ዶይቸ ቬለን | DW AMHARIC


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


DW Amharic News is a global news and information channel from a German international broadcaster Deutsche Welle (DW)
Contact :- @dwamharicnewsbot

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


በኬንያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 172 ደረሱ!

የኬንያ ጤና ሚኒስቴር መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። በሀገሪቱ ተጨማሪ አስራ አራት (14) ሰዎች በቫይረሱ በመያዛቸው አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች 172 መድረሳቸውን ተገልጿል።

@dwamharic_news


በአዲስ አበባ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት ያላቸው የአውቶቡስ ባለንብረቶች በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ባለስልጣን ቢሮ በግንባር በመቅረብ ሪፖርት እንዲያደርጉና በህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ስምሪት ወስደው ወደ ስራ እንዲገቡ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል፡፡

ምንጭ፡- የከንቲባ ጽ/ቤት


ወቅታዊ መረጃዎች!

እስካሁን በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የኮቪዲ የላብራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 2,271 ውስጥ #52 ሰዎች መያዛቸው ታውቋል፡፡ 4ሰዎች ያገገሙ ሲሆን የ2 ሰዎች ደግሞ ሞት ተመዝግቧል፡፡ ከዚህም ውስጥ 42ቱ የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸው ሲሆኑ ቀሪዎቹ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ያላቸው ናቸው፡፡

ቫይረሱ ከአዲስ አበባ ውጪ በአዳማ፣ በባህርዳር፣ በድሬዳዋ፣ በአዲስ ቅዳምና በዱከም ተገኝቷል፡፡ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ በለይቶ ማቆያ የምትገኝ የዘጠኝ(9) ወር ህጻንና እናቱን ጨምሮ 8 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን አስታውቋል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን @dwamharic_news ላይ ይከታተሉ!

[ photo: Tena.et




የታማሚዎች ሁኔታ ፦

- በበሽታው መያዛቸው ከተረጋገጠ ስምንቱ ሰዎች መካከል አምስቱ #ከዱባይ የመጡና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደረግላቸው የነበሩ ናቸው።

- አንድ የዘጠኝ (9) ወር ህጻንና ወላጅ እናቱ ይገኙበታል።

- አንድ የ25 ዓመት ሴት ኢትዮጵያዊት ከታይላንድ መጥታ በለይቶ ማቆያ ክትትል ስታደርግ የነበረች በቫይረሱ መያዟ ተረጋግጧል።

- አንድ የ19 ዓመት ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ጉዞ ታሪክ #የሌለው ሲሆን የንክኪ ሁኔታውም በመጣራት ላይ ይገኛል። ወጣቱ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ እንዳለው ተጠርጥሮ በለይቶ ማቆያ የነበረ ነው።

- ሌላኛዋ የ30 ዓመት ሴት ኤርትራዊት ስትሆን ከእንግሊዝ ለንደን መጥታ በአዲስ አበባ በለይቶ ማቆያ ክትትል እያደረገች የምትገኝ ናት።

@dwamharic_news


በኢትዮጵያ አንድ የ9 ወር ህጻንን ጨምሮ ተጨማሪ ስምንት (8) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ!

ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 264 ሰዎች ውስጥ 8 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ። በቫይረሱ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ የዘጠኝ (9) ወር ህጻን የተያዘ ሲሆን እናቱም ቫይረሱ ተገኝቶባታል።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች መካካል አንዱ ኤርትራዊ ሲሆን ቀሪዎቹ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው። ይህም በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 52 አድርሶታል ነው ያሉት።

@dwamharic_news


#BackToWork

በቻይና ህይወት ወደመደበኛው ሁኔታ እየተመለሰ ይገኛል። ዛሬ ከባለፉት ቀናት እጅግ በተሻለ መልኩ በተለያዩ ከተሞች እንቅስቃሴዎች ጨምረዋል። ዛሬ ቻይና ዴይሊ ያጋራቸው ምስሎችም ይህንኑ የሚጠቁሙ ናቸው።

