የዲያቆን አቤንኤዘር ተክሉ ገጽ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Esoterics


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Esoterics
Statistics
Posts filter


የተሰበረ የውኃ ማጠራቀሚያ አይኹንላችሁ! (ኤር. 2፥9-13)


ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ በሙሾና በልቅሶ፤ ከፍ ባለ ሕመም ውስጥ ኾኖ ያገለገለ፤ ከ“ዐበይት” ነቢያት መካከል አንዱ ነው። ገና እጅግ ወጣት በነበረበት ጊዜ (ኤር. 1፥6) ለነቢይነት የተጠራው ኤርምያስ፣ ሕዝበ እግዚአብሔር ተብላ የተጠራችው እስራኤል እጅግ በኀጢአት በተዘፈቀችበት፤ ከያህዌ ይልቅ ሌሎች አማልክትን በማፍቀር በነሆለለችበት፤ የማያረኩና ጥምን የማይቆርጡ ምንጮችን ለራስዋ በቆፈረችበት ወራት መምጣቱ፣ ልቡን በሥጋትና በፍርሃት፣ በጥርጣሬም ንጦት እንመለከታለን።


የኤርምያስ አገልግሎት፣ “ትነቅልና ታፈርስ ዘንድ፥ ታጠፋና ትገለብጥ ዘንድ፥ ትሠራና ትተክል” (1፥10) ዘንድ እንዲል፣ መንታ ገጽታ ያለው ነው። እግዚአብሔር በሕዝቡ መካከል ሊነቅል፣ ሊያፈርስ፣ ሊያጠፋና ሊገለብጥ ያለው ነገር አለ፤ እርሱም ኀጢአት ነው። ለዚህ ደግሞ ሕዝቡ ኀጢአትን በማድረግ እጅግ አመጸኛ ኾኖ ተገኝቶአል፤ እናም እግዚአብሔር፣ “ሕዝቤ ሁለቱን ክፉ ነገሮች አድርገዋልና” (ቊ. 13) በማለት በሕዝቡ ላይ ክርክሩን ወይም ቅሬታውን ያሰማል፤ (ቊ. 9)፤ እስራኤል፣ በዙሪያቸው ያሉትን አሕዛብ በመመልከት ከእግዚአብሔር ይልቅ ሌሎች አማልክትን ወድደዋል፤ ሕዝቡም ታማኝነታቸውን ከያህዌ ይልቅ ለቆጵሮስ(ኪቲም) እና ከቄዳር የባሕር ዳርቻ ማዶ ላሉ አማልክት ገልጠዋል። በሚያስደንቅ ኹኔታ እስራኤል፣ ኀጢአትዋ አማልክትን ከሚያመልኩ ከነዚህ ሕዝቦች እንኳ ይበልጣል።

በምን? ብለን ብንጠይቅ፣ አማልክትን የሚከተሉ ሕዝቦች አማልክቶቻቸውን ፈጽሞ አልተዉም፤ “ሐሰተኞች አማልክት ቢሆኑም እንኳ አማልክቱን የሚቀያይር ሕዝብ የለም፤” (ቊ. 11 አት) እንዲል። እስራኤል ግን ከነዚህ አሕዛብ እጅግ በሚከፋ ኹኔታ፣ “ክብር ያጐናጸፍኳቸውን እኔን አምላካቸውን ምንም ሊያደርጉላቸው በማይችሉ ከንቱ አማልክት ለውጠውኛል።” (ቊ. 11 አት) የሚል ጠንካራና ሕጋዊ ክስ ከያህዌ ቀርቦባታል። ይህ የይሁዳ ኀጢአት ደግሞ ያመጣው መቅሰፍት አለ፤ ሰማያት እንዲረገሙና እንዲንቀጠቀጡ አድርጎአል (ቊ. 12)።

አሕዛብ ምንም ላላደረጉላቸው አማልክት ታማኝ ነበሩ፤ እስራኤልን ያከበረው የክብር አምላክ እግዚአብሔር ግን በእስራኤል መካከል ተተወ፤ ተካደ፤ ተረሳ፤ ከእርሱ ፊታቸውን መለሱ። እንዲህ ያለ ዓመጽ በፍርድ መዘጋቱ አይቀሬ ነው። አስቀድሞ ግን እግዚአብሔር በተደጋጋሚ ኃጢአተኞችን ከመቅጣቱ በፊት፣ ወደ ንስሐ እንዲመጡ ይማጸናቸዋል። የእግዚአብሔር ልብ በይሁዳ እጅግ አዝኖአል፤ አሕዛብ አማልክቶቻቸውን አልለወጡም፤ ይሁዳ ግን “እኔን የሕያውን ውኃ ምንጭ ትተውኛል፥ የተቀደዱትንም ጕድጓዶች፥ ውኃውን ይይዙ ዘንድ የማይችሉትን ጕድጓዶች፥ ለራሳቸው ቆፍረዋል።” ብሎ እግዚአብሔር ልብን በሚነካ ሃዘን ይናገራቸዋል። የእግዚአብሔር ሕዝብ በደል እጥፍ ድርብ ነው፤ የሕያውን ውኃ ምንጭ መተዋቸው ሳያንስ፣ ውኃ መያዝ በማይችሉ ቀዳዳ የውኃ ማጠራቀሚያዎች እጅግ ታምነዋል።

በጥንቱ ዘመን የጉድጓድ ውኃ እጅግ ውድና አስፈላጊ ነገር ነበር፤ ለብዙ አገልግሎትም ይውላል። ነገር ግን እስራኤል የእግዚአብሔርን የሕይወት ውኃ ምንጭ ትተው፣ ውኃ የማይይዙ የተሰባበሩ፤ እጅግ ያነሰ አቅርቦት ያላቸውን የውኃ ጕድጓዶች ለማግኘት ደከሙ። ከቊ. 14 ጀምሮ እንደምናነበው ከዚህ የተነሣ፣ እስራኤል ሕጋዊ ልጅነቷን አጥታ ባሪያ ኾና በምርኮና በስደት ከገዛ ምድሯ ተነቀለች። ሰው እግዚአብሔር የሠራለትንና ያዘጋጀለትን የሕይወት ውኃ ምንጭ ትቶ፣ ለራሱ ጥም የሚያረካበትን ቢያዘጋጅ መቀጣቱና መተዉ አይቀርም።

እስራኤል የእግዚአብሔር ብቻ ነች፤ ልክ እንዲኹ በአዲስ ኪዳንም ያለነው አማኞች የክርስቶስ ብቻ ነን፤ በኵራትነታችን በክርስቶስ ለእግዚአብሔር አብ ነን፤ ጠጡ የተባልነውና ጥምን የሚቆርጠው የሕይወት ምንጭ ውኃ መንፈስ ቅዱስ ነው (ዮሐ. 7፥37-39)፤ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ” የሚለው ቃል፣ ዛሬም ሕያውና የሚሠራ ነው። ልክ እስራኤል ያህዌን ትታ፣ የአሕዛብን አማልክት በመከተል ያህዌን ብዙ እንደ በደለች፣ ዛሬም ሰዎች እግዚአብሔር በልጁ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሠራውን የቤዝወት፣ የማስታረቅ፣ የማዳን ሥራ ትተው፤ ከክርስቶስ ውጭ ሌላ ቤዛ፤ ከመሲሑ ውጭ እንግዳ መታረቂያ፤ ከኢየሱስ ውጭ ሌላ መድኃኒት፤ ከመንፈስ ቅዱስ ውጭ ሌላ የሕይወት ምንጭ ውኃ በመፈለግ ይንከራተታሉ። በክርስቶስ ዕረፉ፤ በርሱ ላይ ምንም አትደርቡ፤ ብቻውን በቂና ሙሉ፤ ብቃት ያለው አዳኝ ነውና!

ነገር ግን እንደ እስራኤል፣ እንዲህ ያለውን ኀጢአት ማድረግ በፍጻሜው ቅጣትና መተውን ማምጣቱ አይቀርም። እናም የምትባዝኑ፣ ከክርስቶስ ይልቅ ሌላ ቤዛና ተስፋ የምትፈልጉ፤ ከመንፈስ ቅዱስ ውጭም ሌላ እርካታና ጥጋብ የምትሹ አይረባችሁምና ወደ ነፍሳችሁ እረኛ በመመለስ ዕረፉ፤ እፎይ ዐረፍኩ በሉ!

“በማያቋርጥ ፍቅር ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ለሚወዱ ሁሉ ጸጋ ይሁንላቸው።” (ኤፌ. 6፥24)


My blog link - http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/29-13.html


"የምንበላው የማርያምን ሥጋ ነው" እያለ፣ በመሆኑ በማርያም የምንጋርደው ክርስቶስ የለም ከሚሉት በላይ አዚ-ማም ማን አለ?! ከባድ ጥ-ንቆላ ተደርጎባችኹ አታስተውሉምን?!


ጌታ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፤ የወንጌል እውነትን ከሰንበት ትምህርት ቤት ወደ ጳጳሳት ስላሳደግህ ተባረክ። [እነ አባ ማርቆስና ያሬድም እንደ አባ በርናባስ ወደ ፊት ቢመጡ ተመኘነ]!


