የዲያቆን አቤንኤዘር ተክሉ ገጽ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Esoterics


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Esoterics
Statistics
Posts filter


ማዳን የክርስቶስ ብቻ ነው፤ … ሌላ ኹለተኛ ሦስተኛ አማራጭ የለም (ያረጋል አበጋዝ)
ይህ ሕያው እውነት የኦርቶዶክሳውያን ቋሚ ስብከት ቢኾን ደስ ባለን ነበር፡፡ እኛ ግን እንላለን፤ ማዳን የክርስቶስ ብቻ ነው!


ጌታ ኀጢአተኞችን የሚቀበለው፣ ኀጢአተኞች ኾነው እንዲቀጥሉ አይደለም።


ጨዋው ዘበነ ለማ ፣ "ኢየሱስ ማለት አያድንም" ይላል። መልአኩ ለማርያም ሲናገር ግን እንዲህ አለ፣
“... እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ።” (ማቴ. 1፥21) አይ ዘቤ!


“ … ውስጣችሁ ግን ቅሚያና ክፋት ሞልቶበታል።” (ሉቃ. 11፥39)


ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን ሲጽፍልን፣ ትኵረት ካደረገባቸው ታላላቅ መንፈሳዊ ነገሮች አንዱ፣ ድኾችን በተመለከተ ነው። በወንጌሉ ውስጥ ኢየሱስ ቤት አልባ ድኻ ነው (9፥58)፣ አገልግሎቱ አምነው በተከተሉት ሴቶች ይደገፍ ነበር (8፥3)፣ አገልግሎቱ ለድኾች ወንጌልን በመስበክ እንደ ኾነ ተናገረ (4፥18)፣ ቅድስት ድንግል ማርያም ድኻ እናት መኾንዋን በመሥዋዕት አቀራረቧ አሳየ (2፥24)፣ “የተራቡትን በበጎ ነገር አጥግቦአል፤” (1፥53) እንዲል፣ ድኾችን በብዙ እንደሚጐበኝና እንደ አልዓዛር ያሉ ድኾችን በሰማያት በብዙ ደስታ እንደሚያከበር ማስተማሩን ጽፎልናል (16፥19)፤ ይህ ብቻ ሳይኾን ሉቃስ፣ በኤልያስ ዘመን የነበረችውንም የሰራፕታዋንም ድኻይቱን መበለት አንስቶአል (4፥26)።


ጌታችን ኢየሱስ በሉቃስ ወንጌል ውስጥ “የመላለሙ መሲሕ” መኾኑ ሲገለጥ፣ እጅግ በሚያስደንቅ መልኩ ድኾችን የሚያስብ፤ የማይዘነጋ መኾኑንም ይነግረናል። ከላይ በርዕሳችንም እንደ ጠቀስነው፣ ከኢየሱስ በተቃራኒ ግን “ሃይማኖት ለበስ ኾነው” ሕግ እየጠቀሱና መቅደስ ተቀምጠው ድኾችን ስለሚያስጨንቁ ፈሪሳውያንና ሕግ ጸሐፎች በወዮታ ሲናገራቸው እናስተውላለን። ኢየሱስ እጁን ሳይታጠብ በገበታ ሲቀርብ፣ ስለ እጅ መታጠብ ሕጋቸው ይጨነቃሉ ነገር ግን ውስጣቸው ስስታምና ስግብግብነት የተጠናወተው ነበር።

ሃይማኖታዊ መልካቸው ውጫዊ እንጂ ውስጣቸው ፍትሕ አልባነት፣ ስግብግብነት፣ ስስታምነት፣ እግዚአብሔርን ባለመውደድ የተሞላ ነበር። ጌታችን ኢየሱስ ይህን ያደርጉ የነበረው፣ የዕውቀት ችግር ሳይኖርቸው እንደ ነበረ ሲናገር፣ “የእውቀትን መክፈቻ ስለ ወሰዳችሁ …” ብሎአል፤ ያውቃሉ ግን ወደ መንግሥቱ አይገቡም፤ ሰዎች እንዳይገቡም ዕውቀታቸውን በማጣመም ያቀርባሉ።

