ኢትዮ መረጃ - NEWS


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ኢትዮጵያን መውደድ ባትችል አትጥላት
ማክበር ባትችል አታዋርዳት
ማራመድ ባትችል አታዘግያት
መጠበቅ ባትችል አትበትናት።
ይህን በማድረግ ታሪክ ባትሠራም ታሪክ አታበላሽም።

ለአስታየት @ethio_merjabot
@biruke_promotion


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


“ጠላፊው ከላካቸው ሽማግሌዎች ውስጥ የፖሊስ አዛዦች ይገኙበታል”- የጸጋ ቤተሰቦች

በሀዋሳ ከአንድ ሳምንት በፊት የተጠለፈችው ጸጋ በላቸው እስካሁን ያለችበት አልታወቀም።

ጠለፋው እንዴት እንደተፈጸመና ጠላፊው ምን ፍላጎት እንዳለው አል ዐይን ቤተሰቦቹን አነጋግሯል።

ወይዘሪት ጸጋ፥ ግንቦት 15፣ 2015 አመሻሽ ላይ ከስራ ወደ ቤቷ ለማምራት ታክሲ የምትይዝበት ቦታ ላይ ነው የመንግስት መኪና በያዘና አስቀድሞ ለፍቅር ጓደኝነት በሚፈልጋት ግለሰብ የተጠለፈችው። “ከቤቷ ውጭ አድራ ስለማታውቅ አከራዮቿ ወደ ጓደኞቿ እና ፍቅረኛዋ ደወሉ፤ ከዚያም እኔ ጋር ጠዋት ደውለው ጠየቁኝ” የሚለው ወንድሟ ታምሩ በላቸው ፥የስራ ባልደረባዋ እና ጓደኛዋ ግን የጠላፊውን ስም ጠርታ የት እንደሄዱ ጭምር እንደነገረቻቸው ይገልጻል።

ጠላፊው የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የአቶ ጸጋዬ ቱኬ የግል ጠባቂ መሆኑን መግለጿንም ያስታውሳል።እነ ታምሩ ይህን መረጃ ይዘው ይገኙበታል ወደተባለው ይርጋለም ከተማ ከፖሊሶች ጋር  ይጓዛሉ፤ ይሁን እንጂ ይርጋለም እንዳሉ “ሀገረሰላም ቡርሳ ነን” የሚል የጽሁፍ መልዕክት ደረሳቸው።

ከይርጋለም ወደ ሀገረሰላም በመጓዝም ወደ ቡርሳ የገጠር መንደር ማቅናታቸውን ነው ወንድሟ ታምሩ የሚያስታውሰው።“በጨለማ 3 ኪሎሜትር አካባቢ በእግር ሄደን ቡርሳ ደረስን፤ የአክስቱ እና የአጎቱ ቤት ተጠቁመን አይተን ተመለስን፥ ከፖሊስ ጋር ሌሊት 10 ስአት ሄድን እስኪነጋ ጠብቀን እያንዳንዱን ቤት ፈተሽን ግን እህቴን ልናገኛት አልቻልንም። እህቴ ተግታበት የነበረው ቤት ባለቤት እና የጠላፊው የእህቱ ወንድም በቁጥጥር ስር ዋሉ” ይላል።

ጠላፊው ሀገረ ሰላም ሲገባ “እንደ ጀግና ተኩሷል” የሚለው ታምሩ፥ “እህቴንም ከአዲስ አበባ እንዳመጣትና ሊያገባት መሆኑን ሲናገርና ከጓደኞቹ ጋር ሲጨፍሩ መታየታቸውን” ከሀገረሰላም ነዋሪዎች መስማታቸውን ሌላኛው ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የጸጋ ቤተሰብ ነግረውናል።ጸጋ በቡርሳ ለማምለጥ ሞክራ መያዟንም የአካባቢው ነዋሪዎች እንደነገሯቸው በማከል።

የጸጋ እና የጠላፊው ጥያቄ ምንድን ነው?