ግንቦት ልደታና የሕይወት ትዝታዬ!
 (ከዛሬ አራት ዓመት በፊት የተጻፈ)

የዛሬ አሥራ ሰባት ዓመት ገደማ፣ ነፍሴ ከግንቦት አንድ አምላኪያን እጅ ያመለጠችበት ቀን ነው። በዚያን ቀን፣ በአርሲ ነጌሌ ሶጊዶ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓለ ንግሡ ላይ ላገለግል ተጠርቼ በዚያ ነበርኩ። “የተሸሸገ ጣዖት” በሚል ርዕስ፣ የያዕቆብ ሚስት ራሔል ጣዖትን መሸሸጓንና በዚህም የደረሰባትን በማንሳት አንስቼ አገለገልሁ፤ እኛም ይህን ማድረግ እንደሌለብን ብርቱ ማስጠንቀቂያ በማኖር ጭምር። ነገር ግን በዚያን ቀን ሳስተምር፣ ከታቦቱ ጎን ትምህርቴን ቆሞ ይሰማ የነበረ፣ የገጠር ከተማይቱ ጠንቋይ ደም በሰረበ ዓይኖቹ ይመለከተኝ ኖሯል።

ስብከቱን ጨርሼ ስወርድ ቀሳውስቱን፣ ጠንቋዩ ሰውዬ አንቈራጠጣቸው፤ ማን እንደ ኾነ ስጠይቅ ጠንቋይ እንደ ኾነ ነገሩኝ። ወዲያው ታቦታቱን የተሸከሙት ቀሳውስት፣ ለበአሉ ደም ወደ ፈሰሰበት ቦታ አቀኑ፤ ደሙን ተራመዱ፤ ከዚያም ኹሉ ነገር፣ በጠንቋዩ አጋፋሪነት ተከናወነ። የእኔ የጣዖትን ነገር ነቅፎ ማስተማር ጠንቋዩን አላስደሰተውም፤ እናም የምመለስበት ቀን ጠብቀው በመንገድ ላይ እኔን የሚያጠቁ ሰዎች ተዘጋጁ፤ ነገር ግን እጅግ ፈጣን ሯጭ ነበርኩና [“ሚሽነሪ” አገልጋዮች ለካ ስፖርት የሚሠሩትና ሩጫ የሚለማመዱት እንዲህ ባለ ቁርጥ ቀን በረው ለማምለጥም ጭምር ነው?]፣ በበረራ ነፍሴን ከእጃቸው በእግዚአብሔር ረድኤት አስመለጥኹ።

በዚያን ቀን እንዳገለግልና ጣዖትን በመቃወም እንዳስተምር አስበውበት የጋበዙኝ ወንድሞች ለማና አበራ ነበሩ፤ (ዛሬ የት ኾነው ይኾን?)።
በግንቦት አንድ ቀን በማርያም ስም ወደ ወንዝ ተወርዶ ለባዕድ አምልኮ ማረድ፣ የተቀቀለና የተቆላ እህል መድፋት፣ የበሰለ ቂጣ መወርወር፣ ቅቤ ዛፎችን መቀባት፣ አድባራት ሥር መሰብሰብ፣ መለማመንና አማልክትን መማጠን እጅግ የተለመደ ተግባር ነው። ድርጊቱ እጅግ የባዕድ አማልክት ልምምድ ያለበት ቢኾንም፣ አንዳንዶች የማርያምን ልደት የማርያም ወላጆች በሊባኖስ ዱር ውስጥ እንዳከበሩ፣ እኛም ከቤት ወጣ ብለን በዓሏን እናከብራለን ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ ከፍጹም የባዕድ አምልኮ ልምምድ ጋር በማያያዝ ሲያከብሩ ይስተዋላል። የማርያምን ልደት በሚያከብሩ በአንዳንዶች ዘንድ ታቦታት ባዕድ አምልኮ ወደሚፈጸምባቸው ወንዞች የሚወርዱበት ጊዜም እጅግ ብዙ ነው።

ምንም እንኳ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን “ክርስቶስን ብቻ ነው የማመልከው” ብትልም፣ እንዲህ ያሉ ግልጥ ባዕድ አምልኮአዊ ልምምዶችን በአደባባይ ስታወግዝና ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ መኾናቸውን ስትኮንን አይስተዋልም። ግንቦት አንድ ቀን፣ የሚከናወነው ኹሉም ተግባራት ከባዕድ አምልኮ ጋር ፍጹም ቁርኝት ያለው ነው። ይህን ሃይማኖታዊ ሽፋን መስጠት፣ ባዕድ አምልኮን በግልጥ የመደገፍ ያህል እንጂ ፈጽሞ እውነት ነው ሊያስብለው አይችልም። ባዕድ አምልኮ በእግዚአብሔር ፊት ጽዩፍና እጅግ አስነዋሪ ተግባር ነውና። እንዲህ ዓይነት ልምምድ ያላቸውን እግዚአብሔር እጅግ ይጠየፋል። ከእርሱ ውጭ ሊታመን፣ ሊለመን፣ ሊማጠን የሚገባ መለኮታዊ ኀይል በላይ በሰማይ፤ በታች በምድር ፈጽሞ የለምና።

እንዲሁም፣ የክርስቶስን መስቀል የሚጋርድ የትኛውም ትምህርት፣ ልምምድ፣ ማኅበራዊ እሴት እርሱ የክርስቶስ መስቀል ጠላት (ፊልጵ. 3፥18)፣ እንግዳ ትምህርት (2ቆሮ. 10-13)፣ አዲስ ወይም ልዩ ወንጌል (ገላ. 1፥8)፣ በጌታ ትምህርት ደግሞ እንክርዳድ (ማቴ. 13፥25) ተብሎ ተጠርቶአል። “በግንቦት አንድ፣ እኛ ማርያምን እናከብርበታለን እንጂ ጣዖት አናመልክም” የሚል ማመካኛ ወይም ማሳበቢያ ፈጽሞ አያስፈልግም። ምክንያቱም በዕለቱ የሚከናወነው ተግባር ኹሉ መስቀሉን፣ ሞቱን፣ ትንሣኤውን የሚናኝና የሚመሰክር አንዳች ነገር የለውምና።

ጌታ በመስቀል ላይ የሠራው የመስቀሉ ሥራ ሕይወታችን ነው፤ የክርስቶስ ትንሣኤ የደመቅንበት ሞገሳዊ ጌጣችን ነው፤ ከእርሱ ትምህርትና ሕይወት ውጭ ሌላ ትምህርት፣ ሌላ ልምምድ የለንም፤ ከክርስቶስ በቀር የምንሰብከው ሌላ ርዕስና አጀንዳም ፈጽሞ የለንም። እና በአጭር ቃል ግንቦት አንድ ማርያምን የማክበር ተብሎ ሽፋን ቢሰጠውም፤ ባይሰጠውም፣ ፍጻሜው  ከክርስቶስ ወንጌል ውጭ የኾነ ትምህርትና ልምምድ መኾኑን መዘንጋት አይገባም፤ በምትወዱትና በምታከብሩት ነገር በኩል የሚመጣ፣ የትኛውንም ባዕድ ንግግርና ትምህርት ከመከተል ራሳችሁን ጠብቁ።

 ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ባለመጥፋት ከሚወዱ ሁሉ ጋር ጸጋ ይሁን፤ አሜን። (ኤፌ. 6፥24)

565 0 4 10 29

አይ ሄኖክ፤ አንተ የምታስተምረው ምን ኾነና ሌላውን ተሳ-ሳተ ለማለት በቃህ?! ነገ አንተ ከዚህ የባሰ ብታስተምር እንጂ የተሻለ አታስተምርም። ግና አባ ገብርኤል ላይ በአድማ ዘምታችኹ ለማካካሻ እንጂ "ዲያቆን" ጳጳስን የሚናገርበት ሥርዓታዊ መንገድ በቤቱ እንደ ሌለ ይታወቃል። ከዚኹ ንግግርህ ጀምሮ፣ ወደ ወንጌል መመለስ እንዲኾንልህ እመኛለሁ።

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


አባ በርናባስና “ጳጳስ” ሕዝቅኤል - ተቃራኒ ጳጳሳት!


አቡነ በርናባስ አስደናቂ የወንጌልን መልእክትን ያለ ፍርሃት የሚያቀርቡ፤ ያልገባቸውንና ተንኰል አዘል በኾነ መንገድ የተቀየረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ደግሞ፣ በቀናነትና በቀጥተኛነት የሚጠይቁ የሚሞግቱ ናቸው። በቃለ መጠይቃቸው ላይ እንደሚስተዋለው፣ አቡኑ ጠንቃቃና ሙግታቸውን በምን መንገድ እንደሚያቀርቡ በትክክል የሚያስተዋሉ፣ ሲያስረዱም መስመር የማይስቱ፣ የተረጋጉ፣ በትህትና የተመሉ፣ ያመኑበትን የትኛውንም ትምህርት በድፍረት ለመናገር የማያፍሩም፤ የማይፈሩም አባት ናቸው።





ከዚህ ቀደም እንደ ተናገርኹት፣ በዕድሜዬ፣ ስለ ክርስቶስ ምልጃና አስታራቂነት እንደ እርሳቸው ደፍሮ በአደባባይ የመጽሐፍ ቅዱስን ዕውነት መሠረት ባደረገ መንገድ የተናገረ ጳጳስ አላስታውስም። ክርስቶሳዊ ትምህርታቸው ርቱዕ ኦርቶዶክሳዊና እንከን የማይገኝበት ነው። መጽሐፍ ቅዱሳዊውን ክርስትናና ክርስቶስን ሲናገሩ በትክክልና ለእውነት ወግነው ነው።

ስለ ክርስቶስ ሊቀ ካህናትነት ሲናገሩ፣

“ … ወደ አባቱ ሲጸልይ እምቢ የማይባል ጸሎት ነው፣ ለምን? አንደኛ ያለ ኃጢአት የተገለጠ ካህን ነው፣ ንጹሕ ነው፤ ኹለተኛ ደግሞ በአምላክነቱ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ጩኸት ሰሚ ነው፣ አየህ ራሱ ለማኝ ነው፣ ራሱ ደግሞ ተለማኝ ነው። ራሱ ሰሚ ነው፣ ራሱ ፈራጅ ነው፣ ስለዚህ አኹን እርሱ አባቱን ሲለምን በሰውነቱ ነው ማለቴ ነው፣ በሰውነቱ ስል ሥግው ቃል ነው፣ በሰውነቱ የሚናገረው ራሱ ቃል ነው፣ ወልድ ነው። ተግባብተናል? መለኮት ነው፣ ፈጣሪ ነው፣ ፈጣሪ ግን ወደ ፈጣሪ መለመን አይችልም አይደል? አምላክ ወደ አምላክ መለመን አይችልም።

