EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter




የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ (ዐቢይ ጾምን) አስመልክቶ የቅዱስ ፓትርያርኩ መልዕክት::

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤

በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ ፤

የዲያብሎስን የፈተና ወጥመዶች በጣጥሶ በድል ኣድራጊነት የተገለጠው ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ አደረሰን አደረሳችሁ!

“አኮ በኅብስት ክመ ዘየሓዩ ሰብእ አላ በኵሉ ቃል ዘይወፅእ እምኣፉሁ ለእግዚአብሔር፦
ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” (ማቴ.፬÷፬)

ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውነ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡

በአርባዎቹ ቀናት ሁሉ በቀንም ሆነ በሌሊት ምንም አልበላም ነበር፣ ካርባ ቀንም በኋላ ተራበ፤ በመብል ስውን ከእግዚአብሔር ጋር ማጣላት ልማዱ የሆነ ዲያብሎስም መራቡን ኣይቶ ለምን ትራባለህ?

እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ ይሁነ ብለህ እዘዝና ብላ፧ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለህምን? ይህንን ማድረግ ኣያቅትህም ብሎ በመብል ምክንያት የሱ ታዛዥ እንዲሆን ፈተነው::

በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም” የሚል ነበረ፤

ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆነን ኣሳየ፣ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፣ ግን አልተሳካለትም፤

በመጨረሻም ጌታ “ሑር እምድኅሬየ ሰይጣን፣ ሰይጣን ከኋላዬ ወግድ" ብሎ እኩይ ተግባሩን ውድቅ ኣድርጎበታል፣ እሱም ተስፋ ቆርጦና በጌታችን መንፈሳዊ ልዕልና ተሸንፎ ሂዶአል::

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ከጌታችን ጾም የምንወስደው ብዙ ትምህርት አለ፣ ከሁሉ በፊት ሰው በሕይወት መኖርየሚችለው በእንጀራ ብቻ ኣይደለም ብሎናል፣ ይህ ኣባባል በሕይወት ለመኖር እንጀራ አያስፈልግም ማለት ኣይደለም ፧

ሕይወትን ማኖር የሚቻለው በእንጀራ ብቻ እንደ ሆነ አድርገን እንዳናስብ ግን ቃሉ ያስተምራል ይህም በዓለማችን በየዕለቱ የምናውቀው ሓቅ ነው፤ ብዙ ሰዎች እንጀራን ሳያጡ በየዕለቱ ሕይወትን ያጣሉ፤ ምክንያቱም በሕይወት ለመኖር የእግዚአብሔር ቃልም እንጂ እንጀራ ብቻው በቂ አይደለምና ነው::

ዓለማት ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል ሁነ ተብለው በቃሉ እንደተፈጠሩ፣ በቃሉም ጸንተው እንደሚኖሩ ኋላም በቃሉ እንደሚያልፉ ሁሉ የስው ሕይወትም በዚህ ቃል ይወሰናል፤

እንጀራ ኖረም አልኖረ ቃሉ በቃ ካለ ያበቃል፣ ኑር ካለ ደግሞ እንጀራ ባይኖርም ይኖራል፤ ስለዚህ በሕይወታችን ወሳኝ ሥልጣን ያለው የእግዚአብሔር ቃል እንጂ፣ እንጀራ ብቻ አለመሆነ ጌታችን በዚህ አስተምሮናል::

ከዚህም ሌላ የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባርኣሳይቶናል፣ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፣ አለመሆነንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ ልዕልና ነው ማለት ነው::

ይህም ማለት በእግዚአብሔር የተከለከሉትን ግብረ ኃጣውእ እንድንፈጽም ዲያብሎስ ኅሊናችንን ሲገፋፋው፣ ያን ጊዜ ዲያብሎስ ሊፈትነን እየከጀለ እንደሆነ መንቃት ያስፈልገናል::
ጌታችን እንዳሳየንም ለክፉው ግብረ ኃጢኣት የእሺታ መልስ ሳይሆን የእንቢታ ግብረ መልስ መስጠት ይገባናል ማለት ነው፤ ይህንን ኣቅዋም የሕይወታችን ቀዋሚ መርሕ ካደረግን፣ ዲያብሎስ እየተሸነፈ፣ እኛም እያሸነፍን እንኖራለን፣ ይህንን ስንለማመድ ሓሳባችን ወይም መንፈሳችን ከዲያብሎስ በላይ የላቀና የተራቀቀ ይሆናል !

