ኢትዮ መረጃ - NEWS


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@B_promotor

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


አሳዛኝ መረጃ‼️

ንግስ አክብረው በመመለስ ላይ የነበሩ ምዕመናንን ላይ የመኪና አደጋ ደርሶ 18 ሰው ማረፉ ተሰማ።

መነሻቸውን ሐዋሳ እና ሻሸመኔ ከተማ አድርገው የመጋቢት አቦ ክብረ በዓልን በአርባምንጭ ዝጊቲ አቦ በማክበር ወደ መጡበት በመመለስ ላይ የነበሩ ምዕመን

ወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ መሻገሪያ ድልድይ ስር የተሳፈሩበት መኪና ፍሬን ተበጥሶ በመግባቱ ከ18 በላይ ምዕመናንን ከእዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰማ።

አደጋው ዛሬ ምሽት 12:30 አከባቢ የደረሰ ሲሆን የተሳፈሩበት መኪና ወንዝ ውስጥ የገባ ከመሆኑ የተነሳ የሟቾች ቁጥር ከእዚህ በላይ ያሻቅባል ተብሎ ይጠበቃል።

እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ከደጋጎች ጎን ያሳርፍልን

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


በስልጤ ዞን የገዛ ልጁን አንቆ በመግደል አስከሬኗን መፀዳጃ ቤት ጉድጓድ ዉስጥ የጣለው አባት በእስራት ተቀጣ

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን ዳሎቻ ከተማ አስተዳደር የገዛ ልጁን አንቆ በመግደል አስከሬኗን ጥልቅ የመፀዳጃ ቤት ጉድጓድ ዉስጥ የጣለው ተከሳሽ በእስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑ ፖሊስ ገልጿል።

ተከሳሽ ደጀኔ መኮንን ገ/ፃዲቅ የተባለ ሲሆን
ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ገደማ ከባለቤቱ ጋር በመጋጨቱ ምክንያት የገዛ ልጁን በአሰቃቂ ሁኔታ ጎሮሮዋን አንቆ ህይወቷ እንዲያልፍ ካደረገ በኋላ የህፃኗን አስከሬን  አስር ሜትር ጥልቀት ባለው ሽንት ቤት ውስጥ መጣሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ የሚዲያ ክፍል ኃላፊ ም/ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

ይህ መረጃ የደረሰው የደሎቻ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የሟችን አስክሬን ለምርመራ ወደ ወራቤ ኮምፕርሄሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመላክ ለተፈፀመው ድርጊት አስፈለጊ የሆኑ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች አሰባስቦ ምርመራ በማጣራት መዝገብ አደራጅቶ ለስልጤ ዞን ዐቃቤ ህግ ያቀርባል።

ዐቃቤ ህግም ከፖሊስ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ ተቀብሎ ተከሳሹ በፈፀመው ከበድ የሰው መግደል ወንጀል የመሰረተዉ ክስ የተመለከተዉ  የስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍርድቤት የተከሳሹን አድራጎት በሰዉና በሰነድ ማስረጃ በማረጋገጡ የጥፋተኝነት ዉሳኔ ይሰጣል

የስልጤ ዞን ከፍተኛዉ ፍርድ ቤት መጋቢት 4 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ደጀኔ መኮንን ገ/ፃዲቅ በእድሜ ልክ በፅኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑንየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ የሚዲያ ክፍል ኃላፊ ም/ኮማንደር ታጁ ነጋሽ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


የ51 ተሳፋሪዎቹን ሕይዎት የታደገው ጀግና ሹፌር

እጁን በጥይት ተመትቶ ንፁህ ደሙን እያዘራ የ51 ተሳፋሪዎቹን ህይዎት የታደገው ጀግና

ጀግናው ሹፌር አየለ እውነቱ በሙያው የተመሰገነና የተከበረ የህዝብ ማመላለሻ ሀገር አቋራጭ አውቶብስ አሽከርካሪ ነው ።

መጋቢት 03 ቀን 2017 ዓ/ም ምድቡ ወደሆነው ወልድያ ከተማ ፣ እንደወትሮው ሁሉ 51 ተጏዦቹን አሳፍሮ ከሌሊቱ 10:30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ላምበረት ተነስቶ በጭፍራ በኩል ወደ ወልዲያ ጉዞ ጀመረ ።