ግን መለመን እንዲችል ያደረገው ሰውም ስለኾነ ነው። በሰውነቱ ነው፣ በተዋሐደው አካል ነው የሚለምነው። እና ምንድነው ያለው? እነዚህ የምታያቸው የአንተ ደቀ መዛሙርት፣ የእኔ ደቀ መዛሙርት፣ ስለ እነርሱ እለምንሃለሁ፣ ቅዱስ አባት ሆይ! በስምህ ቀድሳቸው፣ “ኦ አባ እቀቦሙ በስምከ ወበኃይልከ፣ ከመ ይኩኑ አሐደ ብነ ከማነ”፣ “እኔና አንተ አንድ እንደ ኾንን አንድ እንዲኾኑ በስምህ ቀድሳቸው፣ አንድ አድርጋቸው” ይላል። እምቢ የማይባል ነው አኹን፣ ስለ እነርሱ ብቻ አይደለም የምልህ አለ፣ በልባቸው አምነው በቃላቸው ስለ መሰከሩ እስከ ዐለም ፍጻሜ ስለሚኖሩት፣ ለምን? በስሜ አምነው የሚጠመቁ ሁሉ እንደነዚህ ናቸው ብሎ፣ እስከ ዕለተ ምጽዓት ማለት ነው፣ …”

ይህ የአባ በርናባስ ትምህርት እጅግ አስደናቂ፣ የፍጡራን ምልጃና አስታራቂነት ገንኖ ላለበት ቤት አዲስና ያልተለመደ አስደናቂ ትምህርት ነው። አዎን፤ ክርስቶስ እስከ ዕለተ ምጽዓት ለሚታመኑበት ኹሉ አስታራቂና ሊቀ ካህናታቸው ነው!

እጅግ በሚያሳዝን መንገድ፣ “ጳጳስ” ሕዝቅኤል የተባሉ አባት ደግሞ ሌላ የኑ-ፋ-ቄ ትምህርት በአደባባይ[በአዲስ አበባ ምስካየ ኅዙናን መድኃኒ ዓለም ቤተ ክርስቲያን] ያስተምራሉ፤ ሳያፍሩ በድፍረት ተመልተው እንዲህ ይላሉ፣

“ … በቀራንዮ የፈሰሰው ደም የማን ነው? እንዴ! ሥጋን የለበሰ ከእሷ ነው፣ የእሷ ደም ፈሷል፣ የእሷን ሥጋ አይደለ እንዴ የተዋሐደው? እምንበላው የምንጠጣው ሥጋ የማን ነው? የእሷ ነው። … ”

ሰው ምንም ያህል ማርያምን ቢያፈቅርና ቢያመልክ በዚህ ልክ ሊሳሳት ይችላል ብዬ አላስብም። ስህተቱ ደግሞ በጳጳስ ደረጃ ሲኾን እጅግ ግር ያሰኛል። የራሱ የክርስቶስን ሥጋ የማርያም ነው ብሎ መሞገት ምን የሚሉት እንግዳ ትምህርት ነው? የኢየሱስን ሥጋ ለሌላ መስጠትና ባለቤቱን ለሌላ አሳልፎ መስጠት እጅግ አሳዛኝ ስ-ህ-ተ-ት ነው። ይህ የማያውቁ ጳጳሳት በመንበረ ጵጵስና መቀመጣቸው በራሱ ያሳፍራል። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ፈሰሰው ደምና ስለተሠዋው ሥጋ ሲናገር፣

“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ… ” (ሐ.ሥ. 20፥28)

“…እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው …” (ሮሜ 3፥25)

“እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።” (ሮሜ 5፥9)

“የዘላለምን ቤዛነት አግኝቶ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ እንጂ በፍየሎችና በጥጆች ደም አይደለም።” (ዕብ. 9፥12)

“ … ኢየሱስ ደግሞ በገዛ ደሙ ሕዝቡን እንዲቀድስ ከበር ውጭ መከራን ተቀበለ።” (ዕብ. 13፥12)

“ … ለወደደን ከኃጢአታችንም በደሙ ላጠበን፥…” (ራእ. 1፥5)

“… በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ።” (ቈላ. 1፥21-22)

“ …በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥ …” (ዕብ. 10፥19-20)

“እርሱ[ክርስቶስ] ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ” (1ጴጥ. 2፥24)

እንግዲህ ክርስቶስ ያዳነንና የዋጀን በገዛ ደሙ፤ በራሱ ሥጋው ብቻ ነው፤ ከእኛ የነሣው ሥጋ የራሱ ገንዘቡ እንጂ የማርያም ነው አንልም፤ ቅዱሳት መጻሕፍት ይህን በግልጥ ይመሰክራሉ። ርሱ ፍጹም ሰው፤ ደግሞም ፍጹም አምላክ ነውና። ኦርቶዶክሳዊት ኹለት ተቃራኒ ጳጳሳትን በአንድ መንበረ ጵጵስና የማታስተናግድበት ዘመን መምጣቱ ወይም እውነተኞቹ ጳጳሳት በመ-ና-ፍ-ቃ-ን ጳጳሳት መባረራቸው አይቀሬ ይመስላል!

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን።” (ኤፌ. 6:24) አሜን።


My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/blog-post_8.html


"[ኢየሱስ] በቀራንዮ ያፈሰሰው ደም የማርያም ነው" [ሎቱ ስብሐት]


"ማርያም ለኀጢአታችን ቤዛዊተ ዓለም አትባልም" ለሚለው ለአባ ገብርኤል ትምህርት ካራ ኦርቶዶክሳውያን እየሰጡ ያሉት ምላሽ፣ አስተማሪና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሳይኾን ፍጹም ከመጽሐፍ ቅዱስና ከጳጳሱ ትምህርት በተቃራኒ የኾነ ምላሽ መስጠትን ተያይዘዋል። በምስሉ ከምትመለከቷቸው አንደኛው አባት "የርሷን ሥጋ ነውና የተዋሐደው የፈሰሰውም የርሷ ደም ነው" ይላል፤ ሌላኛው ደግሞ፣ "በመስቀል ላይ የዋለው ሥጋ የማርያም ሥጋ ነው" ይላል። በርግጥ በዚያ ቤት "ማርያም አራተኛ ሥላሴ ናት" የምንለው በምክንያት ነው።




በአንድ ወቅት አንድ ሰባኪ እንዲህ እያለ "ሰብኮ" ከመድረክ ወረደና ከአንድ አባት ጎን ሄዶ ተቀመጠ። እኒያም አባት "ሰባኪውን" በቁንጥጫ መዠለጉት። ከዚያም "ሰባኪው" ቁንጥጫው አመመውና ጮኾ፣ "ምነው?" አለ፤ እኒያም አባት "የቆነጠጥኹት ሥጋህ የእናትህ መስሎኝ ነው" አሉት። የማርያምንና የኢየሱስን ሥጋ አንድ የማድረግ ትምህርት የ-ኑፋ-ቄ መዘዙ ብዙ ብቻ መኾኑ አይደለም። ጌታችን ኢየሱስ መከራ መቀበሉንና መሰቀሉን ኹሉ ከንቱ የሚያደርግ ትምህርት ነው።

ኢየሱስ ከማርያም ሥጋ ነሣ ማለት፣ በኢየሱስ ኹለንተና የተከናወነው ኹሉ፣ በማርያም ኹለንተና ተከናውኖአል ማለት አይደለም። መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስን በማንነቱ እንከን አልባና ወደር የለሽ፤ በሰማይም በምድርም በሰውነቱ አንዳች ነቀፋ የሌለበት አድርጎ ነው የሚያቀርበው። በግልጥም፣ ስለ ኢየሱስ ማንነት መጽሐፍ ቅዱስ ሲመሰክር፣ "ተንኰል የሌለበት" (ዮሐ. 1፥48)፣ "ቅዱስና ያለ ተንኮል ነውርም የሌለበት" (ዕብ. 7፥26)፣ "ኀጢአት ያላወቀው" (1ቆሮ. 5፥21)፣ "ኃጢአት ያላደረገ፥ ተንኰልም በአፉ ያልተገኘበት" (1ጴጥ. 2፥22)፣ "ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ" (ዕብ. 4፥15) ... ደግሞም ስለ ራሱ ሲመሰክር፣ "ከእናንተ ስለ ኃጢአት የሚወቅሰኝ ማን ነው?" (ዮሐ. 8፥46) "አንድ በደል ስንኳ ያልተገኘበት" (ሉቃ. 23፥4፡14፡22) ብሎ ፍጹም መስክሮአል። ሥጋን ለብሶ በዚህ ልክ ከኢየሱስ በቀር በሰማይም ኾነ በምድር ምስክርነትን የተቀበለ፤ ሊቀበል የተገባውም የለም፤ አይኖርምም።

በደልና ነውር፤ ነቀፋና ኀጢአት ያልተገኘበት መሲህ እንዳዳነን ስናምን፣ ከማርያም ሥጋን ከመንሣት ወጪ ከርስዋ የተቀበለውም፤ የሚቀበለውም አንዳች ነገር የለም። መጽሐፍ፣ "ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም የተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ" (1ቆሮ. 1፥30-31) ነው ይላልና። እናም ክርስቶስ በፍጹም ሰውነቱ ተቤዥቶ ነጻ አወጣን፤ መሥዋዕት ኾኖ ዕዳችንን ከፈለ፤ ንጹሕ ነውና ኀጢአትና ሞት ሊያገኘውም ሊይይዘውም አልቻለም ብለን እንመሰክራለን። ምስክርነታችንም እውነት ነው!

