ETHIO-MEREJA®


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
Buy ads: https://telega.io/c/ethio_mereja
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251966244248
     +251984000520
WhatsApp. https://wa.me/251966244248
Telegram : @TemerRealEstateConsultant


ለፓስፖርት አገልግሎት የፋይዳ መታወቂያ ቅድመ ሁኔታ ሊደረግ ነው

የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት  ከሰኔ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የፋይዳ መታወቂያን ለፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ቅድመ ሁኔታ ለማድረግ እየሰራ ገልጿል፡፡

አገልግሎቱ ለፓስፖርት አሰጣጥ ተጨማሪ ቅድመ ሁኔታ በማድረግ በዘርፉ የሚሰጡ አገልግሎቶች ደህንነታቸውን የጠበቁና ተደራሽ ለማድረግ ከዲጅታል መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በጋራ ለመሥራት ተስማምቷል።

ይህም ማንነትን በማጭበርበር የተለያዩ ሰነዶችን ለማግኘት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመግታት እንደሚያስችል ተገልጿል።

በመሆኑም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የፓስፖርት አገልግሎት ጥያቄ አቅርበው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ግለሰቦች ፓስፖርት ለመውሰድ ሲመጡ በቅድሚያ በፋይዳ ተመዝግበው ልዩ ቁጥር ሊኖራቸው እንደሚገባ ተመላክቷል።

ተገልጋዮች የፋይዳ መታወቂያቸውን በወረቀት መልክ አሳትመው እንዲሁም ዲጂታል ኮፒውን በስልካቸው ይዘው በመምጣት አገልግሎት ማግኘት እንደሚችሉ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


የአለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት #በአማራ ክልል በበድሮን በመታገዝ የሚደረጉ ጥቃቶችን አወገዘ

በአማራ ክልል ምሥራቅ #ጎጃም ዞን ባሳለፍነው ሳምንት በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ሰላማዊ ሰዎች መሞታቸው በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳዘናቸው እና ድርጊቱ እጅግ እንዳሳሰባቸው #የአለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ዋና ጸሃፊ ቄስ ፕሮፌሰር ዶ/ር ጄሪ ፒሌይ አስታወቁ።

በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ባሳለፍነው ሳምንት ሐሙስ ሚያዝያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም በትምህርት ቤት ዙሪያ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ማስታወቃቸውነ የተመለከተ ዘገባ መቅረቡ ይታወሳል።

“ይህ የከፋ ጥቃት በቅርብ ወራት ውስጥ ተፈጽመው የበርካቶችን ህይወት የቀሰፉ ተግባራት ተጨማሪ ማሳያ ነው፤ በርካታ ንጹሃንን የቀሰፉ የድሮን ጥቃቶችመ እ.አ.አ በ2024ትመ ተፈጽመዋል” ሲሉ ዋና ጸሃፊው መናገራቸውን ምክር ቤቱ ትላንት ሚያዚያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

“የአለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት በንጹሃን በብዛት በሚኖሩባቸው አከባቢዎች የሚፈጸሙ መሰል ጥቃቶችን በእጅጉ ይኮንናል” አመላክቷል።

በተጨማሪም ዋና ጸሃፊው ፒሌይ ተዋጎ ያልሆኑ ሰዎችን ከጥቃት በጠበቀ መልኩ እንዲሁም አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህጎችን በጥብቅ ሳይከተሉ በግጭት አካባቢዎች የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች እንዳሳሰባቸው አስታውቀዋል።

ፒሌይ የሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ባለድርሻ አካላት ሁሉን አቀፍ ውይይት እና ሰላማዊ መፍትሄን እንዲከተሉ አሳስበዋል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት አቶ ታዬ ደንዳአ ለምስክርነት የጠሯቸው ጠ/ሚር አብይ አህመድ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፍርድ ቤት ሳይገኙ ቀርተዋል።

የፍርድ ቤቱ ፖስተኛ መጥሪያውን ይዞ ሲሄድ ጥበቃዎች መጥሪያ መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ወደ  ፅህፈት ቤታቸው እንዳይገባ ተደርጎ መመለሱ ታውቋል።

የአቶ ታዬ ጠበቃ "ተራ ፖስተኛ አድርጋችሁ ለምን ተመለሰ ትላላችሁ? የፍርድ ቤት መጥሪያ መሆኑን ሲያውቁ ከበር እንዲመለስ የተደረገው የፍርድ ቤቱን መናቅ ነው" በማለት በቀጣይ ማንኛውም ዜጋ አልቀርብ ሲል ተገዶ እንደሚመጣው ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ከንቲባዋ ተገደው እንዲመጡ ለፌደራል ፖሊስ ትዕዛዝ ይፃፍልኝ ሲል ጠይቋል።(መሰረት-ሚዲያ)