ይሁን እንጅ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ አፋር ገዋኔ አካባቢ እንደደረሱ አምነውት የተሳፈሩ ወገኖችን እንደያዘ ሀገር አማን ብሎ ወደፊት እየከነፈ ባለበት ወቅት ማንነታቸው ያልታወቁ የታጠቁ ሀይሎች ጀግናው (ሽፍቶች) ሹፌር አየለ እውነቱ ላይ አነጣጥረው የጥይት እሩምታ ያወርዱበት ጀመር።

በዚህ የጥይት እሩምታ ቀኝ እጁ ላይ ከባድና ግራ እጁ ላይ ቀላል ጉዳት ቢደርስበትም ህመሙን ዋጥ አድርጎ ንፁህ ደሙን እያዘራ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ የሁለት ልጆቹና መላው ቤተሰቡ አምላክ ጥበቃ ፣ የሚያሽከረክረውን አውቶብስ በብስለት ተቆጣጥሮ እንዳይወድቅ አድርጓል ፣ በዚህም አውቶብስ ውስጥ የሚጏዙ 51 ተሳፋሪዎችን ህይዎት ታድጏል።

ረዳቱ ተስፋዬም የሚፈሰውን ደም በጨርቅ አስሮ በአካባቢው ወደሚገኝ ህክምና ቦታ እንዲደርስ አድርጓል። ሹፌር አየለ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ህክምና በመከታተል ላይ ይገኛል።

ክብር በሞትና በህይዎት መካከል በስንት ፈተና እያለፉ ህዝብንና ሀገርን ለሚያገለግሉ ፣ ክብር ጥቃታቸው ጉዳታቸው ሞታቸው ውለታቸው ቢዘነጋም እነሱ በየመንገዱ እየወደቁ ፣ እየሞቱ አካላቸውን እያጡ ነፍሳቸውን አደጋ ላይ ጥለው ለሙያቸው ለታመኑ ጀግና የሀገራችን አሽከርካሪዎች ። ...

ክብር ለሹፌሮች።

@sheger_press
@sheger_press

6.1k 0 3 13 173

የእስራኤል ወታደሮች ሁለት ኢትዮጵያዊያንና አንድ ኡጋንዳዊ ተኩሰው መግደላቸው ተገለፀ

የእስራኤል ወታደሮች፣ ትናንት ከዮርዳኖስ አቋርጠው ወደ እስራኤል የገቡ ሁለት ኢትዮጵያዊያንና አንድ ኡጋንዳዊ ተኩሰው መግደላቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ወታደሮቹ የተሠጣቸው ትዕዛዝ የማስጠንቀቂያ ተኩስ እንዲተኩሱ እንደነበር ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎችና የሕገወጥ ሰዎች ዝውውር ሰለባዎች ከዮርዳኖስ ወደ እስራኤል እንደሚገቡና ድንበር ጠባቂ ወታደሮች እንዲመልሷቸው ሥልጣን እንደተሠጣቸው ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

ወታደሮቹ ግድያውን የፈጸሙት፤ ማቾቹ "ስጋት የሚደቅን" እንቅስቃሴ በማድረጋቸው እንደሆነ የአገሪቱ መከላከያ ባለሥልጣናት ተናግረዋል ተብሏል።

