Esat tv Official (EMS)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ኢሳት የኢትዮጵያ #አይን እና #ጆሮ
መሳይ መኮንን

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


Join our telegram channel👇

https://t.me/RestoreTech/121


በአባቷ የቀብር ስነስርዓት ላይ ለጓደኛዉ የታገቢኛለሽ ወይ? ጥያቄ ያቀረበዉ ግለሰብ አነጋጋሪ ሆኗል !! 🙆‍♂

የጉድ ሀገር እንዲሉ በአባቷ ቀብር ላይ ለጓደኛዉ ቀለበት ያሰረዉ ደቡብአፍሪካዊ ከሀገሩ እንዲሁም ከሌሎች የዓለማችን ክፍል ነዋሪዎች ዘንድ ከባድ ትችትን እያስተናገደ ይገኛል፡፡

በአባቷ የቀብር ስነስርዓት ላይ ተንበርክኮ ታገቢኛለሽ ብሎ ሲጠይቃት የሚያሳየዉን አስደንጋጭ ቪድዮ የቀብር ስነስርዓቱ ላይ የተገኘች አንዲት ሴት ቀርጻ ወዲያዉ በቲክቶክ የማህበራዊ መገናኛ ላይ ከለቀቀች በኋላ፤ እጅግ በርካታ ሰዎች እንደተቀባበሉት እና ብዙ ተጠቃሚዎችም ትችቶችን እንደሰነዘሩበት ኦዲቲ ሴንትራል ነዉ የዘገበዉ፡፡

ቪድዮዉ ላይ የሚታየዉ የአባቷ አስከሬን ሳጥን ፊት ቁጭ ብላ በማልቀስ ላይ የምትገኘዉ ጓደኛዉን ተንበርክኮ የታገቢኛለሽ ጥያቄ ሲያቀርብ ነዉ። ማይክራፎን በመጠቀምም ንግግር ያደርግ እና የሌሎች ሹክሹክታ እና ተቃዉሞ አንዳች ሳያግደዉ ቀለበት አዉጥቶ በጣቷ ላይ ሲያጠልቅ ያሳያል፡፡

ጓደኛዉ በፍጹም ድንጋጤ ዉስጥ ሆና የምትታይ ሲሆን ምንም ዓይነት ምላሽ ባለመስጠቷም የጋብቻ ጥያቄዉን ትቀበል አትቀበል ምንም ግልጽ የሆነ ነገር የለም፡፡ በቦታዉ እየሆነ ያለዉን ነገር በስርዓቱ ለማጣጣም በትክክለኛዉ የስሜት ሁኔታ ላይ እንዳልነበረችም በግልጽ ይታይ ነበር፡፡

Via ©oddity central

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official

69.3k 0 255 122 608

የኢ.ኤም.ኤስ የእለተ እሁድ አጫጭር መረጃዎች

1. በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይጀመር የኢትዮጵያ ሰብዓው መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አሳሰቧል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን “በፌደራል መንግስት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል” ዳግም እየተካረረ የመጣው የጦርነት ስጋት እንዳሳሰበው ባወጣው መግለጫ ገልጿል። ተቋሙ በመግለጫው እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ዳግም ጦርነት እንዳይጀመር ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ አሳስቧል።
ከ19 ወራት በፊት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በርካቶች ለተለያዩ አስከፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደተጋለጡ ያወሳው ኢሰመኮ አሁንም ዳግም ወደ ጦርነት ለመግባት እያደገ የመጣው መካረር ሊቆም እንደሚገባ ገልጿል።

2. ሕንድ በግዛቷ የሚመረት ስንዴ ወደ ውጭ ሀገራት እንዳይወጣ እገዳ መጣሏን የሀገሪቱ ዜና ወኪል ዘግቧል።ሆኖም አዲሱ የስንዴ የውጭ ሀገራት እግድ ከዚህ በፊት በሂደት ላይ የነበሩ የስንዴ ግብይቶችን እንደማይመለከት አስታውቃለች። የአውሮፓ ሀገራት በበኩላቸው የሕንድን ውሳኔ የኮነኑ ሲሆን ውሳኔው በዓለም የስንዴ ገበያ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል ሲሉ አክለዋል። ሕንድ በስንዴ ሽያጭ ላይ እገዳ መጣሏ በተለይም በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ምክንያት የስንዴ አቅርቦት የተቋረጠባቸው የአፍሪካ እና እስያ ሀገራት ሕንድን እንደ አማራጭ ለመጠቀም አስበው ነበር። በሕንድ አንድ ቶን ስንዴ በ25 ሺህ ሩፒ ወይም በ320 ዶላር የሚሸጥ ሲሆን፤ ወደ ውጪ ሀገራት አዲስ የሚደረጉ የስንዴ ግብይቶችን በሀገር ውስጥ የምግብ እጥረት እንዳይከሰት በሚል የስንዴ ምርት ከሀገር እንዳይወጣ እገዳ ጥላለች።

