ᴇʟɪᴀꜱ ᴍᴇꜱᴇʀᴇᴛ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Politics


Journalist-at-large

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Politics
Statistics
Posts filter


የሶማልያ አየር ተቆጣጣሪዎች ያደረጉት እንደሆነ በተጠረጠረ ድርጊት አንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን እና ሌላ የኤምሬትስ አየር መንገድ አውሮፕላን ባለፈው እሁድ ወደግጭት አምርተው (collision course ላይ ሆነው) በመጨረሻ በፓይለቶች ጥረት እንደተረፉ ታውቋል።

ይህንን ክስተት የሶማሊላንድ ሲቪል አቪዬሽን አረጋግጦ መግለጫ ያወጣ ሲሆን በአየር መንገዶቹ በኩል ግን እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

በዚህ ዙርያ መረጃ የጠየቅኩት አንድ የአቪዬሽን ባለሙያ ክስተቱ ትክክል መሆኑን አረጋግጦ "ነገር ግን ሁለቱም አውሮፕላኖች የግጭት መከላከያ ሲስተም TCAS ስላላቸው ለፓይለቶቹ ያሳውቃቸዋል" በማለት ክስተቱ ግን አሳሳቢ መሆኑን አስረድቷል።

በተመሳሳይ በአንድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በሌላ የኳታር አየር መንገድ አውሮፕላኖች ዙርያ ተመሳሳይ ድርጊት የዛሬ ወር ገደማ አጋጥሞ ነበር።

ታድያ ይህ በአጋጣሚ ሊሆን ይችላል?

ለማንኛውም፣ የዛሬ ወር የፃፍኩትን አሁንም ላስቀምጠው ⬇️

"ብዬ ነበር ማለቱ ዋጋ ስለሌለው በአየር መንገዱ ላይ አደጋ ከመከሰቱ በፊት በረራ ወደ ሶማልያ ከማቋረጥ እስከ የበረራ አቅጣጫ መቀየር የሚደርሱ እርምጃዎችን መውሰድን ሊያጤን ይገባል ብዬ አስባለሁ፣ ቢያንስ የአለም አቀፍ የበረራ እና ሲቪል አቪዬሽን መስሪያ ቤቶች ምን እየሆነ እንደሆነ ምርመራ አድርገው እስከሚያሳውቁ። በዚህ አካሄዳቸው ሌላው ቀርቶ ሞቃዲሾ በረራ አድርጎ የቆመ የሀገራችን አውሮፕላን ላይ ምን ሊያጠምዱ እንደሚችሉ ማን ያውቃል?"

@EliasMeseret


በአንድ እና ሁለት የሶሻል ሚድያ ልጥፎች (ፖስቶች) ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የዚህ የአየር ማረፊያ ጉዳይ አንድ ማሳያ ነው

ተጎጂዋ 'በእኔ ላይ የደረሰውን ልንገርህ፣ በሌላው ተጓዥ ላይም እንዳይደገም መፍትሄ ጠቋሚ ሊሆን ይችላል' በማለቷ ያቀረብኩት መረጃ ግቡን መቷል። በሌሎች ጉዳዮች ላይም እንዲህ በይፋ ባይነገርም ለውጦች እንደሚደረጉ እንሰማለን።

ይሁንና በሌሎች በርካታ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የህዝብ እሮሮዎች ይሰማሉ፣ ስለዚህ አንዳንድ ሚድያዎች በየቀኑ ይህንን የአየር ማረፊያ ጉዳይ እየደጋገሙ ከሚዘግቡ ወደነዚህ ሌሎች ህዝብን እያስጨነቁ ያሉ ጉዳዮች ቢያዞሩ መልካም ነው ብዬ አስባለሁ።

@EliasMeseret


ከሚደርሱኝ ጥቆማዎች በመነሳት ማረጋገጥ የቻልኳቸው የቤት ፈረሳ መረጃዎች

- አያት ዞን አንድ ውስጥ ያሉ በርካታ 'ዘመናዊ' ሊባሉ የሚችሉ መኖርያ ቤቶች ስፍራው ለሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ግንባታ ስለሚፈለግ ተነሱ እንደተባሉ፣ ባለፈው እሁድ እለት በመንግስት አካላት ስብሰባ ተጠርተው ይህ በይፋ እንደተነገራቸው አረጋግጫለሁ። ይህ በአካባቢው ቤቶችን የማንሳት ጉዳይ ቀጣይ እንደሆነም ታውቋል።