አንድ ኢትዮጵያዊን ጨምሮ አምስት የውጭ ዜጎች ደሞ ታስረው ወደ ዮርዳኖስ እንዲመለሱ እንደተደረጉ ተገልጿል።


#ለእሳትነት የቅድስና ማዕረግ የደረሰው አባት

ታላቁ ሊቅ አርእስተ ሊቃውንት ከሚባሉ አባቶች አንዱ ነው። አባቱ ኤስድሮስ እናቱ ኤሚሊያ ይባላሉ። ባልና ሚስት ከተቀደሰ ትዳራቸው አምስት ወንድና አንድ ሴት ልጅ አፍርተዋል። የሚገርመው እህቱ ቅድስት ማቅሪና ገዳማዊት ስትሆን አምስቱም ወንዶች ጳጳሳት መሆናቸው ነው። የሁሉ የበላይ የሆነው ግን ቅዱስ ባስልዮስ ነው። ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ከሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ሊቃውንት አንዱ ነው። የቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊም መምህር ነው። ቅዱስ ባስልዮስ ገዳማዊ ጻድቅ፣ ብዙ ምሥጢር የተገለጸለት ሊቅ፣ የብዙ ምዕመናን አባት፣ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት፣ ብዙ ተአምራት ያደረገና ከከዊነ እሳት ከፍጹምነት የደረሰ ነው። በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳያንን ሆስፒታል ያስገነባ እርሱ ነው።

በርካታ ድርሰቶችም ደርሷል። መጽሐፈ ቅዳሴን ዛሬ በምናውቀው መንገድ ያሰናሰለው እርሱ ሲሆን በርካታ ሥርዓቶች ሰርቷል የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትንም ተርጉሟል። ቅዱስ ባስልዮስ በቂሣርያ ማዛካ ቀጰዶቅያ ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡ በዛም የረጅም ጊዜ ጓደኛው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን ተዋውቋል፡፡ ሁለቱም በአቴንስ በ342 ዓ.ም አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል፡፡ ባስልዮስ አቴንስን በ348 ለቆ ወደ ግብጽና ሶርያ ከተጓዘ በኋላ በሀገሩ በቂሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር እንደቆየ ታሪኩ ያስረዳል፡፡ ቅዱስ ባስሊዮስ ጥሩ ተናግሮ የማሳማን ጸጋ የታደለ ነበር፡፡ እርሱ ግን ሕጋዊ የማስተማር ሥራውን ትቶ ሕይወቱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡                                                                                       

ይልቁንም በመንፈሳዊ ትምህርት ተስቦ በ350 ዓ.ም በአስተሳሰብ ከእሱ ጋር የሚመሳሰሉትን  በክርስትና ሕይወት እንዲጓዙ ወንድሙን ጴጥሮስን ጨምሮ ማሰባሰብ ጀመረ፡፡ አንድ ላይ ሆነው በቤተሰቡ ርስት ላይ አኔዚ አጠገብ ገዳም መሠረቱ፡፡ እኅቱ ማክሪናና ሌሎች ሴቶችም ራሳቸውን ለቅዱስ ተግባር በመነሣት ከባስልዮስ ጋር ይተባበሩ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስና ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ የአርያኒዝም የክህደት ትምህርት የቀጰዶቂያን ክርስቲያኖች እንዳይከፋፍል ሲታገሉ ቆዩ፡፡ በኋላም በትልቅ የጉባኤ ክርክር ከታዋቂ አርያናውያን ቴዎሎጂየንና ተናጋሪዎች ጋር ክርክር ለማድረግ ተስማሙ፡፡ በንጉሥ ቫሌነስ ተወካዮች መሪነት ከተደረገው ክርክር በኋላም ጎርጎርዮስና ባስልዮስ አሸናፊዎች ሆነው ወጡ፡፡

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ባስልዮስ የቂሣሪያን ከተማ አስተዳደር ተረከበ፡፡ አውሳቢየስ ግን በባስሊዮስ ፈጣን ችሎታና ዕድገት በማኅበረሰቡ ባገኘው ተቀባይነት በመቅናት ወደ ነበረበት የገዳም ብቸኝነት ኑሮ እንዲመለስ ፈቀደለት፡፡ ጎርጎርዮስ ግን በዚህም በዚያም ብሎ ባስልዮስን እንዲመለስ አሳመነው፡፡ በዚያች ከተማም ለበርካታ ዓመታት ውጤታማ አስተዳዳሪ ሆነ የተደነቀበትን ሥራ ሁሉ ለአውሳብዮስ ተወለት፡፡ በ362 ዓ.ም አውሳቢዮስ ሲሞት ቅዱስ ባስልዮስ እንዲተካው ተመረጠ፡፡ በዛውም ዓመት የቂሣሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ለሃይማኖቱ ቀናኢ የሆነ፣ በስብከቱ የሚታወቅ ደግና ለሰው አዛኝ ነበረ፡፡ በዚያም ወቅት ድርቅ ባስከተለው ረኀብ ምክንያት በግሉ ምግብና የሚጠጣ ነገር በማዘጋጀት ድሆችንና አቅመ ደካሞችን የሚያበላ፣ ሀብቱንም ድሆች እንዲጠቀሙ በነበረበት ቤተክርስቲያን አካባቢ የሚያድል አባት ነበር፡፡                                   

በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

                     




በትግራይ እየተደረገ ያለ መፈንቅለ መንግስት የለም፥ ሕግ እና ስርዓት ማስከበር እንጂ ሲሉ የህወሓት ከፍተኛ አመራር አቶ አማኑኤል አሰፋ ተናገሩ። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት መቀየር ጨምሮ ሌሎች የፕሪቶስያ ውል ያልተፈፀሙ ይዘቶች ለመከወን ከፌደራል መንግስቱ ጋር ንግግሮች ይቀጥላሉ ሲሉም ጨምረው ገልፀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ጥቆማ‼️

በሀገራችን ታማኝ የዜና ምንጮችን የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናል ነው!

ሊንክ👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


በትግራይ ሕግ እና ስርዓት ማስከበር እንጂ እየተደረገ ያለ መፈንቅለ መንግስት የለም:: ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተቀራርቦ ለመስራት የሚደረግ ግንኙነት ዛሬም ነገም ይቀጥላል።

ስለዚህ መቼ ነው [ወደ አዲስአበባ] የምትሄዱት የሚለው የቀጠሮ ጉዳይ ነው። ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመሆን ነው ግዚያዊ አስተዳደሩን ያቋቋምነው።

በተለይም የፕሬዝደንት ቦታ የሚመለከት ደግሞ ሁለታችን የተስማማንበት ነው የሚሆነው። ሁለታችን ያልተስማማንበት እንደማይሆን ከዚህ በፊትም ተረጋግጦ የቆየ ነው። ስለዚህ በግዚያዊ አስተዳደሩ የሚደረግ ማስተካከያዎች ይሁን የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መፈፀም የሚያስችለን ግንኙነት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ይቀጥላል"
- የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል አሰፋ

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ለጥንቃቄ‼️

44 የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች ሕብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳሰበ፡፡

ባለስልጣኑ በሰራው የገበያ ቅኝት ሥራዎች 44 ዓይነት የምርት መለያ ስም ያላቸው የተለያዩ በአዮዲን የበለፀጉ የምግብ ጨው በሚል ታሽገው ደህንነታቸውና ጥራታቸው ሳይረጋገጥ በተጨማሪም የሀገሪቱን አስገዳጅ ብሔራዊ ደረጃ እና የገላጭ ጽሑፍ ደረጃ ሳያሟሉና ሳይለጥፉ ሲቀርቡ የነበሩ ምርቶች መገኘታቸው ተመላክቷል፡፡