3. የፊንላንድ መንግስት አሜሪካ መራሹን የኔቶ ጥምር ጦር መቀላቀል እንደሚፈልግ በይፋ አስታውቋል። የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳውሊ ኒኒስቶ ከካቢኔያቸው ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ ፊንላንድ የኔቶ አባል ለመሆን በምታቀርበው የአባልነት ጥያቄ ላይ ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል። ይህ የካቤኒው ስምምነት ለመጽደቅ የፓርላማ ይሁንታ ማግኘት ይኖርበታል ተብሏል።

4. ጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ስታካሂድ ውላለች፡፡ ከማለዳ ጀምሮ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እየተካሄደ ይገኛል። ይህ የዛሬው ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ለ6ኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን ረጅም ጊዜ ሲጠበቅ ነበር። ቀጥተኛ ባልሆነው በዚህ ምርጫ ላይ 30 በላይ እጩዎች እየተወዳደሩ ይገኛሉ።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


እስካሁን ያልጠሩ ዩኒቨርስቲዎች ችግራቸው ምንድነው ?

1, ዲላ ዩንቨርስቲ (በቅርቡ ይጠራል )

2, ወሎ ዩኒቨርስቲ ( በጦርነቱ ምክንያት መጥራት አልቻለም፣ ሁሉ ነገር አልተስተካከለም ተመራቂ ተማሪዎችን ገና አላስመረቀም)

3, ወልዲያ ዩኒቨርስቲ ( በጦርነቱ ምክንያት መጥራት አልቻለም፣ ሁሉ ነገር አልተስተካከለም )

4, ደባርቅ ዩኒቨርስቲ (አከባቢ ላይ ያለው የፀጥታ ሁኔታ) & በቅርቡ

5, ደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ (አከባቢ ላይ ያለው የፀጥታ ሁኔታ)

6, ጋምቤላ "(አከባቢ ላይ ያለው የፀጥታ ሁኔታ)

7, ቀብረ ዳር ዩኒቨርስቲ (ማወቅ አልቻልንም)

8, ጅንካ ዩኒቨርስቲ (ታገሱ)

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


❗️❗️❗️የምስራቅ አማራ ፋኖ ማሳሰቢያ!

«መንግስታዊ መዋቅራዊ ፀባጫሪነት ቀጣዩ የህዝባችን
የህልውና ፈተና እንዳይሆን ስጋት አለን። ሰሜን ወሎ ላይ
ይኸ እንዲሆን አበክሮ የሚሠራ ኃይል አለ። ለሚፈጠረው
ሁከት ና ግርግር ኃላፊነቱን የሚወስደው መንግስት ነው።»

የምስራቅ አማራ ፋኖ!!!

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


ማስታወቂያ

የመቁረጫ ነጥብ በሟሟላት በትምህርት ሚኒስቴር በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ 1ኛ ዓመት ተማሪዎች በሙሉ ከግንቦት 8-10 ባሉት ቀናት ብቻ በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡና ትምህርት እንድትጀምሩ ዩኒቨርስቲው አስታውቋል።

ስለሆነም በተጠቀሰው ቀን ምዝገባ እንድታደርጉና ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ እናስታውቃለን።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


ከማኅበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ማሳሰቢያ ተሰጠ

ግንቦት 6/2014 (ዋልታ) በየጊዜው እየተባባሰ ከመጣው የማኅበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ሰለባ ላለመሆን ዜጎች ማንነታቸው ከማይታወቁ ግለሰቦች ጋር በበይነመረብ በሚደረጉት ግንኙነት ላይ ጥንቃቄ እንዲወስዱ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት እና የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ጥምር ግብረ ኃይል አሳሰበ።