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ

14k 0 26 21 307

Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251966244248
     +251984000520
WhatsApp. https://wa.me/251966244248
Telegram :@TemerRealEstateConsultant


የሩሲያ ከፍተኛ የጦር አዛዥ በመኪና ላይ በተጠመደ የቦምብ ጥቃት ተገደሉ
***

የሩሲያ ከፍተኛ የጦር አዛዥ የሆኑት ሜጀር ጄኔራል ያሮስላቭ በሞስኮ ከተማ አቅራቢያ በመኪና ላይ በተጠመደ የቦንብ ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን የሩሲያ ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

ጄኔራሉ በአካባቢው እያለፉ በነበረበት ወቅት በሪሞት የሚዘወር ቦንብ የተጠመደበት መኪና ፈንድቶ ጥቃቱ እንደደረሰባቸው የሩስያው አርቲ ዘግቧል፡፡

ጥቃቱን ተከትሎ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ "ሞስኮ የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ ነበረች፤ ሆኖም ግን ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል" ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ጥቃቱ ከዚህ ቀደም ዩክሬን በሩሲያ አመራሮች ላይ ከሰነዘረቻቸው ጥቃቶች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ዘ ጋርዲያን በዘገባው አመላክቷል፡፡

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


በ ሰባት ዓመቷ ታዳጊ ላይ የመድፈር ጥቃት የፈፀሙት የ75 ዓመቱ አዛውንት በእስራት ተቀጡ

በባሌ ዞን ጎሮ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የ75 አመቱ አዛውንት የሰባት አመቷ ታዳጊ ላይ የመድፈር ጥቃት በመፈፀማቸው በእስራት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው መሆኑን የባሌ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታዉቋል። ብስራት ሬዲዮ ከባሌ ዞን ፖሊስ ዋና መምሪያ የኮምኒኬሽን ፅህፈት ቤት ያገኘዉ መረጃ እንዳመለከተው ተከሳሽ ተሾመ ገመቹ የተባሉት ግለሰብ ህዳር 9 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዐት ላይ በባሌ ዞን ጎሮ ወረዳ ውስጥ የሰባት ዓመቷ  ታዳጊ ከምትጫወትበት ስፍራ በመሄድ ጁስ ልግዛልሽ በማለት አታለው በመውሰድ ወደ እራሳቸው ሱቅ በማስገባት ፍራሽ ላይ በማስቀመጥ ጁስ ከሰጧት በኋላ የተለያዩ የሰውነት ክፍሎቿን በመሣም እራሳቸው ካዘጋጁ በኋላ የመድፈር ጥቃት ሊፈፅሙባት እንደቻሉ በማስረጃ ተረጋግጧል።

ተጎጂዋ በ75 አመቱ አዛውንት የመደፈር ጥቃት ከተፈፀመባት በኋላ በከፍተኛ የደም መፍሰስ በማህፀኗ በኩል የተከሰተ ሲሆን ይህንን የተመለከቱ የህፃኗ ወላጆችም በመደናገጥ በልጅቷ ላይ የተፈፀመውን የመደፈር ጥቃት ወዲያውኑ ለፖሊስ በማሳወቃቸው በልጅቷ ጥቆማ መሠረት የ75 አመቱ አዛውንት በገዛ ሱቃቸዉ ውስጥ በቁጥጥር ስር ዉለዋል። ፖሊስም ተጎጂዋን ልጅ በህክምና ተቋም ሲያስመረምር የ75 አመቱ አዛውንት በግብረስጋ ግንኙነት የሚተላለፍ ህመም እንዳለባቸው እንዲሁም የጤና ክትትል የሚያደርጉ መሆኑ በመረጋገጡ ወዲያዉኑ ለተጎጂዋ የህክምና እርዳታ ተደርጎላት ከተላላፊው ህመም ነፃ መሆኗ ተረጋግጧል።ፖሊስ በ75 አመቱ አዛውንት ላይ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ የምርመራ መዝገቡን በህክምና እና በሌሎች ማስረጃዎች በማጠናከር ለአቃቤ ህግ ልኳል።

አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀል ህግ ቁጥር 627 በህፃናት ላይ የሚፈፀም የግብረስጋ ድፍረት እና በደል እንዲሁም በወንጀል ህግ ቁጥር 514 ህመምን በማስተላለፍ ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡ ክሱን ሲከታተል የቆየው የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሽ ተሾመ የተባሉትን የ75 ዓመት አዛውንት እድሜያቸው 13 ዓመት ባልሞላቸዉ ልጆች ላይ ለንፅህና እና ክብር ተቃራኒ በሆነ መንገድ የመድፈር ጥቃት በመፈፀም እንዲሁም ከባድ ጉዳት የሚያደርስ ህመም እና በሽታ እያለባቸው በተበዳይዋ ላይ የአእምሮ እና የአካል ጉዳት እንዲደርስ በማድረጋቸው በድርብ ወንጀል ጥፋተኛ ብሏል፡፡የባሌ ዞን ከፍተኛው ፍርድ ቤት ሚያዝያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ በ14 ዓመት እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


“ሲም ካርድ በመጠቀም ፈንጂዎችን ለማፈንዳት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ይዣለሁ” ሲል የጎንደር ከተማ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ “ሲም ካርድ በመጠቀም ፈንጂዎችን በማፈንዳት የህብረተሰቡን ሰላም ለማደፍረስ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ ሶስት ተጠርጣሪዎች” ይዣለሁ ሲል ገለጸ።

"ተጠርጣሪዎች ገበያ ስፍራዎች በትምህርት ቤቶችና እንዲሁም ህዝብ በሚሰበሰብባቸው ስፍራዎች ፈንጂዎችን በማጥመድ የሽብር ተግባር ለመፈጸም ዝግጅት እንደነበራቸው" ባካሄድነው ምርመራ አረጋግጠናል ሲሉ የመምሪያው ኃላፊ አቶ አለልኝ ዓለም ትላንት ሚያዚያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

"ፍንዳታውን የሚያካሂደው በፈንጂው ላይ በሚታሰር የሞባይል ቀፎና ሲም ካርድ በመታገዝ ወደ ሲም ካርዱ በመደወል ፍንዳታውን በርቀት ሆነው እንደሚያካሂዱ" ተደርሶበታል ብለዋል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አለልኝ ዓለም በመግለጫቸው "ተጠርጣሪዎቹ ከቀናት በፊት ምሽት ላይ በከተማው አንድ ፖሊስ ጣቢያና በክፍለ ከተማ ጽህፈት ቤት ላይ ፈንጂ በማፈንዳት ተሰውረው የቆዩ ናቸው" ማለታቸውን ከከተማዋ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

"የፀጥታ መዋቅሩ ባደረገው ጥብቅ ክትትልና ስምሪት ተጠርጣሪዎቹ ሌላ የሽብር ተልእኮ ለመፈጸም በአንድ የግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በድብቅ ካዘጋጁዋቸው የፈንጂ መሳሪያዎች ጋር በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል" ማለታቸውንም መረጃው አካቷል።


  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


ቋንቋ ስልጠና በመራህያን
የምንሰጣቸው የቋንቋ ስልጠናዎች ፦
ቻይንኛ 🇨🇳
እንግሊዘኛ 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿
ጀርመንኛ🇩🇪
አረብኛ 🇸🇦
ፈረንሳይኛ🇫🇷

•Online or Inperson

ለመመዝገብ:
       ☎️
0989747878
0799331774

አድራሻ፦ 22 ከ ጎላጉል አጠገብ

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም ቻነላችንን ይቀላቀሉ : @merahyan


#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251966244248
     +251984000520
WhatsApp. https://wa.me/251966244248
Telegram :@TemerRealEstateConsultant


ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶ የነበረው የዘገባ ፈቃድ ለጊዜው ታገደ!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የሚሠሩ ኦርቶዶክሳውያን የሚዲያ ተቋማት በአንድ ማእከል  እንዲያገለግሉ፣ የመረጃ ፍሰቱ ወጥነት ያለውና ተቋማዊ መሆን ይችል ዘንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የሁለት ቀናት ሥልጠና ተሰጥቶ የቤተ ክርስቲያን መሠረተ እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብረው በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ ማከናወን የሚችሉበት ፈቃድ ከመምሪያው መሰጠቱ ይታወሳል።

ከእነዚህ የሚዲያ ተቋማት መካከልም የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን አንዱ ሆኖ ዘገባዎችን ሲያሰራጭ ቆይቷል።

"'ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት "ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም።" በሚል ርእስ  የተላለፈው ትምህርት ውዝግብ በማስነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያችን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው የታገደ መሆኑን እንገልጻለን።" ሲል የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።፡

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


" ሚስቱን ገድሎ ሊሰወር የሞከረዉ ግለሰብ በፖሊስና በሕብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ሊዉል ችሏል " - የጋሞ ዞን ፖሊስ

