንደማትፈቀድ ሴት፣ በጥቢ፞ የሷን ብይን የምትይዝን ሴትም (ለምሳሌ የጥቢ፞ እህት፣ የጥቢ፞ እናት፣ የጥቢ፞ አክስት፣ የጥቢ፞ የሹሜ፣ …) አንድ ወንድ ሊያገባ አይፈቀድለትም፡፡ ጋብቻ ተፈፅሞ ከሆነም መለያየት ግዴታ ነው፡፡

ማሳሰቢያ፡-
~
1. ዋጋ የሚኖረው ጥቢ፞ በሁለት አመት የህፃንነት እድሜ ክልል ውስጥ የተጠባ ጥቢ፞ ከሆነ ነው። [አልበቀራ: 233] ከሁለት አመት እድሜ በላይ እያለ የተፈፀመ ጥቢ፞ ከቁምነገር አይቆጠርም።

2· ጥቢ፞ው አምስት ጊዜና ከዚያ በላይ የጠባ ከሆነ ነው፡፡ [ሙስሊም: 1452]
አንድ ጊዜ ጡቱን ከያዘ በኋላ ለመተንፈስ፣ ውሃ ለመጠጣት፣ ወደሌላኛው ጡት ለመቀየር የሚኖረው ቆይታ ተፅእኖ የለውም። ረጅም ጊዜ ካልኖረ በስተቀር እንደ አንድ ነው የሚቆጠረው። ይሄ አንድ ተብሎ በዚህ መልኩ አምስት ጊዜ ከተጠባ የጥቢ፞ ህግጋት ታሳቢ ይሆናሉ። ከአምስት ጊዜ ያነሰ ጥቢ፞ ከግምት አይገባም፡፡

3. የጥቢ፞ ህግጋት የሚመለከተው የጠባውን አካል ብቻ እንጂ ያልጠቡ የስጋ ወንድሞቹንና እህቶቹን አይደለም፡፡ ማለትም የጠባው አካል ከጠባበት ቤት ቤተሰብ ይሆናል፡፡ እንጂ የሱ የስጋ ቤተሰቦች በሱ መጥባት የተነሳ ለጥቢ፞ እናቱ ቤተሰብ አይሆኑም፡፡

ምሳሌ፡- ፋጢማ፣ ሙሐመድን ብታጠባ እሷ ለሱ እናቱ ነች፡፡ ልጆቿም እህቶቹና ወንድሞቹ ናቸው፡፡ ሴቶች ልጆቿን እህቶቹ ስለሆኑ ሊያገባ አይፈቀድለትም፡፡ ነገር ግን ህጉ እሱን እንጂ የስጋ ወንድምና እህቶቹን አይመለከትም፡፡ ምክንያቱም የፋጢማ እናትነት ለሱ እንጂ ለነሱ አይደለምና፡፡

4. የጥቢ፞ ህግ እስከ መዋረስ፣ ቀለብ መስፈር፣ ለጋብቻ ሃላፊ (ወሊይ) መሆን አይደርስም፡፡ ማለትም ለምሳሌ በጥቢ፞ የተነሳ እናቱ ወይም አባቱ የሆነ ሰው ስለሞተ ንብረት መውረስ አይችልም፡፡ ለጥቢ፞ እህቱ የጋብቻ ወሊይ መሆን አይችልም። ለወላጅ እናቱ ቀለብ የመስፈር ግዴታ ስላለበት ዘካ መስጠት አይፈቀድለትም፡፡ ለጥቢ፞ እናቱ ግን ቀለብ ግዴታ ስላልሆነበት ዘካ መስጠት ይችላል፡፡

5. ጥቢ፞ ተከስቷል ወይስ አልተከሰተም በሚለው ላይ ጥርጣሬ ካለ መነሻ የሚሆነን ጥቢ፞ውን እንደሌለ መቁጠር ነው፡፡ በጥርጣሬ ላይ ተመርኩዘን የጥቢ፞ን ህግጋት አንተገብርም፡፡
የጥቢ፞ው መጠን ላይ ከተጠራጠርንም እርግጠኛ የሆንበትን ማለትም ዝቅተኛውን እንወስዳለን፡፡ [አልሙግኒ፣ ኢብኑ ቁዳማ: 7/537]

6· በጥቢ፞ ጉዳይ ታማኝ ከሆነች የአንዲት ሴት ምስክርነት ብቻውን በቂ ነው። ለምሳሌ አንዲት ሴት ቀርባ "ሁለቱንም አጥብቻቸዋለሁ" ካለች ምስክርነቷ ተቀባይነት አለው። ተጋብተው ከሆነ ይለያያሉ። [ቡኻሪይ: 2659]

7· የተብራራ ያልሆነ ድፍን ምስክርነት ተቀባይነት የለውም። ስለዚህ የጥቢ፞ውን ዘመንና ቁጥር በተጨባጭ መግለፅ ያስፈልጋል። ይሄ ባልሆነበት የጥቢ፞ን ህግጋት አንተገብርም። [አልሙግኒ፣ ኢብኑ ቁዳማ: 7/537]