ማርያምን ለሚያመልኩና ከክርስቶስ ጋር ለሚያስተካክሉ መንፈስ ቅዱስ ልባቸውን ወደ ልጁ እንዲመልሱ በጽድቅ ይውቀሳቸው፤ አሜን።


My blog link - http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/blog-post_7.html


ክርስቶስ ያስታርቃል ወይስ ይፈርዳል?!

በአንድ ወቅት አንድን አባት ለመፈተንና ለማስወገዝ፣ ኹለት ወንድሞች ተመካክረው ጠየቁአቸው። “አባታችን ክርስቶስ ያስታርቃል ወይስ ይፈርዳል?” ብለው፣ እኒህም አባት ራሳቸውን ጠያቂዎቹን ልጆች ጠየቁአቸው፤ አንዱ ያስታርቃል አለ ሌላኛው ደግሞ ይፈርዳል። የኹለቱንም ዐሳብ በሚገባ ካደመጡ በኋላ፦

"ላንተ ያስታርቅ፤ ላንተ ይፍረድ።" አሉ።

በአጭሩ፤ አዎን ክርስቶስ ኢየሱስ ጻድቅ ፈራጅ፤ ቅን አስታራቂም ነው!


አባ በርናባስና የ“ክርስቶስ ያማልዳል” አቋማቸው!

“… በየትኛውም ቋንቋ የተጻፈ መጽሐፍ ቅዱስ አከራካሪ ነገር ከተነሳበት፣ አስታራቂው በግሪክ የተጻፈው መጽሐፍ ቅዱስ ነው። አዲስ ኪዳን በመጀመሪያ የተጻፈው በግሪክ ስለ ኾነ። ግሪኩ “በአብ ቀኝ ያለው ስለ እኛ የሚማልደው” ካለ፣ “የሚማልደው” ማለት ምን ማለት ነው? የሚለውን ማብራራት፤ መተርጐም ነው እንጂ ቃሉን ቀይሮ “ይፈርዳል” ማለት ምን ማለት ነው? … ለምን ተቀየረ? ብሎ መጠየቅ ደግሞ መብቴ ነው … ቃል ቀይሮ መሸሹስ የት ያደርሳል? … ይህ ቢቀየር እኮ ዕብራውያን፣ ቅዳሴ፣ ሃይማኖተ አበው ስንት ቦታ አለ? … ከመሸሽ መተርጐም ይሻላል … ስንቱንስ ቀይረህ ትችለዋለህ? … ”

“ … የብሉይ ኪዳን ካህናት የበግ ደም ይዘው ነው የሚቀርቡት፤ ጌታ ግን ራሱ መሥዋዕት ኾኖ ነው የቀረበው። … ኹል ጊዜ ኢየሱስን ስናይ ሰውም አምላክም መኾኑን መዘንጋት የለብንም።  … በሰውነቱ ሊቀ ካህናት ኾኖ ይጸልያል፤ ወደ አባቱ። ወደ አባቱ ሲጸልይ እንቢ የማይባል ጸሎት ነው የሚጸልየው፤ ምክንያቱም ያለ ኀጢአት የተገለጠ ሊቀ ካህናት ነውና፣ ደግሞም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በአምላክነቱ ጩኸት ሰሚ ነውና። … እናም በሰውነቱ ይለምናል … መለመን እንዲችል ያደረገው ሰውነቱ ነው። … ”

“… እግዚአብሔር ሰውን ሲፈጥር አንድ ጊዜ “ብዙ ተባዙ” በማለቱ በኃያል ቃሉ እስከዛሬ ድረስ ይፈጥራል፤ የክርስቶስም የማስታረቅ ሥራ እንዲኹ ነው።..” (አባ በርናባስ)

ምናልባት “የእግረኛው ሚዲያ - ተይዞ የነበረው ቪዲዮ ተለቀቀ” ሲል፣ ሲኖዶስ የአባ በርናባስን ጉዳይ ከአባ ገብርኤልና ፊልጶስ ጋር እንዲታይ ውሳኔ በሰጠበት ጊዜ መኾኑ፣ “የአባ በርናባስን ጉዳይ በዚህ ንግግራቸው ለማጋጋልና ለውግዘት ተጣድፈው እንዲቀርቡ ለማድረግ” ዐስቦ ሊኾን ይችላል። በመግቢያውም ላይ “ይህ ቪዲዮ እንዳይወጣ ብለውኝ ነበር” ብሎ የማቅረቡ ምክንያቱም ይኸው ይመስለኛል።  ይህ ስውር ዐሳቡ ግን ያን ያህል ሚዛን የሚያነሳለት አይመስለኝም። ምክንያቱም ጳጳሱ ከአቋማቸው ፍንክች አላሉምና።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ከተነሱ አባቶች መካከል፣ ስለ ክርስቶስ አስታራቂነት በዚህ ልክ ደፍሮ የተናገረ አባት ወይም ጳጳስ ስለ መኖሩ እርግጠኛ አይደለሁም። በተለይም ደግሞ “የክርስቶስን አስታራቂነት ለመቀበል” እጅግ አዳጋች በኾነባትና የሚያስወግዝ በኾነባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዲህ መናገር ከመንፈስ ቅዱስ በቀር ማንም ሊያስጨክን አይችልም።

አቡነ በርናባስ ያተኰሩባቸው ነጥቦች፦
-  ደሙ ዛሬም ትኩስ ነው፣
-  ክርስቶስ ዛሬም በሊቀ ካህናትነቱ ያስታርቃል፣
-  አንዴ በመስቀል ላይ የሠራው ሥራው ሕያውና ዛሬም ድረስ የማያቋርጥ ነው፣ ይህን ሲያስረግጡም፣ “አስታርቆአል፤ እያስታረቀ ነው፤ ሲያስታርቅ ይኖራል ማለት ምኑ ነው ነውሩ?” ይላሉ።

አዎን፤ መጽሐፍ ቅዱስ፣ አንድ ጊዜ ለዘለዓለም የሚያገለግል የሚሻል መሥዋዕት ክርስቶስ ስለ ማቅረቡ ይመሰክራል (ዕብ. 9፥23)፤ ስለዚህ ምዕመናንና ምዕመናት የሚሻል ተስፋ አላቸው (ዕብ. 7፥18-19)፤ አሁንም ለዘለዓለም የሚኖር ሊቀ ካህናታችን በእግዚአብሔር ቀኝ በክብርና በባለ ሥልጣንነት ተቀምጦ ለሕዝቡ ይገኛልና በርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል፤ (ዕብ. 2፥18፤ 4፥14-16፤ 7፥24-25)።

ሰው የኾነበትም ዋነኛ ዓላማውም ይኸው እንደ ኾነ አበክሮ ይናገራል፡፡ አሮናውያን ሊቃነ ካህናት ዋና ሥራቸው የነበረው ስለ ኀጢአት መሥዋዕትን ማቅረብ ነበር (ዕብ. 5፥1፤ 10፥11)፡፡ ይህን ለማድረግም ደምን ያፈስሱ ነበር (ዕብ. 9፥7)፤ ነገር ግን አገልግሎታቸው በሞት የተገታና ኀጢአትን ለጊዜያዊነት እንጂ ጨርሶ ማስወገድ ያልቻለ ነበር፡፡ ክርስቶስ ግን ጳጳሱ እንደ ተናገሩት የራሱን ደም አቀረበ (ዕብ. 7፥26፤ 9፥12፤ 10፥2)፤ በዚህ አገልግሎቱም የብሉይ ኪዳን ካህናትን አገልግሎት ኹሉ አስቀረ ወይም ሻረ (ዕብ. 7፥18-19)። ከዚህም የተነሣ ጌታችን ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ የሚገኝ በመኾኑ ሕዝቡን እየረዳ እስከ መጨረሻ ሊያድናቸው ይችላል (2፥18፤ 4፥16፤ 5፥9-10፤ 7፥24-25)።

የአባ በርናባስ የምስክርነት ድፍረት በሌሎችም ጳጳሳት እንዲጋባ እንናፍቃለን። ይህን በምትሰሙና በምታነብቡ ኹሉ ላይ ጸጋና ሠላም በክርስቶስ ኢየሱስ ይብዛላችኹ፤ አሜን።

Blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/blog-post_5.html?m=1


በማኅበረ ቅዱሳን ቴቪ የቀረበውን ስለ ገድላትና ድርሳናት የተደረገውን ውይይት አየኹና፣ እኒህን ዐሳቦች ከመላሹ ከ"መምህር" በጽሐ ዓለሙ አወጣኹ።

" ... ገድላትና ድርሳናት የሃይማኖት መከራከሪያ ሊኾኑ አይችሉም የሚለው ስህተት ነው።

ገድላት ያልነበሩበት ዘመን ሊጻፍ ይችላል።  ይህን በጥናትና በምርምር ማስተካከል ይገባል።

ገድላት በብዙ ገዳማትና አድባራት ይታተማሉ፤ አርትዖት ስለማይደረግባቸው ልዩነት አላቸው። ስለዚህ ታይተው ሊስተካከሉ ይገባል።

በገድላት ያሉትን ቅዱሳን ማንም ሊተቻቸው አይችልም። እግዚአብሔር በውስጣቸው አለና።

በቴሌግራም፣ በፌስቡክ፣ በቲክቶክ የሚያገለግሉት ቤተክርስቲያንን ለሽያጭ ባያቀርቧት ጥሩ ነው።

አዋልድ የተባሉ ገድላትን አፍን ከፍቶ ልብን አስፍቶ መቀበል ይገባል። ችግር ካለ መጠየቅ ይሻላል።

..."