ሀገሪቷ ከወራት በኋላ አዲስ ሞት እንዳልተመዘገበ አሳውቃለች ምንም እንኳን 'ናአንዳንድ አካላት ከሀገሪቱ የሚወጡ ሪፖርቶች ላይ እምነት እንደሌላቸው ቢናገሩም።

በቻይና ዜጎቿ ከከተማ እንዲወጡ እንዲሁም እንዲንቀሳቀሱ ተፈቅዷል፤ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የቱሪስት መዳረሻዎች አገልግሎት እንዲሰጡም ተደርጓል።

ከሶስት ሺ በላይ ዜጎቿን የተነጠቀችው ቻይና በበሽታው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷልም ብላለች።

@dwamharic_news


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#DrTedrosAdhanomGhebreyesus

በሁለት (2) የፈረንሳይ ተመራማሪ ሐኪሞች የተሰጠውን የኮቪድ-19 ክትባት በአፍሪካ መሞከር አለበት የሚል ሃሳብ የዓለም ጤና ድርጅት ጄነራል ዳይሬክተር " ዘረኛ" ሲሉ ተችተዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ጄነራል ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም " አፍሪካ ለማንኛውም ክትባት መሞከሪያ አትሆንም፣ መሆንም የለባትም" ብለዋል።

የሕክምና ባለሙያዎቹ ክትባቱ መሞከር ስላለበት ጉዳይ አስተያየት የሰጡት በቴሌቪዥን ይካሄድ በነበረ የቀጥታ ክርክር ወቅት ነው። ይህ የሐኪሞቹ አስተያየት ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን አፍሪካውያንንን " መሞከሪያ አይጥ" አድርጎ ማሰብ ነው ብሏቸዋል።

ከዚህ አስተያየት በኋላ አንዱ ህክምና ባለሙያ ይቅርታ ጠይቀዋል። ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ስለኮሮና ቫይረስ መግለጫ በሚሰጡበት ወቅት ስለጉዳዩ ሲጠየቁ መናደዳቸው ተስተውሏል።

ከዚያም " የቅኝ ግዛት አብሾ" አልለቀቃቸውም ሲሉ መልሰዋል። "በ21ኛው ክፍለ ዘመን ከሳይንቲስት እንዲህ አይነት አስተያየት መስማት የተዋረደ፣ አሳፋሪ ነው።

እንዲህ ዓይነት ነገርን በማንኛውም ሁኔታ እናወግዛለን። እናም የማረጋግጥላችሁ ነገር ይህ በጭራሽ አይሆንም" ብለዋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@dwamharic_news


ጠ/ሚ ቦሪስ ጆንሰን ወደፅኑ ህሙማን ክፍል ገቡ!

የብሪታንያው ጠቅላይ ሚንስትር ቦሪስ ጆንሰን ወደ ሆስፒታል ከገቡ በኃላ የህመማቸው ሁኔታ ስለጠነከረባቸው ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል እንደገቡ ቃል አቀባያቸው ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1, BBC

@dwamharic_news


በፈረንሳይና አሜሪካ ወረርሽኙ እየከፋ ነው!

- የኮሮና ቫይረስ ሪፖርት ከተደረገ ወዲህ በፈረንሳይ በአንድ ቀን ከፍተኛ የሟቾች ቁጥር ተመዝግቧል። በፈረንሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 833 ሰዎች ሞተዋል። በአጠቃላይ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎችም 8,911 ደርሰዋል።

- በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ሕይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥርም ከ10,000 መብለጡን ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ ይፋ አድርጓል። በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 355,000 በላይ ሆኗል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

@dwamharic_news




የቦሌ ክ/ከተማ ትናንት ለሊት ብቻ 345 ህገ-ወጥ ቤቶች ተሰርተው አድረዋል ብሏል!

ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ከክ/ከተማው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጥላሁን ተሰማ አገኘውት ባለው መረጃ መሰረት እነዚህ ቤቶች ለሊቱን ቦሌ ቡልቡላ ወረገኑ አካባቢ በሸራ ተሰርተው ያደሩ መሆናቸውንና ህገ-ወጥ ደላሎች ሂደቱን እየደገፉ መሆኑን ኃላፊው መናገራቸውን ገልጿል።

ከቀናት በፊትም ቦሌ ቡልቡላ አሰር ኮንስትራክሽን ተብሎ የሚጠራው ስፍራ ተመሳሳይ ድርጊት ተከስቶ እንደነበርና "እኛ በሽታ ለመከላከል ስራ እየሰራንበት ባለበት ወቅት መንግስት ተዘናግቷል ተብሎ የሚደረግ ህገ-ወጥ ስራ ነው" ብለዋል። አቶ ጥላሁን አክለውም "መንግስት እርምጃ እየወሰደ ነው፣ ወደፊትም ይወስዳል" ብለዋል ሲል ጋዜጠኛ ኤልያስ በገጹ ጽፏል፡፡

@dwamharic_news


በኮት ዲቮር የተቃውሞ ሰልፈኞች የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማእከል አቃጠሉ!

በኮት ዲቮር አቢጃን ከተማ አቅራቢያ በግንባታ ላይ የነበረ የኮሮና ቫይረስ ማእከል በተቃውሞ ሰልፈኞች መቃጠሉን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል፡፡ ማእከሉን ከማቃጠላቸው በፊት ሰልፈኞቹ ጎማ ሲያቃጥሉ ነበር፡፡

ከአካባቢው የተውጣጡት ሰልፈኞቹ ማእከሉን በሚያቃጥሉበት ወቅት “ማእከሉን አንፈልገውም፤ ቫይረሱን አምጥታችሁብን ልትገሉን ነው” የሚል የተቃውሞ ድምጽ እያሰሙ እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ተቃውሟቸውን ትናንት የጀመሩት ሰልፈኞቹ በዛሬው እለትም ከፖሊስ ጋር ሲጋጩ መዋላቸውም በዘገባው ተካቷል፡፡ በተፈጠረው ግጭት የተጎዳ የለም ተብሏል፡፡ ሀገሪቱ እስካሁን ከ260 በላይ የቫይረሱ ታማሚዎች የተገኙባት ሲሆን ሶስት ሰዎች ሞተዋል፡፡ ማእከሉ በአቢጃን ከሚገነቡ መሰል ማእከላት አንዱ ነው፡፡

ምንጭ፡- አል ዓይን

@dwamharic_news


#AbiyAhmedAli

በቅርቡ የሚኒስትሮች ምክር ቤት የመከረበት ረቂቅ የኤሌክትሮኒክ ግብይት አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ሲጸድቅ በኤሌክትሮኒክ አገልግሎት አማካኝነት የሚፈጸሙ ሁሉንም የግብይት ሂደቶች ለማከናወን የሚቻልበት ደንብ እንዲኖር ያስችላል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ገልጸዋል፡፡

ሕጉ በሁሉም የኮሙኒኬሽን ዘርፎች የሚታየውን የኢንፎርሜሽን እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ፍላጎት መሠረት በማድረግ፣ የመንግሥት እና የግል ተቋማት ዲጂታል አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚችሉበትን ግልጽ ሕጋዊ መሠረት ያበጃል ሲሉ ነው ጠ/ሚኒስትሩ የገለጹት፡፡

የኤሌክትሮኒክ ንግድ እና የኤሌክትሮኒክ መንግሥታዊ አገልግሎቶች፣ በኤሌክትሮኒክ ግብይት አማካኝነት ዳታን መለዋወጥ እና ማከማቸት፣ ኤሌክትሮኒክ ምዝገባና ፊርማዎች እንደዚሁም የኤሌክትሮኒክ ዳታ መልእክቶች በሥርዓቱ ከተካተቱት አገልግሎቶች ውስጥ ይገኛሉ፡፡