ግብረ ኃይሉ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የሚፈጸሙ የማጭበርበር ወንጀሎች በይዘትም ሆነ በአፈጻጸም ስልታቸው ውስብስብ እየሆኑ ከመምጣታቸው ባሻገር በርካታ ግለሰቦች የጉዳቱ ሰለባ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።

የማጭበርበር ወንጀሎቹ በዋናነት የሚፈጸሙት በውጭ አገር የሚኖሩ፣ በቱሪስት ቪዛ ወደ አገር ውስጥ በሚገቡ የተለያዩ ሀገራት ዜግነት ባላቸው ግለሰቦች መሆኑንም በመግለጫው ተጠቅሷል፡፡

ኢትዮጵያውያን በስፋት የሚጠቀሟቸው ማህበራዊ ሚዲያዎች ማለትም ፌስቡክ፣ ኢ-ሜይል፣ ዋትስአፕ፣ ቴሌግራም፣ ኢንስታግራም፣ ኢሞና ቫይበርን በመጥለፍና ወዳጅ መስሎ በመቅረብ ወንጀሎቹ እንደሚፈጸሙ ከተደረገው ክትትል ማወቅ እንደተቻለም ተገልጿል።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን የዩኤኢ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ!

ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች (ዩኤኢ) ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ፡፡የአቡ ዳቢው ልዑል አልጋ ወራሽ፤ ወንድማቸው ሼክ ኸሊፋ ቢን ዛይድ ትናንት አርብ ማረፋቸውን ተከትሎ ነው የዩኤኢ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡት፡፡የሃገሪቱ ጠቅላይ ምክር ቤት ነው ሼክ መሃመድን ፕሬዝዳንት አድርጎ የመረጠው፡፡ ሼክ መሃመድ ምክር ቤቱ እምነት አድሮበት ለሰጣቸው ትልቅ ኃላፊነት አመስግነዋል፡፡ሼክ መሃመድ የዩኤኢ ጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ አዛዥ መሆናቸው ይታወሳል፡፡

[Alain]

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


መንግስት ለአምራች ኢንደስትሪው የመሬት ፖሊሲውን ቀየረ!

በዚህም መሰረት ለአዳዲስ አምራች ኢንደስትሪዎች የተመቻቸ መሰረተ ልማት ባላቸው የኢንደስትሪ ፓርኮች ውስጥ ቦታ ይመቻቻል ተብሏል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እንዳሉት አሁን ላይ ለሚታየው ምቹ የቢሮክራሲ ጥያቄ እና ብልሹ አሰራር የመሬት ጉዳይ ዋነኛው ነው፡፡

በመሆኑም ይህን ችግር ለመቅረፍ ከዚህ በኋላ በኢንደስትሪው ዘርፍ ለመሰማራት ለሚፈልግ ኢንቨስተር በከፍተኛ ሃብት በተገነቡ ግን በበቂ ባልተያዙ የኢንደስትሪ ፓርኮች ቦታይመቻቻል ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ከዚህ በኋላ በአዲስ አበባም ሆነ በክልሎች ለኢንደስትሪው ዘርፍ መሬት አይቀርብም፤ ለብልሹ አሰራር በር አይከፈትም ብለዋል፡፡ባለፉት ጥቂት አመታት ብቻ 13 የኢንደስትሪ ፓርኮች እና ሶስት የግብርና ማቀነባበሪያዎች የተገነቡ ቢሆንም በባለሃብቶች ሙሉ ለሙሉ አልተያዙም፡፡

Via Capital

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


በሽብር ተግባር ተጠርጥረው የተያዙ የአልሸባብ አባላት !

☪ ሁሉም የእስልምና እምነት ተከታይ ናቸዉ ።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በዚህ ሳምንት ሙፍቲን በወንበር ሊመታቸዉ የነበረዉ ልጅ ይሄ ነዉ !

