Ethiopian Electric Utility


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Career


EEU Official Telegram Channel
Web: www.eeu.gov.et

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Career
Statistics
Posts filter


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

በአዘዞ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 33 ኪ.ቮ ወጪ መስመር ብሬከር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በደልጊ፣ በጭልጋ፣ በሳንጃ፣ በአርባያ፣ በጉሃላ፣ በቀራቅር ፣ በቆላድባ፣ በጯሂት፣ በትክል ድንጋይ እና ማክሰኝት ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል።

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የሃይል አቅርቦት

በአዘዞ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 33 ኪ.ቮ ወጪ መስመር ብሬከር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በደልጊ፣ በጭልጋ፣ በሳንጃ፣ በአርባያ፣ በጉሃላ፣ በቀራቅር ፣ በቆላድባ፣ በጯሂት፣ በትክል ድንጋይ እና ማክሰኝት ከተሞች የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በብሬከሩላይ ያጋጠመው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


የኮሶበር አገልግሎት መስጫ ማዕከል አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ከዕቅድ በላይ መፈፀም ችሏል

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በባህርዳር ሪጅን የኮሶበር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ባለፉት ዘጠኝ ወራት 7መቶ 46 ደንበኞችን አዲስ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ 9መቶ16 ደንበኞችን ተጠቃሚ በማድረግ የዕቅዱን 122.78% አሳክቷል፡፡

አዳዲስ ደንበኞችን ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ 8.7 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣ 15 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታና 18 የተለያየ አቅም ያለው ትራንስፎርመር የማስቀመጥ ሥራ ተሰርቷል፡፡

የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመቀነስ 26 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣ 25ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር የቅድመ ጥገና ሥራ በማዕከሉ አቅም መስራት ተችሏል፡፡

የኮሶበር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ለ9ሺ 5መቶ ደንበኞች አገልግሎት እየሠጠ ሲሆን 16የሳተላይት ጣቢያዎች አሉት፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በእቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1355?lang=am


⚠️እንድታውቁት⚠️

ነገ ቅዳሜ ሚያዝያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡00 እስክ ለሊቱ 8፡00 ድረስ የሲስተም ማሻሻያ ስራ ስለምናከናውን፤ ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባችሁን በዲጂታል የክፍያ አማራጮች የምትፈጽሙ ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንን ተገንዝባችሁ ከላይ ከተገለፀው ቀንና ሰዓት አስቀድማችሁ ክፍያችሁን እንድትፈፅሙ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

11.8k 0 179 36 43

የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ግብዓት አምራቾች የግብዓት እጥረት በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑ ተገለፀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሀገር ውስጥ ከሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማት ግብዓት አምራቾች ጋር በዛሬው ዕለት ባደረገው ውይይት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ባደረጉት ንግግር የአገር ውስጥ ግብዓት አምራቾች ለኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ዝርጋታ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን እጥረት በመቅረፍ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዋና ሥራ አስፈፃሚው አክለውም ተቋሙ ከዓመታት በፊት ለኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ዝርጋታ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ሙሉ በሙሉ ከውጭ ሀገር እያስገባ የነበረ መሆኑን አስታውሰው በአሁኑ ወቅት ለሀገር በቀል አምራች ኢንዱስትሪዎች በተዘረጋው ምቹ ሁኔታ ይህንን በተወሰነ መልኩ ማስቀረት ተችሏል ብለዋል፡፡

አያይዘውም የአገር ውስጥ አምራቾች የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ሙሉ በሙሉ መሸፈን ባይችሉም የግብዓት እጥረትን በመቅረፍ፣ የውጭ ምንዛሬን በማዳን እንዲሁም የቴክኖሎጂና የዕውቀት ሽግግር እንዲረጋገጥ እያበረከቱት አስተዋፅኦ ቀላል አለመሆኑን ገልፀዋል፡፡

በቀጣይ አማራቾቹ የተቋሙን የግብዓት ፍላጎት ሙሉ በሙሉ ለማሟላት ከዚህ በላይ መስራት የሚጠበቅባቸው መሆኑን ጠቁመው በተቋሙ በኩል ካሁን በፊት ሲደረግ የነበረው ድጋፍ በተሻለ መልኩ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

