ትዝብተ-በርናባስ🔎✍️


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


ምድር እጅግ ሰፊ ናት፤ እኔ ወንድማችሁ በርናባስ ደግሞ ያሉኝ ሁለት ዐይኖች ብቻ! አባካችሁን ኑ...ና አጋጭተን (ዐይኖች አዋጥተን) እንይ!✍️
አሳብ አስተያየት ቢኖራችሁ፦ @barnica የግላችሁ ነው።

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የልደቱ እለት ስፍራ የለንም የተባለለት እርሱ የፍጥረተ ዓለሙ ፈጣሪ፣ በአዳም ልጅ ጠባብ ደረት ሊለካ የመጣው ይህ ሕጻን ሰማያትን በስንዝር የለካ ነው።

...እንደ ማንኛውም ጨቅላ ሕጻን እናቱ በመጠቅለያ የጠቀለለችው እርሱ ዓለማት የሚጠቀለሉበት የእግዜሩ የድነት ታሪክ ድውር ዘዋሪ ነው።

ሙሉውን መልእክት ከታች ባለው ሊንክ ታገኛላችሁ።

ይኸው!

👇

https://youtu.be/J90hsSlXE3E?si=rgGxT5xn75xkBMJh


ለደስታ ሳይሆን ከደስታ ተነስተህ ሥራ!
-----●---

እውነተኛ እርካታና ደስታ "ተፈጥሮ ያለ እኔ (አስገኚዋ) እርካታ አይሁንላት" ብሎ የደነገገው እግዚአብሔር ዘንድ ነው።

ይህን አጭር መልእክት በዩቲዩባችን ገብታችሁ ታደምጡ ዘንድ ግብዣዬ ነው። በዚያውም ቤተሰብ ካልሆናችሁ በቶሎ ተቀላቀሉ። አለዚያ... እወዳችኋለሁ። 😊

👇
https://youtu.be/izGTPMBqqeI?si=vOcgRy077SW1lJCi


እየበላሁ የምበላው ነገር!
----◉---

#እኔ፦ Mesye እንዴት ነሽ? ሥራ በዝቶብኝ ምሳዬን አሁን ገና ነው የወጣሁትና ይኸው አዝዣለሁ፣ በልቼ (ከበላሁ በኋላ) ልደውልልሽ?

#Mesy፦ እሺ ባርኒ፣ ካልሆነም ለምን እየበላህ አናወራም (ነገሩ አመሻሽ ላይ ባለን የሥራ ስብሰባ ቀድሞ መረጃ ልንለዋወጥ ነው) መሲ ጎበዝ ናት፤ የተዝረከረከ ነገር አትወድም፤ ነገሩ ላይ ቶሎ አውርተን መስመር እንድናስዝ የፈለገች ይመስላል።

#እኔ፦ መሲዬ እየበላሁ ማውራት አልችልም፤ እየበላሁ ማድረግ የምችለው መብላት ብቻ ነው (ስበላ እየበላሁ ነው የምበላው)።

#Mesy፦ ለምንድነው እየበላህ ማውራት የማትችለው?

#እኔ፦ የምር የተለየ ሕግ ሆኖ አይደለም፤ ግን devotedly (በሙሉ ልቤ) መብላት እንድችል ስበላ አስቸጋሪ ካልሆነ ተጓዳኝ ነገር አላደርግም።

#Mesy፦ በል እንግዲህ በልተህ ደውል!

#እኔ፦ እሺ መሲዬ! (ይኸው ምግቡ እስኪደርስ ነው ይህን የጻፍሁላችሁ)።

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ነብይ እመስላለሁ እንዴ? 😥
----◉----
ከበርናባስ በቀለ

በአናስሞስ አሳታሚ (ጸዴ ጅማሮ) የቀረቡልን መጽሐፍት ምረቃ መርሓ ግብር ተካፍለን እየተመለስን ነው። ሰማዩ ጠቋቁሯል፤ ፋኑ እየነዳ ነው። መገናኛ (የቀድሞ ዲያስፖራ አደባባይ) እንደተሻገርን አንድ ትራፊክ ፖሊስ አገኘን። ቆምን፤ ፋኑ "ውይ ይኽ ሰው ይዞናል በቃ" አለ።

#ትራፊኩ፦ "መንጃ ፈቃድ ይዘሃል?"

#ፋኑ፦ "አዎን፤ 'መዥለጥ!' ይኸው።"

#ትራፊኩ፦ "ግን አልታደሰም።"

#ፋኑ፦ "አዎን፤ ልክ ነው። አንድ ወር አልፎበታል፤ በማልችልበት ሁኔታ ውስጥ ስነበርሁ አላደስሁም።"

#ትራፊኩ፦ "ቦሎም አልለጠፍህም!"

#ፋኑ፦ "አዎን! ይኸው" አለና ከዳሽ ቦርዱ ለይ አንስቶ ሰጠው። እስክትሎም "ከቤት ስወጣ መለጠፊያ አላገኘሁም ነበርና ለዚያ ነው፤ ይቅርታ እለጥፈዋለሁ አባ" አለ።

#ትራፊኩ፦ "እሺ፣ ሦስተኛ ወገን ይዘሃል?" እኔ በልቤ፦ ከዚህ አገር ግን ወገናዊነት መቼ ነው የሚገረሰሰው? እያልሁ አጉተመትማለሁ፤ ለካ ነገሩ ወዲህ ነው።

#ፋኑ፦ "ሦስተኛ ወገን! ይዣለሁ" ብሎ መፈላለጉን ቀጠለ...

