Dagu Media Network-DMN


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


For your comment @dagu_media_network_bot

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


''የደብተር ስጦታ ለአርጎብዬ''
**********
👉👉 ''የደብተር ስጦታ ለአርጎብዬ'' በሚል በአርጎባ ልዩ ወረዳ ዉስጥ  በሚገኙ አቅመ ደካማ ቤተሰቦችን በመለየት አቅማቸዉ  ለትምህርት የደረሱ ሴቶችን እና ህፃናትን ለመደገፍ የተዘጋጀዉን መርሀ ግብር በመቀላቀል ድጋፍ እንዲያደርጉ
👉 ይህንን በጎ ተግባር በመደገፍ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታበረክቱ  አስተባባሪ ኮሚቴዉ በሙሉ በቅንነት ስም ከወዲሁ ልባዊ ምስጋና እናመሰግና  ያቀርባል።

ለቅንነት መስፈርቱ ቅን ልብ ብቻ ነዉ
ቅንነት ከምንም ይበልጣል !

@dagumedianet


ዶክተር ሀሺም ጀማሉዲን (ረሂመሁላህ)

ዶ/ር ሃሺም ጃማሉዲን አሻሚ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን በአገር ውስጥ ከተከታተሉ በኃላ ግብጽ አገር በካይሮ ከተማ ከሚገኘው High Polytechnic Institute በግብርና ኢኮኖሚና በአግሮኖሚ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በ1962 አግኝተዋል፡፡

ሁለተኛ ዲግሪያቸውንም በአሜሪካን አገር ከሚገኘው Arizona State University በግብርና ኢኮኖሚ ትምርት ዘርፍ በከፍተኛ የማዕረግ ውጤት በ1966 ተመርቀዋል፡፡

በመቀጠልም በ1971 ዓ.ም በልማትና የግብርና ኢኮኖሚ ትምሕርት ዘርፍ ከ Wisconsin University በከፍተኛ ማዕረግ ሶስተኛ ድግሪያቸውን (ፒ.ኤች.ዲ) አግኝተዋል፡፡

ዶ/ር ሃሺም ጃማሉዲን አሻሚ በMobil Oil, Ethiopia ፣በታችኛው አዋሽ ሸለቆ ሜካናይዝድ እርሻ ድርጅት፣ በሳውዲ አረቢያ የፕላኒንግ ሚኒስትሪ ውስጥ በኢኮኖሚስትነት፣በጣሊያን ሮም ከተማ በሚገኘው ዓለምአቀፍ የምግብና የእርሻ ድርጅት (FAO) ዋና ጽ/ቤት የመካከለኛው ምሥራቅ እና ሰሜን አፍሪካ ክልላዊ በአማካሪነት፣በተለያዩ ጊዜያት በናይጄሪያና በየመን የFAO ተወካይ በመሆን አገልግለዋል፡፡

ዶ/ር ሃሺም ጃማሉዲን አሻሚ በአፈ ታሪክ ደረጃ የነበረው የመላው የአፋር ህዝብ ታሪክ በመፅሐፍ በማዘጋጀት መሠረት የጣሉ እና የአፋር ህዝብ ማንነት በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቅ በርካታ ጥናታዊ ፅሑፍ አዘጋጅተዋል። ‘አልመንሀል’ “የአፋር/ደናኪል/ ታረክና መረጃ አርኪ ምንጭ” የተሰኘው ባለ ሰባት መቶ ገፅ መፅሀፋቸው በአረብኛ ተፅፎ በትርጉም መልክ በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ተዘጋጅቶ በታወቁ አለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች እና የምርምር ማዕከላት ለታሪካዊ ጥናቶች ግብአትና ማጣቀሻ በመሆን እያገለገለ ይገኛል።

ፈር ቀዳጅ የአፋር ታሪክ የሚያትት መፅሐፍ ከወላጅ አባታቸው ጋር በመሆን የፃፉት ዶ/ር ሃሺም ጃማሉዲን አሻሚ በሕክምና ሲረዱ በቆዩበት ሀገረ ቱርክ ሰኞ ሀምሌ 25/2014 ከዚህ አለም በሞት ተለዩ ። አላህ የጀነት ሰው ይበላቸው።

Via #SU

t.me/dagumedianet




በወቅታዊው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጉዳይ 7 ነጥቦች!