በዕለቱ የተቋሙ ሰፕላይ ቼይን ዲቪዥን ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ መገርሳ የተቋሙን ቀጣይ የግብዓት ፍላጎት በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ አምራቾች የሚያቀርቡት ግብዓት ለኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማትን ለማስፋፋት ወሳኝ መሆኑን ተናግረው በቀጣይ የተቋሙን ሰፊ የግብዓት ፍላጎት ለማሟላት እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡

አክለውም አምራቾች ጥራቱን የጠበቀ ምርት በወቅቱ ማቅረብ የሚገባቸው መሆኑን አንስተዋል፡፡

በውይይት መድረኩ ተሳታፊ የነበሩ የአገር ውስጥ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት አምራቾች በበኩላቸው መድረኩ መዘጋጀቱ መልካም መሆኑን አንስተው ከምርት ጋር በተያያዘ ያሉባቸውን ችግሮች፣ በተቋሙ በኩል ሊደረግላቸው ስለሚገባ ድጋፍ በተመለከተ ሀሳባቸውን አካፍለዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት




በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የሃይል አቅርቦት

ከጋምቤላ - ደምቢዶሎ በተዘረጋው 66 ኪ.ቮ የኃይል አስተላለፊያ መስመር ላይ በአጋጠመ ብልሽት ምክንያት በደምዶሎ ከተማ፣ በሙጊ፣ በመቻራ፣ በደምዶሎ አየር ማረፊያ፣ በደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ እና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ መስመሩ ላይ ያጋጠመው ችግር ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡


በአዲስ አበባ ከተማ የጥገናሥራ ለማከናወን ሲባል በእቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው ቦታዎችን ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡- http://www.ethiopianelectricutility.gov.et/power-interruption?lang=am


ማዕከሉ 5 መቶ 21 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ አደረገ

በባህርዳር ሪጅን ደ/ታቦር ቁ.1 አገልግሎት መስጫ ማዕከል ባለፉት ዘጠኝ ወራት 7 መቶ 34 ደንበኞችን አዲስ ኃይል ለማገናኘት አቅዶ 5 መቶ 21 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ የዕቅዱን 70.98 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡

ማዕከሉ አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ 3.67 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣ 6.03 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታና 3 ትራንስፎርመር የማስቀመጥ ስራ ተሰርቷል፡፡

በጠቸማሪም የትራንስፎርመር አቅም ለማሳደግ በተሰራ ስራ 3 የተለያዩ አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮችን ማሳደግ ተችሏል።

እንደተቋም በተያዘው የኃይል መቆራረጥ ችግር የመቀነስ ዕቅድ ለማሳካት 6.17 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣ 5.42 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር የቅድመ ጥገና ስራ በማዕከሉ አቅም መስራት ተችሏል፡፡

የደ/ታቦር ቁ.1 አገልግሎት መስጫ ማዕከል ለ11ሺ 8መቶ ደንበኞች አገልግሎት እየሠጠ ሲሆን 12 የሳተላይት ጣቢያዎች አሉት፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

ከመንዲ - አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በደረሰ የቴክኒክ ብልሽት ምክንያት በአሶሳ ከተማ፣ በባምባሲ፣ በኡራ፣ በአብራሃሞ፣ በሸርቆሌ፣በመንጌ፣ በኩርሙክ፣ በሆሞሻ፣ በቶንጎ፣ በኡንዱሉ፣ በብልድግሉ ወረዳዎች ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል።

የጥገና ስራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ከ356 ሺሕ በላይ አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ሆኑ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተጠናቀቀው ዘጠኝ ወራት ውስጥ 356 ሺሕ 935 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

ሰሜን አዲስ አበባ 4 ሺሕ 440፣ ባሌ ሮቤ 9 ሺሕ 219 እና ሆሳዕና 14 ሺሕ 83 ደንበኞች አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ በማድርግ ከእቅዳቸው በላይ ያሳኩ ናቸው፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሆኑ አዳዲስ ደንበኞች ቁጥር ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 20 በመቶ በብልጫ አሳይቷል፡፡