ፋኑ ግን ምን ሆኖ ነው? ርሱ እኮ ለእኔ ግልጽና ታማኝ ወንድም እንደሆነ ነው የማውቀው። ገና ከEGST ስንነሳ ለምን ይህን ሁሉ አላጫወተኝም? ለምንስ መንጃ ፈቃዴን አላደስሁም፣ ቦሎ አልለጠፍሁም ሲያልፍም 3ኛ ወገኑን ፊት ለፊት አላደረግሁም" አላለኝም? ይህን ሁሉ ከእኔ የሰወረው ለምን ይሆን!? መኪና እንደያዘ ነበር የነገረኝ፤ እነዚህን ካልያዘ ትላንት እኮ ፋኑዬ መኪና አልያዘም፤ ለምን መኪና ይዣለሁ አለኝ!? በውጭ ቆሜ እነዚህ ሃሳቦች በአዕምሮዬ ይመላለሳሉ። ደግሞ እኮ ከሳር ቤት ሳንነሳ ቢነግረኝ እኔ አግዘው ነበር፤ መኪናው ውስጥ ባለመግባት!😊

#ትራፊኩ፦ ፊቱን ወደ እኔ አዞረ፤ "አንተ ነብይ ነህ አይደል?" አለኝ።

#እኔ፦ አይ... ነብይ እንኳን አይደለሁም! ግን አስተማሪ ነኝ፤ እኔም ባለ መንጃ ፈቃዱ ወዳጄም። ከመኪናው ወርጄ ትንሽ ጨዋታ ጀመርን... ፋኑ 3ኛ ወገን ከፋይሎቹ ውስጥ እየፈለገ ነው።

#ትራፊኩ፦ "ከመኪናው ውስጥ ለምን ወረድህ?"

#እኔ፦ ቁጭ ብዬ እንዳላወራህ ብዬ ነው። ሁለታችንም (እኔም በወንጀሉ ተጠርጣሪው ወዳጄም) ቁጭ ብለን ከምናወራህ እኔ በውጭ ቆሜ ርሱን ብታነጋግረው ይሻላል ብዬ ነው (መገሰጽም ካለብህ)።

#ትራፊኩ፦ "ቁጭ ብትል ምን ችግር አለው?"

#እኔ፦ አንተ ፊት ስቆም ሕግ ፊት እንዳለሁ ነው የማስበው፤ አንተንና ይህን ኃላፊነት የሰጠህን ሕዝብ ማክበር ነበረብኝና ነው የቆምሁት፤ ይህን ስልህ ታዲያ ሁሉም ሰው ይህን ማድረግ አለበት እያልሁህ አይደለም፤ እኔ በዚህ ሰዓት በጥፋት ፊትህ ስንቆም የተሰማኝን ነው ያደረግሁት። ጭንቅላቱን ነቀነቀ...(ነቢያት ግን ከመቼ ነው እንዲህ ሥርዓት የያዙት እያለ ያለ ይመስላል😊)

ልብ አድርጉ አሁንም ፋኑ የ3ኛ ወገን ዶክመንቱን እየፈለገ ነው። የፋኑ ችግር መኪናው ውስጥ የሚነበቡ ማቴሪያሎች (መጽሐፍት) ያበዛልና "የትኛው መጽሐፍ ውስጥ ተሰግስጎ ይሆን!?" እያለ ፍለጋውን ተያይዟል፤ እኔና ትራፊኩ በውጭ ሌላ ታሪክ ውስጥ ገብተናል...

#ትራፊኩ፦ "የሚገርምህ፤ አንተን የሚመስል ነብይ እዚህ ከተማ አለ። ብቻ ግን አገልጋይ ነገር ነህ። አስተማሪ ነኝ አልኸኝ? "ከነቢያቱ ጋር አገናኙማ (አትስማሙማ)!"

#እኔ፦ ምናልባት አንዱን መጽሐፍ ይዘን የተነሳን መሆናችን ያገናኘን ይሆናል፤ ፈገግ አለ። ፋኑ 3ኛ ወገኑን አግኝቷል። "ይኸው!" ብሎ ጨዋታችንን አቋረጠ! ይህን ስታነቡ ትራፊኩ እንዳይቀጣን በውጭ ቆሜ እየጀነጀንሁ ያለሁ መስሏችሁ ይሆናል (ድሮም እናንተ)!😊 ግን በፍጹም እንደርሱ አይደለም ሃሳቤ፤ ሲጀመር ፋኑ እንደምንቀጣ አውቆ ክፍያውን ሁሉ ማዘጋጀት ጀምሮ ነበር።

በመጨረሻም፦ መንጃ ፈቃዱን መለሰልን! "ይኸው! ቶሎ አድሱ። ቦሎውንም ለጥፉ!" እናመሰግናለን ብለን ጉዟችንን ቀጠልን።

ከዚያ ከፋኑ ጋር መንገዳችን ላይ ነገር ተጀመረ! አንተ ይህን ሳትይዝ እንዴት ትወጣለህ? ስንት ራዕይ ያለኝን ሰው መንገድ ላይ አስቀርተኸኝ ነበር እኮ (ማለቴ መሽቶ ነበርና ወደ ሰፈር ታክሲ አላገኝማ!) እያልሁ መጠነኛ ግሳጼ ቢጤ ሰጥቼዋለሁ። 😊