1) በትናንትናው ዕለት የተቋቋመው መጅሊስ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ስኬት እንጂ የተወሰኑ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ውጤት አይደለም።

ሌላ ቢቀር " ያ አላህ የሙስሊሞችን ጉዳይ አንተ አስተካክለው" ብሎ ዱአ ያደረገ ስለ መጅሊስ ምንም የማያውቅ እልም ያለ ገጠር ውስጥ ያለ ወንድም ዱአ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው።

2) አሸናፊ እና ተሸናፊ የለም

ሙስሊሞች የተሻለ የመሰላቸውን መንገድ ይዘው ሊለፉ ሊደክሙ ይችላሉ [ ሸር አስቦ የሚንቀሳቀውን አላህ የውስጡን ያውቀዋል፣ የስራውንም ይሰጠዋል] ግን በመጨረሻ ላይ ድል ሲገኝ በዛንኛው መንገድ የለፋው ሰው ተሸናፊ፣ በዚህኛው መንገድ የለፋው አሸናፊ ብለን የምንሄድበት አይደለም። አላህ የተሻለውን ይመርጣል። ስለዚህ አንዱ ፎክሩ አንዱ አንገቱን የሚደፋበት አይደለም። ሁሉም አላህን ያመስግን፣ በኒዕማውም ይደሰት።

3) ደስታው ልክ ይኑረው

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ለዘመናት የተመኙት ፣ የለፉለት፣ ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን የሚወክል ተቋም፣ የማይደሰት አይኖርም [ኸይር የተጋረደበት ሲቀር]

ይሁንና የተቋሙ መቋቋም ትልቅ ውጤት ሆኖ የመጨረሻ ግብ ግን አይደለም፣ ባለመሆኑን ደስታውን በለከቱ አድርጎ በቀጣይ ላሉ የቤት ስራዎች ሁሉም የአቅሙን ያበርክት [ለዚህም አዲሱ መጅሊስ ግብአቶችን ከሁሉም የኢትዮጵያ አቅጣጫዎች የሚቀበልበት ፕላትፎርም ያዘጋጅ]

4) ተቋሙ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን እንጂ ኢስላምን አይወክልም

መጅሊሱ የኢስላም ተወካይ ሳይሆን፣ ሙስሊሞችን ከዚያም አልፎ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የሚወክል ተቋም በመሆኑ ኢስላም የሞላና አዲስ ጭማሩን የማይፈልግ ስለሆነ ስለ ኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጉዳይ 24/7 ሊሰራ ይገባል። [በቢላሽ የባከኑ በርካታ ጊዜዎች በመኖራቸው በተቻለ መጠን ሊካካሱ እንደሚገባ ልብ ይሏል]

5) ተቋሙ ሙስሊሙ ለሀገሩ እድገት ይበልጥ አበርክቶ የሚሰጥበትን መንገድ ይቀይስ

6) ከቀድሞው መጅሊስ ያሉ መልካም ነገሮችን እንዳሉ መውሰድ፣ ስህተቶችን ደግሞ ዳግም ለላመሳሳት አርሞ፣ ተጫማሪ ተግባራትን በማከል መቀጠል

7) አመስጋኝ እንሁን!

ለዚህ ተቋም በእግሩ መቆም ከአላህ በታች የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ብዙ መስዋእትነት የከፈሉ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ይሁንና በአዋጅ እንዲነገግ ከማድረግ አንስቶ ሂደቶችን ከመገፍ አንፃር የኢትዮጵያ መንግስትን በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን አላመመስገን ንፉግነት ነው።

ሀምሌ 12/2014

ዳጉ ሚዲያ ኔትዎርክ

አስተያየት ይስጡበት
Dagu media network

@dagumedianet






ከዘመቻ ስራ የምንወጣው መቼ ይሆን?