በተመሳሳይ በተጠናቀቀው በጀት አመት ዘጠኝ ወራት 107 አዳዲስ የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን 102 ከዋናው የኃይል ቋት 5 ደግሞ ከፀሐይ ኃይል ማመንጫ ያገኙ ናቸው፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የ15 ሺሕ 295 ኪ.ሜ የማሳራጫ መስመር ማስፋፊያ እና 3 ሺሕ 42 አዲስ ትራንስፎርመር ተከላ ስራ ተከናውኗል፡፡

የብልሹ አሰራርና የሙስና ጥቆማ መቀበያ መተግበሪያ በሥራ ላይ መዋሉ፣ የዲጂታል ክፍያ ተጠናክሮ መቀጠሉ፣ በኮሪደር ልማት ላይ የተከናወነ የመልሶ ግንባታ ስራዎች በጠንካራ ጎን የተነሱ ሲሆን የመሰረተ-ልማት ሥርቆት፣ የፕሮጅክት አፈፃፀም መዘግየት እና የሲስተም መቆራረጥ በውስንነት የታዩ ናቸው፡፡

የተቋሙ አጠቃላይ ደንበኞች ቁጥር ወደ 5 ሚለየን 81 ሺሕ 405 የደረሰ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 81 በመቶ የድህረ ክፍያ፣18 በመቶ የቅድመ ክፍያ 1 በመቶ የሚጠጉት የዘመናዊ ቆጣሪ ደንበኞች ናቸው ተብሏል፡፡

የተቋሙ ከፍተኛ ማኔጅመንት አባላት የአገልግሎቱን የ9 ወር ዕቅድ አፈጻፀም እየገመገመ ይገኛል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን (የዜና ሽፋን እንዲሰጠን ስለመጠየቅ)

ተቋማችን ከሃገር በቀል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ግብዓቶች (ትራንስፎርመር፣ ኬብል፣ ኮንዳክተርና ሌሎች) አምራቾችና አቅራቢዎች ጋር ነገ ሚያዚያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም የግማሽ ቀን የምክክር መድረክ ያካሂዳል፡፡

ከጠዋቱ 2፡00 ጀምሮ በሂልተን ሆቴል በሚካሄደው በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ተገኝታችሁ የዜና ሽፋን እንድትሰጡን የተለመደ ትብብራችሁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡


በ72 ከተሞች የኤሌክትሪክ መስመሮችን ማሻሻል የሚያስችል ፕሮጀክት ለመጀመር ዝግጅት እየተደረገ ነው

በ11 ክልሎች በሚገኙ 72 ከተሞች ላይ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ለማሻሻልና ዓቅም ለማሳደግ የሚያስችል የኢነርጂ ዘርፍ ሪፎርም ኢንቨስትመንት እና ዘመናዊነት በኢትዮጵያ (ፕራይም-1) የተሰኘ ፕሮጀክት ለመተግበር ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ፕራይም-1 ፕሮጀክት በዋናነት የኃይል አቅርቦት ጥራትን ለማሻሻል፣ የከተሞችን ኢኮኖሚያዊ ልማት ለማሳደግ፣ የህዝቡን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እና የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦትን አስትማማኝ ለማድረግ ያለመ ነው።

ፕሮጀክቱ በ72 ከተሞች የሚገኙትን የመካከለኛና ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ መስመሮችን የሚያሻሻል እና የሚያዘመን ሲሆን፤ በዚህም የትራንስፎርመሮችን አቅም ማሻሻል፣ የኃይል ብክነት መቀነስ፣ የቮልቴጅ መዋዠቅ ማስተካከልና በኤሌክትሪክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያለውን የጥራት ጉድለት መቀነስ እንዲሁም አስተማማኝነትን ለመጨመር ያስችላል…..ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡- http://www.eeu.gov.et/contents/press-release?lang=am


በአዲስ አበባ ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በእቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው ቦታዎችን ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡- http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1351?lang=am


በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የኃይል አቅርቦት

በመንዲ አሶሳ ግዳሚ ‎132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል አስተላለፊ መስመር ላይ ዛሬ ሚያዚያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡27 ጀምሮ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በግዳሚ፣ በቤጊ ፣ በቆንዳላ፣ በአሶሳ ከተማ፣ በባምባሲ፣ በኡራ፣ በአብራሃሞ፣ በሸርቆሌ፣በመንጌ፣ በኩርሙክ፣ በሆሞሻ፣ በቶንጎ ፣ በኡንዱሉ፣በብልድግሉ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ መስመሩ ላይ ያጋጠመው ችግር ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በዲስትሪቢዩሽን መስመሮች እርጅና ምክንያት በከተሞች እያጋጠመ ያለውን የኃይል መቆራረጥ ችግር ለመቅረፍ በተመረጡ 10 ከተሞች የዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ስራ ለመስራት ፕሮጀክት ቀርፆ ወደ ስራ ገብቷል፡፡ 

የዲስትሪቢዩሽን መስመር መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ የሚደረገው በነቀምት፣ አምቦ፣ ሱሉልታ፣ ቢሾፍቱ፣ አሰላ፣ ደብረ ብርሃን፣ ዲላ፣ ሆሳዕና፣ አሶሳ እና በጅግጅጋ ከተሞች ነው፡፡

ፕሮጀክቱ በሶስት ምዕራፍ ተከፍሎ የሚከናወን ሲሆን፤ በመጀመሪያው ዙር ቢሾፍቱ፣ ሱሉልታ እና ደብረብርሃን፣ በሁለተኛው ዙር አሰላ፣ ሆሳዕና፣ ዲላ እና ጂግጅጋ እንዲሁም በሶስተኛው ዙር አምቦ፣ ነቀምት እና ኦሶሳ ከተሞችን ይሸፍናል…..ሙሉውን ለማንበብ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ http://www.eeu.gov.et/5BFA219C-19A5-CA28-EB4D-F5F69FD5C386/press-release/preview/1349


ሪጅኑ 15ሺ 3መቶ 28 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ አደረገ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የባህርዳር ሪጅን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 15ሺ 3መቶ 28 አዳዲስ ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ በማድረግ የዕቅዱን 76 በመቶ አሳክቷል፡፡

አዳዲስ ደንበኞችን ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ 63 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣134 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታና 175 ትራንስፎርመር የማስቀመጥ ስራ ማከናወን ችሏል፡፡

በዚህም ከመኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ደንበኞች በተጨማሪ የትምህርት፣የውሃ ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች ደንበኞችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

በሪጅኑ ባለፋት 9 ወራት በተሰራ የመልሶ ግንባታ ስራ 194 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር፣ 123 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር እንዲሁ 41 የተለያየ አቅም ያላቸው የትራንስፎርመር ተከላ ስራ አከናውኗል። በዚህም የኃይል መቆራረጥ ችግር ያለባቸውን አካባቢዎች መቅረፍ ተችሏል።

እንደተቋም በተያዘው የኃይል መቆራረጥ ችግር የመቀነስ ዕቅድ ለማሳካት 3ሺህ 982 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር 1641 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ቅድመ ጥገና ስራ ማከናወን ችሏል፡፡

በቅድመ ጥገና ስራው ያዘመሙ ምሰሶዎች የመቀየር ስራ፣ በኤሌክትሪክ አስተላላፊ መስመሮች ላይ የገቡ ዛፎችን ማፅዳት፣ የተሰባበሩ ስኒዎችን የመቀየር ስራ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ሪጅኑ ለ228 ሺህ 126 ደንበኞች አገልግሎት እየሠጠ ሲሆን 29 የደንበኞች ማዕከላት እና 417 የሳተላይት ጣቢያዎች አሉት፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ የመልሶ ግንባታ ሥራ ለማከናወን ሲባል በእቅድ የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1347


በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የሃይል አቅርቦት

በመቱ ሃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 15 ኪ.ቮ ወጪ መስመር ብሬከር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በመቱ ከተማ፣ በበቾ፣ በበሀሉ፣ በአሌ፣ በዲዱ፣ በሱጴ፣ በአሌጌ፣ በዳሪሙ፣ በሁሩሙ፣ በያዮ፣ በዶሬኒ ወረዳዎች እንዲሁም በመቱ ዪኒቨርሲቲ የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በብሬከሩ ላይ ያጋጠመው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኩል ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

20 last posts shown.