ዲያብሎስ ረቂቅ ነው፤ የሚጣላንም ረቂቁን አእምሮኣችን በመጠቀም ነው: እኛም እሱን መዋጋትና ማሸነፍ የምንችለው ረቂቁ ኣእምሮኣችን ከሱ የላቀና የረቀቀ ኣድርገን በመጠቀም መሆኑን መገንዘብ ይገባል ይህን ካደረግን እሱ በኛ ላይ አቅም ኣይኖረውም::

• የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

ጾመ ኢየሱስ እያልን በየዓመቱ የምንጾመው የታላቱ ጾማችን ዓላማ ዲያብሎስን ለማሸነፍ ነው፤ የዲያብሎስ ማሸነፊያ ስልት የመልካም ጎሊና ልዕልና ነው!

ሰውነታችን በመብልና በመጠጥ ሊደነድን መልካም ኅሊና በውስጣችን ዓቅም ያጥረዋል፣ መልካም ኅሊና ሲያጥረን ዲያብሎስ ዘው ብሎ ይገባና ወደ ክፉ ኅሊና፣ ከዚያም ወደ ግብረ ኃጢኣት ይወስደናል፣ በዚህ ጊዜ እኛ ተሸናፊዎች እሱ ኣሸናፊ ይሆናል፣

በአንጻሩ ደግሞ ስውነታችን ከመብልና ከመጠጥ ሊለይ መልካም ኅሊና፤ ቍጥብነት፣ ማስተዋልና ማመዛዘን በውስጣችን ትልቅ ጉልበት ያገኛሉ :

እነሱ ጕለበቱ ማለት ዲያብሎስ መግቢያ አጣ ማለት ነው፤ እሱ ካልገባ ግብረ ኃጢኣት አንፈጽምም፣ በዚህ ጊዜ ዲያብሎስ ተሸናፊ እኛ ኣሽናፊዎች እንሆናለን፤ ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ ነው::

ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን፣ እንግዲህ በወርኃ ጾም ከመልካም ኅሊና የሚመነጭ መልካም ስራ ማከናወን ግድ ይለናል።

ምክንያቱም ጾምን የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፤ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርት፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፣ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፤ ጥላቻ፤ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀርልናደርግ ነው!

በዚህ መንፈስ ጾሙን ከጾምን ጾማችን ግቡን መትቶአል፤ ዲያብሎስም ተሸንፎአል ማለት ነው፤ ስለሆነም በዚህ መንፈስ ጾሙን ልንጾም ይገባል፡።

በመጨረሻም-

ጠርጎ ጾሙን የተራበውን በመመገብ የተራቈተውን በማልበስ በኃላፊነት ያለን የኅብረተሰብ መሪዎችም ፍትሕንና እኩልነትን በማስፈንና ከነገሮች ሁሉ በፊት ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ በመስጠት ጾሙን እንድናሳልፍ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን::

መልካም ወርኀ ጾም ያድርግልን

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ

ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ

ተክለሃይማኖት

የካቲት 12 ቀን 8977 ዓ.ም




📢 ቀጣዩን የትንሳኤ ጉዞዎን ወደ እየሩሳሌም ከጳጉሜን ጋር ያስይዙ✨✨✨
ከቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት ከርእሰ ሊቃውንት አባ ገ/ኪዳን ግርማ እና ከመምህር ብርሃኑ አድማስ ጋር አስደሳች ጉዞ እንዳያመልጥዎት

🟠 የጉዞ ምዝገባ ቀድሞ ስለሚያልቅ ቀድም ብለው መመዝገብዎን እንዳይዘነጉ 🟠

ለበለጠ መረጃ
📍 22 አክሱም ሆቴል ጎን ኮሜት ህንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ እንግኛለን፡፡
📞 ስልክ፡ 0942111213 | 0930796578 | 0116686063 | 0903131313


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር መምህራንን በማፍራትና ድሆችን በመርዳት ላይ ትኩረት ያደረገ ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ የማኅበሩ ዋና ሥራአስኪያጅ መምህር ኤልያስ ሙላቱ ገለጹ።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የኢኦተቤ ቴቪ ≠EOTC TV


📢 ቀጣዩን የትንሳኤ ጉዞዎን  ወደ እየሩሳሌም ከጳጉሜን  ጋር ያስይዙ✨✨✨
ከቤተክርስቲያናችን ሊቃውንት ከርእሰ ሊቃውንት አባ ገ/ኪዳን ግርማ እና ከመምህር ብርሃኑ አድማስ ጋር አስደሳች ጉዞ እንዳያመልጥዎት

🟠 የጉዞ ምዝገባ ቀድሞ ስለሚያልቅ ቀድም ብለው መመዝገብዎን እንዳይዘነጉ 🟠


ለበለጠ መረጃ
📍  22 አክሱም ሆቴል ጎን ኮሜት ህንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ እንግኛለን፡፡
📞 ስልክ፡ 0942111213 | 0930796578 | 0116686063 | 0903131313









17 last posts shown.