ETHIO-MEREJA®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ጎንደር!

የጎንደርና አካባቢው ሕዝብ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የሚሰሩትን ስራ በማድነቅ ዝናብ ሳይበግረው በአፄ ፋሲለደስ ስታዲየም በመገኘት የእውቅና ድጋፉን እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለፀ።

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


📍አዲስ አበባ እና አቅራቢያ ለምትገኙ በሙሉ!!

የTikTokና የOnline እቃዎችን በቅናሽ ዋጋ👇

👉 https://telegram.me/AddisEka1 (Join)

👉 https://telegram.me/AddisEka1

👉 https://telegram.me/AddisEka1

👉 https://telegram.me/AddisEka1 (Join)

👉 https://telegram.me/AddisEka1 (Join)

ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ! በቅናሽ ይሸምቱ!
  👉ተአማኒነት እና ጥራት መገለጫችን ነው!

🏃‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♀‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♀‍➡️🏃‍♀‍➡️.... Join us


አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በጎፋ ዞን በደረሰው አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ1 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ!

አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የአንድ ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው ድንገተኛ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፉን በማድረግ በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ወገኖች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ፣ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች ለማገዝ የተለያዩ አካላት ድጋፋቸውን እያደረጉ ሲሆን፤ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችም አደጋው በደረሰበት ስፍራ በመገኘት ተጎጂዎችን እያፅናኑ ይገኛል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያ ከነገ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ማወጁን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያስታወቀ ሲሆን፤ ብሔራዊ ሐዘኑ የታወጀው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰውን የመሬት መንሸራተት አደጋ የዜጎች ሕይወት በማለፉ መሆኑ ተገልጿል፡፡

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


በኢትዮጵያ ከነገ ጀምሮ ለ3 ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን ታወጀ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን ገዜ ወረዳ የደረሰውን የመሬት መንሸራተት አደጋ ተከትሎ ሕይወታቸው ላለፉ ዜጎች የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከነገ ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ቀናት የሚቆይ ብሔራዊ ሐዘን አውጇል።

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የመሬት ናዳ በተከሰተበት ጎፋ ዞን ዛሬ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል_ የወረዳው ኃላፊዎ

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የመሬት ናዳ በተከሰተበት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ዛሬ ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የገዜ ጎፋ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ ቢሮ ኃላፊ አቶ የዓለም መርህነህ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ኃላፊው አክለውም የእርዳታ እና ድጋፎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰው ያለው የአየር ጸባይ ፈታኝ በመሆኑ የተቀሩ አስከሬኖችን የማውጣት ሥራውን ፈታኝ አድርጎታል ብለዋል።

አስከሬናቸው ያልተገኙ 39 የሚሆኑ ሰዎች መኖራቸውን አክለው ገለጸዋል። የአካባቢው የመሬት አቀማመጥ አመቺ ባለመሆኑ ለቅሶ ለመድረስ እንዲያመች ሁሉም ለቀስተኛ በአንድ ስፍራ እንዲሰበሰቡ መደረጉንም ለአዲስ ስታንዳርድ ገልጸዋል። ሰኞ ዕለት በተከሰተው የመሬት ናዳው ከ257 በላይ ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።


       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


ኢትዮጵያ በ39 ስፖርተኞች የምትሳተፍበት የ ፓሪስ_ኦሊምፒክ ዛሬ ይጀመራል

በፓሪስ የሚካሄደው 33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የመክፈቻ ስነ ስርዓት ዛሬ ሐምሌ 19 ከምሽቱ 2 ሰዓት ከ30 በይፋ ይጀመራል።

ከ100 ዓመታት በኋላ ለ3ኛ ጊዜ ታላቁን የስፖርት መድረክ የማስተናገድ ዕድል ያገኘችው ፓሪስ፤ የዘንድሮው ኦሊምፒክ መክፈቻ በውድድሩ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከስታዲየም ውጪ በወንዝ ላይ ታደርጋለች።

ይህ የመክፈቻ መርሃግብር በፓሪስ ሰሜናዊ ክፍል ዘወትር የመዝናኛ ጀልባዎች በሚንሸራሸሩበት ሴን ወንዝ ላይ የሚከናወን ሲሆን፤ ተሳታፊ ሃገራትም ባንዲራቸውን ይዘው የሚታዩት በተዘጋጁላቸው 94 ጀልባዎች ላይ ሆነው የ3 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር ጉዞ ያደርጋሉ፡፡

