ETHIO-MEREJA®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
.
.
.
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @antenehg1
👉 @ethio_merejabot


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ሌስተር ሲቲ ሊድስ ዩናይትድ እና ሳውዝአምተን ወደ ሻንፒዮን ሺፕ መውረዳቸውን አረጋገጡ

የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የመጨረሻው ዙር  38ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ ሲደረግ ወደ ታችኛው ዲቪዚዮን የወረዱ ቀሪ  ሁለት  ቡድኖች ተለይተው ታውቀዋል።

ከነዚህም ቶትናሃም የገጠሙት ሊድስ ዩናይትድ  የ3ለ1 ሽንፈት በማስተናገዳቸው  መውረዳቸውን ሲያረጋግጡ ፥  ዌስትሃምን የረቱት ሌስተር ሲቲ ደግሞ  ኤቨርተን በማሸነፉን  ሳውዝአምተንን ተከትለው ዛሬ መውረዳቸውን አረጋግጠዋል።

በሜዳቸው ጉዲሰን ፓርክ ስታዲየም በርንማውዝን የገጠሙት ኤቨርተን ደግሞ 1ለ ዐ በመርታት በፕሪምየር ሊግ መቆየታቸውን አረጋግጠዋል።

የ2015/16 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ቻምፒዮኖቹ ሌስተር ሲቲ  በሜዳው ኪንግ ፓወር ስታዲየም ዌስትሃምን 2ለ1 ቢያሸነፉም በኤቨርተን ተበልጠው  በፕሪምየር ሊጉ መቆየት አልቻሉም። የ2022/23 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ዋንጫን ማንቸስተር ሲቲ አስቀድሞ ማንሳቱ የሚታወስ ሲሆን አርሰናል፣ ማንቸስተር ዩናይት እና ኒውካስል  ደግሞ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ተሣትፎአቸውን አረጋግጠዋል።

  ---ETHIO-MEREJA---
T.me/ethio_mereja


ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን በድጋሚ የቱርክ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ!!

ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን በቱርክ ለሁለተኛ ዙር የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በማሸነፍ በድጋሚ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ከ20 ዓመታት በላይ ቱርክን የመሩት ኤርዶኻን በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሁለተኛ ዙር ምርጫ ብርቱ ተፎካካሪያቸው የነበሩትን ከማል ኪሊዳሮግሉን በማሸነፍ ነው ሀገሪቱን ለቀጣይ አምስት ዓመታት መምራታቸውን ያረጋገጡት ሲል አልጀዚራ የሀገሪቱን ሚዲያ ጠቅሶ ዘግቧል።

  ---ETHIO-MEREJA---
T.me/ethio_mereja


Call:-0941759900

የወዳጅ  ዘመዶን photo እንድህ ባማረ መልኩ በቆዳ እና እንጨት(MDF) እንድሁም በከለር(color print) በትዕዛዝ እንሰራለን።

INBOX:-@kiyamik
@firamk

Location:-#megenagna_24
Free delivery in addis ababa
ክፍለሀገር በፖስታና ትራንስፖርት እንልካለን

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም channel ይቀላቀሉ👇👇
@afripix1
@afripix1
@afripix1


የሞባይል ስልኩ ግድብ ውስጥ የገባበት ባለስልጣን 2 ሚሊየን ሊትር ግድብ ውሃ እንዲለቀቀ አደረገ!!

ህንድ ውስጥ አንድ ባለስልጣን ሰልፊ ፎቶ ራሱን ለማንሳት ሲሞክር ስልኩ ወደ ግድቡ ውስጥ ይገባበታል።

ይህ የምግብ ቁጥጥር ባለስልጣን 1 ሺህ 200 ዶላር ዋጋ ያለቀው ሳምሰንግ የእጅ ስልኩ ወደ ግድቡ ገብቶብኛል፣ ስልኩ በርካታ እጅግ አንገብጋቢ የመንግስት መረጃዎችን ይዟል በሚል ግድቡ እንዲመጠጥ አስደርጓል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ባለስልጣኑ መጀመሪያ ላይ ስልኩን ለማስወጣት በአካባቢው ያሉ ዋናተኞችን ቢያሰማራም አለመገኘቱን ተከትሎ በውሃ መሳቢያ ፓምፕ የግድቡ ውሃ እንዲመጠጥ አስደርጓል ተብሏል።