ጸጋ በላቸው ከተጠለፈች ስምንተኛ ቀን ቢሆናትም ድምጿን የሰማሁት ሁለት ጊዜ ብቻ ነው ይላል ወንድሟ ታምሩ።“እኔን ነጻ ማውጣት አትፈልግም ወይ? እኔን ነጻ በሚያወጣ መልኩ ተደራደር” ብላኛለች፥ ይሁን እንጂ  ለድርድር ከተቀመጥን ደግሞ እሷ በሰላም የምትወጣበትን ዋስትና አላገኘንም ባይ ነው። ጠላፊው ግለሰብ ደግሞ ሽምግልና መቀመጥ ግዴታ መሆኑን ደጋግሞ መግለጹን ነው የሚናገረው። በሽምግልና የማይፈታ እና ጉዳዩን በህግ የሚይዙት ከሆነም እንደሚገላት እየዛተ ነው። “ሊልካቸው ያሰቡ ሽማግሌዎች ደውለው አውርተውኛል፤ እስካሁን የት እንዳሉ አያውቁም፤ ደህንነቷን አላረጋገጡልኝም" ይላል ታምሩ በላቸው።

የጸጋ በላቸው ጠለፋ ከቤተሰቦቿ አልፎ የመላው ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ሆኖ መነጋገሪያነቱ ቀጥሏል። እናትና አባቷ እስካሁን የልጃቸውን ጠለፋ እንዳልሰሙ ነግሮናል።“አባቴ ሆስፒታል በህክምና ላይ ነው፤ እናቴም እያስታመመችው ነው፤ በጣም የሚወዷትን ልጃቸውን ጠለፋ ከሰሙ ወላጆቼን በሞት አጣቸዋለሁ” ሲልም ስጋቱን ይገልጻል።

እጮኛዋን ለማግባት እየተሰናዳች የነበረችው ጸጋ፥ ጠላፊዋ ሽማግሌ ልኮ ሚስቴ ካላደረኩሽ እያላት ነው። በቴክስት የተለያዩ መልዕክቶችን ሲልክና ፍላጎቱን ሲገልጽ መቆየቱን የሚያወሱት ቤተሰቦቿ በዚህ ዘመን የጠለፋ ወንጀል ይፈጸማል ብለው በፍጹም እንዳልጠበቁ ይናገራሉ።

የሃዋሳ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ የጸጥታ አካላ ጉዳዩን ያልሰማ የለም የሚሉት ቤተሰቦቿ፥ መረጃው እንዴት እንደሚሾልክ ባናውቅም ደብዛውን አጥፍቶ ስምንት ቀናት መቆጠራቸውን ያነሳሉ።ጠላፊው ሊልካቸው ካሰባቸው ሽማግሌዎች ውስጥ በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ውስጥ ከፍተኛ የስራ ድርሻ ያላቸው ግለሰብ እንደሚገኙበት በመጥቀስም፥ የህግ ያለህ እያሉ ነው ቤተሰቦቿ።

የጸጋ ቤተሰቦች ከጠላፊው ጋር ተመሳጥራ ያስጠለፈቻት ብለው የሚጠረጥሯትና በቁጥጥር ስር ውላ የነበረችው ባልደረባዋም በ30 ሺህ ብር ዋስ መውጣቷን ገልጸዋል።(ምንጭ፣ አልአይን)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ዶ/ር ደብረፂዮን‼️

የህወሓት ሊቀ መንበር ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል በትግራይ ክልል ምርጫ ‘በአስቸኳይ’ እንዲካሄድ ጠይቀዋል።

በፕሪቶሪያው ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት መሠረት በትግራይ የተቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ክልሉን መምራት የሚችለው ከስድስት ወር እስከ አንድ ዓመት መሆኑን ዶ/ር ደብረጽዮን በህወሓት የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ግንቦት 21/ 2015 ዓ.ም በወጣው ጽሁፍ አስታውሰዋል።
በፓርቲው እና በጊዜያዊ አስተዳደሩ ሊሰራ የሚገባው ትልቁ ስራ የትግራይን ክልል በአስቸኳይ ማረጋገጥ ነው ሲሉም ተደምጠዋል። በዚህ ዙሪያ ከፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ ጋር ​​ተወያይተናል።

መሬታችንን(ወልቃይት እና ራያ) እንመልሳለን አሉ ግን መቼ ነው የሚመለሰው? ካስረከቡንም ከክረምት በፊት  መሆን አለበት።

የእርዳታ አቅርቦት ሌላው የተነሳው ጉዳይ ነው።ለምሳሌ በሽሬ የሚገኙ ተፈናቃዮች በአስር ወራት ውስጥ አንድ ጊዜ ብቻ እርዳታ ያገኛሉ። ጉዳዩን በምሬት አንስቷል።

በአስተዳደርና በጸጥታ ጉዳይም የተጠያቂነት ጉዳይ ተነስቷል። መቀዛቀዙ በአጠቃላይ በህዝባችን ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም።

ለሰላም መጠንቀቅ ጥሩ ነው ነገር ግን ግፍ በመናገር ለአለም መታወቅ አለበት።

(የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ከተናገሩት)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


አሳዛኝ ዜና‼️🕯🕯

በአርሲ ሀገረ ስብከት በጢዮ ወረዳ በዴራ አማኑኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን "ሸኔ" በተባለ ታጣቂ ቡድን በኦርቶዶክሳዊያን ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ መፈፀሙን ተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ዘገበ!