ቀጥዬም ጠየቅሁት፦ ፋኑዬ ምኔ ነው ግን ነብይ የሚመስለው?😥 እርሱም "ሁሉ ነገርህ" እኔም ታዲያ አንተና ወንድሞችህ ለምን አልተገዛችሁለኝም!? (መቼስ ትራፊኩ ያመሳሰለኝ ያለው ሕዝቡን ለጥቅማቸው አስጨንቀው ከሚገዙ ነቢያት ጋር መሆኑ ግልጽ ነውና)።

ከሰማነው ነገር ዋናው ቁም ነገር፦ በቃ እዚህ አገር "ነቢያቱ" እና "የቃሉ አስተማሪዎች" ሊስማሙ እንደማይችሉ በሁሉም ዘርፍ ባለሞያዎች ጭምር ተረጋግጧል ማለት ነው!? ሌላው፦ ቆይ እኔ ምኔ ነው ነብይ የሚመስለው!? እሺ፣ ነብይ ማንን?

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


መሬት መንቀጥቀጡ!
----◉-----

የመሬት መንቀጥቀጡ ነገር ትንሽ ጋብ ብሎልን ነበር፤ ግን ከጥቂት ሰዓታት በኋላ በአይነቱ ለየት ያለና በሬክተር ስኬል ከፍተኛ ቁጥር ሊመዘገብበት የሚችል ርዕደ መሬት ሊከሰት እንደሚችል አንዳንድ የመረጃ ምንጭች እያመለከቱ ነው። ማለትም፦ ትራንፕ ምርጫውን ካላሸነፈ!😊

ደህና ናችሁ? ካሚላ ታሸንፍ ትራንፕ? ወይስ አይመለከታችሁም? "ጦሴን ያላችሁ ደግ አደረጋችሁ! ግን ስለ ምርጫው መስማት አልፈልግም ብትሉም ከውጤቱ ግን ነጻ መሆን አትችሉም። ለማንኛውም እግዚዖ እያልን ውጤቱን እንጠብቅ! አይመስላችሁም? ከአያያዙ እንዳስተዋልሁት ትራንፕ ካላሸነፈ የመሬት መንቀጥቀጡ አይቀሬ ነው። ምን አለ በሉኝ።

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ሁሉ እያለው ግን በተውሶ ሊሠራ ሁሉን ያጣ ንጉሥ ማነው?

ለምን ይህን አስቸጋሪ መንገድ መረጠ? ይህ አጭር ቪዲዮ ምላሽ አለው!

SUBSCRIBE ብናደርግ ደግሞ ብዙ ሥራዎችን ይዘው ሊመጡ ያሉ አዘጋጆቹን እናበረታታለን!


https://youtu.be/LaV4uUNxgyo?si=LT6Sz7pplrQjlTPr


የዘፋኞች ሰማያተ መንግሥት
----◉-----
ከበርናባስ በቀለ

#ጎበዙ (ወጣቱ)፦ ደወለ፣ አስከትሎም፦ "ዘፋኞች መንግሥተ ሰማያት አይገቡም (አይወርሱም) አይደል?"

#እኔ አንተ ትገባለህ?

#ጎበዙ "እንዴ፤ በቀጥታ መልስ እንጂ ባርኒ theology አታድርገው!"

#እኔ እና የጠየቅኸኝ ሃሳብ እንደ መሬት መንቀጥቀጡ ጉዳይ Geology የሚመልሰው ነው? የጠየቅኸኝ መስማት የምትፈልገውን እንድነግርህ ከሆነ ቀጥዬ ለማውራት እቸገራለሁ።

#ጎበዙ "እሺ፤ አንተ ገብተሃል/ወርሰሃል? አልኸኝ? እኔማ ገብቼ እኮ ነው ስለ'ነርሱ የጠየቅኩህ፤ በመንግሥቱ ያልሆነ ፍጥረታዊ ሰው ይህን ጥያቄ ይጠይቃል? አይመስለኝም።"

#እኔ ኦውው! ከውስጥ ወደ ውጭ ነዋ ጥያቄው?

#ጎበዙ "ይህን አጥተኸው አይደል መቼስ!"

#እኔ እሺ፣ በእግዚአብሔር መንግሥትስ ተወርሰሃል?

#ጎበዙ በርግጥ በጥቂቱ፤ ቢሆንም እርሱ በሂደት የሚቋጭ አይደል ባርኒ?

#እኔ መቼ ነው የምትወረሰው? በመንግሥቱ ለመወረስ ምን አቅደሃል? በእነዚህ ጊዜያት ምን እየሠራህ ነው? ምናልባትም ከዘፋኞቹ ንጽረተ ዓለምና የሕይወት ፍልስፍና የአንተን ተግባራዊ ክርስትና የሚለየው ምንድነው? እንደ ማኅበረሰብ ስታስብስ ይህን እንዴት ታየዋለህ?