ትዝብቴ

አቅራቢው ገድልን እንደ መጽሐፍ ቅዱስ እንድንቀበል ግፊቱ ጠንካራ ነው። መላሹ ደግሞ በተቻለ መንገድ "ነባሩን ትምህርት" ለማጽናት ይተጋሉ። ገድል ከመጽሐፍ ቅዱስና ከሊቃውንት በታች ሊጠቀስ ይገባል በሚል አቋም። መላሹ በተጨማሪ ገድላት በእንከኖች መታጨቃቸውን "በለስላሳ ቃላትም" ቢኾን ከመናገር አልተቆጠቡም። ቲክቶዶክሶቹ "ገድላትና ተአምራት፤ ድርሳናት ለሃይማኖት መከራከሪያ አይጠቅሙም" ያሉትን ኹለቱም በግልጥ ነቅፈዋል። የማኅበረ ቅዱሳን ትልቁ ግብም ይኸው ነው።

መልእክቴ!

ለእውነት ጥብቅና ለመቆም ያለን ፍላጎት፣ ፍቅር የለሽና ታጋሽ፣ እንዲኹም መጽሐፍ ቅዱስን ገፊ እንድንኾን ካደረገን ሰይጣን ትልቅ ድል አስመዝግቧል። እናም ገድላትን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የማስተካከልና ትክክል ናቸው የሚለው አቋም፣ ኦርቶዶክስን ከባድ ዋጋ ያስከፍል እንደኾን እንጂ ከቶውን አይጠቅማትም።

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


ገድላት በስህተት ትምህርትና ልምምድ የታጨቁ መኾናቸውን በሚያሳብቅ መንገድ፣ ማኅበረ ቅዱሳን ይህን ርዕስ ሲጠቀም ለመጀመሪያ ጊዜ ይመስለኛል። እንጂማ በሐመር መጽሔቱ፣ በሐመረ ተዋሕዶ መጽሐፉና በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣው በተደጋጋሚ ለገድላት "ዋስና ጠበቃ" ኾኖ ኖሮአል። ብቻ ግን በገድላት ስህተት መኖሩን ማመኑ በራሱ "ለተሐድሶ አንድ ትልቅ እርምጃ" ነው።

ግን ማን አስገባ ሊሉ እንደሚችሉ ግምታችኹን አስቀምጡ!
የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


ኢየሱስን የቀመሰው ብቻ ይሰብከዋል!


መጽሐፍ ቅዱስ ቃል በቃል ስለ ስብከት ሲናገር፣ “እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤” (1ቆሮ. 1፥23) ይላል። ይህ ክርስቶስን የቀመሱትና አምነው በነፍስ ተወራርደው የሚከተሉት ኹሉ፣ በቃልም በሕይወታቸውም የሚመሰክሩት ነው። ለዚህም ነው፣ “ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን” የሚለው ቃል የመዳን መሠረት ኾኖ የተቀመጠው፤ (ሮሜ 10፥9)።


ስብከት ግልጥ ምስክርነት ነው፤ “አድኖኛልና እናንተም ዳኑ” የሚል ጥልቅ መልእክትን በውስጡ የያዘ ነው፤ የሰማርያ ሰዎች በኢየሱስ ያመኑትና ከእነርሱ ጋር እንዲኖር የለመኑት ሳምራዊቷ ሴት፣ “ያደረግሁትን ሁሉ ነገረኝ ብላ ስለ መሰከረችው ቃል” ነው፤ (ዮሐ. 4፥39) እንዲሁም ትሁቱ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ፣ በክርስቶስ አምኖ የተጠመቀውና የዳነው፣ “ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት” ከተባለ በኋላ ነው፤ (ሐ.ሥ. 8፥35)።

ስብከትና ሕይወት፤ ሕይወትና ስብከት ሊነጣጠሉ አይችሉም። ሰባኪውም ተሰባኪውን ሕይወታቸው ከኢየሱስና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ካልተነካካ በቀር፣ ስብከት ነፋስን የመጎሰም ያህል ከንቱ ነው። በሌላ ንግግር የሚሰብከው ሰው፣ ከቃሎቹ ይልቅ በሕይወቱ ሊሰብክ ይገባዋል፤ ጌታችን ኢየሱስ “እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤” (ዮሐ. 8፥31) በሌላ ስፍራም፣ “እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ።” (ዮሐ. 13፥35) እንዲሁም፣ “ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል።” (ዮሐ. 15፥8) ሲል፣ ትምህርቶች ውስጥ ፍሬና ሕይወት ተያያዥ፤ አልፎም ለሌሎች ብርቱ መልእክት ያለው መኾኑን ያሳያል።

ጌታችን ኢየሱስ ስለ ጨውና ብርሃንም ባስተማረበት ክፍሉ፣ “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ።” (ማቴ. 5፥16)፣ “በነፍሳችሁ ጨው ይኑርባችሁ፥ እርስ በርሳችሁም ተስማሙ።” (ማር. 9፥50) ብሎ ሲናገርም፣ ሰዎች ከስብከታችን በላይ ሕይወታችንን ጭምር እንደሚመለከቱና የሕይወታችን ጤናማነት የስብከታችንን ኃይልና ጥራት ከፍ እንደሚያደርገው ተናግሮአል።

ስለዚህ ክርስቲያን ከዳነ መዳኑን፣ ከተማረ ምሕረቱን፤ ይቅር ከተባለ ይቅርታውን ሊያወራ ተጠርቶአል፤ የዳንንበትን እውነት በውክልና እንድናወራ አልተጠራንም፤ በምሳሌም እንድንመሰክር አልተባለም፤ ምክንያቱም በምሳሌና በጥላ የሚነገርበት የብሉይ ኪዳን ዘመን አልፎአልና፤ አኹን አዲስ ዘመን፤ አዲስ ኪዳን ነው፤ ኢየሱስ በከበሮና በጸናጽል፤ በመቋሚያና በበገና ክሮች ምሳሌነት አይሰበክም፤ በምንናገረውና በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በሚሠራው በቅዱስ ቃሉና በቃሉ ብቻ እንደሚሠራ እናምናለን።

የተሰቀለውን ክርስቶስ ኢየሱስን በትክክል የምትወዱትና የምትከተሉት ከኾነ፣ “ሐዋርያትም የጌታን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በታላቅ ኃይል ይመሰክሩ ነበር፤” (ሐ.ሥ. 4፥33) ተብሎ እንደ ተጻፈው፣ ልክ እንደ ሐዋርያት አበው በአንደበታችሁ መስክሩለት፤ “ከኢየሱስም ጋር እንደ ነበሩ አወቁአቸው፤” (ሐ.ሥ. 4፥13) ተብሎ እንደ ተጻፈውም በሕይወታችሁ አውጁት፤ በከበሮና በጸናጽል ምሳሌነት፤ በጉልላትና በነጠላ ጥለት በማለት አትሸፍኑት!

ቃሉ ከከበሮ፤ መንፈሱም ከጸናጽል ይበልጣልና! ኢየሱስን በሚበልጠው ቅመሱትና ወድዳችሁ ስበኩት!

መጽሐፍ እንደሚል፣ “እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቅመሱ እዩም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው።” (መዝ. 34፥8)

“ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን።” (ኤፌ. 6፥24) አሜን።

My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/blog-post_42.html


ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት እየረገጡ፤ የተሰቀለውን ክርስቶስን የሚጋርዱ የማይወገዙ ግን ስለ ክርስቶስ ጥቂት ሲናገሩ የሚረገሙበት ቤት “ኦርቶዶክስ! መኾኑ እጅግ ያሳዝናል፤ ነገር ግን ጌታ ስለ ቃሉ ታማኝ ነውና ለኦርቶዶክሳውያን የወንጌል ብርሃን እንደሚበራ አምናለሁ!

“ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን።” (ኤፌ. 6፥24) አሜን።

My telegram link - https://t.me/ebenezertek
My blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/blog-post_2.html
My youtube link - https://www.youtube.com/shorts/IwYHr-9KgpQ


ማርያምን ከጌታ የሚያስበልጡማ በኦርቶዶክስ ቤት አይነኩም!


ማስረጃው ይኸው!

በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ውስጥ፣ ስለ ማርያም የሚሰሙ “ስብከቶች” ማርያም ያለ እግዚአብሔር ሳይኾን፣ እግዚአብሔር ያለ ማርያም ሕይወት አልባ የሚያስብል ብካይና የተመረዘ ትምህርት አለ። ነገረ ማርያም በነገርነቱ ሳይኾን፣ “እንደ ተሰቀለው ክርስቶስ” በደረጀ ስብከቱና እምነቱ አለ!

ሊቀ ጳጳስ ገብርኤል “ማርያም ቤዛ አይለችም” ብለው ሲናገሩ፣ ከኢየሱስ የመስቀል ሥራ ጋር አነጻጽረው መናገራቸው በአደባባይ እየታወቀ፣ የኦርቶዶክስ ካራ ጀማ በአንድነት ተሰባስቦ፣ “ቤዛ ዐውድ አለው፣ እንኳን ማርያም ወ/ሮ ቤዛና ነቢይ ሙሴም ቤዛ ተብለዋል” ... የሚል ኢየሱስንና የመስቀሉን ሥራ በግልጥ የሚነቅፍ ምላሽ ሲሰጡ አየን። ከዚህ የሚከፋው ደግሞ፣ ማርያምን ያከበሩ ለማስመሰልና እውነተኞች ለመምሰል፣ ከእግዚአብሔር በላይ አድርገዋት ሲያቀርቡ ነው።