በአርሲ ሀገረ ስብከት በጢዮ ወረዳ በጨፌ ሚሶማ ቀበሌ ገበሬ ማኀበር ( #ከአሰላ ከተማ በቅርብ ርቀት የሚገኝ) በዴራ አማኑኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን በግንቦት 20 ለ 21 ቀን 2015 አጥቢያ ከሌሊቱ 5 ሰዓት ጀምሮ በኦርቶዶክሳዊያን ላይ ጥቃት ደርሷል።

የዚህም ጥቃት ሰለባ የሆኑትና በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ የተፈጸመባቸው ቄስ ታደለ የቡልጋወርቅ እድሜ 46 ሲሆኑ የስድስት ልጆች አባት እና የቤተሰብ ኃላፊ ፣ ቄስ ካሱ መንገሻ እድሜ 72 አዛውንት ሲሆኑ የአራት ልጆች አባት እና የቤተሰብ ኃላፊ ፣ ወጣት እንዳለ የቡልጋወርቅ እድሜ 34 የአንድ ልጅ አባት ፣ አቶ አድነዉ ቶላ የቤተክርስቲያን የጥበቃ ሠራተኛ ሲሆኑ እድሜያቸውም 55 አመታቸው እና የሁለት ልጆች አባት ናቸው ሲሆኑ በጥይት በግፍ ገድለዋቸዋል።

በተጨማሪ ፋንታሁን ዳኛቸዉ እና ስንታየሁ ዳንኤል የ12 ዓመት ሴት ልጅ አፍነው ወስደው ለመልቀቅም ቤተሰቦቻቸውን ገንዘብ እንዲከፍሉ በመጠየቅ ላይ እንደሚገኙ ተዘግቧል።

በአከባቢው እና በአቅራቢያው ያሉ ንፁሀን ዜጎችም ለደህንነታቸው ስጋት እንዳደረባቸው እና መንግስት አስፈላጊውን ጥበቃ እንዲያደርግላቸው በአፅንኦት ጠይቀዋል።
ፎቶ - ስምዐ ተዋሕዶ

(ምንጭ ፣ ተሚማ)
    

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


በሹመኛ ጠባቂ ስለተጠለፈችው ሴት ተጨማሪ መረጃ!

የተጎጂዋ ቤተሰቦች እንደተናገሩት፤ የግል ተበዳይ በቤተ ክርስቲያን ደንብ መሰረት የጋብቻ ትምህርት ከወደፊት የትዳርአጋሯ ጋር ተምረው በማጠናቀቅ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ ለመጋባት ቀን ቆርጠው የቤት ዕቃዎችን በማሟላት ላይ ነበሩ። ይሁን እንጂ ጠለፋውን አድርሷል በሚል በፖሊስ የሚፈለገው ተጠርጣሪ የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ ይዝትባትና ያስፈራራት እንደነበር ተሰምቷል።

የግል ተበዳይ ቤተሰቦች ፀጋ ያለችበትን ባለማወቃቸው ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከመሆናቸውም ባለፈ የተበዳይ አባት በጠና ታመው ሕክምና እየተከታተሉ ስለሚገኙ ጉዳዩ ቤተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩንም ጨምረው ገልጸዋል።

ግንቦት 12/2015 የግል ተበዳይ ፀጋ በላቸው፤ ከሥራ ወጥታ ወደ ግል ጉዳይ በምታመራበት ወቅት በተለምዶው አሮጌው #መነሃሪያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጠለፋው እንደተፈፀመባት በሐዋሳ ከተማ አስተዳደር የመነሐሪያ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል። ፖሊስ አያይዞም፤ የተበዳይን ሁኔታ በተመለከተ በአሁኑ ሰዓት በውል የሚታወቅ ባይሆንም ፖሊሳዊ ሥራዎችን በከፍተኛ ርብርብ እና ቅንጅት ከሌሎች አካላት ጋር በመሆን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጿል።

