የጥቅምት 11/2017 አበይት የዓለም ዜናዎች
🇺🇸🇮🇱🇮🇷 የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ማይክ ጆንሰን እስራኤል ኢራንን ለመምታት ያዘጋጀችውን ዕቅድ ያሳያል የተባለ በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨ ያፈተለከ መረጃ ጉዳይ አሜሪካ መመርመር መጀመሯን ተናገሩ።
🇸🇸 በደቡብ ሱዳን በተከሰተ የጎርፍ መጥለቅለቅ ከ1 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለጉዳት መዳረጉ ተነገረ።
🇰🇷🇺🇦🇷🇺 ደቡብ ኮሪያ ሩሲያን ወግነው በዩክሬን ጦርነት ለመሳተፍ በሩሲያ ሥልጠናዎችን በመውሰድ ላይ የሚገኙ 1 ሺህ 5 መቶ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች በአስቸኳይ አገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ለሞስኮ ጥያቄ አቀረበች።
🇺🇸 የአሜሪካ የዘንድሮ 2024 በጀት ጉድለት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ8 በመቶ ጨምሮ ከ1.8 ትሪሊዮን ዶላር በላይ መሆኑ ተሰማ።
🇰🇵 ሰሜን ኮሪያ በሀገሯ ላይ ህገወጥ ማዕቀብ የሚጥሉ ሀገራት ዋጋ ይከፍላሉ ስትል አስጠነቀቀች።
#EBS
#EBSTVNEWS
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnew