Posts filter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የወይን ጠጁን ተፋው

#share
@diyakonhenokhaile


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በርባን

#share
@diyakonhenokhaile


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#share
@diyakonhenokhaile




ሲመስለኝ ከዲያቆን ምሕረት የጠበቁት መልስ “The Bible” የሚል ነበር:: እርሱን ካለ “If the Bible is the ultimate authority, where does it say that the first Christians believed it is the actual body and blood?” ብለው ሊዘጉትና መጽሐፍ ቅዱስን ከጻፈው እውነት በላይ ያንን እውነት ሰዎች እንዲህ ተረድተውት ነበር እንዲል ጠይቀው ውይይቱን ሊዘጉ ነበር::

ምሕረት የለሹ ዲያቆን ግን Bible በማለት ፈንታ Bibleን በቀኖና የወሰነችውን The Body of Christ ይዞ የሙጥኝ አለ:: የእናቱን የቤተ ክርስቲያንን ቀሚስ ይዞ ድርቅ ሲል

Good to meet you brother አሉና ጨበጡት በአማርኛ ሲተረጎም
“አንተን ብሎ ምሕረት መዓት ሆንክብን እንጂ” እንደማለት ነው::

My beloved brother, Deacon Mihret, may God bless you. We saw ‘Berekete Estifanos’ in you. May God guide your path

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሚያዝያ 3 2017 ዓ.ም.
#share #share
@diyakonhenokhaile


ከዚህ በኋላ ያለው ውይይት ዲያቆን ምሕረትን በግድ ካቶሊክ ካልሆንክ የሚል ንትርክ ነው:: inflability of the councils, vatican 1 2 3 etc

“የቅዱስ ቁርባን ደምን የሰጠው ከእጁ እየፈሰሰ ነበር” የሚል ያላልነውን በሉ የሚል ቃልም በጌታ እንደመዘበት እያለው ተናገረ:: It is not right to ridicule Christ for the sake of argument.
@diyakonhenokhaile

አራት መቶ ዓመት አልፎ ሃሳቡን የAugstine ሊያደርግበት ሲጥር ምሕረት ውይይቱን ወደ አግናጥዮስ ዘመን መለሰው:: የመጨረሻው ጥያቄያቸው

Who is the ultimate authority? የሚል ነበር::


“It is now becoming a salvation issue” እያለ ሲቅበጠበጥ አሁን ገና ተመቻቸህልኝ ብሎ ደስ እንዳለው ያስታውቅ ነበር:: ምሕረቱ “ድናችኋል ብቻ ሳይሆን ትድናላችሁም ይላል” ብሎ የድህነትን ሒደታዊነት አብራራ::


ይህን ጊዜ ሌላው ፓስተር ጸጋ አላስቻለውምና ገባ

ፓስተር ጸጋ “ በጸጋው ድናችኋል” ይላል አለና ዘሎ ገባ::

ድኅነት synergetic ስለሆነ የጸጋው energy የእኛን ትብብር ይሻ የለም ወይ? አለና ምሕረቱ “መዳናችሁን ፈጽሙ”ን ጠቀሰ:: አብርሃምም ልጁን የመሠዋቱን ሥራ አነሣ:: እነርሱ ግን “work out your salvation” የሚለው ቃል ውስጥ “work” የሚል ቃል ሲሰሙ ደስታቸውን መሸከም አልቻሉም:: ቃሉን ጳውሎስየተናገረው መሆኑም አላሳሰባቸውም::

ሥራን ለማጣጣል የቀኙን ወንበዴ ጠቀሱ:: ተቸንክሮ ምን ሊሠራ ይችላል አለ:: (Though the thief on the cross was nailed, he still worked on his salvation. He confessed his sin, saying that he was worthy of the cross. He taught his companion to fear God, and he professed the purity of Christ and the coming of His kingdom)

እግዚአብሔር ባልሠጠው መክሊት አይጠይቅምና circumstantial ነው አለ:: ሊሞት አልጋ ላይ ስላለ ሰው አለመጠመቅ አላወራሁም ብሎ ሞገተ::
@diyakonhenokhaile