ከምንም ነገር በላይ ደግሞ ሕጉን ተገን አድርገው፣ ከአዝሙድና ከጠጅ ሳር ሳይቀር ከጥቃቅኑ ነገር ከድኾች አስጨንቀው አሥራትን ያስወጣሉ፤ ያወጣሉም። ግን ድኾች የሚገባቸውን ዋናውን ነገር አይሰጧቸውም። ውስጣቸው በክፋትና በመበደል፤ ሌላውን ከመጕዳት የማያርፍ ነበር።

ስለ ድኾች ሳስብ አያሌ ነገር ወደ ልቤ ይመጣል፤ ምዕራባውያን በሌሎች አገራት ላይ ጦርነት የሚቀሰቅሱበት ዋነኛ ምክንያት ጦርነት ከሚደረግበት ምድር ሃብት ለመዝረፍና በራስ ወዳድነት በተለይም አፍሪካን እንደ ፈረንሳይ ያሉ ምዕራባዊ አገራት ውድ ማዕድናትን ለመውሰድና በረጅም እጃቸው በጦርነት ድኾች አገራትን የሚያምሱት የድኾችን መቀነት ለመበዝበዝ ነው፤ በኢትዮጵያ መሪዎች እጅ፣ ዓለም ዓቀፍ የገንዘብ ተቋም የተባለው በስግብግብነቱ አቻ የሌለው አስፈሪና ጨካኝ ድርጅት ድኾችን በማስጨነቅ እየረካ ይመስለኛል … በሚያሳዝን መንገድ፣ አንዱ ከሌላው በስስታምነትና ባለመጥገብ የሚሰበስበው “ብዙ” ነው።

በአይሁድ ማኅበረ ሰብ ዘንድ ሊረሱ የማይገባቸው ድኾች ተዘንግተው ነበር፤ ይህ የፈጠጠ እውነት እስከ ጌታ መምጣት ድረስ ፈክቶና ጐልቶ ይታይ ነበር። እግዚአብሔር ለድኾች ስስ ልብ ያለውን ያህል፣ ሕዝቦቹ የእግዚአብሔርን ልብ አለመያዛቸው እጅግ አሳዛኝ ተግባር ነው። ኢየሱስ፣ በሉቃስ ወንጌል ውስጥ ትኵረቱ፣ ድኾች፣ እስረኞችና ዐይነ ስውራን ናቸው። እጅግ በሚያደንቅ መንገድ ሉቃስ በጻፈው በሐዋርያት ሥራ ውስጥ የተጠቀሰችው የመጀመሪያዪቱ ቤተ ክርስቲያን አብዛኛዎቹ ድኾች ነበሩ። ነገር ግን የኢየሱስ መንፈስ ፈጽሞ አልናቃቸውም፤ አበረታቸው፤ አጽናናቸው!

ደቀ መዛሙርትም ድኾችን በብዙ ወደዷቸው፤ በጋራ ማዕድ አክብረው አቀረቡአቸው። በብርቱ የእግዚአብሔርም ቃል አጽናኑአቸው! የዛሬዋም ቤተ ክርስቲያንም ድኾችን በማግለል የምታገለግለው የትኛውም “ጠንካራና ሳቢ አገልግሎት” በእግዚአብሔር ፊት ከወቀሳና ከነቀፋ አያመልጥም። አርቲስቶችን፣ ባለሥልጣናትን፣ ዓለም ያገነነቻቸውን፣ ባለጠጎችን … በማቅረብና ድኾችን ችላ ብለን የምንሄድበት መንገድ ርሱ የተወዳጁ የናዝሬቱ ኢየሱስ መንገድ አይደለም!

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን።” (ኤፌ. 6:24) አሜን።


My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/03/1139.html


ፕሮፌቲክ ዕራት ግብር ደጋሹ "ዘራፊ"!