በኦሊምፒክ ጨዋታዎች ከ203 ሀገራት የተወጣጡ 10 ሺህ 500 አትሌቶች በ32 የስፖርት አይነቶች እንደሚወዳደሩ የዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያ በዋናነት በተለያዩ ርቀቶች በሚደረጉ የአትሌቲክስ የስፖርት ውድድሮች በ39 ስፖርተኞች የምትካፈል ሲሆን አትሌቶቹ ከሚያዚያ 2016 ዓ.ም አንስቶ ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ፈረንሳይ የኦሊምፒክ ተሳታፊ ሀገራትን ቀይ ምንጣፍ በመዘርጋት እየተቀበለቻቸው ሲሆን ለታላቁ ድግስ 9 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ያደረገች ሲሆን በአጠቃላይ እስከ 12 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ገቢ ታገኛለች ተብሎም ይጠበቃል፡፡የማሊና የፈረንሳይ ጥምር ዜግነት ያላት የ29 ዓመቷ ድምጻዊና የዜማ ደራሲ አያ ናካሙራ በመክፈቻው ስነ ስርዓት ስራዋን ታቀርባለች። አሜሪካዊቷ ሌዲ ጋጋና ካናዳዊቷ ኮከብ ሴሊን ዲዮን የሙዚቃ ስራቸውን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።(ኢዜአ,ኢፕድ)

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግሥ በዓል እየተከበረ ነው

ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግሥ በዓል በቁልቢ እና ሐዋሳ በተለያዩ ሐይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶች እየተከበረ ነው፡፡

የንግሥ በዓሉ በየዓመቱ ሐምሌ 19 ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ-ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


"ዜጎች የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም አገልግሎት የማግኘት መብት አላቸው" የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም

 “በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት አንሰጥም" የሚሉ ተቋማት የወንጀል ኃላፊነት እንዳለባቸው ሊያውቁ ይገባል ሲል የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ አዋጅ 1284/2015 ማንነትን በማረጋገጥ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ተቋማት የብሔራዊ መታወቂያን በመጠቀም ሊሰጡ እንደሚገባቸው ተደንግጓል።

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የሕግና ፖሊሲ ክፍል ኃላፊ ጋብሬላ አብርሃም "አንዳንድ ተቋማት በተለይም የመንጃ ፈቃድ ትምህርት የሚሰጡ ተቋማት በፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎት አንጠቀምም የሚሉ አሉ” ሲሉ አንስተው ይህንን የሚያደርጉ ግለሰቦችና ተቋማት ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል ብለዋል። (ኢፕድ)

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


ያንጎ ሲሰሩ ብዙ ያተርፋሉ!! 💸🚗

ደንበኞችን በከፍተኛ ቅናሽ ሲያንበሸብሽ የነበረው ያንጎ አሁን ደሞ የአንበሳው ድርሻ የሚዘውን አሽከርካሪ የተሻለ ተጠቃሚ እና አትራፊ ለማድረግ በ ገቢ እና በቦነስ ሊያንበሸብሾ እንሆ ይሎታል 🎁🚖

በሳምንት በ ጉርሻ ብቻ እስከ 11,000 ብር በማግኘት ሳምንታዊ ገቢዎን ወደ 20,000 ያሳድጉ። 💰📈

ኑ ተቀላቀሉን!! በ ቴሌግራም ወይም በዋትስ አፕ በ 0939506059 ዶክመንቶትን በመላክ ያሉበት ሆነው በመመዝገብ ስራዎትን ወዲያውኑ ይጀምሩ ገቢዎትን ያሳድጉ። 📲✨


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጎፋ ዞን ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በደረሰው የመሬት ናዳ ሳቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

ባንኩ ዛሬ ያደረገው የገንዘብ ድጋፍ የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በግላቸው እያደረጉ ካለው ድጋፍ በተጨማሪ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሠራሽ አደጋዎች ለተጎዱ ወገኖች ፈጥኖ በመድረስ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም ገልጿል፡፡በጤናው ዘርፍ፣ በትምህርት፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በሰብዓዊ ሥራ ድጋፍ እና በሌሎችም ዘርፎች ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባለፉት አምስት ዓመታት ከ3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ እንዳደረገም ከባንኩ ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።

       T.me/ethio_mereja
             ኢትዮ-መረጃ


🪟ዋው የሚያስብሉ የግድግዳ ምስሎች😍

👉Shine laminated(የሚያብረቀርቅ)ናቸው።
👉በውሀ የሚፀዳ እና HD ማራኪ ናቸው!
👉በቀላሉ ባለው ማንጠልጠያ ሚሰቀል!!

  ዋጋ :-  1.50*80 - 3500ብር

አድራሻ፣ መገናኛ አለን

     በትዛዝ በ3ቀን እናደርሳለን።
     ☎️ 0901882392 /
     ☎️ 0931448106

ተጨማሪ T.me/Dinkwallarts


🌺Silver Crest Digital Touch Stove

🇩🇪Germen technology

♦️Ceramic Stove
♦️3500watt power
♦️ፈሳሽ ወደውስጥ የማያስገባ
♦️Timer እና Lock የተገጠመለት
♦️ለሁሉም ድስቶች የሚስማማ

   💦 ዋጋ፦ ✅ 6,700 ብር

       ☎️ 0901882392
       ☎️ 0931448106

12 last posts shown.