ይህ “ሰባኪ” የሚናገረውን ከዚህ በታች ልጥቀስ።

“… እርሷ[ማርያም] የኹሉም ነገር ጥንስስ ናት፤ ሰማይና ምድር እየተባሉ የሚጠሩት ነገሮች በሙሉ መነሻቸው ለፍጥረት ይኾናል እንጂ ፍጻሜያቸው ለእመቤታችን ነው። ኸረ እንደውም ይህ ነገር አይድነቃችሁ፣ እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረትን ያዘጋጀው፣ ለእመቤታችን ነው ብዬ ብነግራችሁስ! ኹሉም ነገር የተፈጠረውና የተገኘው ስለ እርስዋ ሲባል ነው። በጣም የሚደንቃችሁ እነዚህ ፍጥረታት ሁሉ ከመኖራቸው በፊት፣ … እግዚአብሔር የራሱ ዓለም ነበረው። ያ ዐለሙ በኅሊናው ታስባ የነበረችው እመቤታችን ናት። ለእግዚአብሔር ኅሊና መታሰቡ እንደ እናቱ ብቻ እንዳይመስላችሁ፤ እመቤታችን ለእግዚአብሔር ዓለሙም ጭምር ናት …”

በዚህ ልጅ ንግግር ውስጥ አእላፋት ኑ-ፋቄ--ዎች አሉ። ኹለቱ ላይ ብቻ ላተኲር፣

1. እውን ፍጥረት የተፈጠረው ለእመቤታችን ሲባል ነው? የፍጥረት ፍጻሜስ ማርያም ናት? … እኒህ ጥያቄዎች ቀላል ግን ሙሉውን የነገረ መለኮት ትምህርት ሊቀይሩ የሚችሉ ናቸው፤ ምክንያቱም ፍጥረት ለፍጥረት እንደ ተፈጠረ ጨርሶ አይነግረንምና፤ የፍጥረት መፈጠርን ዓላማ ከመጽሐፍ ቅዱስ ልጥቀስ፣

በአጭር ቃል መጽሐፍ፣ “ምድርና ሞላዋ ለእግዚአብሔር ናት፥ ዓለምም በእርስዋም የሚኖሩ ሁሉ።” (መዝ. 24፥1) ይላል። ሲፈጥርም አዝዞ የተፈጸመለት፤ ምድርን በቃሉና በኃይሉ የፈጠረ፣ ዓለሙን በጥበቡ የመሠረተ፣ ሰማያትን በማስተዋሉ የዘረጋ ጌታ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ (ዘፍ. 1፥3፡6፡9፡11፡14፡20፡24፡26፤ ኢሳ. 40፥12-14፤ ኤር. 10፥12-16፤ ዮሐ. 1፥3)፤ ይህ ብቻ ያይደለ በቀንና በሌሊት ላይ ፀሐይና ጨረቃን ያሠለጠናቸው፤ የፈጠራቸውም ርሱ ብቻ ነው (ዘፍ. 1፥16፤ መዝ. 136፥7፤ አሞ. 4፥13፤ ዮሐ. 1፥3፤ ቈላ. 1፥15-16፤ ዕብ. 11፥3)

- ፍጥረት የተፈጠረው ለእግዚአብሔር ሊሰግድና ለክብሩ ሊኖር ብቻ ነው፣

“አንተ ብቻ እግዚአብሔር ነህ፤ ሰማዩንና የሰማያት ሰማይን ሠራዊታቸውንም ሁሉ፥ ምድሩንና በእርስዋ ላይ ያሉትን ሁሉ፥ ባሕሮቹንና በእነርሱ ውስጥ ያለውን ሁሉ፥ ፈጥረሃል፥ ሁሉንም ሕያው አድርገኸዋል፤ የሰማዩም ሠራዊት ለአንተ ይሰግዳሉ።” (ነህ. 9፥6)፣

“ … በስሜ የተጠራውን ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ” (ኢሳ. 43፥7)፣

“ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ፦ ጌታችንና አምላካችን ሆይ፥ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ።” (ራእ. 4፥101-11)።

- ፍጥረት በክርስቶስ ለክርስቶስ ተፈጥሮአል፣

“እርሱም የማይታይ አምላክ ምሳሌ ነው፤ የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኵር ነው፤ ሁሉ በእርሱና ለእርሱ ተፈጥሮአል፤” (ቈላ. 1፥15-16)።

ጥቂት ነገር ልጨምር፣ አስቀድሞ፣ የእስራኤል ልጆች ምድርን በተመለከተ ልክ እንደ አሕዛብ ወይም እንደ አንዳንድ የኦርቶዶክስ ሰባኪያን ደካማ አመለካከት ነበራቸው፣ ያሉበትና የሚኖሩበትን ብቻ የእግዚአብሔር እንደ ኾነ ያስባሉ፡፡ ዮናስና አንዳንዶች እግዚአብሔር የሌለበት የምድር ክፍል ያለ መሰላቸው፤ እንደ ዳዊት ያሉ ቅዱሳን ግን እስራኤል ብቻ ሳትኾን አሦርም፤ ግብጽም፤ ባቢሎንም ምድር ኹሉም የእግዚአብሔር ናቸው ብለው ያምናሉ።

ጌታ እግዚአብሔር በእነዚህ አገር ካሉ አማልክት እጅግ የተለየና ታላቅ ነውና። ምድርና መላዋ የርሱ ከኾነች፤ ለርሱ ክብርና ፈቃድ ብቻ ትታዘዛለች ማለት ነው። ምክንያቱም “ምድርና በእርስዋ የሞላባት ሁሉ የጌታ ነውና።” (1ቆሮ. 10፥26)፡፡

የፍጥረት ፍጻሜ ግቡም፣ “በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።” (ኤፌ. 1፥10) ተብሎአል፡፡

2. ማርያም ከፍጥረት በፊት ነበረችን? ማርያም ዓለም በሌለበት ዘመን ለእግዚአብሔር ዓለሙ ነበረች? … እንዲህ ብሎ ማስተማር በራሱ፣ “ከሰንበት ተማሪ” ያነሰ ማንነትን መያዝ ነው። አንድ ጤናማ የኦርቶዶክስ ሰንበት ተማሪ የማርያምን ፍጡርነት እንዴት ይስታል? “እናቷ ሐና አባቷ ኢያቄም” ብሎ ገና በማለዳ እየሰማ አድጓልና። ግን ከኦርቶዶክስ ውጭ ያለ የካቶሊክንም ትምህርት የቀዳ ሰው፣ እንደዚህ “ሰባኪ” መቃዠቱ አይቀርም።

ካቶሊካውያን ማርያምን “ኃይለ አርያማዊት” ማለታቸውን ከዚህ በፊት አንስተን መልስ ሰጥተንበታል፤ ኦርቶዶክሳውያንም በመጽሐፋቸው ያለውን ትተው ከካቶሊክ የተቀዳ ትምህርት ይዘው “ከፍጡራን በላይ፤ ከፈጣሪ በታች” የሚል አስተምህሮ ይዘዋል። ይህን እውን ለማድረግም፣ እግዚአብሔር ፍጥረትን ሲፈጥር፣ አስቀድሞ ሚካኤልን እንዳማከረውና ሲያማክረውም “ስለ ማርያም ብሎ ፍጥረትን እንዲፈጥርና ጊዜው እስኪደርስ ማርያም በሚካኤል ክንፍ ሥር ታትማ ትቆይ” የሚል ተረት ተዘጋጅቶለታል።

መጽሐፍ ግን በግልጥ፣ “የጌታን ልብ ያወቀው ማን ነው? ወይስ አማካሪው ማን ነበር? ወይስ ብድራቱን ይመልስ ዘንድ ለእርሱ አስቀድሞ የሰጠው ማን ነው?” (ሮሜ 11፥34-35) ይላል፡፡ ማርያም በእግዚአብሔር ኅሊና ትታወቅ ነበር ማለት የእግዚአብሔርን ቅድመ ዕውቀት እንጂ የማርያምን ብቃት አያሳይም፡፡ እግዚአብሔር ገና ያልተደረገውን ሲያውቅ አማካሪም ረጅም የለበትምና!

ዐሳቤን ልቋጭ፣ መጽሐፍ፣ “ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።” (ሮሜ 11፥36) እንደሚል፣ ፍጥረት ያለ ሰው ዐሳብ በእግዚአብሔርም ዕቅድ ብቻ መጥቶአል። ደግሞም ኹሉም ነገር በርሱ በኩል ካልኾነ በቀር፣ ሊሳካና ሊዋብ፤ ሊራመድና ሊጸና አይችልም፤ ፍጥረተ ዓለሙ ያለ እግዚአብሔር መናና ወና ነው። እኛ ከኀጢአታችን እንኳ ነጻ መውጣት ያልቻልን ደካማ ፍጥረት ነበርን! ኹሉም እንደገና “የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ” (ኤፌ. 1፥6) በውዴታ ምስጋናና ክብርን ለእግዚአብሔር ይሰጠዋል።

ቅዱስ ጳውሎስ በጥቂቱ እግዚአብሔርን በማወቁ በታላቅ ደስታ ያመሰግነዋል፤ በርግጥም እኛም እግዚአብሔርን ያወቅነው በፍጥረቱና (ሮሜ 1፥20-21) በተለይም ደግሞ በልጁ በኩል በኾነልን መገለጥ ነው (ዮሐ. 1፥18)፤ ያወቅነውን እግዚአብሔርን ባለማወቃችን ይበልጥ እናመልከዋለን እናመሰግነዋለን እንጂ ከቶ ወዴትም አንሄድም!


ካራው “አቡነ” እንድርያስና “ዝክረ ኒቂያ” ስለ ወንጌላዊው አቡነ ገብርኤልና …!