- በቦሌ ክ/ከተማ በተለምዶ ጉርድ ሾላ ንግድ ባንክ አካባቢ አስፓልት ዳር ያሉ የግል ቤቶች ተለክተው አንዳንዱ ቤት እስከ ሳሎኑ፣ አንዳንዱ ደግሞ እስከ መኝታ ቤት ድረስ እንዲፈርስ መደረጉ ታውቋል። እስከ ሳሎን ድረስ ብቻ በልኬት የፈረሰባቸው ቀሪውን መኝታ ቤታቸውንና ኪችናቸውን ዛሬ ለመሸፈን መግቢያና መውጪያ በራቸውን ሲሰሩ በድጋሜ አፍርሰውባቸው እንደገና ፍቃድ አውጡ እንደተባሉ ተረጋግጧል።

#AddisAbaba

Photo: File

@EliasMeseret


ይህን መጋቢት 4/2016 ያጋራሁትን መረጃ መልሼ ላጋራው!

ቤተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ታጣቂዎችን አስጠልለዋል፣ የመሳርያ ማከማቻ ሆነዋል፣ ማሰልጠኛ ናቸው እየተባለ በከፍተኛ የወታደራዊ አመራሮች [እና ፖለቲከኞች] ጭምር እየተሰነዘሩ ያሉ የጅምላ ፍረጃዎች ውጤታቸውን እናያለን።

መረጃው ትክክለኛ ከሆነ እነዚህን ቤተ ክርስቲያናት እና ገዳማት በትክክል ለይቶ አውጥቶ ህግ ማስያዝ ያስፈልጋል፣ ነገር ግን በደፈናው "ቤተ ክትስቲያናት እና ገዳማት" እየተባለ በሀገሪቱ ዙርያ ያሉ የእምነት ስፍራዎችን እና የሀይማኖት አባቶችን ለጥቃት እያጋለጠ ይገኛል።

Mark my word... በመንግስት ሀላፊዎች እና በአክቲቪስቶቻቸው ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈፀመው የስም ማጥፋት እና የደፈና የጥላቻ ንግግር ካልቆመ ጥቃቶች፣ ግድያዎች ይቀጥላሉ።

ድርጊቱን ፈፃሚዎችም "መንግስት ራሱ መስክሮ የለ" በሚል የልብ ልብ ተሰምቷቸው ማድረጋቸውን ይቀጥላሉ።

@EliasMeseret


"አሁን ቀብር ተፈፅሟል፣ የጭካኔ ግድያ የተፈፀመባቸው ለዘመናት በአካባቢው ያገለገሉ ሰዎች ጭምር ናቸው"

ሁለት የዶዶላ ደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ከነቤተሰቦቻቸው በትናንትናው እለት መገደላቸውን በስፍራው ካሉ ሰዎች እና በደብሩ ቀደም ብለው ካገለገሉ አንድ አባት የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል።

በዚህ በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ያገለግሉ የነበሩ መሪጌታ ስምረት የተባሉ አባት ባለቤታቸውን እና ሁለት ልጆቻቸውን፣ እንዲሁም ዲያቆን ዳንኤል የተባለ አገልጋይ ከነባለቤቱ እና ሌላ አንድ ሰው ጋር በድምሩ ሰባት ሰው እንደተገደለ እነዚህ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

"አሁን ቀብር ተፈፅሟል፣ የጭካኔ ግድያ የተፈፀመባቸው ለዘመናት በአካባቢው ያገለገሉ ናቸው። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ምሽት ሶስት ሰአት ገደማ ነው" ያሉኝ ምንጮች ከዚህ በፊትም በጥቅምት 2012 ዓ.ም ብዙ ሰዎች ተግድለው እንደነበር አስታውሰዋል።

ነፍስ ይማር።

@EliasMeseret


ከፒያሳ ተነሺዎች የሚደርሱኝ ሆረር ታሪኮች እንደቀጠሉ ነው!