የሕጉ መጽደቅ ከንግድ፣ ከቀረጥ፣ ከሰነድ ማረጋገጥ፣ ከማኅተም፣ ከምስክር፣ ከዲጂታል ክፍያ አኳያ ታላቅ አስተዋጽዖ እንደሚኖረው የታመነበት ሲሆን የተጠቃሚዎችን መብት ለማስከበርና ዳታ በጥሩ ይዞታ እንዲቆይ ለማድረግም የተሻለ ጥቅም ይሰጣል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ አክለው ገልጸዋል፡፡

@dwamharic_news


ኬንያ ውስጥ ባለፉት 24 ሰዓት 441 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል፤ ከእነዚህ ውስጥ ነው 16 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] መያዛቸው የተረጋገጠው። በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 4,277 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል።

@dwamharic_news


አዲስ አበባ አንዳንድ ቦታዎች ቤት እየፈረሰ መሆኑ ትክክል አይደለም የሚሉ ቅሬታዎች ዛሬ በማህበራዊ ድኅረገጾች እየተንሸራሸሩ መሆኑን ተመልክተናል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በበኩሉ ወቅታዊ ሁኔታ ተገን በማድረግ የመሬት ወረራዎች እየታዩ እንደሚገኙ ጠቁሟል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ህገወጥ ይዞታዎችን እያፈረሰ እንደሚገኝና ፈፃሚዎችና ተባባሪዎችን በህግ እጠይቃለሁ ሲልም ገልጿል፡፡


የስፔን የ24 ሰዓት ሪፖርት ፦

በስፔን በ24 ሰዓት የ637 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ቁጥሩ ባለፉት 2 ሳምታት ከተመዘገበው ዝቅተኛው ነው። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር ከ13ሺህ በልጧል።

በተጨማሪ ባለፉት 24 ሰዓት 4,373 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን ቁጥር ባለፉት ቀናት ከተመዘገበው ዝቅተኛ ነው (ቅዳሜ - 7,000 , እሁድ - 6,000) ጥብቅ የሆነ የአካላዊ ርቀት ውጤት እያመጣ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia


የጋና ጤና ባለሞያዎች ለ3 ወር ከታክስ ነፃ ሆኑ!

የጋና ፕሬዝዳንት ናና አኩፎ አዶ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ሕሙማንን የሚንከባከቡ እንዲሁም የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ጦርነቱን ከፊት መስመር ሆነው ለሚመሩት የጤና ባለሙያዎች ወርሃዊ ደሞዛቸው ላይ #ጭማሪ እንደሚኖር ግልፀዋል። በተጨማሪ በጋና ውስጥ ያሉ ሁሉም ጤና ሰራተኞች ለሶስት (3) ወራት ከታክስ ነጻ እንደሚሆኑ አስታውቀዋል

@dwamharic_news


#DrLiaTadesse

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦

• በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 164
• ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 1
• በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 1
• ያገገሙ - 4
• በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2
• እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 44

@dwamharic_news


በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 44 ደረሱ!

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው 164 ሰዎች ውስጥ አንድ ግለሰብ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳስታወቁት፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች መካካል 26ቱ በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ናቸው።

ቀሪዎቹ ደግሞ ለቫይረሱ ተጋላጭ ከሆኑ ማህበረሰቦች ናቸው ተብለው የተመረመሩ መሆናቸውን ነው የገለጹት።

ዛሬ በቫይረሱ የተያዙት ግለሰብ የ65 ዓመት ሴት ኢትዮጵያዊት ሲሆኑ የዱከም ከተማ ነዋሪና የውጭ አገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸው ናቸው።

ግለሰቧ ተጓዳኝ ለሆነ በሽታ ወደ ህክምና ተቋም ከሄዱ በኋላ የቫይረሱን ምልክት በማሳየታቸው ነው ምርመራ የተደረገላቸው።

በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተያዙ ግለሰቦች ቁጥር 44 የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ መካከል አንድ ግለሰብ በጽኑ ህሙማን ማቆያ ይገኛሉ።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@dwamharic_news

20 last posts shown.

1 720

subscribers
Channel statistics