ተጠርጣሪው ተበዳይን ጠልፎ ከተሰወረ በኋላ ወደ ትውልድ መንደሩና ከሐዋሳ በቅርብ ርቀት ወደምትገኘው #ሐገረሰላም ወደምትባል መንደር ይዞ እንደሄደ ለማወቅ ተችሏል። ይህንንም ተከትሎ ፖሊስ መረጃው እንደደረሰው ወደ አካባቢው በስውር ቢያቀናም ተጠርጣሪ መረጃው ቀድሞ ደርሶት ስለነበር ስፍራ እንደቀየረ ታውቋል።

ግለሰቡ የፖሊስን እንቅስቃሴ ቀድሞ #መረጃው እንዲደርሰው የሚያደርጉ አካላት ከመኖራቸው ጋር ተዳምሮ የክትትል ሥራውን አስቸጋሪ ማድረጉንም ፖሊስ አስታውቋል። 

- CR(ምንጭ ፣ አዲስ ማለዳ) -

@ethio_mereja_news


በሀዋሳ ልታገባ ቀናቶች ብቻ የቀሯት ወጣት መጠለፏ ተሰማ!

የዳሽን ባንክ ሰራተኛና የሀዋሳ አላሙራ ሙሉወንጌል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆነችው ፀጋ በላቸው በሀዋሳ ከንቲባ የግል ጠባቂ በሆነው ተጠርጣሪ ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ታግታ(ተጠልፋ) ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዷም ተገልጿል።


ፀጋ በላቸው ትባላለች፤ ትውልድና እድገቷ በወልቂጤ ከተማ ሲሆን ግንቦት 15 2015 ዓ.ም ስራዋን አጠናቃ ወደቤቷ በምታመራበት ሰዓት (አሮጌው መነሀሪያ አከባቢ፤ ከምሽቱ 1 ሰዓት) ከዚህ ቀደም ይዝትባት በነበረና የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ ፀጋዬ ቱኬ የግል ጠባቂ በሆነው ተጠርጣሪ ኮንስታብል የኋላመብራት ወ/ማሪያም ታግታ(ተጠልፋ) ወዳልታወቀ ቦታ ተወስዳለች። ከተጠለፈች 6 ቀን አልፏታል።

ጉዳዩን ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት በማሳወቅና የፍርድ ቤት መጥሪያ በማውጣት ተጠርጣሪውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ለማዋል የተደረገው ሙከራ ጥረት ካለማስገኘቱም በላይ የህግ አካላት ድርጊቱን ቀለል አድርገው ለመመልከት ሞክረዋል።

በሐዋሳ ከተማ ውስጥ ተመሳሳይ ድርጊቶች እየተበራከቱ መምጣቸው የከተማዋን ስም የሚያጎድፍ፤ የሴት እህቶቻችንን የግል ውሳኔ የማያከብርና የነዋሪውን ነፃነት የሚጋፋ በመሆኑ የከተማው፣ የክልሉና የሚመለከታቸው የፌደራል መስሪያ ቤቶች ይህንን ለመፍታት ተገቢውን ርቀት በመጓዝ ተጠርጣሪውን ለህግ እንዲያቀርቡልን እንጠይቃለን።