ራጂሽ ቪሽዋስ የተባለው ይህ ባለስልጣን ስልኩን ለማግኘት ሲባል ባለሙያዎች የግድቡን ውሃ ለመምጠጥ እና ለማፍሰስ ሶስት ቀናት እንደፈጀባቸው ተገልጿል። በመጨረሻም የባለስልጣኑ ስልክ ቢገኝም በውሃ ተሞልቶ የመስራቱ ነገር አጠራጣሪ ነው የተባለ ሲሆን ጉዳዩ በህንድ ዋነኛ መነጋገሪያ ሆኗል።

ይህን ተከትሎም የሐገሪቱ መንግስት ባለስልጣኑ በፈጸመው ድርጊት ስልጣኑን ያለ አግባበብ በመጠቀም ከስራ የታገደ ሲሆን ጉዳዩ አሁንም መነጋገሪያነቱን ቀጥሏል ተብሏል።ለዚህ ባለስልጣን ሲባል እንዲመጠጥ እና እንዲባክን የተደረገው ውሃ ከስድስት ሺህ በላይ ሄክታር መሬት መስኖ የማልማት አቅም እንደነበረው ተገልጿል።

  ---ETHIO-MEREJA---
T.me/ethio_mereja

13.8k 0 20 14 144

✅Cartier Brand Original Watch

Price :- 3000birr ብቻ | በቅናሽ ይግዙ

ለማዘዝ👉 0901882392 / @antenehg1

በTelegram ለማዘዝ 📲 @AntenehG1
በPhone ለማዘዝ ☎️ 0901882392/ በስራሰአት

👉👉 t.me/ethiobrandwatches
👉👉 t.me/ethiobrandwatches


የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የፖሊስ አባላት ምረቃ እያካሄደ ነው

በቅርቡ በተሰራው የልዩ ኃይል ፖሊስ አባላትን መልሶ የማደራጀት ሥራ መሰረት ወደ አማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የተቀላቀሉ የቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል አባላት በዓለም በር ፖሊስ ማሰልጠኛ ጣቢያ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ዛሬ የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ተከናውኗል።

በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያድረጉት የክልሉ ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን "ወደ ላቀ ኃላፊነት የተሰማራችሁ የፖሊስ አባላት እንኳን ደስ አላችሁ፣ ምን ጊዜም በላቀ የሥራ አፈጻጸም፣ በላቀ ወታደራዊ ዲስፕሊን ሀገርና ሕዝባችሁን እንደምታገለግሉ እንተማመናለን" ብለዋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሰልጣኞች ተገቢውን ስብዕናና ክህሎት እንዲጨብጡ መደረጉን አሚኮ ዘግቧል፡፡

  ---ETHIO-MEREJA---
 
T.me/ethio_mereja


በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ!

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች እና ከተሞች ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

ሰልፉ በአምቦ፣ ቦረና፣ ባሌ፣ ጉጂ፣ ቢሾፍቱ፣ መቱ፣ ነቀምቴ፣ ጅማ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ጭሮ፣ አሰላ፣ ጊምቢ፣ ሆለታ፣ ሸኖ፣ ሆሮ ጉዱሩ፣ ሜታ ሮቢ፣ ምዕራብ እና ምሥራቅ ሐረርጌ እንዲሁም በሌሎች ዞኖች እና ከተሞች የተካሄደ ሲሆን ሰልፈኞቹ በኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ላይ የሚፈፀመውን ስም ማጥፋት በፅኑ በመቃወም ድጋፋቸውን ለሠራዊቱ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

ለመከላከያ ሠራዊቱ ያላቸውን አክብሮት የገለጹት ሰልፈኞቹ፣ “ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያዊያን ዋስትና በመሆኑ ሁሌም ከሠራዊታችን ጎን እንቆማለን” ሲሉ ድጋፋቸውን አሳይተዋል። ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት ሀገርን ለመታደግ ዋጋ እየከፈለ መሆኑን ገልጸው፣ ሠራዊቱን የሚያጥላሉ እና የስም ማጥፋት የሚፈፅሙ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ ጥሪ አቅርበዋል።