በእዉነቱ ያሳፍራል እንደዚህ አይነት ሀገር አጥፊ ስንፈኛ ሙሉሞችን መቃወም ያስፈልጋል ።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ትዊተር ላይ እየተዘዋወረ ባለው በዚህ ቪዲዮ ስር ከአንድ ዩክሬናዊ የተሰጠ አስተያየት
👇👇

////'Police chase' ነው።ተፈላጊው ሞተረኛ ወደ ኪየቭ ከተማ ለመግባት እየከነፈ ነው።ሞተረኛው ሩሲያዊ እንደሆነ በፖሊሶቹ ተጠርጥሯል።በሌላኛው አቅጣጫ መንገድ ዘግተው ሞተረኛውን እንዲያቆሙት ከታዘዙት ፖሊሶች መካከል አንደኛው የራሱን ደህንነት ችላ ብሎ በመጋፈጡ የሆነው ሆነ ። በኋላ ላይ የሞተረኛው ማንነት ሲጣራ ግን ዩክሬናዊ ሆኖ ተገኘ .....ጠጥቶ የሰከረ ዩክሬናዊ! ////

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


የሆነስ ሆነና…

"…ሌላው ቢቀር ብርሃኑ ጁላና የአበባው ታደሰ ጦር ለፍርጠጣው ስልታዊ ማፈግፈግ ብሎ ከመቀሌ ወደ ሞለሌ በፈረጠጠ ጊዜ፣ እነ አገኘሁ ተሻገርና እነ አቶ አብርሃም የፓርቲ ገንዘብ በሚልዮን በሚልዮን ተከፋፍለው በፈረጠጡበት ጊዜ፣ እሱ ግን ህዝብ አስተባብሮ፣ ወጣቱን አደራጅቶ የተሾመባትን ከተማ የሚወዳትን ወልድያን ላለማስደፈር ብሎ በብርቱ የተዋደቀውን የወልድያ ከንቲማ ጀግና ክቡር አቶ መሀመድ ያሲንስ ተሸለመ ወይ? እኔ እስከአሁን ስላላየሁ ስላልሰማሁም ነው። ሸለሙት ግን?

ኢትዮጵያ ሃገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ … እንደይሆን ብዬ ነው።

"…እየኮመታችሁ…!!

መሳይ መኮንን

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


#መልካምዜና ጉግል የትርጉም መስጫ አገልግሎቱ (Google Translate) 24 አዳዲስ ቋንቋዎችን ማስጀመሩን ያስታወቀ ሲሆን በዚህ ውስጥ አፋን ኦሮሞ እና ትግርኛ ተካተዋል!

ከኢትዮጵያ ከአማርኛ በተጨማሪ ሌሎች ሁለት ቋንቋዎችን በ Google Translate አማካኝነት መተርጎም ይቻላል ማለት ነው። ከዚህ በኋላ "የተፃፈው ምን ይሆን?" ከማለት በቀጥታ ኮፒ አርጎ በማስገባት ትርጉሙን ማየት ይቻላል። አንዳንድ ግዜ የጉግል ትርጉሞች ችግር ያለባቸው ቢሆንም ብዙ ግዜ ግን እጅግ ጠቃሚ ናቸው።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


ሰበር ሰበር ዜና ‼️

ሽብርተኛው ህወሓት በወልቃይት ጠገዴ በማይጋማ እና መደማመር አካባቢ የከፈተው ጦርነት እንዳለ ሆኖ ህወሓት ወደ ኤርትራ ከባድ መሳሪያዎችን በመተኮስ ጦርነት ከፍቷል::

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official


ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ተይዞ ስለቆየበት ሁኔታ በዝርዝር ተናገረ

#Ethiopia | ከአንድ ሳምንት በላይ ደብዛው ጠፍቶ የነበረው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፤ ከመኖሪያ ቤቱ 'የተደራጀ የሕገ-ወጥ ቡድን' በሚመስል አካል ከተያዘ በኋላ ጦር ኃይሎች አካባቢ ባለ 'የድሮ ቤት' ውስጥ ሳያቆዩኝ አይቀርም አለ። ከአንድ ሳምንት ቆይታ በኋላ ትናንት ግንቦት 01/2014 ዓ.ም. ወደ መኖሪያ ቤቱ የተመለሰው ጋዜጠኛ ጎበዜ፤ ተይዞ ወደቆየበት 'የድሮ ቤት' እስኪደርስ ድረስ እንዲሁም ጥያቄ ሲቀርብለት ዓይኑ በጨርቅ ታስሮ እንደነበር ለቢቢሲ ተናግሯል።

ጋዜጠኛ ጎበዜ ተይዞ የቆየው ጦር ኃይሎች አካባቢ ባለ ቤት መሆኑን ያወቀው የያዙት ሰዎች ወደ ሥፍራው ለመሄድ አቅጣጫ ሲነጋገሩ ከሰማ በኋላ መሆኑን አስረድቷል።
ጋዜጠኛ ጎበዜ እንዴት ተያዘ?