በዚህ ዓመት መግቢያ ላይ አብያተ ክርስቲያናት በተጠሩበት ስብሰባ ላይ ይህ ሰው ተገኘ። የስብሰባው ዓላማ ገንዘብ ማሰባሰብ ነበርና፣ ብዙዎቹ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ከ5-10ሺ ብር ቃል ሲገቡ፣ ይህ ሰው ግን አርፍዶ ገብቶ ብዙም ሳይቆይ፣ 100ሺ ሰጥቻለኹ አለና ወጥቶ ሄደ። እየተሳቀቁ ቃል ይገቡ የነበሩ መሪዎች አሳዘኑኝ። ለአንድ ወንድሜ ይህን ሳጫውተው፣ "በቃ፤ የሰጠውን ሊቀበል ነው የወጣው" አለኝ። ልክ ነበር!

በርግጥ "የነጠጠ ድኻ ባለባት ምድር ላይ" አንድ ዕራት "5ሚሊየን" የተሸጠ ዕለት፣ እኔን የዕራት ነገር በቅቶኛል። የሐ*ሰት አገልጋዮች ክፉ ምሳሌ በመከተል አቻ የላቸውም። ይኸው "ግብር ጥሎ"፣ ቀረጥ ሊቀርጥ ደረሰ ደገሰ። በኪሳችሁ ላይ እንዲ*ቦጠ*ቡጥ የፈቀዳችኹለት ሂዱ፤ ኢየሱስን በማይጠፋ ፍቅር የምትወድዱ ግን ተጠንቀቁ!

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


ስልክ በቅዳሴ ሰዓት የከለከለው የአዲስ አበባ ሐገረ ስብከት፣ በነካ እጁ ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር የሚላተሙ ገድልና ድርሳናት፣ ነገራትና ተአምራትንም ጠራርጎ ቢያስወግድ እንዴት ሸጋ ነበር?!


"ማርያም ጥንተ አብሶ አለባት።" (ኦርቶዶክስ)
"ማርያም ጥንተ አብሶ የለባትም።" (ካቶሊክ)
“ኹሉ[ከኢየሱስ በቀር] ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤” (ሮሜ 3፥23)
ቅዱስ ቃሉ ብቻ እውነት ነው!


አቡነ ገብርኤል ስለ ሚሰበከው ወንጌል በግልጥ ይናገራሉ፦

" ... ድርሳን፣ ገድል ... ይተረካል ይነገራል እንጂ አይሰበክም። የሚሰበከው የተሰቀለው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ... የኹለት ሺህ ዘመን ትኩስ ዜና ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ..."


ebs የሚያሳየው "የአዲስ ምዕራፍ" ፕሮግራም አንዳንዱ "ሰቅጣጭ" ነው። አኹን በዚህ ሰዓት ሰውን ለመርዳት በሚል ሕፃናትን እንዲህ ማሳቀቅና ማስለቀስ ምን ይሉታል? ምናለ ፕሮግራም ሲሠሩ ለሕፃናት ቢጠነቀቁ? በተደጋጋሚ እመለከታለኹና። የሚረዱትና የሚያገኙት ገንዘብ ምንም ሊኾን ይችላል፤ ነገ ላይ በሚያዩት ነገር ሕፃናቱ እንዳይሰቀቁ መጠንቀቁ እጅግ መልካም ይመስለኛል። የምዕራቡ ዓለም ፊልም ሠሪዎች የውሸት ደም እያፈሰሱ ነገር ግን ሕፃናትን ፊታቸውን ሲከልሉ፤ ጭቅጭቅና ሐዘን ሲኖር ሲሸሽጓቸው ይስተዋላል። የእኛዎቹ ግን ኹሉ በሚያየው የቴቪ መስኮት፣ የሚታዩ ሕፃናትን ቅስም በሚሰብር መልኩ ያቀርባሉ። እባካችሁ "ስትፈውሱ" ዕዥ ቁስል አታሰንብቱ!

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


ሰውና እግዚአብሔር የታረቁበት አማናዊው ኪዳነ ምሕረት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!


ከኢየሱስ ወደ ማንም አንሄድም፤ እርሱ የመጀመሪያም የመጨረሻም ተስፋችን ነውና!


"ሥጋዋን አንጽቶ በማርያም አደረ
ቃሉን በነቢያት ቀድሞ ያናገረ"
የሚለው "ዝማሬ" በአእላፋት ዝማሬ ሲዘመር ማን ትንፍሽ አለ? መቼም ሥጋ ከምን እንደሚነጻ ሳይታወቅ ቀርቶ ነውን?