#ማይ_ከስከስተም_በአዳዲስ_ዲዛይን_ብቅ_ብለናል!
💁‍♂️እንዲህ የሚያምር ሹራቦች፣ቲሸርት፣ቁምጣዎች እንዲሁም የአፍሪካ እና የሀገር ባህል ልብሶች።                                            ረቂቅ ዲዛይን ዘመን ከማይሽረው ውበት እና ጥራት ጋር አዋህደን በብዙ አማራጮች አቅርበናል::  ቢፈልጉ ለማዘዝ ፣ ቢያሻዎ ለመግዛት ፣ አልያም ለመከራየት የሚሆኑ ልብሶችን አዘጋጅተናል ::
ለበለጠ መረጃ :-  0906609792
                           0982044194
                           0936724570 ይደውሉልን👍
Telegram ይቀላቀሉን
👇👇👇
https://t.me/tshirt_x


የሚያስፈልግዎትን የጥርስ ህክምና ለመስጠት በጥራት እና በብቃት መጥተናል፡፡

✅ መንቀል ፣ መሙላት ፣ ማጠብ ፣ ማንጣት…..ብዙ ብዙ አገልግሎቶችን እንሰጣለን።

📌ባዘጋጀነው አማራጭ የክፍያ መንገዶችም ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡

💎ዕንቁ ስፔሻሊቲ  የጥርስ ህክምና ክሊኒክ💎

አድራሻ
📍ቄራ, የጨርቆስ ታክሲ መያዣ ፤ውልና ማስረጃ አጠገብ ፀናገ ህንጻ 5ኛ ፎቅ ያገኙናል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ
📞 +251 907 43 44 45
📞 +251 936 65 01 92
https://t.me/enqudentalclinic


ባየርሙኒንክ ለ11ኛ ተከታታይ አመት የጀርመን ቡንደስሊጋ ዋንጫን አነሳ

በአሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል የሚመሩት ባየር ሙኒክ የ2022/23 የውድድር ዓመት የጀርመን ቡንደስሊጋ ውድድር ሻምፒዮን መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የቡንደስሊጋው መሪ ቦርስያ ዶርትመንድ ዛሬ በ34ተኛ ሳምንት ጨዋታ ከማየንዝ 2 አቻ ሲለያይ፤ ባየር ሙኒክ ደግሞ ኮሎኝን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ባየር ሙኒክ በቡንደስሊገው 71 ነጥቦችን በመሰብሰብ በግብ ክፍያ ዶርትመንድን በመብለጥ ለተከታታይ 11ኛ የውድድር አመታት የጀርመን ቡንደስሊጋ ዋንጫን ማንሳት ችሏል።

  ---ETHIO-MEREJA---
 
T.me/ethio_mereja


🔖EthioBrand Watches - በቅናሽ ይግዙ!

ከ1500ብር ጀምሮ የተለያዩ ብራንድ ሰአቶችን ከኛ ያገኛሉ!

የቴሌግራም ቻናላችንን ከታች👇 ይቀላቀሉ
https://t.me/EthioBrandWatches
https://t.me/EthioBrandWatches

ለስጦታም፣ ለራስዎም ብዙ ምርጫዎች ያሉትን አዱሱን
የOnline ሰአት መገበያያ ቻናላችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ!!

➦ 0901882392 @antenehg1 (Tg)

ለሴቶችም፣ ለወንዶችም ምርጥ ብራንዶች አሉን!
የማይለቁ የማይዝጉ፣ ለብዙ አመታት የሚያገለግሉ

✅እዚህ ይጫኑ👇👇👇(Join ይበሉ)
https://t.me/EthioBrandWatches


Call:-0941759900

የወዳጅ  ዘመዶን photo እንድህ ባማረ መልኩ በቆዳ እና እንጨት(MDF) እንድሁም በከለር(color print) በትዕዛዝ እንሰራለን።

INBOX:-@kiyamik
@firamk

Location:-#megenagna_24
Free delivery in addis ababa
ክፍለሀገር በፖስታና ትራንስፖርት እንልካለን

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም channel ይቀላቀሉ👇👇
@afripix1
@afripix1
@afripix1


ጠቅላይ ምክር ቤቱ በመንግሥት ዉስጥ ሆነው ሕዝብንና መንግሥትን የሚያጋጩ አካላት ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድባቸው ጥሪ አቀረበ!!