የሰው ልጅ ለራሱ የሚጥቀመውን ስራ የሚሰራው ለማንም ብሎ ሳይሆን ለራሱ ሲል ነው። ስራዎች የሆነ ገፊ አካል ሲመጣ በዘመቻ ሆ ተብሎ ይሰራሉ፣ አለቀ ከዚያ በኋላ ሌላ ዘመቻ ይጠበቃል።

ከሰሞኑ በየአካባቢው የፅዳተት ዘመቻ እየታየ ነው።።ፅዳት መልካም ነገር ነው። ነገር ግን ዛሬ የተጀመረው ፅዳት ሌላ ዘመቻ ፈልጎ እስከሚነሳ መጠበቅ የለበትም።

ለምሳሌ ከታች የምታዩት የውሃ ፕላስቲክ እንዲህ እስኪጠራቀም ድረስ የት ነበርን?

ከቆሻሻ ጋር አብሮ መኖርን ለምን ለመድን?

ከዘመቻ ስራ መውጣት አለብን፣ ዘመቻዎች ዘላቂ ስራዎችን ማስጀመሪያ፣ ማጠናከሪያ እንጂ ከዘመቻ እስከ ዘመቻ ስራን ማቆያ መሆን የለባቸውም።

ዳጉ ሚዲያ ኔትወርክ

t.me/dagumedianet

https://youtube.com/channel/UCNCpF9ZGpDAymtnBu8LoIbA




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
Mastar Casan Moomin

Qunxaaneytah Ceelallo Yakkem Xiiqa Agiru

Qafar Tv Qiddi Qaffaydat axaw haak Mango ximmoomal Mastar Casan Moomin Walalisseh.

Takkel Mango Ximmooma Ugutteh

☞Xagar dig caagidi
☞ barittô caagidi
☞ dayli caagidi
☞ giclo
☞ meqem abitto

Kalah tan mango ximmooma ugutteh

Mastar Casan Moomim Chayna Ispoor barittoh gexe wak Xaah salat ab kak iyyeb waka ma gacsa yece?

Casan Moomin Agbi xormi cule...

kalah tan qajaaibik tan ximmooma qunxaaneytah kas takke ugutteh youtube fan culak maqaytaanam duddaanah, subscribe abak nee aydikumussaanam massakaxxa luk sin esserra.

Video ☞ Qafartvik beyne

Qafar tvih kulsa le gadda gacisna, tannah yan ceelallo yakkem xiiqa qunxaaneyta neh xayyosseenimih

Ciggiila linkit mukuna

https://youtu.be/2CGrIBnKaMU




ትኩረት ለይለፍ ቃል!
⚠️ እባክዎ የይለፍ ቃልዎን ደህንነት እና አስተማማኝነት ዛሬ ነገ ሳይሉ አሁኑኑ ያረጋግጡ፤ ለሌሎች አሳልፈው አይስጡ!

@dagumedianet


⚠️ የረብሻው ትክክለኛ መነሻ ከቦታው

ከመስቀል አደባባይ በቦሌ መስመር ከቀይ ሽብር ትንሽ ከፍ ብሎ ሀያት ሪጀንሲ በሚገኘው ቦታ ላይ ክስተቱ ሚጀምረው።

ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዒዱን እየተከታተለ ባለበት ሰዓት ፌደራል ፖሊስ ምንም ባልተፈጠረበት ሁኔታ ሰላም ቁጭ ብሎ የነበረው ሰጋጅ ላይ ከመስቀል አደባባይ በቦሌ መስመር ከቀይ ሽብር ከፍ ብሎ ሀያት ሪጀንሲ ጋር በሴቶች በኩል አስለቃሽ ጭስ ጣለ ወደ ሰጋጆችም በእግሩ ገፋ አደርጎ ወደ መሃል ከተተው ይህ በቦታው ከነበሩ በብረቱ አይናቸው ያዩት የአማኞች ምስክር ነው። ማህበረሰቡ በመዋከብ ግማሹ ፊኛ ነው ግማሹ ሽጉጥ ነው እያለ ባለበት ሁኔታ ጭሱ መውጣት ጀመረና አማኞችን ማቃጠል ሲጀምር ሴቶችም መሸሽ ጀመሩ ግርግር ተፈጠረ ፌደራል ፖሊሱ ለምን እንዳደረገ ሲጠየቅ አባርቆብኝ በስህተት ነው በማለት የመለሰ ቢሆንም በእግሩ ወደ ሰጋጆቹ ገፋ ሲያደርገው ያዩት ስለነበሩ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ፌደራል ፖሊሱን ለመያዝ ጥረት ቢያረግም ፖሊሱን ለማዳን ወደ ቀይ ሽብር ግቢ ውስጥ ይዘውት ገቡ ! ሙስሊሙ ማህበረሰብም ከቀይ ሽብር ግቢ ውስጥ እንዲወጣ ጥያቄውን አቀረበ በዛ መሃል ወደ ቀይ ሽብር ፖሊሱን ለማውጣት በተደረገው ትግል ላይ ቀይ ሽብር ላይ አነስተኛ ጉዳት ደረሰ ከዛ ወደ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተጨማሪ ቶክሶች አስለቃሽ ጭሶች ተቶከሱ በዒዱ ቀን ረበሹት በሰላም እንዳያከብር አደረጉት እውነተኛ እና ትክክለኛ የረብሻው መነሻ ይህ ነው ።