#ጎበዙ "ኡ! ትንሽ አወሳሰብክብኝ! ስለ ጥቅሱ (አይወርሱም ስለሚለው) ብቻ አስረግጠህ እንድትነግረኝ ነበር አደዋወሌ (ከልጆች ጋር እያወራን)።"

#እኔ መጽሐፍ ቅዱስ የጥቅሶች ስብስብ አይደለማ! እንደውም የአንተ በመንግሥቱ የመወረስ ጉዳይ ስንመክር (ስንጫወት) ስለ ዘፋኞቹም በሂደት እናወራለን ወንድ'ማለም። የእግዚአብሔርን መንግሥት ምንድነው? መውረስ/ መግባት ማለትስ ምን ማለት ነው? ሲቀጥል፦ "ይገባሉ አይገቡም!" ረጅም ከምናወራ እንዴት በወንጌሉ እንድረሳቸው? የሚለው ላይ እንምከር፤ ዘፋኞቹስ እነማናቸው? የሚለውንም እየለየን እያደር እንመክራለን፤ አትጨነቅ።

#ጎበዙ አንተ ጋር ደውዬ ግን በቀጥታ ምላሽ የማገኘው መቼ ይሆን?

#እኔ ምናልባት በቀጥታ ማሰብ ስጀምር (ፈገግን😊)፤ ደግሞ ቀጥታ ራሱ ምንድነው? በቃ በርታልኝ፤ እናወራለን።

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ስለ'ርሱነቱ የተሰዋ እኔነት!
----◉-----
ከበርናባስ በቀለ

ቸርነትህ ያቆመው፣ ምህረትህ የደገፈው፣ መግቦትህ ዋስትናው የሆነው፣ ታማኝነትህ ያጸናው፣ ዘላለማዊነትህ በሕይወት ያኖረው፣ በጎነትህ ቀኑን ያበራለት፣ ታጋሽነትህ የተሸከመው ርሱነቱን ስለ አንተነትህ እየሰዋ ይኖራል፤ ርሱነቱ 'ያንተነትህ ምልክትና ማሳያ ነውና!

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ዓለማትን የፈጠርህ የደኅንነታችን አምላክ እግዚአብሔር ፍጡር በሕያውነት ይቀጥል ዘንድ ብቸኛው ተስፋና የዋስትናው መሠረት ነህ። ያልተደገፈብህ ለነፍሱ መድኅን አላገኘም፤ ትምክህቱ ያላደረገህ ለፍጻሜው ተስፋ አልዘየደም!

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ከመሬት መንቀጥቀጡ በኋላ...
----◉-----
ከበርናባስ በቀለ

ትላንት ምሽት አዲስ አበባና በአካባቢው የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ (እነርሱ ንዝረት ነው ብለዋል፤ እኔ ግን እላለሁ፦ መንቀጥቀጥ ነው!😶) የእኛንም ሰፈር ለደቂቃዎች በአንድ እግሩ አቁሞት ነበርና ሰው እየሮጠ ሲወጣ እኔና ቤቴም ከሕንጻው ወደ መሬት ስንወርድ ከለበስነው የምሽት (የቤት ውስጥ) ልብስና በእጄ ከያዝሁት ስልክ በቀር ምንም ይዘን አልወጣንም።

ከሰፈሩ ሕዝብ ጋር በውጭ ስንገናኝም ማንም ምንም አልያዘም፤ ሁሉም ደንብሮ ራሱን ብቻ ይዞ ባዶ እጁን ወጥቷል። ሁሉም ሰው በተመሳሳይ ጭንቀት ውስጥ ሆኖ በውጭ ተሰብሷል፤ ድሃ የለ፣ ሃብታም የለ! ባለ ሥልጣን የለ... ወዛደር የለ... ወቶ አደር የለ... ሁሉም በምሽት ልብሱና በነጠላ ጫማው ወጥቶ በፍርሃት ተውጦ ቆሟል። ክልል የለ፣ ኦሮሞ የለ አማራ የለ...ካምባታ የለ... ጉራጌ..! ሁሉም ሰላም ወጣችሁ!? አራሷ ወጣች? ነፍሰ ጡሯስ? በቃ ሁሉም እኩል ሆኖ ተሰልፏል አልኳችሁ! እመኑኝ፤ ማንም ምንም ይዞ አልወጣም።

በቅርቡ አንድ ባሕር ማዶ የተከሰተ ተመሳሳይ story ሰምቻለሁ፤ አንድ ባለ ሕንጻ (ባለ ሃብት) ሰውዬ ፎቁ ላይ የተከራየውን ነጋዴ ኪራይ ሳምንት አሳልፎ በመክፈሉ ውጣልኝ ብሎ ያስወጣዋል፤ ተከራዩም የከፈለበትን ወር ብቻ ሠርቶ እያለቀሰ ሌላ ሱቅ ፍለጋ ይዞራል። በሳምንታት ውስጥ በአገሪቱ በተከሰተ ርዕደ መሬት ሕንጻው ወድሞ ባለ ሱቁም ሌላ ሱቅ ሳያገኝ ስራውን አቁሞ ሁለቱም መንግሥት ለተጎጂዎች በሠራው መጠለያ ተገናኙ የሚል ዘገባ አንብቤአለሁ (ቃል በቃል አላሰፈርሁ እንደሆነ ይቅርታ!)። ባለ ሕንጻ የነበረው ሰውዬ (የቀድሞ ባለ ሃብት) አሁን ግን ተረጂ፣ ባለ ሱቁም (የቀድሞ ባለ ሱቅ) አሁን ግን በመንግሥት የሚረዳ ሆነው ቁጭ አሉ። አይገርምም!? ሕይወት ይህችው ናት። በመጨረሻም የምታስመልጡት ራሳችሁንና ራሳችሁን ብቻ ነው።