አዋቂው አላ፞ህ ነው። እርምት ያለው ሰው ቢያጋራኝ ደስ ይለኛል።

(ኢብኑ ሙነወር፣ ረቢዑል አወል 17/1441)
(ህዳር 04/2012)
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor

* የዋትሳፕ ቻናል፦
https://whatsapp.com/channel/0029VaA3X1e5kg7BlsJboa2M

* ፌስቡክ
https://www.facebook.com/Ibnu.Munewor?mibextid=ZbWKwL


ለሰዎች ስትል አሏህን አታምፅ!

አሏህን የመፅክላቸው ሰዎች ልብ በአሏህ እጅ ነው እንደፈለገ ያደርገዋል ነጋ የንተ ጠላቶችህ ሊሆኑ ይችላሉ ከአሏህ ጋር አትጣለ !

ሁሌም አስተውል አሏህን ባመፅክበት ልክ የአሏህ ማዋረድ/ ኹዝላን ተከትሎክ ይመጣል !

የነዚያን ታሪክ ተመልከት ስላለፈ ተመልሶ አይመጣም አትበል!

ለሀቅ ፣ ለሱና ፣ለተውሒድ ፣ ለጀማዓ፣ ለኢስላም ፣ ልብ ሰጥተህ ምን ልባል እችላለው ሳትል በተባልክበት ሳትበገር በሱናህ ፅና ሀቅን ግለፅ !

በሁሉም ስራ ለይ አንተ ተፈላጊ ነህ መረጃህን ካአሁኑ አዘጋጅ 100% እርግጠኛ ነህ ምክንያት ንፁ ነው ?

ለምን ሰራህ? ለምን ተናገርክ ?ለምን ተውክ ?ለምን ራቅክ ?ለምን ቀረብክ ? ሁጃክ ሁሉ ትክክል ነውን?

ነገር ግን እወቅ አስተውል አሏህ ስለአንተ ካንተ በላይ አዋቂ ነው በምንም ብለህ ማምለጥ አትችልም በሁሉ ነገራችን አሏህን እንፍራ!

አሏህን የሚገባውን ፍረሃት ከሚፈሩት ባሮቹ ያድርገን

  ቻናል:-
t.me/hafugraphics


🥀የፈጅር ሰላት ለሀሳብ ለጭንቀት  ለችግር ለሀዘን ሁሉ መድሐኒት ነው:: አል ወዱድ ከፈጅር ሰዎች ያድርገን🥀


እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሰይጣንን እርምጃዎች አትከተሉ፡፡ የሰይጣንንም እርምጃዎች የሚከተል ሰው (ኀጢአትን ተሸከመ)፡፡ እርሱ በመጥፎና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ በእናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ ከናንተ አንድም ፈጽሞ ባልጠራ ነበር፡፡ ግን አላህ የሚሻውን ሰው ያጠራል፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡

ሱረቱል አል ኑር [ 24 : 21 ]


✍ከሰጋጆች ነን ወይስ እነኛ ለሸይጧን ከተሸነፉት⁉️


ቁርአንን በተጅዊድ ለመማር ለምትፈልጉ በሙሉ:-

ከጀማሪ እስከ ሒፍዝ ድረስ በኦንላይን መርሐ ግብር ለመማር ፍላጎቱ ላላችሁ ተማሪዎች ምዝገባ እያደረግን ሲሆን ለመማር የምትፈልጉ ከታች ባለው የቴሌግራም አድራሻ ምዝገባዎን ያድርጉ።

ማሟላት የሚገባችሁና ተጨማሪ ስለ መድረሳው ገለፃዎች
  ህግና ደንቦቹ
- ከመድረሳው ጋር ጥሩ ስነምግባር ማሳየት
- የቂርአት ሰአትን ጠብቆ ለመቅራት ቆራጥነት
- በአሳሳቢ ምክኒያት ከቀሩ ማስፈቀድ


የቂርአቱ ሰአት :- ማታ ከዒሻ በኋላ
ወይም ጠዋት ከሱብሒ በኋላ

ስትመዘገቡ ከጧቱና ከማታው ክፍለ ጊዜ የትኛው እንደሚመቻችሁ አብራችሁ ማሳወቁን አትርሱ!

ለመመዝገብ :- 👇👇
@allahumesolialamu
@Abu_luqman_ibn_idris

«ቁርአንን አስተካክለህ ማንበብን አንብበው»


🔅 ሰላት ከተገለፀባቸው መገለጫዎች ውስጥ
Poll
  •   A. አሰላቱ ኑር
  •   B. አሰላቱ ቡርሀን
  •   C. አሰላቱ ጀናህ
  •   D. A. እና B.
42 votes

20 last posts shown.