ቤተሰቦቿ በከባድ ጭንቀት ውስጥ ይገኛሉ።
ፍትህ ለእህታችን (ቤተሰቦቿ እና ጓደኞቿ )
Share | ሼር

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


መርጌታ ደረሰ ባሕላዊ መድሀኒት ቀማሚ ባሉበትሆነዉመጠቅይችላሉ ቦታዉ እሩቅነዉ ካገርዉጭነኝብለዉእዳይጨነቁ ። ያስታዉሱ👇
ከምንሰጣቸዉአገልግሎቶች በጥቂቱ
1, ዓቃቤ_ርእስ (ጠላት እንዳይጎዳን የሚጠብቅ)
2, ለመክስተ_ምስጢር (ትምህርት የሚያጎብዝ)
3, ለመስተፋቅር
4 ;ለግርማ_ሞገስ (ሰው እንዲያከብረን እንዲወደን)
5,የትዳር አጋር ላጣ ወይም ላጣች
የሚያስገኝ
6,ለምስያጥ ለገበያ (ገበያ እንዲቀናን እንድናገኝ)
7, መንድግ(በገበያ ገንዘብ ማግኛ)
8, ለዓይነ_ጥላ (የፍራቻ መንፈስ ማስለቀቂያ)
9,ለእግረ_መልስ (ጥሎ ለጠፋ ሰው መመለሻ ማምጫ
10,ለሙግት
11,ለስንፈት ወሲብ
12,ለጥይት (ጥይት የማያስመታ)
13, መንስኤ_እስኪት (ለወንድ የመራቢያ አካሉ ለደከመ ላነሰ)
14,ህገ_ጠብቅ (የትዳር አጋራችን ወደሌላ እንዳይሄድ የሚያስር
እንዳይዘሙት የሚከለክል)
15;ለአዙሪት
16,የወገብ ህመም
17;ለደም ግፊት
18;በመኝታ ሽንት ለሚያመልጠው
19;የአእምሮ ጭንቀት፣ ድብርት፣ ከሰው  መገለል፣እንቅልፍ ማጣት;ክብደት ለመቀነስ
20; የሳይነስ ህመም
21;የሆድ ድርቀትና የሆድ ህመም
22;የወር አበባ ችግር ካለ ን
23;ለከፍተኛ ራስ ምታት
24;ማስታወስ፣ንቃት፣ተነሳሽነት ለሌላቸው
25;ለድምፅ መታፈን
26;ከአጫሽነት ለመላቀቅ
27;ራስን ስቶ በስቃይ ለሚኖር
28,ለስኳር
39ለፎረፎር
30,ለጸ መሰውር
31,ለቁማር
32,ለሁሉ መስተፍቅር
33,ለስራ እድል የሚሆን
34,ለዛር ዉላጅ ለተዋረሰው
35,ለኤችአይቪ መድሀኒት
36,ነገረ ሚስጥርራት (ሚስጥር የሚነግር)
በጥቂቱ ይህን ይመስላል እርስወ ምን ይፈልጋሉ??
👉0968320296❤ይደውሉልን ወይም በቴሌግራም አካውንታችን  https://t.me/derese68


ዐበይት ዜናዎች‼️

1፤ ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በጦርነቱ ትምህርት ያቋረጡ የትግራይ ሕጻናት የትምህርት ቁሳቁሶችን ለማሰባሰብና የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት በአዲስ አበባ እርዳታ ማሰባሰብ ሊጀምር መኾኑን ዋዜማ ሰምታለች። ፓርቲው ይህንኑ እንቅስቃሴ የሚጀምረው ነገ ሲኾን፣ ዕቅዱ በክልሉ ከ10 ሺህ በላይ የተዘጉ ትምህርት ቤቶችን እንደገና ትምህርት ለማስጀመር ያለመ መኾኑን ዋዜማ ተረድታለች። በክልሉ ከ2.3 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ውጭ መኾናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ በቅርቡ ገልጦ ነበር።

2፤ ብሄራዊ የምክክር ኮሚሽን ዛሬ በሲዳማ ክልል የምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎችን መለየትና አጀንዳ መሰብሰብ እንደሚጀምር ትናንት ሀዋሳ ላይ በሰጠው መግለጫ መናገሩን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ኮሚሽኑ የመጀመሪያውን ዙር የተሳታፊ ልየታና አጀንዳ የመሰብሰብ ሥራ የሚያካሂደው፣ በሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና ሐረሬ ክልሎችና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እንደኾነ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ኮሚሽኑ ትግራይ ክልልን ጭምር በብሄራዊ የምክክር ሂደቱ ለማካተት፣ ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በቅርቡ መወያየቱን ገልጧል ተብሏል።

3፤ በኢትዮ-ጅቡቲ መስመር የሚመላለሱ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ታጣቂዎች የሚያደርሱባቸው ጥቃት እየተባባሰ ስለመሄዱ መናገራቸውን ቪኦኤ ዘግቧል። አሽከርካሪዎቹ ታጣቂዎች አግተው ከፍተኛ ገንዘብ ከመጠየቅ ጀምሮ እስከ ግድያ የሚደርስ  ጥቃት እንደሚፈጽሙባቸው መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ትራንስፖርት ሚንስቴር ግን፣ ለችግሩ መፍትሄ እንደሚፈልግ ቀደም ሲል ቃል ገብቶ ነበር።

4፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወሰኑ አገልግሎት ሰጪ ተቋማቱን ሥራ ለግል ተቋማት በውክልና ሊያስተላልፍ መኾኑን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ሥራቸውን ለግል ተቋማት የሚያስተላልፉ ሠራተኞች ወደሌላ መስሪያ ቤት ይዛወራሉ መባሉን ዘገባው አመልክቷል። የከተማዋ ፐብሊክ ሰርቪስ ኮሚሽን በውክልና ከሚያስተላልፋቸው አምስት ተቋማት መካከል፣ የንግድ፣ ትራንስፖርት፣ ገቢዎችና የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮዎች ይገኙበታል ተብሏል። የካቲት 12፣ ዳግማዊ ምኒሊክና ዘውዲቱን ጨምሮ ስድስት ሆስፒታሎችም ለግል ተቋማት በውክልና እንደሚተላለፉ ዘገባው አመልክቷል። [ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