መቼም ከተማ ሳይዘምን፣ ሳይቀየር እና ሳይነካ የትም አለም ላይ አይቆይም። ዱባይ የዛሬ 30 አመት ብትታይ የዛሬውን ትሆናለች ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ነገር ግን፣

- ለልማት እና ለከተማ ለውጥ የሚነሱ ሰዎች ለምን ብዙ ግዜ 'ሰለባ' ይሆናሉ? ስንቶች ግቡበት ተብሎ የተሰጣቸውን ለማመን የሚከብድ 'ቦታ' (ቤት ለማለት አልደፍርም) በቴሌግራም ልከውልኛል፣ ታድያ እነዚህ ቤተሰቦች ህፃናትን እና አቅመ ደካሞችን ይዘው ውሀ፣ መብራት፣ ሽንት ቤት፣ መንገድ... ወዘተ ያለሌበት ቦታ እንዴት ይኑሩ?

- ተነሱ ሲባል በሳምንታት፣ ካለም በወር ውስጥ ለምን ይሆናል? ቢያንስ ስራም ሆነ ኑሮ ማመቻቸት የሚችል ፋታ እንዲያገኝ ለምን ግዜ አይሰጥም? ጥድፊያው እና እሽቅድድሙ ከምን እና ከማን ጋር ነው? የከተማ ልማቱ፣ እድገቱ እና ማማሩ ለማን ነው? ለህዝብ ከሆነ ህዝብን ያማከለ ለምን አይሆንም?

በዚህ ዙርያ አቶ ሙሼ ሰሙ ባሰፈሩት አንድ ፅሁፍ ይህን ብለዋል፣

- በኮሪደር ልማቱ ምክንያት ከ200 ሺህ ያላነሱ ነባር ይዞታዎችና ሱቆች እንደሚፈርሱ ይገመታል። ይህ ማለት ከነባር ባለ ይዞታዎቹና ከተከራይ ባለሱቆች ጋር መስተጋብር ፈጥረው የሚሰሩ ደላሎች፣ ጥበቃዎች፣ ጽዳት ሰራተኞች፣ ተቀጣሪ የምግብና መጠጥ አገልግሎት ሰጭዎች ሲደምሩበት ቁጥራቸው ከ500 ሺህ ሊበልጥ ይችላል። ቤተሰቦቻቸውንና ጥገኞቻቸውን ስናክልበት ደግሞ ከ1.5 ሚሊየን በላይ ሊሆኑ ይችላሉ።

ግድ የለም... ሰው፣ ሰውነት እና ሰብአዊነት ከየትኛውም ልማት ይቀድማል።

ፎቶ: የጥንቷ ፒያሳ

@EliasMeseret

51k 0 102 1.8k

የትዊተር (ኤክስ) አካውንት እንዳለኝ ለጠየቃችሁ፣ ይህ 181,000 ተከታታይ ያለው አካውንቴን መቀላቀል ትችላላችሁ: https://x.com/EliasMeseret?s=09

መልካም ሰንበት።


ይህን ኮሚክ አሁን ገና ማየቴ ነው...!

ማስለቀቂያ ብር እንደተከፈለ ያለው ማረጋገጫስ ምን ይሁን?

እንደው ህዝቡን እንዴት ብታስቡት ነው?

@EliasMeseret


ለስራ ከቤታቸው ወጥተው ለበርካታ ቀናት ተይዘው የቆዩት እነዚህ ወገኖች ተለቀው አዲስ አበባ መድረሳቸው ተሰምቷል

ትላንት ማምሻውን እንደተለቀቁ እና በሠላም ተጉዘው አዲስ አበባ ሲደርሱ የዞኑ ዋና አስተዳዳር አቶ ብርሃኑ ኩናሎ በስፍራው ሆነው ተቀብለዋቸዋል ብሎ ዞኑ አስታውቋል።

ወደ ስፍራው ያቀኑት ለስራ እንደነበር የሚያሳዩ ደብዳቤዎች እና መረጃዎችን ከዚህ ቀደም አጋርቼ ነበር፣ በርካቶች በወቅቱ ሊቀበሉት ባይፈልጉም።

ለማንኛውም እንኳን ነፅ ሆናችሁ።

@EliasMeseret


30 ሺህ ሰው ያሳተፈው 'ብኩን' ፊልም!