አዝናኙ ውይይት እንደቀጠለ ነው:: ሰውዬው ጥያቄውን መመለስ ትቶ Unworthy ማለት worthy ያልሆነ ነው ብሎ ቃሉን አብራራ:: ቀጠለና ጉዳዩን ከማይገናኘው የሴት ጠጉር አለመሸፈን ጋር አገናኘው:: (ሲጀመር ጠጉር ስላልሸፈነች የሞተች የለችም እየተወራ ያለው ቆርበው ስለሞቱ ሰዎች ነው) አልበቃው ብሎ ስለ sex godess ስለ me too movement ዘባረቀ:: መልስ ስታጣ የምታውቀውን ሁሉ ልትዘባርቅ እንደምትችል ያሳያል::

ዲያቆኑን ማባበልም ጀመረ “የአንተን ሃሳብ የሚያራምዱ ሰዎችን ከልቤ አከብራለሁ:: እውነት እውነት እላችሁዋለሁ የሚለውን ይዘው ይህ እውነተኛ ሥጋው ነው የሚሉት ከልብ አከብራለሁ” አለ:: አክባሪ ይሥጥልን ግን እኛ ይሄን ጥቅስ እንደማስረጃ አላነሣንም:: ዲያቆኑ እዚያው ቆሞ “ለተራ እንጀራ ሰው እንዴት ይሞታል?” ብሎ የጠየቀውን ፍጥጥ ያለ ጥያቄ ትቶ ከዚህ በፊት ሌሎች ሰዎች ያነሡትን weak argument እየጠቀሰ እንዲህ በለኝና ልርታህ ብሎ ተለማመጠ:: (ተው ባልወልድህም አባትህ እሆናለሁ is in my head)

ከዚያ ደግሞ በmystical change የሚያምነውን ኦርቶዶክሳዊ በግድ transubstantiationን ካላመንክልኝና እርሱን ለመቃወም ያጠራቀምኩትን መከራከሪያ አንተ ላይ ልጠቀመው ይል ጀመር::

ቀጥሎ የተነሣው ድኅነት ሒደት ነው የሚለው ሃሳብ ነው:: ይሄን ጊዜ ፓስተሩ ከቁርባን ርእስ እርፍ ያለ መስሎት ፈነደቀ::


ፓስተሩ “ጊዜው ምን ያደርጋል” አለ:: ስለ ታሪክ እየተወራ ጊዜው ምን ያደርጋል ከሚል ሰው ይሰውራችሁ::

“ከታሪክ አንጻር ክርስትና ጌታ ለሐዋርያት የሠጠው እምነት ነው ብለህ ካመንህ በመጀመሪያው ክፍለ ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች የምታምነውን እንደሚያምኑ የሚያሳይ ነገር ልታገኝ ይገባሃል” አለው::

ፓስተሩ “ወዳጄ እመነኝ በዚያን ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች ሁሉ ክርስቶስ ‘የራሱን ሥጋ’ በልቶአል ብለው አላመኑም” ብሎ ነገሩን ridiculous ሊያደርገው ሞከረ:: ይህን ስሰማ ትዝ ያለኝ “ይህ ሰው ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይችላል?” ብለው አይሁድ የተከራከሩት ክርክር ነው:: ዮሐንስ 6:52
ጌታ ሥጋዬ እነሆ እያለ የለም ሥጋህ አይደለም ብሎ ክርክር እንዴት ያለ ነው::

ዲያቆኑ ሐዋርያውን ጠቅሰ “ሳይገባው ይህን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት። ስለዚህ በእናንተ ዘንድ የደከሙና የታመሙ ብዙዎች አሉ አያሌዎችም አንቀላፍተዋል” 1 ቆሮ. 11:30 ከዚያም : “ሥጋና ደሙ ተራ እንጀራና ወይን ብቻ ከሆነ እንዴት ሳይገባቸው ተቀብለው የሞቱ ሰዎች ሊኖሩ ቻሉ?” ብሎ ጠየቀ::


እዚህ ላይ እንኳን ደንግጠው ነው እንጂ እርሱ የጠቀሳቸው እነ ቅዱስ ሄሬኔዎስና ቅዱስ አግናጥዮስ መልስ የሰጡት ታዲያ ለማን ነበር? ብለው መጠየቅ ይችሉ ነበር:: ዶሲቲስቶችና ግኖስቲኮች ሙሉ በሙሉ የፓስተሮቹን ሃሳብም ባይሆን ቁርባን ላይ ተቃዋሚዎች ነበሩ:: የምሕረት መልአክ ቀሳፊ መልአክ ሆኖባቸው ግን ትንሽ እንኳን አልታገሉም:: ግን ዶሲቲስቶችና ግኖስቲኮች ተጠቃሽ ክርስቲያኖች ስላልሆኑ ሁለት ወገን አልነበረም ቢል ዲያቆን ምሕረት ልክ ነው::