🛑 ♨️ USA WORK VISA 2023 🛑💯✔️  
---—-----------------------      Congragulation For Ethiopian

✅ ከ 10,000- በላይ ክፍት ቦታዎች በ0 አመት እና በልምድ

✅ Number of Positions: 10,000+ positions 0 EXP and with Exp

✅ በተለያዩ የትምህርት ደረጃዎች የወጣ የስራ ማስታወቂያ

🔺United States Of America
🔺0 Year Experiance And Experianced
🔺2 Years Contrat
🔺Quantity 10,000+
🔺Salary:  Based On Profation
🔺Full Sponsership By US Government
🔺

🟥 ፈጥነው ታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ

👇👇👇👇👇Apply Now👇👇👇👇👇👇👇
                        👇👇👇👇         
https://addiszemenvacancy.com/2023/04/27/usa-jobs-recruitment-2023-2024-apply-for-ongoing-job-vacancies/


----------Follow Our Website------
                            👇👇👇👇👇👇
         https://addiszemenvacancy.com

----------Join Our Telegram-------
                               👇👇👇👇👇
     https://t.me/Addis_Zemen_Vacancy


NewsAlert‼️

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ እየሱስ በጋምቤላ ክልል ባንድ የቤተክርስቲያኗ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የደቡብ ሱዳን ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ግንቦት 12 ቀን ባደረሱት ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች እንደተገደሉ ዛሬ ባወጣችው መግለጫ አስታውቃለች።

ጥቃቱ 11 ሰዓት ገደማ የተፈጸመው፣ በምዕራብ ጋምቤላ ቤተል ሲኖዶስ አገልግሎት ክልል "ማታራ" በተባለ ቀበሌ ውስጥ መኾኑን መግለጫው አመልክቷል።

ከ2 ሺህ 700 በላይ የመንፈሳዊ ጉባዔው ተሳታፊ ወጣት ሴቶች፣ እናቶችና ሕጻናት የዕለቱን መንፈሳዊ መርሃ ግብር አጠናቀው ለእራት በተቀመጡበት ወቅት፣ ድንገት የደረሱ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች ሕጻናትን አፍነው ለመውሰድ በሞከሩበት ወቅት በተፈጠረ ግብግብ፣ መንፈሳዊያኑ ላይ ተኩስ እንደከፈቱ ቤተክርስቲያኗ ጨምራ ገልጣለች።

ከተገደሉት መካከል አንዲት ሕጻን እንደምትገኝበትና፣ በጥቃቱ የቆሰሉ በርካታ ምዕመናን ጋምቤላ ሆስፒታል ውስጥ ሕክምና ላይ እንደኾኑም በመግለጫው ላይ ተገልጧል። [ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_new
s


ሙሽራ አጅበው ሲሄዱ የነበሩ ስድስት ሰዎች በመኪና አደጋ ህይወታቸው አለፈ

በሐረሪ ክልል ትናንት ምሽት በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ።

አደጋው የደረሰው ትናንት ምሽት አራት ሰዓት ተኩል አካባቢ በክልሉ ሶፊ ገበሬ ማህበር ቂሌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የከፍተኛ አደጋ መርማሪ ዋና ሳጅን ረስተም መዝሃር ገልጸዋል።

የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ3- 88036( ኦሮ) የጭነት አይሱዙ እቃ ጭኖ ከአወዳይ ወደ ጅጅጋ በመጓዝ ላይ እንዳለ ሙሽራን አጅበው የነበሩ የአካባቢ ነዋሪ ሰርገኞችን  ገጭቶ መንገዱን ስቶ በመገልበጥ አደጋው መድረሱን አስረድተዋል።

በአደጋውም ዕድሜያቸው ከ20 እስከ 25 የሆኑና አጃቢ የነበሩ የስድስት ሰዎች ህይወት ማለፉንና ከሟቾቹም መካከል አምስቱ ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም በስምንት ሰዎች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ዋና ሳጅን ረስተም  ጠቁመዋል፡፡

አደጋ ያደረሰው የተሽከርካሪው ሹፌር ለጊዜው ከአካባቢው ሸሽቶ ቢያመልጥም ለመያዝ ክትትል እየተደረገበት መሆኑን ጠቁመው፤ የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