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መንግሥት ኢስላም ጠል የሆኑ እና በመንግሥት መዋቅር ዉስጥ በተለያዩ እርከኖች ያሉትን አካላት በመገምገም እና በማጥራት ሕዝብንና መንግሥትን ሆነ ብለው ለማጋጨትና አገሪቷን ወደ ለየለት ቀውስ ለመውሰድ እየሰሩ ያሉ አካላትን ፈትሾ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ መዋቅሩን እንዲያጠራ ጥሪ አቀረበ።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ትናንት ግንቦት 18/2015 በአዲስ አበባ አንዋር መስጂድ በአዲሱ ሸገር ከተማ አስተዳደር እየተከናወነ የሚገኘውን የመስጂዶች ፈረሳ እንዲቆም ለማሳሰብ ሰላማዊ ሰልፍ በወጡ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እና በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ፤ በዛሬው ዕለት በጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ የምክክር ጉባኤ ባለ አስራአንድ ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ያወጣው አቋም መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦

እኛ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በግንቦት 19/2015 በጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ የምክክር ጉባኤ ላይ የተሳተፍን የጠቅላላ ጉባኤ አባላት፥ የዑለማ ምክር ቤት እና የክልል የእስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አባላት በወቅታዊ የህዝበ ሙስሊሙ ጉዳዮች ላይ ባደረግነው ምክክር የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

1. በሸገር ከተማ እየተደረገ ካለው የመስጂድ ፈረሳ ሂደትን አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ በአንዋርና ኑር መስጊዶች ዙሪያ የመስጂድ ፈረሳውን በሚቃወሙ ሙስሊሞች ላይ በተፈጸመው ጥቃት ሕይወታቸውን ላጡ ንጹኃን ሙስሊሞች አላህ በሸሂድነት(ሰማዕትነት) እንዲቀበላቸው፥ ለቤተሰባቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን አላህ እንዲሰጣቸው እንማጸነዋለን። በግጭቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖቻችን  በቶሎ መሻርን አላህ እንዲለግሳቸው እንማጸነዋለን።

2. በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ በአንዋርና ኑር መስጊድ የተፈጠረው ክስተት እንዴት እንደተፈጠረና የደረሰውን ሞትና ጉዳት መንስኤዎች የሚያጣራ ከመንግሥትና የእስልምና ጉዳይ ም/ቤት በጋራ ያሉበት ገለልተኛ አጣሪ ቡድን በአስቸኳይ እንዲቋቋም እንጠይቃለን።

3. በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በሸገር ከተማ ኢስላምንና ሙስሊሞችን በናቀ መልኩ በመስጂዶች ላይ እየተደረገ ያለው የጅምላ ፈረሳ ሂደት በአስቸኳይ እንዲቆም፥ እንዲሁም ለፈረሱት መስጊዶች የክልሉ መንግስት ምትክ ቦታ በመስጠት በአስቸኳይ ተመልሰው እንዲገነቡ በማድረግ ሕዝበ ሙስሊሙን በይፋ ይቅርታ በመጠየቅ እንዲክስ እናሳስባለን።

4. በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በሌሎች የአገራችን ክልሎች ለእምነት ቦታዎች ተገቢውን ክብርና ጥበቃ እንዲደረግ፥ እንዲሁም ለመስጂዶች ካርታ በመከልከልና ሆነ ብሎ ቢሮክራሲውን በማንዛዛት ሕዝቡን ላማረሩ ዘርፈ ብዙ ችግሮች መንግስት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በአፋጣኝ እንዲፈታቸው እናሳስባለን።

5. በሕገ መንግሥቱ እውቅና የተሰጣቸው የእምነት ነጻነትን በመጻረር በአገራችን አንዳንድ አከባቢዎች በተለይም በጉራጌ ዞን በጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎችን ለይቶ ከትምህርት የማባረር ሂደት በአስቸኳይ እልባት እንዲሰጠበት። መሰል ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትም በኢስላም ጠልነት ምክንያት በሙስሊሞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን በዘላቂነት የሚያስቀርና ለሃይማኖታዊ መብቶቻችንን የሚጥሱ አካላትን የሚቀጣ ሕግን መንግስት እንዲያወጣ እንጠይቃለን።

6. ሕዝበ ሙስሊሙ ከመሪ ተቋሙ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ጎን በመቆም ሃይማኖታዊ መብቶችን ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት በሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲያደርግ ጥሪ እናደርጋለን።

