በኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በየአመቱ 53,000 ሰዎች በካንሰር በሽታ ህይወታቸውን እያጡ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ተናገረ‼️
80,000 ሰዎች ደግሞ በየዓመቱ በካንሰር ህመም ይያዛሉ ሲባል ሰምተናል።
ወሬውን የሰማነው #የካንሰር_በሽታን ለመከላከል እንዲሁም ታማሚዎችን ለማገዝ መቋቋሙ የተነገረው ‘’በልሻ ፋውንዴሽን’’ ምስረታው ይፋ በተደረገበት ስነ ስርዓት ላይ ነው።
በሰውነት ውስጥ ያሉ ሴሎች ሲበዙ ወይም ከመጠን በላይ ሲያድጉ በሚፈጠረው የካንሰር በሽታ በኢትዮጵያ ያለው ስርጭት እየጨመረ መሄዱ ተነግሯል።
በኢትዮጵያ ብዙ ሰዎችን እየያዘ ያለው እና እየገደለ ያለው የካንሰር አይነት #የጡት_ካንሰር ሲሆን የአንጀት ካንሰር ደግሞ ይከተላል።
ለካንሰር በሽታ አጋላጭ የሆኑ ሲጋራ ማጨስ፣ ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ፣ አልኮል አብዝቶ መጎንጨት፣ የአየር መበከል፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ።
በኢትዮጵያ በካንሰር በሽታ በየዓመቱ 53.000 ያህል ሰዎች እንዲሞቱና አሃዙም በየዓመቱ እንዲጨምር ያደረገው ዋነኛው ምከንያት ስለ በሽታው ህዝቡ ያለው ዝቅተኛ አመለካከት ነው ሲሉ የጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ድኤታ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ሌሊሳ አማኑኤል ተናግረዋል።
ብዙውን ጊዜ በካንሰር የተያዙ ሰዎች ወደ ህክምና ማዕከላት የሚሄዱት በሽታውን ታክሞ ለመዳን አስቸጋሪ በሆነበት 3ኛ እና 4ኛ ደረጃ ላይ ከደረሰ ብኋላ ነው ሲሉ ሚኒስትር ድኤታው አስረድተዋል።
በየጊዜው የጤና ክትትል አድረጉ፣ ጮማ መቁረጥን የመሳሰሉ ጤናማ ያልሆኑ አመጋገቦችን አስወግዱ፣ አይበለውና በበሽታው ከተያዛችሁም በጊዜ ህክምናችሁን ጀምሩ ሲሉ አቶ ሌሊሳ ጥሪ አቅርበዋል።
መንግሥት የካንሰር በሽታ ተፅዕኖን ለመቀነስ የህክምና መስጫ ማዕከላትን ማብዛት፣ የባለሞያዎች ስልጠና፣ የመድኃኒት አቅርቦትን ማስፋት ላይ እየሰራ አንደሆነ አማካሪው ጠቅሰዋል።
ዛሬ ምስረታው ይፋ የሆነው የበልሻ ፋውንዴሽን ስያሜውን ያገኘው ነዋሪነታቸውን በአሜሪካን ሀገር አድርገው በነበሩትና በበጎ አድራጎት ሥራቸው በሚታወቁት ወ/ሮ በለጠች ሞላ (በልሻ) መሆኑ ተነግሯል።
እኚህ በጎ አድራጊ ሕይወታቸውን ያጡት በካንሰር ህመም በመሆኑ በእሳቸው ሕልፈት ሐዘንና ቁጭት ያደረባቸው ባለቤታቸው፣ ቤተሰባቸውና ወዳጆቻቸው የበልሻን የበጎ አድራጎት ሥራ ለማስቀጠል እና እሷን የነጠቃቸውን ካንሰርን ለመዋጋት በማሰባቸው ይህ የበጎ አድራጎት ድርጅት እንዲመሠረት ምክንያት ሆኗል ሲባል ሰምተናል፡፡
ፉውንዴሽኑ የካንሰር በሽታን የመከላከል ሥራ ይሰራል፣ ህሙማን የህክምና አገልግሎት እና ድጋፍ እንዲያገኙ ያግዛል ሲሉ የበልሻ ፋውንዴሽን መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ እንዲሁም የወ/ሮ በለጠች ሞላ ባለቤት አቶ አበበ መብራቴ ተናግረዋል።
በካንሰር እና በሌሎች ምክንያቶች ወላጅ አልባ የሆኑ እና ለችግር የተጋለጡ ህጻናትን መደገፍ እና መንከባከብ ሌላው ፋውንዴሽኑ የተቋቋመለት አላማ መሆኑ ተነግሯል።
Sheger
====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2shttps://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s