“የዝክረ ኒቂያ” ጉባኤ ትላንት ማምሻውን ማጠቃለያ ዐሳብና “የአቋም መግለጫ” በማውጣት ተጠናቅቆአል፤ “የመዝጊያ ንግግር” የሚመስል የካራ ትምህርት የተንሠራፋበትን ንግግር ያቀረቡት አቡነ እንድርያስ ናቸው፡፡ አቡኑ ገና ከጅማሬያቸው፣ “"ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም የሚለው ስብከት ሕገ ወጥ ነው!" ማለታቸው እምብዛም አላስደነገጠኝም፤ ከዚህ የተሻለ ከነርሱ አልጠብቅምና፡፡ ነገር ግን በዚያ ኹሉ ንግግራቸው ማርያም ለኦርቶዶክስ አስፈላጊነቷን ደጋግመው ያጐሉትን ያህል፣ ክርስቶስ ኢየሱስን ደጋግመው ለማንሳት ይቅርና አንድም ጊዜ “እርሱ በርግጥ ቤዛና መድኃኒታችን ነው” አለማለታቸው እጅግ አስደንቆኛል፡፡


ጌታችን ኢየሱስ በናዝሬት ገሊላ በተደጋጋሚ ተአምራት አድርጎ፤ ትምህርትም አስተምሮ ነገር ግን አለማመናቸውን ማርቆስ ወንጌላዊው ሲነግረን፣ “ስለ አለማመናቸውም[ኢየሱስ] ተደነቀ” (ማር. 6፥6) ይለናል፡፡ እንደ አቡነ እንድርያስ ያሉ ጳጳሳትን ስመለከት፣ ዘወትር ትዝ የሚለኝ ቃል ማርቆስ ወንጌላዊ በወንጌሉ የጠቀሰው ቃል ነው፡፡ በንግግራቸው በአንድ በኩል በጣም ደስ ብሎኛል፤ ጨለማው ግጥጥ ብሎ ወደፊት በመውጣቱና “በማኅበራዊ ሚዲያው እነሄኖክ ኃይሌና ያረጋል አበጋዝ፤ ብርሃኑ አድማስ የሚሏትና ውስጥ ባለችው ኦርቶዶክስ መካከል የፈጠጠ ልዩነት መኖሩን እንዲህ አደባባይ በመውጣቱ ደስ ብሎኛል፤ በትላንትናው የአቡነ እንድርያስ ንግግር እንድትታደስ ወይም በዚሁ ትምህርቷ የምትጸና ከኾነ፣ “ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ስንኳ ብታውቂ፤ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሰውሮአል።” (ሉቃ. 19፥42) የሚለውን ጌታ ኢየሱስ ለኢየሩሳሌም በሃዘን ስብራት ኾኖ የተናገረውን ቃል በድጋሚ መናገር ይገባናል፡፡

እውነት ለመናገር “ኢየሱስ የኀጢአታችን ቤዛ ነው፤ ሌላ ቤዛ የለንም፤ ማርያም ቤዛችን አይደለችም” የሚለው ትምህርት፣ ይህን ያህል የድንጋጤና የሽብር ድምጽ ሳይኾን የመዳንና የምሥራች ድምጽ ነው፡፡ ክርስትና ያለ ማርያም “ከንቱ” እንደ ኾነ ለሚያስቡ ይህ ትምህርት ሁከትና ድንጋጤ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት ደግሞ አባ ገብርኤልን “ለቁም እስር” መዳረግ፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ምን ያህል ኢ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት እንደ ገነነ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡ በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ የኀጢአት ቤዝወትነት ተገፍቶ፣ ከማርያም ቤዝወት ጋር ተካክሎ አለመነገሩ ለምን ብዙዎችን እንዳስቆጣና እንዳስገነጠ ለማወቅ ይቸግራል፡፡

አንድ ሊቀ ጳጳስ ስለማርያም ተቆጭቶ፣ ስለ ኢየሱስ ግን አንድም የስብከት ቃል ትንፍሽ ሳይሉ መውረዳቸው እጅጉን ያስደንቃል፡፡ በዚያው ትይዩ ደግሞ ወንጌል የሰበከን ጳጳስ በዚያ ልክ ማጣጣልና ማልኮስኮስ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ፤ ከጳጳስ እስከ ምእመን የተካኑበት መኾኑ እጅግ አስፈሪ ያደርገዋል፡፡ አባ በርናባስና አባ ገብርኤል እንዲህ ባሉ ጳጳሳት መካከል ተከብበው ስመለከት ጥቂት ተስፋ በውስጤ ቢኖርም፣ የትላንቱን ዓይነት “ዝክረ ኒቂያ” ጉባኤ ስመለከት ግን “ፍርድ የሚጠብቅ ብርቱ ጨለማ” መኖሩን አስተውላለሁ!

ወንጌል ግን እንዲህ ባሉ ሰዎች መካከልም እያሸነፈ መሄዱ አይቀርም፤ ቃሉ በብርቱ ተቃዋሚዎችም መካከል እያሸነፈ ይሄድ ነበርና፣ “የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፥ በኢየሩሳሌምም የደቀ መዛሙርት ቍጥር እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙ ሰዎች ለሃይማኖት የታዘዙ ሆኑ።” (ሐ.ሥ. 6፥7) እንዲል ይህ ቃል በኦርቶዶክስ እንደሚፈጸም ከአቡኑ የጨለማ ንግግር ጀርባ ተስፋ አደርጋለኹ!

My blog link - http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/05/blog-post.html


"ኢየሱስ ክርስቶስ ለኀጢአታችን የተሠዋ ብቸኛ የዓለም ቤዛ ነው" ማለት በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ያስወቅሳል ያስከስሳል። በሚያሳዝን መልኩ "ማርያም ቤዛዊተ ዓለም፤ መድኀኒተ ዓለም ናት" ማለት ግን አያስወቅስም፤ አያስከስስም። አባ ገብርኤልን "የቁም እስረኛ" ያደረገው የሲኖዶስ ውሳኔ፣ እርግጠኛ ነኝ ዘበነን ወይም ምሕረተአብን ወይም ደግሞ እንግዳወርቅ የተባለን ዘማሪ እንዲያ ማድረግ አይችልም። ምክንያቱም እነርሱ የእግዚአብሔርን ቀጥታ ለማርያም የሚናገሩ "አፍቃሪያነና አምላክያነ ማርያም" ናቸውና።

ኦርቶዶክስ የኢየሱስ ቤዝወት ስብከት እንደገና ያሻታል ከሚሉት ነኝ።

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ ከዲያብሎስ ጋር ለምን ተከራከረ?!


ይሁዳ በመልእክቱ ውስጥ በሙሴ ሥጋ ምክንያት የሊቀ መላእክት ሚካኤልና የዲያብሎስ ክርክር መቅረቡን ይነግረናል። ስለ ሙሴ ሥጋ ጥቂት ብናነሣ፣ በዘዳ.  34፥5-6 እንደ ተጠቀሰው በሞዐብ ምድር እንደ ሞተና ከቤት ፌጎር አንጻር ባለው ሸለቆ ውስጥ እንደ ተቀበረ ይነግረንና የመቃብሩን ስፍራ ግን እስከ ዛሬ ድረስ የሚያውቅ እንደሌለም ይነግረናል።

ይሁዳ የክርክሩን መረጃ ከየት እንዳገኘ ባይነግረንም፣ በመንፈስ ቅዱስ መነዳት እንደ ጻፈው ግን እናምናለን። ስለ ክርክሩ ደግሞ የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች ኹለት ጠንካራ ምክንያቶችን ይጠቅሳሉ። እኒህም፦

1.  ዲያብሎስ እስራኤላውያንን ወደ ጣዖት አምልኮ ለመምራት የሙሴን አካል እንደ ጣዖት አምልኮ ሊጠቀምበት ፈልጎ እንደ ነበር ይጠቅሳሉ።  ሥጋውን አድርቀው እንደ ልዩ ኃይል እንዲጠቀሙበት ለማድረግ።
2. ዲያብሎስ፣ እግዚአብሔር ለሙሴ አካል ያለውን ዓላማ አስቀድሞ ገምቶ ሊኾን ይችላል፤ እና ዲያብሎስ ያንን እቅድ ሊያከሽፍ ሞከረ። ሙሴ በኋለኛው ዘመን፣ በክብሩ ተራራ ከኤልያስ ጋር መገለጡን ብዙዎቻችን አንዘነጋም። ስለዚህ እግዚአብሔር ለወደፊት እቅዱ የሙሴ አካል አስፈልጎታልና ዲያብሎስ እንዲወስደው አልፈቀደም።

ይሁዳ በመቀጠል ቅዱስ ሚካኤል ከዲያብሎስ ጋር እንዴት እንደ ተከራከረ ይነግረናል። ሚካኤል ተዋጊ መልአክ ነውና ዲያብሎስን "እግዚአብሔር ይገስጽህ" ብሎ በጽድቅ ተዋጋው እንጂ አልተሳደበም። የዲያብሎስ አንደኛው ዕቅድ፣ የእስራኤል ልጆች የሙሴን ሥጋ ከአሕዛብ እንደ ተመለከቱት እንዲያመልኩት ማድረግ ነበር። መልአኩ ግን ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ እንዲመለክ የማይፈቅድ ቀናተኛ ነውና ተቃወመው።

በርግጥ ሙሴ የታወቀ የፊተኛው ኪዳን መሪና ሊቀ ነቢያት ነው። እግዚአብሔርን በተደጋጋሚ ቃል በቃል ያነጋገር የነበረ ነቢይ ነው። ግን ለኪዳኑ ሕዝብ እንደ ጣዖት እንዲኾን አልተፈቀደም። ከሰሞኑ የሙሴና የማርያም ነገር ከክርስቶስ ቤዝወት ጋር ተያይዘው መከራከሪያ ኾነው ሲቀርቡ አይተናል።  እስራኤል ዓይናቸውን ከእግዚአብሔር አንስተው፣   የሙሴን ሥጋ ላይ እንዲያደርጉ ያኔ የጣረው ዲያብሎስ፣ ዛሬም የክርስቶስን የመስቀል ቤዝወት፣ በማርያምና በሙሴ ለመከለል የፈለገ አይመስላችኹም?!

እግዚአብሔር ይገስጸው።

Blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/04/blog-post_27.html?m=1


Furiin dhugaa Yasuus malee hinjiru!