ያከማቻችሁት ሃብት የእናንተ አይደለም፤ እጃችሁም ያለው እናንተን (ራሳችሁን) አይደለም። እናንተ ማለት ይዛችሁ የወጣችሁት ማንነታችሁ ነው። በዚያ ሰዓት ዘር፣ ዝና.. ታዋቂነት እና አዋቂነት አይሠሩም። ሁሉም እኩል! "አለኝ" የምትለው በፍጻሜ የአንተ አይደለምና ይዘኸው መሸሸ የቻልኸው ራስህን (አንተነትህን) በትኩረት እይ! ትምክህትም አለኝ በምትለው አይሁን፤ ከተፈጠረው ክስተት "አለኝ" የምትለው እንደማይከተልህ አስተውለሃልና!! ይኸው ነው።

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ከዚህ በፊት በዚሁ ቻናሌ የቀረበው ዘለግ ያለ ጽሁፌ በዚህ የዩቲብ ቻናል በሌላ መልክ ቀርቧልና ገብታችሁ እንድትሰሙት ይሁን!😊

ረዘም ያለ በመሆኑ በሦስት ክፍሎች ነው ያቀረብነውና ሌሎች ክፍሎች በቻናሉ ሲጣዱ እንዲደርሷችሁ SUBSCRIBE ማድረጉንም አትዘንጉ!!!

መሰል ዝግጅቶችን ይዤ የምቀርብበት አዲስ የዩቲዩብ ቻናል ነውና እናንተም SUBSCRIBE በማድረግም ሆነ ለሌሎች በማጋራት አብረን እንሥራ!!

መሲሑ እና የዚህ ዓለም መንግሥት!
https://youtube.com/watch?v=3T6zJCYH1-0&si=t00Uqw1WmNrfq8wG


አዲሱን አስረጅተሃል!
(ድንቄም አዲስ)😊
----◉-----
ከበርናባስ በቀለ

አንተ እግዚአብሔር "እዚያ" የምትለው ስፍራና "ወደፊት" የምትለው ጊዜ የለም። ለአንተ ለኢ-ውስኑ አምላኬ ሥፍራዎች ሁሉ እዚህ፣ ጊዜያትም ሁሉ "አሁን" ናቸውና ያልኖርኳቸው ዘመኖቼ ሁሉ በፊትህ "እዚህና አሁን" ናቸው።

አዲስ ያልሁት ዓመት (2017) በዘንድህ ያረጀ፣ ይመጣል ያልሁትም ዘመን በፊትህ ያለፈ ነው። ምጡቅ ነህና ከጅማሬው ፍጻሜውን ተናግረሃል፣ ረቂቅ ነህና ከቀኖቼ ቀድመህ ኖረሃል፣ ከዘላለም ነህና አዲስ ያልሁትን አስረጅተሃል!

ድንቄም አዲስ!
አዲስስ አንተው ራስ ነህ!


ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ጭፍን ፍርጃ ይቅር!
----◉-----
       ከበርናባስ በቀለ

ራሳቸውን ብቻ በማዳመጥ ለነገሮች ብያኔ የሚሰጡ ሰዎች ሲገጥሟችሁ ምን ታደርጋላችሁ? ራሳቸው ጠይቀው ራሳቸው ይመስልሳሉ፤ እንዳገኟችሁ ሲነግሯችሁ "ተረድቼሃለሁ" ይሏችኋል፤ ግን እኮ የተረዷችሁ በራሳቸው ጫማ ቆመው ነው። ተፈጥሯችን (ሰውነት) በራሱ ሌሎችን ለማዳመጥ የተሰጠ (committed የሆነ) አይደለም። በኃጥአት የወደቅነው የራሳችንን እውነት በራሳችን መንገድ ልንገነባ ስንሞክር እንደሆነ አንዘንጋ። ጠይቀው የጥያቄአቸውን ምላሽ ከእናንተ ማግኘቱ ወራት ሲፈጅባቸው ራሳቸው የሚመልሱ ሰዎች አልገጠሟችሁም?

እኔም ራሴን ብቻ በማዳመጥ ያሳዘንኋችሁና የፈረድሁባችሁ ወዳጆቼ ይቅርታ እንድታደርጉልኝ እለምናችኋለሁ። ከእናንተ ብቻ ለመስማት መታገስ የነበረብኝን የዝምታችሁን gap ለመሙላት ብዬ ለራሴ በሰጠሁት ምላሽ ላበላሸኋቸው ግኑኝነቶች ኃላፊነት እወስዳለሁ፤ በቀጣዩ ዓመት ሰዎችን በተሻለ መልኩ ለማዳመጥ ቃል እገባለሁ። ሳትሰሙኝና ልቤን ሳታገኙ ራሳችሁ ጠይቃችሁ ለራሳችሁ መልሳችሁ የፈረዳችሁብኝ እናንተም በሌላው ላይ እንዲህ ከማድረግ ተቆጠቡ፤ ለረጅም ዓመታት በሂደት የተሠራው ማንነቴን በጥቂት ሰዓታት ግምታችሁ ድምዳሜ ስትሰጡ ድጋሚ እንዳትሳሳቱ ተጠንቀቁ!

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


በዋዛ ከመኖር በዋዛ መሞት!
----◉-----
ከበርናባስ በቀለ

እኔ፦ እንዴት ነህ Bro? ጠፍተሃል! በሕይወት አለህ?

እርሱ፦ "እንዲሁ በዋዛ መሞት አለ ወይ?"