ምርቶቹም የሚከተሉት ናቸው፡-

1. አበሩሰ አዮዳይዝድ ጨው

2. ዛክ የገበታ ጨው

3. ሉሉ የገበታ ጨው

4. ሙሪዳ አዮዳይዝድ ጨው

5. እቱ የገበታ ጨው

6. እቴቴ የገበታ ጨው

7. እፍታ ጨው

8. ኤልሳ የገበታ ጨው

9. ሴፍ  የገበታ ጨው

10. NS አዮዳይዝድ ሳልት

11. ማሚ የገበታ ጨው

12. ሣሊህ  የገበታጨው

13. እማ የገበታ ጨው

14. አዮዲን የገበታ ጨው

15. ቃና የገበታ ጨው

16. ሀርመኒ የገበታ ጨው

17. ውዛት አዮዳይዝድ ሳልት

18. ሐበሻ ባለ አዮዲን ጨው

19. ሪል የገበታ ጨው

20. ሸጋ የገበታ ጨው

21. ጆይ አዮዳይዝድ ሳልት

22. ኮከብ የገበታ ጨው

23. ስኬት የገበታ ጨው

24. ፎር ኤም አዮዳይዝድ ሳልት

25. አዲስ የገበታ ጨው

26. ኤመሬት ጨው

27. አስቤዛ የገበታ ጨው

28. ቶም የገበታ ጨው

29. በረከት የገበታ ጨው

30. ሜናታ የገበታ ጨዉ

31. ቤስት አዮዳይዝድ  ጨዉ

32. አፊአ  የገበታ ጨው

33. ዋን በአዮዲን የበለፀገ የገበታ ጨዉ

34. አቢሲኒያ የገበታ ጨዉ

35. ማሩ የገበታ ጨዉ

36. ባና ኤዳይዝድ ጨው

37. ማራኪ ጨዉ

38. መክሊት የገበታ ጨዉ

39. ዳግም የገበታ ጨዉ

40. አዲስ የገበታ ጨዉ

41. አፍያ ጨዉ

42. ኦማር የገበታ ጨው

43. ገዳ የገበታ ጨው

44. NITSUH IODIZED SALT ናቸው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ 13 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው።

የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፤ ባሳለፍነው ሳምንት በሁለት ክሶች ጥፋተኛ የተባሉት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ላይ 13 ዓመት ፅኑ እስራትና 21 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ፍርድ ማሳለፉን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ቤተሰብ አባል መረጃውን አድርሷል።

ፍርድ ቤቱ የቀድሞዉ ከንቲባ ካቀረቡት 8 የቅጣት ማቅለያዎች 4ቱን በመቀበል እና አራቱን ዉድቅ በማድረግ ነዉ የ13 ዓመት ፅኑ እስራት የፈረደባቸው።

በዚሁ በእሳቸው መዝገብ ተከሳሽ የነበሩት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታርኩ ታመነ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት እነ 41 ሺህ ብር ፤ አቶ ታፈሰ ቱናሻ በ8 ዓመት ከ5 ወር ፅኑ እስራትና 51 ሺህ ብር እንዲሁም አቶ ሰይፉ ሌሊሴ የተባሉ ግለሰብ እንደዚሁ በ8 ዓመት ከ5 ወር እና 76 ሺግ ብር የገንዘብ ቅጣት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።


#ክብሩና ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል አባት


ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ አባታችን በተወለዱ ጊዜ አንደበታቸው ከምስጋና የተገኘ፣ ስለሀገራችን መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው የጸለዩ፣ ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ፣ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩ፣ ከጌታችን ጋር መሞት አይገባኝም ብለው የተከራከሩ ታላቅ ቋድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡

አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር የቆዩት ቅዱሳን በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ ይህም ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን እየለመኑ ነው፡፡

በተጋቡ በሰላሳ ዘመናቸው አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ክብሩና ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል ክህነቱ እንደ መልከጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምም ባረከችው ቅዱሳን መላዕክት ዘወትር ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡

ሕፃኑንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ሰጡት፡፡ ፍጹም የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮበታልና ሥራው ሁሉ በዕውቀት የተመላና የተቃና ሆነ፡፡ እንደ ቅዱስ እንጦንስም አስኬማ ሰጡት፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ ወደ ሰማያት አርገው በረከትና ጸጋ የተቀበሉ፣ አጋንንትን የሚያሳድዱበት፣ ድውያንን የሚፈውሱበት ታላቅ ጸጋ ተሰጣቸው፡፡ ከሰው ተለይተው ወደ ጫካ ገብተው ከስድሳ አንበሶችና ከስድሳ ነብሮች ጋር የሚኖሩት አባታችን፣ እንስሳቱ እርሳቸውን የረገጡትን መሬት ልሰው ጠግበው ይኖራሉ፡፡