Jechoota gurguddoo dubbii Waaqummaa keessaa inni tokko Furii dha. Kakuu duraa keessatti qabeenyi lubbuudhaaf furii ta'e caqasameera (Fkn. 13:8); warri Israa'el lafa ykn mana isaani erga gurguratan booda furii gochuudhaan deebisifachuu danda'u ture (Leewo. 25:24-34). Raajiin Muuseen ummata Israa'el gabrummaa Gibxi jalaa sababa bilisa baaseef furii ykn bilisa baasaa ta'eera ykn jedhamee yaamameera. (Ho. Erg. 7:35).

Kana irraa kan ka'een hiikni furii, (1) waan qabamee gad lakkisisuuf ykn deebisisuuf gatii kafalamuu; (2) beenyaa (3) jijjiiraa jedhamee hiikamuu danda'a. Isaan kun hundi  garuu gaadiduudhaan kan tajaajilan malee isaa furii dhugaa fi dhumaa miti.

Goftaan Yasuus Kristoos garuu warra isatti amanan hundaaf furii dhugaa ta'e mul'ate (Mar. 10:45; Room 3:24; Efe. 1:7; 1Ximo. 2:5-6; Hibr. 9:13). Furii ta'uudhaafis wantootni armaan gadii akka dirqamaatti ka'aamu;
1. Qaamni tokko furii namaaf ta'uudhaaf, matummaan isaa idaa kaffaluu fi broo irraa bilisa ta'u qaba. Yasuus cubbu kan hinbeeknee waan ta'eef idaa cubbuu nurraa kafaluu danda'a,
2. Furii ta'uudhaaf akka keenya ta'u qaba. Foon uffachuun Goftaa Yasuuf kanaaf ture,
3. Waaqayyoo gadiitti cubbuu namaatiif furii kan ta'u danda'u tokkolee hinjiru. Sababni isaas murtoo du'a kan nurratti dabarsee isa. Murtoo dabarsee kana kan nurraa furuus isa malee kan biraa hinjiru.

Kanaafis cubbuu raawanneef du'a kan nuratti murteesse innumtii furii nuuf ta'e nu fayyisee. Maqaan isaa yaa ebbifamu. Dhugaan kana yoo ta'e furiin nuuf raawatamuu isaatiin maal argannee? kan jedhuuf;

(1) ammaaf Dhiifama cubbuu  arganeerra; guutumaan guututti  immoo dhufaati 2ffaa Kristoosiin arganna (Room 8:23)

(2) Cubbuu mo'achuudhaan Kristoosiin duuka bu'udhaaf mana Hafuura Qulqullu taaneerra;

(3) Kana irraan kan ka'eenis gara boqonnaa Kristoositti galleera. Kanaaf furii arganneen dhiifama cubbuu argachuudhaan jireenya hinduune Kristoos wajjiin arganneera.

Eegaa Kristoosiin alatti uumamaan kamuu furii cubbuu ta'u hin danda'u; Kristoos garuu "... jireenya isaatiif muummee ka hin qabne ta'uu isaatiin... "(Hib. 7:16) furii bara baraa warroota isatti amananiif ta'eera.

"Jaalala addaan hin cinneen Gooftaa keenna Yesus Kristosiin warra jaalatan maraaf, kennaan isaa ka bilisaa isaaniif haa ta'u." (Efe. 6:24)

Liinkii telegraami - https://t.me/ebenezertek
Liinkii biloogii - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/04/furiin-dhugaa-yasuus-malee-hinjiru.html?m=1


የትክክለኛ ቤዛ መስፈርቱ ይኸው!


በአጭር ቃል ስብከት፣ "... እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤" (1ቆሮ. 1፥23) እና "ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤" 1ጢሞ. 1፥15) የሚለው ብቻ ነው። ቅዱሳን ሐዋርያትም፣ የስብከታቸው ማዕከል፣ "መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።" (ሐ.ሥ. 4፥12) የሚል ነበር።

ከዚህም ባሻገር በቅዱሳት መጻሕፍት የተጠቀሱት ደቀ መዛሙርት ኹሉ የሰበኩት የተሰቀለውን ክርስቶስን ብቻ ነው።

"ፊልጶስም ወደ ሰማርያ ከተማ ወርዶ ክርስቶስን ሰበከላቸው።" (ሐ.ሥ. 8፥5)

"... ወዲያውም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በምኵራቦቹ[ጳውሎስ] ሰበከ።" (ሐ.ሥ. 9፥20)

"ማንም ሳይከለክለው[ጳውሎስን] የእግዚአብሔርን መንግሥት እየሰበከ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እጅግ ገልጦ ያስተምር ነበር።" (ሐ.ሥ. 20፥28)

አዎን፤ "በስሙም ንስሐና የኃጢአት ስርየት ከኢየሩሳሌም ጀምሮ በአሕዛብ ሁሉ ይሰበካል" (ሉቃ. 24፥47) ተብሎ እንደ ተነገረ፣ ከኢየሱስ በቀር ሌላ ስብከት የለም። ቅዱስ ጴጥሮስም፣ "ለሕዝብም እንድንሰብክና በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ በእግዚአብሔር የተወሰነ እርሱ እንደ ሆነ እንመሰክር ዘንድ አዘዘን።" (ሐ.ሥ. 10፥42) ብሎ እንደ ተናገረው፣ እንድንሰብክ የታዘዝነው፣ ከክርስቶስ በቀር ሌላ የለም።

ምክንያቱም፣ ክርስቶስ የመላለሙ ቤዛ ነውና፣ ሰዎች አምነው ይድኑበት ዘንድ እንሰብከዋለን። ጌታ ኢየሱስን እመኑና ዳኑ እንላለን። ጌታ ኢየሱስን በማመንና በመቀበል የዘላለም ሕይወት አለ ብለን እንሰብካለን። "በልጁ[በክርስቶስ] የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።" (ዮሐ. 3፥36)

በርግጥም በቅዱሳት መጻሕፍትም የታዘዘው ይኸው ነው። ለመስበክና ለማወጅ የክርስቶስ ትንሣኤው ኃይላችን ነው። ከክርስቶስ በቀር ሊታወጅ በሞት ላይ የሠለጠነ ሌላ የለም።

ካለ "እልፍ ቤዛ" ወዳዶቹ የትክክለኛና ከኀጢአት የሚቤዠው ቤዛ መስፈርቱ ይህ ነው! መስፈርቱም፦ ማርያምም ኾኑ ሙሴ፣ አምላክ ኾነው ሳለ ክብራቸውን ጥለው በበረት ተወልደው፣ በገሊላና በኢየሩሳሌም  አደባባዮች በኪደተ እግራቸው ተመላልሰው፣ ተወቅሰውና ተተችተው፣ ስለ በደላችን ቤዛ ለመኾን አንዳች በደልና ነቀፋ፣ ነውርና ዕድፈት ሳይገኝባቸው መከራን ተቀብለው፣ ተሰቅለው፣ ተቀብረው፣ አብን ፍጹም አርክተው በሦስተኛው ቀን ከሙታን መካከል ከተነሡና ዐርገው፣ በአብ በግርማው ቀኝ መቀመጥ ከቻሉ ምናልባት "ቤዛ ብለን" እንሰብካቸው ይኾናል።

ነገር ግን ከክርስቶስ በቀር ሌላ ቤዛ የለምና ርሱን ብቻ እንሰብከዋለን! እንኪያስ እንደ ደቀመዛሙርቱ እንዲህ እንላለን፣

"ወንድሞች ሆይ፥ በእርሱ በኩል የኃጢአት ስርየት እንዲነገርላችሁ፥ በሙሴም ሕግ ትጸድቁበት ዘንድ ከማይቻላችሁ ሁሉ ያመነ ሁሉ በእርሱ እንዲጸድቅ በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን።" (ሐ.ሥ. 13፥38-39)

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን።” (ኤፌ. 6:24) አሜን።


Blog link - https://abenezerteklu.blogspot.com/2025/04/blog-post_26.html?m=1


ርቱዕ ኦርቶዶክሳውያን ነን!

"ኢየሱስ ብቸኛ የኀጢአታችን ቤዛ ነው" ማለት፣ "ተሐድሶ፣ ኦርቶ ጴንጤ..." የሚል ስም ካሰጠና "ማርያም ቤዛዊተ ዓለም" ማለት ደግሞ፣ ኦርቶዶክሳዊ መኾንን ከጠቆመ፣ ለዘለዓለም "የተቋሙን ኦርቶዶክስ" ባልባል ደስ ይለኛል። ልክ ቅዱስ ጳውሎስ፣ በክርስቶስ ጉዳይ የገዛ ወገኖቹ በከሰሱት ጊዜ፣ " ... በሕጉ ያለውን በነቢያትም የተጻፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ ኑ_ፋ-ቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ፤" (ሐ.ሥ. 24፥14) ብሎ እንደ ተናገረው፣ እኔም የክርስቶስን ብቸኛ ቤዝወት ተቀብዬ... ተሐድሶ፣ ኦርቶ ጴንጤ ... ተብሎ መኖር ደስታዬ ነው።

እንዳትዘነጉ! "ክርስቶስ ብቸኛ ቤዛ ነው" የሚለው ትምህርት ኦርቶዶክሳዊ ነው፤ ስም ግን አለቦታው ሲውል፣ መ-ና-ፍ-ቅ ሊባል የሚገባው ኦርቶዶክስ ተብሎ ይጠራል! እኛስ በስም ያይደለ፣ አክብሮተ እግዚአብሔር ያልተለየው ርቱዕ ሕይወት (orthopraxy) እና ርቱዕ ጥልቅ ፍቅር (orthopathy)  እንዲሁም በክርስቶስ ላይ የጸና ርቱዕ እምነት (orthodoxy) ያለን ኦርቶዶክስ አኅውና አኀት ነን!
አትደናገጡ!

ጸጋ ይብዛላችኹ፤ አሜን።

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek

1k 0 6 13 48
20 last posts shown.