እኔ፦ እንዲሁ በዋዛ መኖር አለ ወይ?

እርሱ፦ "ኧረ! ባርኒ ምንም ቢሆን መኖር ጥሩ ነው!"

እኔ፦ Bro ዋናው ሃሳቤ ለመኖርም መሞትም ዋዛ አያስፈልግም! በዋዛ ከመኖር ደግሞ በዋዛ መሞት ይሻላል፤ አይመስልህም!?

እርሱ፦ "ኧረ! ሰላምታችንን ካቆምንበት እንቀጥል ባርኒ፤ አንተ ግን ደህና ነህ?"

እኔ፦ አንተ ደግሞ መኖር ስትወድ! 🙂

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


የቃየል ሚስት ነገር
----◉----
ከበርናባስ በቀለ

ትራንስፖርት ውስጥ ነኝ፤ መኪናዋ 5Lነች። የምታውቋት ትንሽዬ መኪና በሚገራርሙ ጨዋታ አዋቂ ወጣቶች ወግ ደምቃለች። ሾፌሩ ወደ ፊት ሲነዳ ወጣቱ ረጅም ርቀት የኋሊት ኼዶ በአንድ ወሳኝ ጉዳይ እየመከረ ነው። ደግሞ ወጣቶቹ ሁለት ቡድን ሆነዋል፤ የፊት ወንበርና የኋላ! ከፊት ወንበር፦ "ቃየል ሚስት ያገኘው ከየት ነው?" አንደኛው ከኋላ ቀበል አደረገና፦ "ሔዋን የወለደችው መንትዮችን ነበርና ቃየል ያገባው የአቤል መንትያ ሆና የተወለደችውን ልጅ ነው። እንደውም ቃልየና አቤል መጀመሪያ የተጣሉት እኮ በችኮቹ ነበር፤"

ከኋላ ወንበር ያለው ጎረምሳ፦ "እንዴ! አንተ ቃየልና አቤል የተጣሉት በመስዋዕት አይደለም? ከፊት ወንበር ምላሽ ተሰነዘረ፦ "እርሱ (የመስዋዕቱ ነገር) እኮ immediate ኮዙ ነው፤ ግን ቁርሾው የቆየ ነው! የአቤል መንትያ ሆና የተወለደችው ሴት ልጅ በጣም ቆንጆ ነበረችና አዳም ቃየል እንዳይነካት አራርቆ ያስቀምጣቸዋል፤ ቃየል ግን እየኼደ ይረብሸ ነበር። በዚያ ከአቤል ጋር (በችኳ ምክንያት) ተጣሉ። ይገረምሃል ጸቡ ከባድ ነበር። እንግዲህ በዚያው ሰሞን ነው የመስዋዕቱ ነገር ተደርቦ ሲመጣ ቃየል ጓ ያለው!"

ከፊት ወንበሩ ቡድን አንደኛው ጎረምሳ በጣም ተገረመ። "የሚገርም ነገር ነው! መጽሐፍ ቅዱስን በዚህ መልኩ አይቼ አላውቅም። እውነትም የእግዚአብሔር ቃል ጥልቅ ነው!" አለ። ከዚህ በላይ ልሰማቸው ስላልቻልኩኝ የኋላ ወንበሩን ወጣት በድንቅ ትንታኔህ ተገረሜአለሁ! ግን ይህን ቃየልና አቤል የተጣሉበትን ምክንያት ከየት ነው ያነበብኸው? ከየትስ አየመጣኸው? አልሁት።

ልጁም፦ "ከትውፊት ነው ያነበብሁት Bro!" እኔም ትውፊቱን እንዴት አመንኸው? እርሱም ቀበል አደረገና፦ "ትውፊቱን የተረጎሙልንን አባቶች አምናቸዋለሁ።" እኔም፦ ከየት ነው የተረጎሙት? እርሱም፦ "ከቃሉ ነዋ።" እኔም ቀጥዬ፦ ጉዳዩን ከዘገበው የዘፍጥረት ጸሐፊ በላይ በሌሉበት ዘመን የተከሰተውን ታሪክ የተረጎሙ ሰዎችን ትርክት ስለምን አመንህ!? እርሱም፦ "ውይ! ይገርማል። እንደዚህ አስቤ አላውቅም። ያወራኸኝ ጥሩ ነገር ይመስላል"

ቅድም ላይ ተረቱን ለጓደኛው ሲያስረዳ "የእግዚአብሔር ቃል ጥልቅ ነው፤ እንደዚህ አስቤ አላውቅም" ያስባለው ይኸው ልጅ እኔ ደግሞ በተራዬ እርሱን ስጠይቀው እርሱም "ውይ! እንደዚህ አስቤ አላውቅም" ምን አይነት ትውልድ ነው? ቃሉን ትተው ከንቱ ተረታቸውን ለትውልዱ የሚግቱ ሰዎች ግን!😥

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


"የሞት መድኀኒቱ" የተሰኘው ጥንቅሬ በአይ ኬር ሚዲያ ቀርቧል! በሚቀጥሉትም ጊዜያት መሰል መሰናዶዎችን ይዤ የምቀርብበት ሚዲያ ነውና LIKE እና SUBSCRIBE ብታደርጉ በዚያም አቅጣጫ አብረን መጓዝ እንችላለን!