"የያዙኝ የኢድ በዓል ዋዜማ ዕለት እሁድ ዕለት ረፋድ 4 ሰዓት አካባቢ ነበር" ይላል። 7 ወይም 8 የሚሆኑ ሲቪል የለበሱ እና የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የማይመስሉ ግለሰቦች አያት አካባቢ ወደሚኖርበት ግቢ ዘለው መግባታቸውን ጎበዜ ያስረዳል።

"የፀጥታ ኃይል ናቸው ለማለት ይከብዳል። ድርጊታቸው የመንግሥት የፀጥታ ኃይል አይመስልም። ግቢ ውስጥ ገብተው ሲጯጯሁ ሰው አምልጧቸው የሚፈልጉ እንጂ እኔን ሊይዙ የመጡ አልመሰለኝም ነበር። 'አንተን ነው የምንፈልገው' አሉኝ" ይላል።

ጋዜጠኛ ጎበዜ የግለሰቦቹን ማንነት ቢጠይቅም ወዲያው ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ እንዳልነበሩ ይናገራል።

"መሳሪያ ይዘዋል። ማናችሁ ብዬ መታወቂያ ስጠይቃቸው መታወቂያ ለማሳየት ፍላጎት የላቸውም። ሲሳደቡ ነበር" ይላል።

በግለሰቦቹ አለባበስ እና ሁኔታ የመንግሥት ኃይሎች ስለመሆናቸው ጥርጣሬ አደረብኝ የሚለው ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ፤ ሊይዙት የመጡ ሰዎችን እንዲህ ሲል ይገልጻቸዋል።

"አለባበሳቸው የተለያየ ሲሆን ኮፍያ ባለው ሹራብ የተሸፈኑ አሉበት። ፀጉራቸው ያደገ። ሁኔታቸው እንደ 'ጋንግስተር' [አደገኛ ቦዘኔ] ነው። . . . የተደራጀ የሕገ-ወጥ ቡድን መጣ ብዬ ነው ያሰብኩት" ይላል።

ጨምሮም ሊይዙት ከመጡት ሰዎች መካከል አንዱ ቪዲዮ መቅረጽ መጀመሩን ጎበዜ ይናገራል። በተደጋጋሚ ማንነታቸውን ሲጠይቅ ከግለሰቦቹ መካከል አንዱ የፀጥታ ኃይል መሆናቸውን እንደነገረው እና መታወቂያ እንዳሳየው ያስታውሳል።

"ያሳየኝ መታወቂያ የመከላከያ ሠራዊት አባል እና የመረጃ ምናምን ይላል። ከዚያ ወደ ውጪ ይዘውኝ ወጡ" በማለት ጎበዜ ይናገራል።

ጎበዜ ግለሰቦቹ ይዘውት የሄዱበት መኪና የአገር መከላከያ ሠራዊት ሰሌዳ እንዳለው ይናገራል።

በግለሰቦቹ ተይዞ ከመኖሪያ ቤቱ ከወጣ በኋላ ዓይኑን በጨርቅ ሸፍነው ይዘውት እንደሄዱ ይናገራል። በመኪናው እየተጓዙ፤ "በጣም እየተጯጯሁ ይነጋገራሉ። ከንግግራቸው ጦር ኃይሎች አካባቢ እንደወሰዱኝ ማወቅ ችያለሁ" ይላል።

ጋዜጠኛ ጎበዜ ግለሰቦቹ ይዘውት ወደሚሄዱበት ቦታ 'ጀነራል' እያሉ ከሚጠሩት ግለሰብ ትዕዛዝ ይቀበሉ ነበር ይላል።

"አቅጣጫ እየነገራቸው ነበር ግን ያወቁት አይመስለኝም። መጨረሻ ላይ አንድ ግቢ ውስጥ ይዘውኝ ገቡ። ሰፊ ግቢ ነው። ግቢ ውስጥ ያሉት ቤቶች የድሮ ቤቶች ናቸው። ወለላቸው ጣውላ ነው። እዚያ ነው ይዘው ያቆዩኝ"።