ከትግራይ እስከ አማራ እና አፋር ክልሎችን አዳርሶ ቢያንስ 600,000 ሺህ ህዝብ እንዳለቀበት የሚገመተው የሰሜኑ ጦርነት ዳፋ ገና ተነግሮ እንኳን አላለቀም።

በውጊያ ወቅት ሞተው አስከሬናቸው ገና ያልተቀበሩ በርካቶች አሉ፣ የአካል ጉዳተኞች ዊልቼር ሳያገኙ መሬት ለመሬት እየዳሁ እያየን ነው፣ የተደፈሩ ሴቶች ስነ ልቦና ገና አልተጠገነም፣ የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለመገንባት የሚደረገው እንቅስቃሴ ገና ከመሬት አልተነሳም፣ የሰላም ስምምነቱን ማፅናት ላይ እንኳን ከሰሞኑ እንደሰማነው ውይይት ገና እየተደረገ ነው።

በዚህ ሁሉ መሀል በታንክ፣ ጀት፣ መድፍ፣ ክላሽ እና RPG የታገዘ በጭካኔ የተገዳደልንበትን ፊልም በ30 ሺህ ህዝብ አጅቦ የሚተርክ ፊልም በተለይ አሁን ባለንበት ወቅት ምን ሊጠቅመን ነው?

ዳግም ግጭት የመቀስቀስ ሙከራ ወይስ ሌላ? በዚህ ፊልም እናት፣ አባት፣ እህት፣ ወንድም... ወዘተ ለዘላለም ያጡ ወገኖች አሟሟታቸውን በፊልሙን ቢመለከቱ ምን ይሰማቸዋል?

ከማውቃቸው ሰዎች ተደጋግሞ እንደሰማሁት የፊልሙ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ፊልሙ በብዙ መቶ ሚልዮን ብሮች እንደወጣበት፣ በመንግስት በኩል የቁሳቁስ እና የሰው ሀይል ድጋፍ ተደርጎለት እንጂ ተጨማሪ ብዙ መቶ ሚልዮን ብሮች ሊያስወጣ የሚችል ፊልም እንደሆነ ተናግሯል።

ሌላው ቀርቶ በቅርቡ ወደ አሜሪካ ፊልሙን ለትርዒት ይዞ በሄደበት ወቅት "ፊልሙን እዚህ አሜሪካ ተቃውመው የሚንከባለሉ ሰዎች ይኖራሉ" ሲል እንደነበር በስፍራው የነበሩ ሰዎች አጫውተውኛል።

ጊዜውን ያልጠበቀ 'ብኩን' የሆነ የ image ግንባታ ፊልም ብዬዋለሁ። Timing የሚባል ነገር ወሳኝ ነው።

@EliasMeseret




#FactCheck ማምሻውን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ- ኃይል በአዲስ አበባ እና አዋሳኝ አካባቢዎች በትጥቅ የታገዘ ሁከት እና ብጥብጥ ለመፈፀም በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 50 ተጠርጠሪዎች በቁጥጥር ሥር  መዋላቸውን አስታውቋል።

የመንግስት ሚድያዎች ከእነዚህ ተጠርጣሪዎች ፎቶ ጋር የተለያዩ የጦር መሳርያዎች ፎቶዎችን አብረው አያይዘው አውጥተዋል።

ሁለቱ ምስሎችን reverse image search በማድረግ ለማጣራት ስሞክር የቆዩ ምስሎች መሆናቸውን ለመመልከት ችያለው።

አንደኛው ፎቶ የዛሬ ስምንት አመት የቱርክ የፀጥታ ሀይሎች የፍተሻ ቦታ ተደብቆ ያገኙት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የዛሬ ሁለት አመት በራሳቸው የሀገራችን የመንግስት ሚድያዎች ከአይኤስ የሽብር ቡድን ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ መሳርያዎች እንደሆኑ ተደርጎ ቀርቦ ነበር።

የሁለቱም ቆየት ያሉ ምስሎች ውጤት ተያይዟል።

@EliasMeseret


እውቁ የሰርጀሪ ህክምና ባለሙያ ዶክተር በሀይሉ ሀይሉ እሁድ ጠዋት አዲስ አበባ ውስጥ የጠዋት ሩጫ በማድረግ ላይ ሳሉ ግድያ እንደተፈፀመባቸው ታውቋል።

ዝርዝር መረጃውን ከፖሊስ እንጠብቃለን።

ነፍስ ይማር፣ ዶክተር።

@EliasMeseret


ምን እያለን ነው?