በቀረበው ጽሁፍ ተጨማሪ ወይም ገንቢ ሃሳብ ያላችሁ ወዳጆቼ እንደ ሁልጊዜው በውስጥ እንደምታደርሱን ተስፋ አደርጋለሁ። የምወዳችሁ ነኝ። አሁን ወደ ሊንኩ፦ 😊

https://youtu.be/iqZ_csBuBUw?si=iGrHDG9ILh66VmSl


የምር ራሳችሁን ናችሁ!?
----◉----
ከበርናባስ በቀለ

ራሳችሁን መሆን እንዳትችሉ የሚያስገድዷችሁ ኔትዎርኮች የሏችሁም? ወይስ ራሳችሁን ለመሆን (to live your conviction) እድሎቻቸውን ከሚያርዱት መካከል ናችሁ? መልካም የሚመስሉ እና ያጀቧችሁ ነገሮች ሁሉ ወደ ፍጻሜያችሁ የሚያስቸኩሏችሁ አይደሉም፤ እንደውም ይባስ ወደ ኋላ የሚጎትቷችሁ ሊሆኑ ይችላሉ።

ራሳችሁን ለመሆንና የምታምኑትን በእውን (በተግባር) ለመኖር ቢያስፈልግ ሁሉን ማጣትን ምረጡ። ምናልባት ኑሮን በአጀብ ለምዳችሁ ዙሪያችሁ ጭር ሲል ይከብዳችሁ ይሆናል፤ ግን ታጅባችሁ የእናንተ ማንነትና color ባልሆነ አኗኗር ዘመናችሁ ከሚያልፍ ለምታምኑለት እውነት ጭው ባለ በረሃ ብቻችሁን ብትሆኑ ይሻላችኋል፤ እኔም ለነፍሴ የምመክራት ይህንኑን ነው።

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


መንግሥቱ አልባ ወንጌል!
----●----
ከበርናባስ በቀለ

የመንግሥቱን ወንጌል እንድትሰብክ በምድር የተተከለችው መሲሓዊት ማኅበር ቤተ ክርስቲያን መንግሥቱን ትታ ወንጌሉን ብቻ በመስበክ ባተሌ የሆነች ይመስላል። ወንጌሉ ደግሞ የእግዚአብሔር መንግሥት ዜና ነውና ይህን መዘንጋቱ "አንዱን ጥሎ ሌላውን አንጠልጥሎ" ጉዞ ይሆናል።

የእግዚአብሔርን መንግሥትና የአስተዳደር ስርዓቱን በቅጡ ሳይረዳ በጸጋ ስጦታዎች የተንበሸበሸ ማኅበር የስጦታዎቹን ዓላማ አያውቅምና ለሕንጸቱ ሥራ ከአርያም የተሰጠውን ለግል ጥቅሙ ይቸበችባል!

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


ትንሿ ጆሮዬ...
----●----
         ከበርናባስ በቀለ

ጆሮዬ ዲሿ (ውጫዊ ክፍሉ) በተፈጥሮ ትንሽዬ ነው። የቅርብ ወዳጆቼ አስተውላችኹ ታውቁ እንደኾነ አላውቅም። "አሁን ይኽ ጆሮ እንዴት ይሰማል? ደግሞ እኮ ልቅም አድርገህ ነው የምትሰማው" ላላችኹኝ ጆሯችን በዋናነት የሚሰማው በውስጥ ክፍሉ እንጂ በውጭው አንቴና እንዳይደለ ያወራሁትንም አልረሳውም።

ሙባረክ ይባላል፤ የምኖርበት ሰፈር ያለ ሕጻን ልጅ ነው። ሰላም ካልኹት በኋላ ጆሮውን ይዤ ይኽ ምንድነው? አልኹት፤ "እንዴ! ጆሮ ነዋ!" አለኝ። "ያንተም ያው!" ብሎ ወደ ጆሮዬ አመለከተኝ ("አንተ የሌለህን ባዕድ ነገር ያገኘኽብኝ መሰለህ?" ይመስላል አባባሉ)።

ከዚያም ጆሮዬን እያየ "ያንተ ግን ትንሽ ነው!" አለኝ። እኔም አዎን ትንሽ ነው። አላሳዝንም? አልኹት። "ምን ኾኖ ነው?" ሲለኝ በቃ የተሰጠኝ ይኽ ነው! ብዬ መለስሁት። ከንግግሬ የጆሮዬ ማነስ ጉዳይ በጣም ያሳሰበኝ እንደኾነ አስቧልና እኔም፦ 'ያንተ በጣም ትለቅ ነው! ታድለህ! ለእኔ ትንሽ አትሰጠኝም? አልኹት። "እንዴት ልስጥህ?" ሲለኝ መቁረጫ አለኝና ከዚህ መልስ ልውሰድ? ስለው "ውሰድ!" ብሎ እርፍ።

ኪሴ አካባቢ ተፍ ተፍ ብዬ ከቁልፍ ማንጠልጠያዬ ስለት ያለውን አንዳች ፈለግሁ። "በዚህ እድሜ ግን ቁልፍ ማንጠልጠል?" ያላችኹኝን አልሰማችኹም። ወደ ልጁ ልመልሳችኹ፦ ስለታም ነገሩን ይዤ ወደ ጆሮው ሳቀርብ ጸጥ! "ውሰድ..." ይለኛል። ፍርሃትና መርበትበት ፊቱ ላይ አይነበብም! ምን አይነት ቅንነት ነው? 😥