የትራፊክ አደጋን ለመከላከል አሽከርካሪዎች ፍጥነታቸውን በልክ አድርገው እንዲያሽከረክሩ ዋና ሳጅኑ አሳስበዋል ሲል ኢዜአ ነው የዘገበው።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገለጸ‼️
ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ ተሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታወቀ።

በባለሥልጣኑ የተሽከርካሪ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በድሉ ሌሊሳ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ መንግሥት ሕገወጥነትን ለመከላከል በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ሲሆን፤ ከዚህም ውስጥ አንዱ ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎችን የመለየት ሥራ አንዱ ነው። ይህም ከተጀመረ አንድ ወር ሆኖታል።

‹‹ባለሥልጣኑ ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን ባደረገው ጥናት በባለሥልጣኑ የሚመዘገበው የገንዘብ መጠን እና ለገቢዎች ቢሮ የሚቆረጠው ደረሰኝ ተመሳሳይ ያለመሆን ሁኔታዎች አሉ። በዚህም በተለይ የአዲስ ተሽከርካሪዎች ዋጋ የሚቆረጥበት ደረሰኝና ገዢዎች ለመኪናው የሚከፍሉት ዋጋ ሰፊ ልዩነት ያለው መሆኑ ተረጋግጧል፡፡›› ብለዋል።

በዚህም መንግሥት ከተሽከርካሪዎች ግዥና ሽያጭ ማግኘት የሚገባውን የታክስ ገቢ እያገኘ አለመሆኑን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፤ ይህንን እና መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎችን የመለየት ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል።

‹‹ተቋሙ በተለያዩ ጊዜያት ኹለት አይነት ሕገወጥ ተግባራት ይገጥሙታል›› ያሉት ኃላፊው፤ እነሱም ከክልል በዝውውር የሚመጡ መኪናዎች ላይ እና በተጭበረበረ ሰነድ የተመዘገቡ መኪናዎች መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ይህንን ለመከላከል የሚያግዝ ዘመናዊ ሥርዓት የመኪናዎቹን ሕጋዊነት የማጣራት ሥራ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

‹‹ይህም የማጣራት ሥራው የሚሠራው ካለፉት ዘጠኝ ዓመታት ጀምሮ ነው፡፡›› ያሉት በድሉ፤ ከዚህ በፊት አንድ የመኪና ሻጭ በሥሙ የነበረውን መኪና ለሌላ ሰው ሲያስተላልፍ የማጣራት ሥራ እንዳልተሠራ በመግለጽ፤ ‹‹በዚህም መንግሥት ማግኘት የሚገባውን ታክስ አላገኘም። አሁን ግን ከጉሙሩክ ኮሚሽን ጋር በጋራ በመሆን አዲስ ሥርዓት መዘርጋት ተችሏል፡፡›› ብለዋል።

‹‹ሥርዓቱም መንግሥት ከተሽከርካሪዎች ማግኘት የሚገባውን ታክስ እንዲያገኝ ከማድረግ ባለፈ መኪና ገዢዎች እንዳይጭበረበሩ እና መንግሥት ሕገወጥነትን ለመከላከል የሚያደርገውን ጥረት የሚያጠናክር ነው። በሂደቱም በሕገወጥ መንገድ የገቡ መኪናዎች የሚወረሱ ይሆናል፡፡›› ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም፤ ‹‹የአዲስ መኪና ገዢዎች የሚከፍሉት ዋጋ በደረሰኙ ላይ መጠቀሱን በማረጋገጥ ሊገዙ ይገባል። ይህንን ማድረግ ለገዢው በርካታ ጠቀሜታ የሚያስገኝ ከመሆኑ ባለፈ የሚሰበሰበው ገቢ ለከተማዋ መሠረተ ልማት የሚውል በመሆኑ በኃላፊነት ሊታይ ይገባል›› ሲሉም ተናግረዋል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ በሥራ ላይ እያለ በኤሌክትሪክ አደጋ ሕይወቱ ማለፉ ተነገረ

በትላንናው ዕለት እሁድ ግንቦት 20/2015 በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ዓለም ባንክ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በኤሌክትሪክ አደጋ የአንድ ሰዉ ሕይወቱ ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

አደጋዉ ያጋጠመዉ ወጣት እድሜዉ 28 ዓመት የሆነ የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኛ ሲሆን፤ ባለገመድ የስልክ መስመር በመዘርጋት ላይ እያለ ከከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ጋር ተገናኝቶ የሞት አደጋ መድረሱን የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።