ጎበዜ በቀጣይ ግን መርማሪ መጥቶ ጥያቄ እንዳቀረበለት ይናገራል።

"መርማሪው ሲመጣ ፊቴ ይሸፈናል" ያለው ጋዜጠኛ ጎበዜ፤ ጥያቄ ሲያቀርብለት ከነበረው ግለሰብ ሦስት ጉዳዮች በተደጋጋሚ ማንሳቱን ያስታውሳል።

"የመጀመሪያው አንተ ፋኖን ትደግፋለህ፤ የፋኖ አባል ነህ የሚል ነው። ሁለተኛ ደግሞ አንተ ኦሮሞ ጠል ነህ የሚል ነው። ሦስተኛው ደግሞ በተለያዩ ግጭቶች ውስጥ እጅህ አለበት የሚል ነው" በማለት ያስረዳል።

ጋዜጠኛ ሲሳይ ጥያቄ ሲያቀርቡለት የነበሩት ጉዳዮች በመገናኛ ብዙሃኃን ከሚናገራቸው እና በማኅብራዊ ሚዲያዎች የሚጽፋቸው ጉዳዮች እንደሆኑ ይናገራል።

ጎበዜ ተይዞ በነበረበት ወቅትም ስለያዙት ግለሰቦች ማንነት ጥያቄ ሲያቀርብ እንደነበረና "አንዳንዴ መከላከያ ነን ይላሉ። መከላከያ እና ደኅንነት ተቀናጅተው እንደያዙኝም ይናገራሉ።"

ጋዜጠኛ ጎበዜ ከመኖሪያ ቤቱ ተይዞ ሲወጣ የአገር መከላከያ ሠሌዳ ባለው መኪና መወሰዱ እና ግለሰቦቹ መንገድ ይጠቆሙ የነበሩት 'ጀነራል' እያሉ በሚጠሩት ግለሰብ በመሆኑ ተይዞ የነበረው በአገር መከላከያ እንደሆነ እንደሚያምን ይገልጻል።

ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ታስሮ በነበረበት ወቅት ምንም አይነት አካላዊ ጥቃት እንዳልተፈጸመበት እና የምግብ ችግር እንዳልነበረበት ለቢቢሲ ተናግሯል።

ጋዜጠኛ ጎበዜ ትናንት ግንቦት 1/2014 ዓ.ም. ምሽት 3 ሰዓት አካባቢ ይዘውት የቆዩት ሰዎች ዓይኑን በጨርቅ አስረው መኖሪያ ቤቱ ጥለውት እንደሄዱ ተናግሯል።

ጎበዜ የያዙት ግለሰቦች ከመልቀቃቸው በፊት " 'እንደዚህ አይነት ሥራ አትስራ። አገራችንን የምንገነባው አንድ ላይ ነው። የትም ቦታ ብትሆን ከእኛ አታመልጥም።' የሚል ማስፈራሪያ ምክር ያለበት ንግግር ተናግረውኛል" ይላል።

ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ተይዞ የቆየበት ሁኔታ እና የቀረበበት ማስፈራሪያ ከሚዲያ ሥራው እንደማያዛንፈው ተናግሯል።

"ሊከታተሉኝ ይችላሉ። ቤተሰብ ጓደኛ 'ተው ይቅርብህ' በሚሉ ምክንያቶች ጫናዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ይህ ግን እኔን ወደ ኋላ አይመልሰኝም። በሚዲያ ሥራዬ እቀጥላለሁ።"

ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ከዚያም ደግሞ የኛ በሚባል ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ሲሰራ ነበር።

ጋዜጠኛ ጎበዜ በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት የህወሓት ኃይሎች ወደ አማራ ክልል ዘልቀው በገቡ ወቅት በፌስቡክ ገጹ በሚያጋራቸው መረጃዎች የብዙዎችን ትኩረት ስቦ ነበር።

በጉዳዩ ላይ የአገር መከላከያ ሠራዊት አስተያየትን ለማካተት ያደረግነው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል።

BBC

https://t.me/esat_television_official

21k 0 10 2 78



75 አመራርና ሰራተኞች ላይ እርምጃ ወሰደ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥነ-ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 75 አመራርና ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡

በአገልግሎቱ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክተር አቶ ህብረወርቅ ይመኑ÷ተቋሙ ባለፉት 9 ወራት ከተለያዩ አካላት የቀረቡ 97 ጥቆማዎች እና 163 አቤቱታዎችን ተቀብሎ የማጣራ ስራ መስራቱን ተናግረዋል፡፡