በዚህ ጊዜ ብዙ ሰው እንኳን የጆሮውን አካል ቆርጦ ሊሰጥህ ጥቂት ሊሰማህ (ጆሮውን ሊሰጥህ) አይፈቅድም እኮ። ምናለ ይኽ ብላቴና እኛ ወደምንኖርበት የብልጠት ዓለም (Calculative ኾኖ ወደሚኖርበት stage) ባይመጣና በዚሁ ልብ ቢያድድግ ብዬ አስብኹና ይህ የልጅነት ንፁህ ልብ ብቻ እንደኾነ ተረድቼ ስሜው አለፍሁ። ትንሿን ጆሮዬን ሰጥቼ የሰማኹት ልጅ ጆሮውን ቆርጦ ሊሰጠኝ የሚፈቅድ ኾኖ ሳገኝ ጆሮዬን ስለነሳዃቸው ሰዎች ንስሐ እየገባኹ ወደ ጉዞዬ!

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊


የመሲሑ ተከታዮች officially እንደሚሰደዱ እንጂ register እንደሚደረጉ ከመሪያቸው የተሰጣቸው ተስፋ የለምና ያላቸው አማራጭ በመከራው እስከ መጨረሻ መጽናት ነው። ሲያልፍም የተሰጣቸው ትልቅ ተስፋ የአምላካቸው የእግዚአብሔር መንግሥት ንጉሥ ዳግመኛ መመስ ነው። መከራቸው officially የሚያበቃው ያኔ ነውና እስከዚያው officially ይሰደዳሉ፣ ይወገዛሉ፣ ይሞታሉም።

የአዲስ ኪዳን ጸሐፍት የሚነግሩን በጊዜው ዙፋን ለተቆናጠጡ ገዢዎች በጌታ (having Christ's mind) እንድንታዘዝ እንጂ ከአሠራሩ ጋር ጋብቻ እንድንፈጽም አይደለም። በእኛ ዘመን ጭራሽ የሮም መንግሥት ተሿሚዎች፣ የፍልስፍናው አሳላጮችና ካቢኔዎቹም እኛው ነን። የሮምን መንግሥትና ክርስቶስን ያፋቀርንና አብሮ ሠራተኞች ያደረግን በዓለም ታሪክ ምርጦቹ የእርቅ ኮሚሽን ጀግኖች እኮ ነን!😎

ስለ ዕውቅና ያለን አመለካከት ደግሞ እንዴት ሸውራራ (ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ) እንደኾነ ሳስብ ሃዘኔ ይበዛል። ክርስትና በመንግሥት ዕውቅና የነበረው ከ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ይልቅ በ1ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው። ከአሁኑ ብልጽግና ይልቅ በጥንቱ ደርግ ዘመን ነው። እንዴት ማለት ጥሩ አይደል?

ሕጻኑ ኢየሱስ የተወለደ ጊዜ ሄሮድስ ጨቅላ ሕጻናትን ሁሉ ያስጨፈጨፈው ለምን ነበር? እርሱ የአይሁድ ንጉሥ እንደኾነ አውቆ አይደለምን? የሮም መንግሥት መሲሑን የሰቀለው ለምን ነበር? መንግሥቱና አሠራሩ ከእነርሱ የማይገጥም መኾኑን ስላወቀ አይደለምን? የኮሙኒስት እምነቱ (እግዚአብሔር የለሹ) የደርግ መንግሥት ቤተ ክርስቲያን የሚያሳድደው ለምን ነበር? "እግዚአብሔር አለ" የምትል ወኪል ድምፅ መሆኗን ስላወቀ አይደለምን? የዚህ ዓለም መንግሥት እውነተኛ የመሲሑ መንግሥት ተከታይ መኾንህን ሲረዳ ያሳድድሃል፤ ያኔ አንተ በእነርሱ ዘንድ ታውቀሃል።

መታወቅ የሚባል እውነታ የሚረጋገጠው እግዚአብሔር እኛን በሚያውቀን መንገድ ሰዎች ሲያውቁን ነው። ቅዱሱ መጽሐፍ በነገረን ሕይወትና ማንነት ሰዎች እኛን ሲያውቁን ያኔ በርግጥ ታውቀናል፤ ለመታወቅ ብለን የምናደርገው ነገር አይኖርም እኮ፣ ግን የመሲሑ መንገድ ተከታዮች መኾናችን እንዲያው ይታወቃል።

እኛ መታወቅን ከአደባባዮች ስብሰት፣ ከቤተ እምነቶች ግንባታ፣ ከመቃብር ስፍራዎች፣ ከሚዲያ ሽፋን፣ ከሥልጣን መደብ እኩልነት እናም በመሰል ርካሽ መወደዶች ተክተናል። በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር እኛን በሚያውቀን መንገድ የታወቅን ይመስላችኋል? ከዚያም ተደራጅተን ስደትንና መከራን የሚከላከል ተቋም መሠረትን ክርስቶስን የሰቀለው የዓለም መንግሥት ለክርስቲያኖች ከለላ እንዲያደርግ ተማጽኖ አቀረብን።

አቤቱ አምላኬ ሆይ፦ አንተ በምታውቀን በዚያ መንገድ ብቻ እንድንታወቅ የርካሽ ዕውቅና ቅጥሮቻችንን አፍርስልን።

ለአስተያየትዎ፦ @barnica
Join ➘ & Share ➝
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊
     ◊   @barnabasism  ◊

20 last posts shown.