ሰውነታቸው አንድ ክንድ ከስንዝር በሚረዝም ጠጉር የተሸፈነው አባታችን ወደ ሀገራችን መጥተው ተጋድሏቸውን ቀጠሉ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ገዳማቶቻቸው ወዳሉባቸው ወደ ምድረ ከብድና ወደ ዝቋላ ተራራ ወሰዳቸው፡፡ በእነዚህ ገዳማት እየተመላለሱ ሲጸልዩና ሀገራችንን ሲባርኩም ኖረዋል፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ በሀገራች ያለውን የኃጢአት ስራ ባዩ ጊዜ በዝቋላ ሐይቅ አንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው መላው ኢትዮጵያን እንዲምርካቸው ጸልየው ቃል ኪዳን ተቀብለዋል፡፡ የመጨረሻ እረፍታቸውም በምድረ ከብድ ገዳም ነው፡፡ ይህ እረፍታቸውም በየዓመቱ መጋቢት 5 ታስቦ ይውላል፡፡ ገዳማትንና ገዳማውያንን እያሰብን ከበረከታቸው እካፈል፡፡
     

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




የኤርትራ መንግስት ምላሽ ሰጠ‼️

ኤርትራ የፕሪቶርያውን የሰላም ስምምነት የማፍረስ ምንም ፍላጎት የላትም ሲሉ የኤርትራው የመረጃ ሚኒስተር አስታወቁ።
“የኤርትራ ጦር በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል አለ” የሚለውና ተደጋጋሚ የሆነ በተወሰኑ አካላት የሚነሳ ውንጀላ ፍፁም ሀሰት እና ግጭት ለመቀስቀስ ምክንያት ለመፍጠር ነው፤ የኤርትራ ወታደሮች ሙሉ በሙሉ በሉዓላዊ ግዛታቸው ውስጥ ተሰማርተው ይገኛሉ ሲሉ አቶ የማነ ገብረመስቀል ገልፀዋል።

ሚኒስተሩ አክለው ከዚህ ቀደም በብዙ አጋጣሚዎች በማያሻማ መልኩ እንደተገለጸው፣ ኤርትራ የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት ለማፍረስ ምንም ፍላጎት የላትም፤ በመሰረቱም ስምምነቱ የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ነው ብለዋል።

በተመሳሳይ ኤርትራ በህወሓት የፖለቲካ አንጃዎች ውስጥ የተፈጠረውን የውስጥ ሽኩቻ የማባባስ ፍላጎት የላትም ይህም በትግራይ ህዝብ ላይ አላስፈላጊ እና ሊወገድ የማይችል ስቃይ ያስከትላል ብለዋል።

በቀይ ባህር ዙሪያ የተለያዩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች ሌት ተቀን የሚያወጡት የማያቋርጥ ግጭት ቀስቃሽ መግለጫዎች ለአላስፈላጊ ውጥረቱ አባባሽ ምክንያት ሆነው ቀጥለዋል ያሉ ሲሆን ይህ ያለምንም ማወላወል በጠንካራ ሁኔታ መወገዝ አለበት ሲሉም የኤርትራው የመረጃ ሚኒስተር አቶ የማነ ገብረመስቀል በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልእክት አስታውቀዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ፑቲን ለአሜሪካ የተኩስ አቁም ሀሳብ ምላሽ ሰጡ

ቭላድሚር ፑቲን በአሜሪካ የቀረበው የ 30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነት ሀሳብ በመርህ ደረጃ እንደሚቀበሉት ገለጹ።

ፑቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "ዘላቂ ሰላምን ማምጣት እና የዚህ ቀውስ መንስኤዎች ማስወገድ" አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