በዚህም የሥነ-ምግባር ጥሰት በፈፀሙ 75 አመራርና ሰራተኞች ላይ የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዱን እና ቀሪ 87 የሚሆኑት ጉዳያቸው በስነ ምግበር በመታየት ሂደት ላይ እንደሚገኙ ነው ያስረዱት፡፡

አስተዳደራዊ እርምጃው የተወሰደው በተቋሙ ህብረት ስምምነት እና በማኔጅመንት መተዳደሪያ ደንብ መሰረት መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተሩ÷የገንዘብ ቅጣት፣ ከኃላፊነት ቦታ ማንሳት እንዲሁም እስከ ስራ ስንብት የሚደርስ እርምጃ መወሰዱን ጠቁመዋል፡፡

አብዛኛው የተቋሙ ሰራተኛ ጥራት ያለውና አስተማማኝ አገልግሎት ለመስጠት የበኩሉን ጥረት እያደረገ ቢሆንም ጥቂቶች በህገ-ወጥ መንገድ አገልግሎቱን ለማግኘት ከሚፈልጉ አካላትና ደላሎች ጋር በመሆን ብልሹ አሰራር የሚፈጽሙ መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡

በህገ-ወጥ መንገድ ቆጣሪ ማስገባት፣ ቆጣሪ ለማስገባት በሚደረገው ሂደት ጉቦ መጠየቅ፣ ደንበኛን በአግባቡ አለማስተናገድ፣ ያለበቂ ምክንያት ስራን ማዘግየትና ደንበኛን ማጉላላት፣ በአስቸኳይ ጥገና ስራ ደንበኞች ገንዘብ በማዋጣት እንዲከፍሉ ማስገደድ፣ ያለደረሰኝ የቆጣሪ ማስገቢያ ክፍያ መቀበል እና የመሳሰሉት በተደረገ ማጣራት ስራ የተገኙ የብልሹ አሰራር መገለጫዎች መሆናቸውን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡

ተቋሙ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ ከመውሰድ ባለፈ ብልሹ አሰራርን ለመከላከል የተለያዩ ስራዎች እየሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ተቋሙ የተለያዩ የቅሬታ ማስተናገጃ ስርዓት መዘርጋቱን የገለፁት አቶ ህብረወርቅ÷ ደንበኞች በተዘረጉ የቅሬታ ማቅረቢያ ስርዓቶች ቅሬታቸውን፣ ጥቆማቸውን እና ሃሳባቸውን ማቅረብ ይችላሉ ማለታቸውን ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

https://t.me/esat_television_official




“በአንድነት ለጋራ ዓላማ መቆም ተግዳሮቶችን ለመሻገር እንዲሁም ለሀገር ዘላቂ ብልጽግናን ለመገንባት አቅም ይሆናል” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

*********

በአንድነት ጋራ ዓላማ መም ተግዳሮቶች ለመሻገር እዲሁም ለሀገር ዘላቂ ብልጽግን ለመገንባት አቅም ይሆናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በባህርዳር ከተማ በተካሄደው የአማራ ክልል የጸጥታ ኃይሎች የእውቅናና የምስጋና መርሀ ግብር ላይ ተገኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ንግግርም በአሁኑ ወቅት የሁሉም ክልሎች ልዩ ሀይሎች በተሻለ አቋምና ብቃት ላይ ይገኛሉ፤ የእነዚህ ሀይሎች የተሻለ ብቃትትና አቋም ላይ መሆን የኢትዮጵያን ሰላም አንድነትና ህልውና ዋስትና ናቸው ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ጠላቶች ይህንን ሳይረዱ ኢትዮጵያዊያን በብሄር፣ በቋንቋ፣ በሀይማኖት በፖለቲካ ተከፋፍለዋል በሚል የተሳሳተ ስሌት ስህተት እንዳይፈጽሙ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያሳሰቡት።

በዛሬው እለት የተሰጠው ሽልማት የህይወት እና የደም ዋጋ ለከፈሉ እንዲሁም በገንዘብና በእውቀት ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱት መላ ኢትዮጵያዊያን የተሰጠም ነው ብለዋል።

https://t.me/esat_television_official
https://t.me/esat_television_official

20 last posts shown.

40 838

subscribers
Channel statistics