እንናፍቃለን!

ከሰሞኑ ኦርቶዶክሳውያኑን በዋናነት በገድላት፣ “ማርያም ኀጢአት አለባት ወይስ የለባትም?” እና በሌሎችም ጉዳዮች “እየተፈሳፈሱ” ይመስለኛል፡፡ ቀሲስ ዲበኩሉ በላይ የተባሉት “አባት”፣ “ሐዋርያዊ መልሶች” በሚል ስያሜ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከሚያገለግለው አክሊል ከሚባል “ወጣት” ጋር በተለይ “ገድልን መርምሬ እንጂ በደፈናው አልቀበልም” በማለቱ ብዙዎች ቲክቶዶክሶች ጥርስ ነክሰውበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፣ “ማርያም ኀጢአት አለባት” ብሎአል በሚል ሌላኛው አባት አስጠንቅቀዋል ተባለ፡፡ ነገሩ እንደ ዘበነ ለማ ያሉ ሰዎችም ፊት ለፊት ስሙን ጠቅሰው ባይናገሩም፣ ነገር ግን “ገድል አልቀበልም የሚል ኦርቶዶክስ አይደለም” በማለት አቋማቸውን አንጸባርቀዋል፡፡

በአጭሩ የገድልና የማርያም “ልዕለ ልዕልትነት” ጉዳይ ይህን ያህል ያጨቃጨቀው እነ ዘበነንም ኾነ ቄስ ዲበ ኩሉን፤ አስጠንቃቂውን አባት ጠቅሞ አይደለም፤ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቱ ወደ እውነተኛ ወንጌል ፊቷን እንዳትመልስ ተግተው ስለሚሠሩና ስለሚፈልጉ እንጂ፡፡ ጌታ ኢየሱስ ይገስጻቸው!

እንደ በፊቱ በጥቂቱም ቢኾን፣ ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ አቋምን የያዙ ሰዎች፣ በዚያው መድረክ ብቅ ማለታቸው ይበል የሚያሰኝ ነው፡፡ እኛም አቋማችን ለኦርቶዶክስ ሌላ ሐዳሲ እንዲመጣ አንሻም፤ የራስዋ ልጆች በትክክልና በእውነት፤ በማያመቻምች አቋም ትክክለኛ ሐዳሲ እንዲኾኑ ነው ናፍቆታችን፤ አክሊል የተባለውም ወጣት “ኹሉን አውቃለሁ ባይነቱን” ትቶ፣ በክርስቶስ ባለው መዳንና ጸጋ ተግቶ፣ በቤቱ ውስጥ ያለውን የተነቀፈ ጽድቅና ቅድስና፤ መካከለኛና አስታራቂ በመናገር፤ በመስበክ ቢተጋ በእግዚአብሔር ሉዓላዊነት ብዙዎች ወደ ወንጌል ይመጣሉ የሚል እምነት አለኝ!
አክሊል፤ ወደ እኛም ኾነ ወደ ወንጌላውያን መምጣት አለበት ብዬ አላምንም፤ ሸክሙ ወገኖቹ፤ ጭንቀቱ ኦርቶዶክሳውያን ሊኾኑ ይገባል፤ ጨርሶ ካልተገፋ በቀር ሊወጣ አይገባውም ከሚሉ አንዱ ነኝ!

ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ እንደ ቃሉና እንደ መንፈስ ቅዱስ ምሪት ብቻ እንዲኾን እንናፍቃለን!




ሕይወት ቴቪን "የእውነት ቃል አገልግሎት" ሊታደግ?


መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ቃል፣ “አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።” (1ቆሮ. 15፥33) ይላል። “አትሳቱ” የሚባለው ለሚያውቁና ለተረዱ አማኞች ነው። የሚባልበትም ምክንያት፣ የሚያስቱና የሚያሳስቱ ስላሉ ነው። ከክፍሉ እንደምንረዳው በቆሮንቶሳውያን መካከል ትንሣኤ ሙታንን በመናቅና በማቃለል፣ ሕይወትን፤ ዕለታዊ ኑሮን ከመብልና ከመጠጥ ጋር ብቻ ያያያዙትን “አማኞች” ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ካሉት መራቅና ኅብረታቸውን መተው እንደሚገባ ይናገራል። ምክንያቱም ክፉ ባልንጀርነት የመልካሙን ዐመል ስለሚያጠፋ ነው ይለናል። ከበላተኛ ከጠጪ ወይም የሆድን ነገር ብቻ ከሚያወሩ ጋር መዋል፣ ትንሣኤ ሙታንን እንድንንቅ ያደርጋሉና። በሌላ ንግግር የማይገባ ግንኙነት እንደ ጭንቁር እንደሚባላ ማስተዋል እንችላለን።


ይህን እንድል ያደረገኝ፣ ገና ከመከፈቱ "የታደጉኝ" ጥሪ ያቀረበውና ንብረትነቱ የቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የኾነው ቴቪ፣ ምን ገጥሞት ታደጉኝ እንዳለ ለመገመትም ለማመንም ይቸግራል። ቤተክርስቲያኒቱ ሚሊዮናትን ያለፈ አባላትና አማኞች እንዳላት አውቃለኹ። ከወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የቀደምትነት ሥፍራ ከሚሰጣቸው መካከል ናት። ምናልባትም ለኦርቶዶክሳዊው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትና ሕይወት እንዲጸናና እንዳይበረዝ በዕቅበተ እምነት ላይ የሚሠሩ፤ እንዲኹም በማኅበራዊ ሕይወትና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የሚሳተፉ እንደ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌና ጌታሁን ሔራሞ ያሉ “ጉምቱዎችን” ያፈራች ቤተክርስቲያን ናት።

ቤተክርስቲያኒቱ ለተከታዮቿ በቴቪ አገልግሎት መምጣትዋ ይበል የሚያሰኝና እጅግ መልካም ነው። አማኞቿን ይዛ አብነትና ምሳሌነት ያለው ትልቅ ሥራ ትሠራለች፤ በግለኝነትና በከበርቴነት እንደ ፈለጉ ከሚፋንኑ “ነቢይና ሐዋርያ ተብዬዎች” በምታቀርበው ጠንካራ መርሐ ግብር ትኰንናለች፤ በተለየ መንገድ በኅብረትና ብዙዎችን በማሳተፍ የተዋጣለት ሥራ ያቀርባሉ ስንል፤ በጌጃ ያሉትን ከ40 ዓመታት በላይ እስከ ዛሬ ድረስ በዝማሬ የቆዩ እናትና አባቶችን ሕይወትና የአገልግሎት ፍሬአቸውን እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች ያሉትን ውብ የወንጌል ምስክርነቶችን ያቀርባሉ ብለን ገና እየጓጓን ሳለ ... ድንገት “ታደጉን” የሚል የድካም ጩኸት አሰሙን። ግን ለምን?

ሕይወት ቴቪ ከኤልሻዳይ ቴቪ ሊማር ይገባዋል። ኤልሻዳይ ቴቪ እንደ ኃይሉ ዮሐንስ፣ ግርማ በቀለና ዘላለም ጌታቸው ላሉ ሐ*ሰ*ተኛ አስተማሪዎች መድረኩን በመክፈት፣ የኢትዮጵያ ክርስትና እንዲቀየጥና እንዲመረዝ የላቀ ሚና ከተጫወቱት የሚመደብ ነው። ሕይወት ቴቪ ከዚህ ከኤልሻዳይ ቴቪ “ስብራት”፣ “እሳት እንደ ነካ ሕፃን” መማሪያ ካልኾነው ከምንም ሊማር አይችልም። አጉል ባልንጀርነት ዳፋውና ጦሱ ብዙ ነውና።