“So you are saying” አለ ፓስተሩ:: የJordan Peterson እና የCathy Newmanን አስቂኝ ቃለ መጠይቅ ከሰማሁ ወዲህ ክርክር ላይ “So you are saying” ብሎ ተከራካሪው አፍ ውስጥ ቃላት ለመክተት የሚሞክር ሰው የራሱን ቀብር ጡሩምባ እየነፋ ይመስለኛል::

ፓስተሩ “እሺ ሉተርስ?” አለ:: (ኸረ ባልወልድህም አደርስሃለሁ ተው በሰው ፊት አታዋርደኝ:: ሉተር እንኳን ቁርባንን ተቃውሞአል በልልኝ [በሆዱ ያለ ይመስለኛል])

ምሕረት ወይ ፍንክች የሉተርን መፍቀሬ ቁርባን የሆነ “I would rather drink pure blood with the pope than mere wine with the radicals” የሚል ንግግር ሊጠቅስበት ጀመረ:: (በዚህ ጉዳይ ሉተርና ሚካኤል የሚል ያልታተመ መጽሐፍና ያልተለቀቀ የYoutube video ስላለ ሁለቱንም በቅርብ እዚሁ ላይ Link አደርጋለሁ) “ነገሩ የመጣው ገና 500 ዓመት ከሆናቸው ከራዲካል ሪፎርመሮች ነው” ብሎ የሉተርን ባላንጦች ጠቀሰበት::
@diyakonhenokhaile


ዲያቆን ምሕረት በዚህ ጥያቄው ሰዎቹን ጨርሶ ወደማውቁት ጨለማ ክፍል ወስዶ ቆለፈባቸው:: የአንደኛው ክፍለ ዘመን አባቶች ሥነ ጽሑፍና ታሪክ ለእነርሱ የማያውቁት የውጊያ ዐውድ ነው:: ወደ በኋላም በምሥጢረ ቁርባን ዙሪያ ባለው ግልፅ አቋምና ከሐዋርያት ጋር በነበረው ቅርበት የተነሣ የፕሮቴስታንት ሊቃውንት “ምነው ባልተፈጠረ” የሚሉትንና አንዳንዶቹም “እሱ አልጻፈውም” ብለው መጽሐፉን ለመካድ የሚገደዱበትን ቅዱስ አግናጥዮስን በመጥቀስ አስጨንቆአቸዋል::

የሚገርመው የሠጡት መልስ :-

የምትለው እውነት ከሆነ ለምን ሚልዮኖች ሳይቀበሉት ቀሩ? የሚል ልፍስፍስ ጥያቄ ነው::

ምሕረት መለሰ :- ይህማ እጅግ ብዙ ሰዎች ወንጌልን ላለመቀበላቸውም የሚቀርብ ምክንያት ነው::

ብሎ የራሳቸውን አመክንዮ በራሳቸው ላይ መለሰው:: በሳልሽው ተመተሪ!

ፓስተሩ :- እስቲ በሁለቱም ወገን (ጥምቀትና ቁርባን ለድኅነት ያስፈልጋል አያስፈልግም) ከሚሉ ወገን አባቶችን በስም ጥቀስልኝ አለው::

“መረጃ ተጠናክሮ በሁለቱም ወገን ይቅረብልን” እንደሚል ዳኛ ውይይቱን ትቶ ዳኛ ሊሆን ተማጸነው::

“በሁለት ወገን ብሎ ነገር የለም:: ከዚህ ውጪ ሃሳብ ያለው ሰው ስለመኖሩምንም የተቀመጠ ታሪካዊ ማስረጃ የለም” አለ ምሕረት የለሹ ምሕረት::
@diyakonhenokhaile


ነገሩ እንዲህ ነው:: መጽሐፍ ቅዱስን አሁን ባለው ቅርጽ እንዲህ አድርጋ የሠራችው ቤተክርስቲያን ናት:: ይህ እውነታ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከሐዋርያት እጅ የተቀበሉትንና ሐዲስ ኪዳን በቀኖና ወስነው ለእኛ ያስተላለፉትን የመጀመሪያዎቹን ክርስቲያኖች ትርጉምና አረዳድ እንድንቀበል ያስገድደናል:: ልክ እስራኤል ሕግን ተቀብሎ የመጣውን ሙሴን እንደ ባለ ሥልጣን እንደተቀበሉትና ስለ ሕጉ የእርሱን አሳብ ያለማወላወል እንደተቀበሉ ሁሉ ሐዲስ ኪዳንን ከሐዋርያት እጅ የተቀበሉትን የመጀመሪያው ክፍለ ዘመን አባቶችም በሐዲስ ኪዳን ትርጉም ላይ ያላቸውን ሃሳብ መቀበል ግድ ይለናል:: ይህን ጠንቅቆ የተረዳው ዲያቆን ምሕረት:-