በሚሰራበት ተቋምም ሆነ በግሉ የህዝብን ብሶት እና ችግር ለአመታት ትንፍሽ ሳይል ቆይቶ አሁን ደግሞ ችግሩ ታምኖበት ባለ ጉዳይ ላይ ቀጥተኛ ባልሆነ መልኩ ወደዚህ የሰነዘረው ትችት የፈሪ ዱላ ሆነብኝ።

የዛሬ ስድስት እና ሰባት አመት ከነበረው የኦሮሞ ወጣቶች ተቃውሞ እና እንቅስቃሴ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በሀገር ውስጥ ባሉ ጉዳዮች ላይ በሚፅፉ በተለይ የውጭ ሀገር ጋዜጠኞች ላይ ማስፈራርያ በማድረስ የሚታወቀው ይህ ሰው...

ከንግድ ባንክ የሚበልጥ ፎቅ ከሚያሰራው GTNA ሚድያ 😅 እስከ ባለሀብቶች 'እየደወለብን' ቅሬታ ብዙ ማለት ይቻላል። ሰከን ማለት ሳይሻል አይቀርም፣ ከግል ጥቅም የህዝብ ድምፅ ይቀድማል።

@EliasMeseret


"ውሸት ነው" ብሎ ማለፍ ለዛሬ ሊሰራ ይችላል፣ ነገ ግን እውነታው ሲወጣ ሀፍረት ነው

ቢሾፍቱ ስለተከሰተ አንድ የእገታ ድርጊት እና በለቡ ወረዳ 1 በካድሬዎች ስለሚከናወን ጉዳይ በትናንትናው እለት ባቀረብኳቸው ሁለት መረጃዎች ዙርያ የተለያዩ አስተያየቶች ደርሰውኛው።

- በቢሾፍቱ ኤግዚቢሽን ያዘጋጁ ሰዎች ታግተው ተወስደው ከአምስት ቀን በኋላ ገንዘብ በትራንስፈር እንዲያደርጉ ተገደው በአምስት ቀናቸው መለቀቃቸውን "ውሸት ነው" ያሉ በርካቶች አሉ። እርግጥ ነው የከተማው ስም ከድርጊቱ ጋር መነሳቱ ደስ ያላለው ሊኖር ይችላል፣ እውነት ግን አንድ ናት። ምናልባት አሳጥሬ ስላቀረብኩት ግርታ ከፈጠረ ማጣራት ለሚፈልግ ማንኛውም አካል ተጨማሪ መረጃ ይኸው: ድርጊቱ የተፈፀመው የካቲት 19 ቀን ከቀኑ 11 ሰዓት ገደማ ሲሆን ታግተው የተወሰዱት ደግሞ ቁጥራቸው 13 የሆኑ በአብዛኛው ሴቶች የሆኑ በእደጥበብ ሙያ የተሰማሩ ነጋዴዎች ናቸው። ድርጊቱ እንደተፈፀመ አዘጋጆች ጉዳዩን ወዲያው ለቢሾፍቱ ፖሊስ እና ለከተማ አስተዳደሩ አመራሮች አሳውቀዋል፣ ይህ ማለት የከተማው አመራር ጉዳዩን በደንብ ያውቃል። በተጨማሪም "ለደህንነት ሲባል ቀድማችሁ አሳውቁ" ስለሚባል ለፖሊስ ቀድመው ስለ ኤግዚቢሽኑ አሳውቀዋል። ድርጊቱ ሲፈፀም ታጋቾቹ ጩኸት ስላሰሙ በሆራ ሀይቅ አቅራቢያ የነበሩ በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተመልክተዋል። አንድ የኦሮሚያ ክልል የስራ ሀላፊ በስርዐት ተጨማሪ መረጃ ጠይቀውኝ ከድርጊቱ ሰለባዎች የሰማሁትን እና የማውቀውን ሰጥቻቸዋለሁ። ይኸው ነው።

- የለቡ ካድሬዎቹ እንኳን "ስክሪንሾት" እንደምናስደርግ ለምን አወቅክብን አይነት ድርቅና ነው። የሚገርመው ደግሞ የፃፍኩት መረጃ ስር በኮመንት ተሳድበው በውስጥ መስመር ግን "ካልተቃወምን ተጠያቂ ስለምንሆን ነው፣ አንተ ገፅ ላይ የተሳደብነውን ራሱ ስክሪንሾት አርገን ለበላይ አመራር (ጠርናፊ) ልከናል" ያሉኝ በርካታ ናቸው።

ይኸው ነው፣ "ውሸት ነው" ብሎ ማለፍ ለዛሬ ሊሰራ ይችላል፣ ለነገ ግን ሀፍረት ነው። በቦሌ ኤርፖርት በአንዲት ተጓዥ ላይ የደረሰውን መረጃ ሳቀርብ እንኳን ዛሬ እውነታው ሊወጣ "ስም ማጥፋት ነው፣ ከውጭ ሀይሎች ጋር በመተባበር..." ምናንም ተብሎ አልነበር?