"ጠብን ለማቆም በአሜሪካ በተቀረበው ሀሳብ እንስማማለን፣ ሀሳቡ ትክክል ነው እንደግፈዋለን ሲሉም ነው በመግለጫቸው ያነሱት።

በዩክሬን ውስጥ ጦርነቱ ማብቃት አለበት ያሉት ፑቲን የተኩስ አቁም ሀሳቡ "ጥሩ ነው፤ ሙሉ በሙሉ እንደግፋለን ፣ ነገር ግን ከአሜሪካ ጋር ልንወያይባቸው የሚገቡ ጉዳዮች አሉ ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ከአውሮፓውያኑ የካቲት 2022 አንስቶ በሩሲያ እና በዩክሬን በተቀሰቀሰው ግጭት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ለሞትና ለአካል ጉዳት ተዳርገዋል።

በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል ፣ ከተሞች ወደ ፍርስራሽነት ተቀይረዋል ሲል ሮይተርስ በዘገባው አስታውሷል።


#ስለሃይማኖታቸው ክብር ንጉሱን ያልፈሩት ጻድቅ


በአጼ ሱስንዮስ ዘመነ መንግሥት በአሥራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ድንቅ ሥራ የሰሩ፣ ተአምረኛና ገዳማዊ አባት ናቸው። እኒህ ታላቅ ጻድቅ ሐዋርያዊ አባት አቡነ ዓምደ ሥላሴ የካቲት 27 ጎጃም ውስጥ ነው የተወለዱት።

የካቲት 17 ቀን መንኩሰው ወደ ተጋድሎ ገብተዋል። በተለያዩ ገዳማት በነበራቸው ቆይታም እመቤታችን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት የካቲት 16 ቀን በነበራቸው ፍቅር ይታወቃሉ። ጻድቁ በበርካታ ገዳማት የነበሩ ሲሆን በገዳማዊ ሕይወታቸው በትህርምት፣ በጸሎታቸውና በተጋድሏቸው ዛሬም ድረስ ከሚታወቁ አባቶች አንዱ ናቸው። ጻድቁ አባታችን ዓምደ ሥላሴ ከሚነገሩላቸው ታሪኮች ቅድሚያውን የሚይዘው የተዋሕዶ ጠበቃነታቸው ነው።


በ1603 ዓ.ም ጴጥሮስ ወይም ፔድሮ ፓኤዝ የሚባል ካቶሊካዊ ከሀዲ ወደ ሃገራችን ገብቶ ነበር መኖር ጀመረ፡፡ ከዚያም  ውስጥ ለውስጥ ሲሰብክ ቆይቶ በ1609 ዓ.ም ነገሩ በመገለጡ እነ ራስ ዮልዮስ ለሃይማኖታቸው ጠዳ ላይ ተዋግተው ግንቦት 6 ቀን ተሰው። በ1622 ዓ.ም አጼ ሱስኒዮስ ከነቤተሰባቸው ተጠምቀው ካቶሊክ ሆኑ፡፡ ይህ ነገር ሲሰማ ወንድ ሴት፣ ትልቅ ትንሽ ሳይመረጥ በገጠሩም፣ በከተማውም፣ በገዳሙም ያሉት ሁሉ የተዋሕዶ ልጆች መንቀሳቀስ ጀመሩ። በ1626 ዓ.ም ካቶሊክ የኢትዮጵያ እምነት ነው ብለው ሲያውጁ ግጭቱ በይፋ ተጀመረ። "ተዋሕዶን ካልካዳችሁ" በሚል በቀን እስከ ስምንት ሺህ ሰው በሰይፍ ታረደ። ይህን ያደረጉት ደግሞ አልፎንሱ ሜንዴዝ፣ ንጉሡ ሱስንዮስና ጀሌዎቻቸው ነበሩ።