ጥምቀትና ቁርባን ተምሳሌቶች እንጂ ለድኅነት ፍቱን አይደሉም ስትሉን ነበር:: ከአንደኛ እስከ ሦስተኛው ክፍለ ዘመን ያሉ ክርስቲያኖችን ሃሳብ ስናይ ደግሞ እነዚህ ነገሮች ለመዳን የግድ እስፈላጊ መሆናቸውን ጽፈው እናገኛለን:: የእኔ ጥያቄ መጽሐፍ ቅዱስን በቀጥታ ከተቀበሉትና ሐዲስ ኪዳንን በቀኖና ከደነገጉ ክርስቲያኖች ጋር ትርጓሜያችሁ ካልገጠመ ምኑን በመጽሐፍ ቅዱስ አመናችሁ ይባላል? አላቸው::

በአጭሩ መጽሐፍ ቅዱስን ያዋለዱትን አዋላጆች ካልሰማችሁ ምኑን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሆናችሁት “ድምፅህ የያዕቆብን ይመስላል ጸጉርህ ግን የኤሳው ነው” ያለው ለእናንተ አይደል ወይ? እንደማለት ያለ ነው::
@diyakonhenokhaile


+ ምሕረት የለሹ ምሕረት +

የወንድሜ የዲያቆን ምሕረት መላኩንና የሁለቱን ፓስተሮች ውይይት ዘግይቼም ቢሆን አየሁት:: ውይይቱ በጣም በሰከነው የዲያቆኑ ኦርቶዶክሳዊ ጨዋነት የተነሣ ሁለቱን የፕሮቴስታንት ዋርካዎች በትሕትና ብቻ የገነደሰ ነበረ:: ቅመሙ ዲያቆን ምሕረት ውይይቱ እንደሚቀረጽ በደንብ ስላስተዋለ ጠይቆአቸው ሳይመልሱ ያለፉትን ወይም ያልተጠየቁትን ጉዳይ ያነሡበትን ቦታ ሁሉ ልክ ነጥብ “ተመልካች ይፍረድ” በሚመስል ብልጠት እየተወ ወደ ቀጣዩ ነጥብ የሚሸጋገርበት ፍጥነት ድንገት የገባበት ውይይት ሳይሆን የተጠና (scripted) ውይይት እንዲመስል አድርጎታል:: በጣም በትሕትና ሆኖ እየጠየቀ ዕርቃናቸውን ያሳየበት መንገድ ምን ያህል ሊያናድዳቸው እንደሚችል ሳስብ ውይይቱ በሰላም አለቀ እንጂ “ከአሁን አሁን ይመቱት ይሆን?” ብዬም ተሳቅቄያለሁ::

በውይይቱ ላይ ካየኋቸው ያስገረሙኝን ጥቂት እውነታዎች ላስቀምጥ:-

1. ቤተ ክርስቲያንን የሙጥኝ ማለት

ዲያቆን ምሕረት ውይይቱን የጀመረው የፓስተሮቹን አስተምህሮ ከቤተ ክርስቲያን ቅድምና አንጻር በማንሳት ነበር:: በዚህም ለፕሮቴስታንቱ ዓለም ደካማ ጎን የሆነውን ስስ ብልት በመምታት ጀመረ::
@diyakonhenokhaile


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#share#share
@diyakonhenokhaile


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#share #share
@diyakonhenokhaile


አሁን ተለቅቆአል::

#share #share
@diyakonhenokhaile

https://youtu.be/4oGa4gd0PX4?si=OXgC-L07tpRCCW_5


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የመጀመሪያው ቪድዮ ተለቀቀ

ዘወትር ዐርብ በ Henok Haile - Official Channel ይጠብቁ
#share #share
@diyakonhenokhaile


We are now on TikTok

አሁን ቲክቶክም ላይ ያገኙናል
@diyakonhenokhaile





20 last posts shown.