በአርባ ምንጭ ከተማ ባለቤቱ ገድሎ ሊሰወር የነበረ ግለሰብ መያዙን ፖሊስ ገልጿል።

የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ሬታ ተክሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ አርባ ምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ ግድብ ሠፈር ነው።

ኮማንደር ሬታ ፤ የገዛ ባለቤቱን በመሳሪያ ተኩሶ በመግደል ሊሰወር የሞከረዉ ተጠርጣሪ በሕዝቡና በፖሊስ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪው አቶ ነብዩ ጌታቸው ኤፍሬም እንደሚባልና ከሟች ጋር በትዳር ዓለም አብረዉ እንደነበሩ በመካከላቸዉ በነበረው አለመግባባት ሟች ወላጆቿ ጋር በመሄድ ላለፉት 5 ወራት ከቤተሰቦቿ ጋር ትኖር እንደነበር ገልፀዋል።

በትናትናዉ ዕለት ተጠሪጣርዉ አስቦና አቅዶ ጧት 4 ሰዓት ገደማ " ላናግርሽ እፈልጋለሁ " በማለት ካስጠራት በኋላ ሰዉ የማያይበትን ሁኔታ በማመቻቸት በሽጉጥ አንገቷ ስር ደቅኖ ተኩሶ እንደ ገደላት አስረድተዋል።

በኃላም ለመሸሸግና ለመሰወር ሲሞክር በፖሊስ ክትትልና በሕብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዉና ሟች በትዳር አብረዉ በነበሩበት ወቅት አንድ ልጅ አፍርተዉ እንደነበርም የፖሊስ መረጃ ያመለክታል።

ተጠርጣሪዉ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመበትን ሽጉጥ ወንዝ ዉስጥ እንደጣለ ቢገልፅም ፖሊስ ባደረገዉ ማጣራት ከደበቀበት በኤግዚቢትነት ይዞታል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


ቻይና በባሕር ላይ ማረፍ እና መነሳት ለሚችለው አውሮፕላን የገበያ ፈቃድ ሰጠች

በባሕር ላይ ማረፍ እና መነሳት የሚችለውየቻይናው AG600 አምፊቢየስ አውሮፕላን በሀገሪቱ ሲቪል አቪዬሽን አስተዳደር የገበያ ፍቃድ ሰርተፊኬት በይፋ ተሰጥቶታል።

‘የውሃ ድራጎን’ የሚል ስያሜ የተሰጠው አውሮፕላኑ ግዝፈቱ እና ክብደቱ የዓለማችን ትልቁ አምፊቢየስ አውሮፕላን እንዲሆን አስችሎታል፡፡

AG600 አምፊቢየስ አውሮፕላን በውኃ እና በመሬት ላይ ማረፍ እንዲችል ተደርጎ የተሰራ ነው።

አንድ ጊዜ በተሞላ ነዳጅ 4 ሺህ 500 ኪሎ ሜትር የመሸፈን አቅም ያለው ይህ አውሮፕላን፣ ከባድ እሳት አደጋን ለማጥፋት፣ የባሕር ላይ ፍለጋ ለማካሄድ እና ለነብስ አድን ተልዕኮዎች እንደሚውል ተጠቁሟል።

አውሮፕላኑ 12 ቶን ውኃ እና 50 ሰዎችን የመጫን አቅምን እንዳለውም ተጠቅሷል። ይህ የአውሮፕላን ስሪት ቻይና በአቪዬሽን ኢንደስትሪ የበላይነት እንድትቀዳጅ ከማስቻሉ ባሻገር፣ ለሚከሰቱ አደጋዎች ፈጣን እና አመርቂ እርምጃ ለመውሰድ የሚስችላት ነው ሲል ሲጂቲኤን በዘገባው አመላክቷል።

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


ቋንቋ ስልጠና በመራህያን
የምንሰጣቸው የቋንቋ ስልጠናዎች ፦
ቻይንኛ 🇨🇳
እንግሊዘኛ 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿
ጀርመንኛ🇩🇪
አረብኛ 🇸🇦
ፈረንሳይኛ🇫🇷

•Online or Inperson

ለመመዝገብ:
       ☎️
0989747878
0799331774

አድራሻ፦ 22 ከ ጎላጉል አጠገብ

ለበለጠ መረጃ ቴሌግራም ቻነላችንን ይቀላቀሉ : @merahyan


በትራፊክ አደጋ የ16 ሰዎች ህይወት አለፈ

በምዕራብ አርሲ ዞን ኔጌሌ አርሲ ወረዳ ራፉ ሃርጊሳ ቀበሌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ16 ሰዎች ህይዎት ሲያልፍ በ22 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል አካል ጉዳት ደረሰ፡፡