መልካም ምሽት።

@EliasMeseret




የዛሬ አስር ዓመት በዛሬው ቀን በህዳሴ ግድብ ጋዜጠኞች ጉብኝት እያደረግን እንደነበር ፌስቡክ አስታወሰኝ

ኢ/ር ስመኘው በቀለ በዛ እጅግ ከፍተኛ ሙቀት ውስጥ በርካታ ስፍራዎች በራሳቸው ተሽከርካሪ አሳፍረው እየወሰዱን በደስታ እና ኩራት ሲያስረዱን "ምን ያህል ስራቸውን እና ሀገራቸውን የሚወዱ ጀግና ናቸው" አስብሎኝ ነበር።

የእሳቸው ነገር ተዳፍኖ እንደማይቀር ተስፋ አደርጋለሁ፣ አባታቸው አባ በቀለም በህይወት እያሉ ሲመኙት የነበረ ጉዳይ ነው።

@EliasMeseret


ጥቆማ ለሚመለከተው አካል!

አንዳንድ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ቲክቶክ ላይ ዩኒፎርም ለብሰው ላይቭ ገብተው ሲሰዳደቡ፣ ያሉበትን አካባቢ እየጠቀሱ ሲያወሩ እና ከሌሎች ሰዎች ጋር ሲጣሉ ማየት እየተለመደ ነው (የተወሰነው ስክሪንሾት ላይ ይታያል)።

ግርታ የፈጠረባቸው በርካቶችም ይህን መረጃ ሲያደርሱኝ ቆይተዋል፣ እኔም መረጃውን ለመከላከያ በኢሜይል አድራሻው ልኬ ነበር፣ ጉዳዩ ግን አሁንም ቀጥሏል።

ይህ ከወታደራዊ ዲሲፕሊን አንፃር ትክክል ስላልመሰለኝ ጥቆማ ማቅረብ ወደድኩ።

@EliasMeseret


በካሜራ እገዛ በቁጥጥር ስር ውለዋል!

ያቀረብኩት መረጃው ውሸት እንደሆነ ጠቅሰው ሲያጣጥሉ ለነበሩት ይድረስ። እውነት ሊቆይ ይችላል እንጂ መውጣቱ አይቀርም።

Good job, Ethiopian Airlines

@EliasMeseret


ቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ ዳርቻ የተከሰተ ድርጊት!

ድርጊቱ የተፈፀመው የዛሬ ሁለት ሳምንት በቢሾፍቱ ሆራ ሀይቅ ዳርቻ ነው። በርካታ በጥቃቅን እና አነስተኛ የእደጥበብ ምርት እና ሽያጭ ላይ የተሰማሩ አብዛኞቹ ሴቶች የሆኑ ዜጎች በአንድ ጃማይካዊት አስተባባሪነት አነስተኛ ባዛር/የንግድ ትርኢት ያዘጋጃሉ።

ከቀኑ 11 ሰአት ሲሆን የታጠቁ ሰዎች ይመጡና እቃዎቻቸውን አይሱዙ መኪና ላይ ይጭናሉ፣ ሰዎቹንም እየመቱ በጫካ ውስጥ ሁለት ሰአት የፈጀ የእግር ጉዞ አድርገው ወስደው ወደ "ካምፓቸው" አደረሷቸው።

በዚህ ካምፓ ለአምስት ቀን ተይዘው ከቆዩ በኋላ ገንዘብ ይጠይቃሉ፣ ገንዘብ የለንም ሲሉ ግን መታወቂያዎቻቸውን በመቀበል በቀጥታ ወደ ባንኮች እየደወሉ ያላቸውን የገንዘብ መጠን አረጋገጡ፣ ከዛም በግድ ገንዘብ ትራንስፈር አስደረጓቸው።

ይህን ከፈፀሙ በኋላ በአምስተኛው ቀን ከለሊቱ 8 ሰአት ለቀዋቸው በድጋሜ 2 ሰአት በእግራቸው ተጉዘው ቢሾፍቱ ተመልሰዋል።

@EliasMeseret

20 last posts shown.