በጊዜውም ከቤተ መንግሥት የሱስንዮስ ሚስት እነ ንግሥት ወልድ ሰዓላ፣ ከጻድቃን አበው ዘርዓ ቡሩክ ዘግሸን፣ ሐራ ድንግል ዘደራ፣ ምዕመነ ድንግል ዘጩጊ፣ ዓምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ፣..... ከቅዱሳት እነ ፍቅርተ ክርስቶስ፣ ወለተ ጴጥሮስ፣ ወለተ ጳውሎስ፣ እኅተ ጴጥሮስ፣..... ለሃይማኖታቸው ተዋሕዶ ጥብቅና ቆመው ሕዝቡን አስተማሩ፤ መከራም ተቀበሉ። ብዙ ኢትዮጵያውያን የመከራ ጽዋን ተጐንጭተው በክብር ሰማእትነት ከተቀበሉ በኋላ የእግዚአብሔር ፍርድ ተገለጠ። በጻድቃኑ በእነ አባ ዓምደ ሥላሴ ሐዘን ንጉሡ ታመሙ ከዚያም ምላሳቸው ተጐልጉሎ ወጣ። በዚህ ጊዜ አቤቶ ፋሲለደስ ለአባ ዓምደ ሥላሴና ለሌሎቹ ቅዱሳን "አባቴን አድኑልኝ! ተዋሕዶም ትመለስ።" አላቸው።

ጻድቁም ከባልንጀሮቻቸው ጋር ጸልየው ንጉሡን አዳኗቸው። እርሳቸውም "ፋሲል ይንገሥ! ተዋሕዶ ሃይማኖት ይመለስ! የሮም ሃይማኖት ይፍለስ!" ብለው አሳወጁ። ከዚህ በኋላ አጼ ፋሲል ሲነግሡ አባ ዓምደ ሥላሴ ለገዳማቸው ብዙ ቦታ አስከልለው በተጋድሎ ኑረው የካቲት 27 ዐርፈዋል።

ገዳማውያን ሃይማኖት ሲነካ አንገታቸውን አሳልፈው እስከ መስጠት መስዋዕትነት ይከፍላሉ፡፡ ሕዝቡን ለማጽናናትና ለማስተማር ከገዳማቸው ይወጣሉ እንጂ በተጋድሎ ጸንተው፣ በትህርምት ረግተው፣ በጸሎት ተግተው ከዓለም ርቀው ነው የሚኖሩት፡፡ በዓለም ላለነው ለኛና ለቅድስት ቤተክርስቲያን ለሀገራችንም ይጸልያሉ፡፡ ገዳማቸውን በመርዳት፣ በዓታቸውን በማጽናት ከበረከታቸው እንሳተፍ፡፡ 


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




አስቸኳይ የጥንቃቄ መልዕክቱ በቶሎ ይሰራጭ‼

በዚ ሰዓት ቀርካቶች እየተሸወዱ ነው።
«የቴሌግራም ፕሪሚየም በነፃ ተቀብለዋል!» የሚል የአማርኛ ጽሑፍ ከስሩ ሊንክ ያለው እየተሰራጨ ነው።
ልብ በሉ! ሊንኩን ከተጫናችሁት አካውንታችሁ 100% ተጠልፏል።

በምታውቁት ሰው አካውንት ቢላክም፤ አውቆ ሳይሆን እርሱም ተበልቶ ነው።
ሊንኩን በፍፁም እንዳትከፍቱ።

ሳታውቁ በስህተት የከፈታችሁ ካላችሁ በአስቸኳይ ይህን አድርጉ።

መጀመሪያ ፕሮፋይላችሁ ላይ ወዳለው Settings ላይ ግቡ Devices የሚለውን ንኩት። በቀይ የተፃፈውን Terminat All Other Sessions የሚለውን ተጫኑና ከሁሉም አካውንታችሁ ሎግኢን ከተባለባቸው ዲቫይሶች ውጡ።  Ok በማለት 24 ሰአት ሳይቆይ አስወግዱት። 24 ሰዓት ከቆዬ ይህን ማድረግ ላትችሉ ትችላላችሁ። ምክንያቱም እነርሱ ይህን ስቴፕ ተከትለው እንደ ዋና ባለቤት ሆነው እናንተን ያባርሯችኋል። 

ብዙ ሰው እየተበላ ስለሆነ ሼር it.
አሁን ማነው የ 5000 ብር የቴሌግራም ፕሪሚየም በነፃ የሚሰጣችሁ?
በሊንኩ ገብታችሁ email እና password ካስገባችሁ አካውንታችሁን አታገኙትም።
በአቋራጭ ለመበልፀግ አትጣደፉ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

8.6k 0 122 3 56
18 last posts shown.