7. የሃይማኖታችንን ክብር ብሎም የአላህ ቤት የሆነውን መስጂድ መድፈርና ማዋረድ እጅግ ዉስጥን የሚያደማ ብሎም ስሜታዊ የሚያደርግ መሆኑን የመንግስት የጸጥታ አካላት በመገንዘብ ወደ ሕብረተሰቡ ከመተኮስ እንዲቆጠቡ እናሳስባለን።

8.ሕዝበ ሙስሊሙ የመብት ጥያቄዎቹን ለማስከበር ከመሪ ተቋሙ መጅሊስ ጎን በመቆም በሚያደርገው ህጋዊ ትግል ለራሳቸው የፖለቲካ ፍላጎት ሕዝበ ሙስሊሙን መረማመጃና መጠቀሚያ ሊያደርጉ ከሚችሉ አካላት የማባባስና ግጭትን የማስፋፋት ቅስቀሳና ሴራ ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ እናደርጋለን።

9.የሕዝበ ሙስሊሙን የመብት ጥያቄዎች የምናስከብረው በአንድነትና በመደማመጥ በመቆም ሕዝበ ሙስሊሙ በየእርከኑ ካሉ የእስልምና ጉዳዮች ም/ቤቶች ጎን በመቆም አንድነቱን በማጠናከር ለመብቱ ትግል ስኬት በአንድነት እንዲቆም ጥሪ እናደርጋለን።

10. መንግሥት ኢስላም ጠል የሆኑ እና በመንግሥት መዋቅር ዉስጥ በተለያዩ እርከኖች ያሉትን አካላት በመገምገም እና በማጥራት ሕዝብንና መንግሥትን ሆነ ብለው ለማጋጨትና አገራችንን ወደ ለየለት ቀውስ ለመውሰድ እየሰሩ ያሉ አካላትን ፈትሾ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ መዋቅሩን እንዲያጠራ ጥሪ እናደርጋለን።

11. በአገራዊ የምክክር ሂደት ላይ ሕዝበ ሙስሊሙ በንቃትና በስፋት በመሳተፍ ለዘመናት ሲንከባለሉ የቆዩ የሕዝበ ሙስሊሙ ችግሮችን፥ ጥያቄዎችንና አጀንዳዎችን በማንሳት ኹሉንም ኢትዮጵያውያንን በፍትሃዊነትና በእኩልነት የምታስተናግድ አገር ለመግንባት በሚደረገው ጥረት የበኩላችንን ጥረት እንድናደርግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

  ግንቦት 19/2015 || አዲስ አበባ
  ---ETHIO-MEREJA---
 
T.me/ethio_mereja

17k 0 10 11 109

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የተመራ ልዑክ በአንዋር መስጂድ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ጎበኘ!!

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የተመራ ልዑክ፤ ትላንት አርብ ግንቦት 18/2015 በአዲስ አበባ ከተማ አንዋር መስጂድ በጸጥታ ኃይሎች ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተገኝተው ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ፤ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሱልጣን አማንን፣ የፌደራል መጀሊስ አማካሪ ኡስታዝ አህመዲን ጀበል እንዲሁም የአዲስ አበባ መጅሊስ ሥራ አስፈፃሚ እና ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ካሊድ መሀመድ ተገኝተው የተጎዱትን ማጽናናታቸውን የአ/አ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አስታውቋል።

በተያያዘ ዜና፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንቱ ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ትናንት በታላቁ አንዋር እና ኑር (ሠፈር በኒ) መስጊዶች ከስግደት በኋላ በሙስሊሞችና ፖሊስ ጋር በተፈጠረው ግጭት ዙሪያ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች ጋር መወያየታቸውን ምክር ቤቱ አስታውቋል።

በውይይቱ ግጭቱን ተከትሎ የተዘጋው ኑር መስጊድ ለሰላት ክፍት እንዲኾን እንደተደረገ ምክር ቤቱ ገልጧል።

ወደፊት ተመሳሳይ ችግር እንዳይፈጠር፣ ከፖሊስ፣ ከጠቅላይ ምክር ቤቱና ከአዲስ አበባና ኦሮሚያ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤቶች የተውጣጡ መፍትሄ አፈላላጊ ቡድኖች መቋቋማቸውን ምክር ቤቱ ጨምሮ አስታውቋል።

  ---ETHIO-MEREJA---
 
T.me/ethio_mereja

14 last posts shown.