ሆኖም ግን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የመንግስትም ሚድያዋች እንደዘገቡት ጥቂት አሸባሪዋች በፈጠሩት ሁከት ረብሻ ተነስቶ ነበር ብለው ዘግበዋል! ጥቂት አሸባሪ የተባለው አስለቃሽ ጭሱን የለቀቀው ፌደራል ፖሊስ ከሆነ ትክክለኛ ዘገባ ነው ፣ በሰላም የዒድ ሰላትን በመጠባበቅ ላይ የነበረውን አማኝ ከሆነ ጥቂት አሸባሪዋች ያሉት ? ትልቅ ውሸትን ዋሽተዋል እና ዘገባቸውን ያስተካክሉት። በዒዱ ቀን ተሰቃይቶም የውሸት ዘገባም የሰሩበትን ሙስሊም ማህበረሰብ በተለይ ሴት እህቶቻችና እናቶቻችንን በይፋ ይቅርታ ይጠይቅ !

ፌደራል ፖሊሱም ተይዞ ይመርመር ተሳስቶ ሳይሆን ሆን ብሎ ረብሻ ለማስነሳት ያቀደው እቅድ እንጂ በስህተት የተፈፀመ አደለም ! ያ ቢሆን ቀላል መፍትሄዋችን መውሰድ ይቻል ነበር ቶሎ ከሰጋጁ ማሰወገድ እና ጉዳት ማይደርስበት ቦታ ማስቀመጥ ፣ ማፈን እና ወደ ምእመናኑ እንዳይደርስ ማድረግ ፣ እና መሰል መፍትሄዋችን ተጠቅሞ ማስቆም ይቻል ነበር። ያም ሳይሆን በእግሩ ወደ ሰጋጂች እንደገፋው በቦታው ላይ የነበሩ የአይን እማኞች ተናግረዋል።

#ረበሹን_ከሰሱን 😢

እውነታን በማሰራጨት የውሸት ክሶችን እንቃወም መልአክቱን ሼር በማድረግ ስለ እውነት እንጩህ !
🍂✒️.... @zizuQ




የሸዋል ጨረቃ አልታየችም ነገ የረመዷን ማሟያ 30 ነው።

አላህ ይቀበለን

BREAKING NEWS | The Crescent for the month of Shawwal 1443 was NOT SEEN today, subsequently:

Monday, 2nd May 2022 will be the day of Eid Al Fitr

The month of Ramadan 1443 will complete 30 days tomorrow

Haramain Sharifain
t.me/dagumedianet


ኦርዶጋን ኡምራ አደረጉ!

አላህ ይቀበላቸው፣ አላህ ይጠብቃቸው!

Turkey’s President Recep Tayyip Erdogan visited Masjid Al Haram, Makkah and performed Umrah along with his delegation today

His Excellency also prayed Voluntary Prayers inside the Holy Ka’bah

t.me/dagumedianet


Muxxó le Bara/ Laylatul qhadri

Yalli nee yawaafaqhay

t.me/dagumedianet




«ለተፈጠረው ሁሉ አዝናለሁ። በህግ አግባብ በካቢኔው የተወሰነውን የመስጊድ ይዞታ ከታች ያሉት የመንግስት አካላት ማስቆምም መንጠቅም አይችሉም። የተቀረውንም ጥያቄም ማስረጃዎች ይቅረቡና በህግ አግባብ ይታያል።» ወይዘሮ አዳነች አቤቤ