አደጋው የደረሰው፤ ከሻሸመኔ ወደ አዲስ አበባ የሚጓዝ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በተቃራኒ አቅጣጫ ሲጓዝ ከነበረ ባለ ተሳቢ የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ጋር በማጋጨቱ መሆኑ ተገልጿል፡፡

አደጋውን ተከትሎም ከሟቾች በተጫመሪ በ16 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም በ6 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የኔጌሌ አርሲ ከተማ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

  T.me/ethio_mereja
        ኢትዮ-መረጃ


#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251966244248
     +251984000520
WhatsApp. https://wa.me/251966244248
Telegram :@TemerRealEstateConsultant


ቻይንኛ ቋንቋ ኮርሶች ምዝገባ ጀምረናል!

Registration Now Open for Chinese Language Course!

🇨🇳 Beginner Level (HSK 1-2)
🇨🇳 Intermediate Level (HSK 3-4)
🇨🇳 Advanced Level (HSK 5-6)

Interactive, immersive learning

Small class sizes for personalized attention

Online and in-person options available

Spots are limited—register now and take the next step in your Chinese language journey!

0988747878 / 0799331774

ለበለጠ መረጃ : @merahyan


#የእርዳታ_ጥሪ

ቀና ልብ ላላችሁ ወገኖች በሙሉ  የወንድማችንን ነፍስ ከሞት እንታደግ🙏🙏

ይህ ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት ኤርምያስ ፍቅሬ ይባላል።

ተወልዶ ያደገዉም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ በሀድያ ዞን፣ በፎንቆ ከተማ ስሆን፤ #ከልጅነቱም ጀምሮ ትሁትበስነ-ምግባሩ የታነፀበትምህርቱም ጎበዝና ለሌሎችም እንደ አራአያ የምታይ ወጣት ነዉ።

   የ2ተኛ ደረጃ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት አጠናቆ በ2009ዓ.ም ወደ #ሀዋሳ_ዩንቨርስቲ በመግባት በቴክስታይል ኢንጅነርንግ(Textile Engineering) ት/ት ክፍል ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ተመርቆ በሀዋሳ እንደስትርያል ፓርክ ውስጥ እየሰራ ባለበት ወቅት ድንገት ባጋጠመዉ የኩላሊት ህመም ምክንያት ስራውን አቋርጦ ህክምናዉን እየተከታተለ እያለ ህመሙ ብሶበት ሁለቱም ኩላሊቶቹ መስራት ስላቁመ ዶክተሮቹ በአፋጣኝ ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንዲደረግ ወስነዋል።

እናም ወደ ውጭ ሀገር ወስደን ለማሳከም የተጠየቅነዉ ብር ከአቅማችን በላይ በመሆኑ እናንተ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭም የምትኖሩ ደጋግ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እጃችሁን በመዘርጋት ወይም በምትችሉት ነገር ሁሉ ከጎናችን በመሆን ይህንን ወጣት ህይወት እንድትታደጉ ስንል እንማፀናለን🙏🙏።


ወንድማችን ኤርሚያስ ፍቅሬ በምርመራ 2 ኩላሊቴ Fail እንዳደረገ የተነገረው ሲሆን አሁን እየኖረ ያለው በየወሩ 60,000 ብር በሚጠይቀው የዳያሊስስ ድጋፍ ነው። ከዚህም በላይ የኩላሊት ንቅለ ተከላ በውጭ አገር እንዲሰራ ተናግሮታል ለህክምናውም ወደ 3.5 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ለ3ሰው የአየር ቲኬት፣ ለ2 ወር መቆያ እና ተያያዥ ወጪዎች 1.5ሚሊየን አከባቢ በአጠቃላይ ወደ 5 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል። ይህ ከሱ እና ከቤተሰቡ አቅም በላይ ስለሆነ እና የሁላችንም ድጋፍ ይሻል።

ለድጋፍ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:-1000268155938
በአዋሽ ባንክ:- 013201523182800
ERMIAS FIKRE MESSELE

ለመደወልና ኤርምያስን ለማናገር ለምትፈልጉ
📞 0941414057
📞0920992184 ወይም
📞0939580869

የተቻላችሁን ብትረዱንና የወንድማችንን ህይወት በማትረፍ ትተባበሩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏 ለምታደርጉልን ማንኛውም ቀና ትብብር እናመሰግናለን ፈጣሪ ጨምሮ ይስጥልን።

እሱን ለማገዝ በተዘጋጀው ግሩፕ ይቀላቀሉ
     👉 T.me/Go_Fund1



19 last posts shown.