እኔ በግሌ፦ አስተዳደራዊ መዋቅር ቢያስተካክሉ፣ ወደ ሥራ የሚተገበር ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ቢያዘጋጁ፣ አማኞቻቸውን በማስተባበር የገንዘብ አያያዝና አጠቃቀማቸውን ቢያስተካክሉ ... ሌሎችን ታደጉን ከሚል ልመና ነጻ ይወጣሉ ብዬ አምናለኹ። ከዚህ የሚከፋውና የሚያሳዝነው ግን ለትድግና የመጡት አካላት ናቸው። “የእውነት ቃል አገልግሎት” ይባላሉ። መሪያቸው ግርማ በቀለ ይባላል። ስለ “እውነት ቃል አገልግሎት” የተሳ*ሳተ ትምህርትና ልምምድ በአደባባይ ሲናገሩ ከነበሩት አንዱ እኔ ነኝ። እነርሱ ከእነርሱ ውጭ ያሉትን ኹሉ፣ በተለይ ኦርቶዶክስንና ቀደምት ወንጌላውያንን “ጋለሞታዎች” በማለት የሚጣሩ፣ ጤናማ የኾነ የትምህርትም ኾነ፣ የልምምድ ሕይወት የሌላቸው ናቸው። እናም ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ከኤልሻዳይ ቴቪ ተምራ ከቅይጥነት ነጻ እንድትወጣ እመኛለኹ። በርግጥ “ጋለሞታ” ወደሚሏት ቤተክርስቲያን ሊጠቅሟት አልመጡም።

የተሐድሶ አገልግሎትን በትምህርታቸውና በልምምዳቸው ከሚያዳክሙና በተጣ*መመ ትምህርታቸው ወደ ዓለማዊነት ከሚነዱት መካከል ቀዳሚዎቹ “የእውነት ቃል አገልግሎት” ቡድኖች ናቸው። የሚያሳዝነውና ልብ ሰባሪ ሥራቸው፣ የሚያጠምዱት “የዳኑትንና ወደ ጌታ የመጡትን” እንጂ ሌሎችን አያጠምዱም። እናም ቃለ ሕይወታውያን በቃለ ጥፋት እንዳትወረሱ ለራሳችኹ ተጠንቀቁ።

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ባለመጥፋት ከሚወዱ ሁሉ ጋር ጸጋ ይሁን፤ አሜን።” (ኤፌ. 6፥24)

My telegram link - https://t.me/ebenezertek
My blog link -http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/02/blog-post_68.html
My youtube link - http://www.youtube.com/@-abenezertekludiyakon8842


መላእክት፣ ቅዱሳን ሰዎች፣ ቅድስት ማርያም … ኹሉ እያሉ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ለመዳናችን ሰደደልን።


እኛ ኢትዮጵያውያን እኮ፣ ሚሊዮናትን የፈጀ ጦርነት አካሂደን ምንም ያልመሠለንና እንዲህም ኾነን ፍጹም "አማኝና ጻድቃን" እንደ ኾንን የምንናገር "የአሥራት አገር ሕዝብች ነን"¡ መገን!


"ገድል ካልተቀበልህ ኦርቶዶክስ አይደለህም" (ዘበነ ለማ)
"ገድል ለሃይማኖት ክርክር አንጠቀምም" (ቲክቶዶክሶቹ)
ለመዋሸት እንኳ ተስማሙ እንጂ!


ነክቶ መመለስ፤ ርኩ*ሰት ማስለመጃ መንገድ!

ከአዲስ አበባ አንዱ ትምህርት ቤት፣ የሰዶ*ማ*ዊነት ርኩ*ሰት ሥልጠና ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን መናገራችንን ተከትሎ፣ በትር ሲበዛበት ከታች ባለው ደብዳቤ "መሠረዙን" ገልጾአል።

ኢትዮጵያ ሌሎች ዐገራት የወደቁበትን የርኩ*ሰት መንገድ፣ የተያያዘችው ይመስላል። ዐሳቡን ወደ አደባባይ ያወጡትና፣ ወዲያው ደግሞ ተውነው ሲሉ ይሰማል። መተዋቸው ለበጣ ይመስለኛል። ምክንያቱም ሲጀመር አይነኬ ነገር የሚነኩት በዐላማና በዕቅድ ነውና።

ትምህርትና አደባባያዊ ወስ*ላታ*ነት የሚገለጠው፣ ከጀርባ የዳበረ ልምምድ ሲኖር ነው!
ተጠንቀቁ!
ተጠበቁ❗️

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
Fayyisuun kan Waaqayyooti (Yonas 2:9)

20 last posts shown.