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የኢማም አሕመድ መስጊድ ጉዳይ አስመልክቶ አህመዲን ጀበል በማህበራዊ ሚዲያው ያጋራው
❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በአሁኑ ወረዳ 02 ዉስጥ የሚገኘው «ኢማም አሕመድ መስጊድና የእውቀት ማዕከል» ለዓመታት መፍትሄ ሳያገኝ ሲንከባለል ቆይቶ ቀድሞ በአያት ሪል ስቴት አማካኝነት በ1996 ለመስጊድና ለቤተክርስቲያን የተሰጠው ስፍራ በቤተክርስቲያኑ ስፍራ ላይ ገብርኤል ቤተክርስቲያን (40ሺ ካሬ ይዞታ ያለው) ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ሲገኝ መስጊዱ ግን በ2005 እንዲፈርስ ተደረገ። የመስጊዱ መሬትም አላግባብ ተነጥቆ ለመናፈሻ ተሰጠ።

የአከባቢው ሙስሊም ማህበረሰብም በህጋዊ አግባብ ከከተማ አስተዳደሩ እስከ ፍ/ቤት ጉዳዩን በማደረስ ከአስር 12 ዓመታት መፍትሄ ፍለጋ ሲንከራተት ከቆየ በኋላ ጉዳዩ መፍትሄ እንዲያገኝ ከመንግስት ሲወሰን ታች ባሉ የከተማ አስተዳደሩ ሠራተኞች የመሬቱ አንድ ሦስተኛ ብቻ ማለትም ከ12ሺው ካሬ ዉስጥ 4ሺህ ካሬ ሜትሩን ብቻ ለመስጊዱ እንዲሰጥ አድርገው የዉሳኔ ሀሳብ ለከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ አቀረቡ። ከቢኔውም በ4ሺው ላይ ለመስጊዱ ህጋዊ ካርታ እንዲወጣለት ወሰነ።ካርታውም ወጣ።

የተቀነሰውም መሬት በህግ አግባብ ተጠይቆ ምላሽ እየተጠበቀ ባለበት የአከባቢው ህዝበ ሙስሊም እስከዚያው ካርታ ባገኘው መሬት ላይ የግንባታ ፈቃድ በማውጣት ቀድሞ በከተማ አስተዳደሩ በፈረሰው መስጊድ ምትክ በዛሬው እለት ጊዜያዊ መስጊድ ለመስራት ሲንቀሳቀሱ የጸጥታ አካላት አላግባብ አስቁመው ችግር መፈጠሩ እጅግ አሳዛኝ ጉዳይ።የጸጥታ አካላትም ህጉን ብቻ ተከትለው ህጋዊ ስለመሆኑ ማጣራት ሲገባቸው ህጋዊ ሰነድ እየቀረበላቸው በደፈናው ስራውን ማስተጓጎላች ተቀባይነት የለውም።የካሳ ጥያቄ ያለውም አካል ካለ በህግ አግባብ የከተማ አስተዳደሩን መጠየቅ መብቱ ሆኖ ሳለ ሆነ ብሎ በሚመስል መልኩ ህዝበ ሙስሊሙን መተናኮስ ተቀባይነት የለውም።

በዚህ ጉዳይ ላይ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከወይዘሮ አዳነች አቤቤ ጋር በስልክ ተወየይተናል። ከንቲባዋ «ለተፈጠረው ሁሉ አዝናለሁ። በህግ አግባብ በካቢኔው የተወሰነውን የመስጊድ ይዞታ ከታች ያሉት የመንግስት አካላት ማስቆምም መንጠቅም አይችሉም። የተቀረውንም ጥያቄም ማስረጃዎች ይቅረቡና በህግ አግባብ ይታያል።» ብለዋል። በመጨረሻም ጉዳዩንም የኢማም አሕመድ መስጊድና የእውቀት ማዕከል ኮሚቴዎች የፊታችን ሰኞ ጠዋት በ4:00 ላይ በከንቲባ ጽ\ቤት ማስረጃዎቻቸውን ይዘው በመቅረብ እንዲያስረዱ ቀጠሮ ተይዟል።

T.me/ahmedin99

18 last posts shown.

435

subscribers
Channel statistics