በተመሳሳይ ዓርብ ግንቦት 18/2015 በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፖርክ ሰራተኛ በሥራ ላይ እንዳለ በኤሌክትሪክ አደጋ ሕይወቱ ማለፉ ተነግሯል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ዐበይት ዜናዎች‼️

1፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግሥት ለማዳበሪያ ግዢ የመደበው በኩንታል 15 ቢሊዮን ብር ድጎማ አልደረሰም በማለት መውቀሳቸውን ሪፖርተር ዘግቧል። ገንዘቡ ከባንክ ባለመውጣቱ፣ አርሶ አደሮች በነፍስ ወከፍ ማግኘት የነበረባቸውን ከ2 ሺህ እስከ 15 ሺህ ብር የሚደርስ ድጎማ ሳያገኙ መቅረታቸውን ግብርና ሚንስቴር ለምክር ቤቱ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ገልጸዋል ተብሏል። ግብርና ሚንስቴር በበኩሉ፣ ድጎማው የተለቀቀው አርሶ አድሮች ማዳበሪያ ከገዙ በኋላ እንደኾነ ገልጧል። በኦሮሚያ ክልል 2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል፣ በአማራ ክልል 1 ነጥብ ሦስት ሚሊዮን ኩንታል ለአርሶ አደሮች ሳይደርስ መቅረቱንም ሚንስቴር መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል።

2፤ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ከሱዳኑ ግጭት ሸሽተው ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ሱዳናዊያን ስደተኞች በስደተኛ ካምፖች የሚቀመጡ ከኾነ የመግቢያ ቪዛ እንደማይጠይቅ አስታውቋል። ስደተኞች ከመጠለያ ውጭ ኢትዮጵያ ውስጥ የመቆየት ወይም ወደ ሦስተኛ አገር የመሻገር ፍላጎት ካላቸው ግን፣ መግቢያ ቪዛ እንደያስፈልጋቸው ሚንስቴሩ ገልጧል። ግጭቱ ከተቀሰቀሰ ወዲህ፣ እስካለፈው ዓርብ ድረስ 31 ሺህ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ እንደገቡ የዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት መረጃ ያመለክታል።

3፤ የናይጀሪያ አየር መንገድ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ በተሰጠው አንድ ቦይንግ-737 አውሮፕላን አማካኝነት ከ10 ዓመት በኋላ እንደገና መቋቋሙን ይፋ አድርጓል። ላለፉት 10 ዓመታት በኪሳራ የተነሳ ከበረራ ውጭ ኾኖ የቆየው አየር መንገዱ፣ እንደገና ተዋቅሮ በረራ እንዲጀምር የተያዘለት ቀነ ገደብ ዛሬ ፕሬዝዳንት ሞሐመዱ ቡሃሪ ሥልጣን በሚያስረክቡበት ዕለት ነው። ኾኖም የአገሪቱ የግል አየር መንገዶች የናይጀሪያ አየር መንገድና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የፈጠሩትን አጋርነት በመቃወም የመሠረቱት ክስ ገና መፍትሄ ባለማግኘቱ፣ አየር መንገዱ ገና በረራ አልጀመረም። አየር መንገዱን በ5 አውሮፕላኖች ይፋ እንደሚደረግ ተገልጦ የነበረ ቢኾንም፣ ይህ ግን ሳይሳካ ቀርቷል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየር መንገዱ ውስጥ የ49 በመቶ ድርሻ የያዘ ሲኾን፣ የናይጀሪያ መንግሥት ደሞ የ5 በመቶ ድርሻ አለው።

4፤ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት እና አብዛኞቹ የፌደራል ግዛቶች መንግሥታት የአገሪቱ መንግሥታዊ አወቃቀር ፕሬዝዳንታዊ ብቻ እንዲኾን መስማማታቸውን አስታውቀዋል። የስምምነት ሰነዱ የተፈረመው፣ ፌደራል መንግሥቱና የፌደራል ግዛቶች ለቀናት የምክክር ጉባዔ ካካሄዱ በኋላ ነው። ስምምነቱ የጠቅላይ ሚንስትርነትን የሥልጣን ቦታ ባማስቀረት፣ ፕሬዝዳንቱ ሁሉንም ሥልጣኖች እንዲጠቀልል የሚያደርግ ነው። ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ቅራኔ ያላት ፑንትላንድ ራስ ገዝ ግን፣ ሰነዱን አልፈረመችም። ስምምነቱ ቀጥተኛ ይኾናል ተብሎ ከሚጠበቀው የ2026ቱ ጠቅላላ ምርጫ በፊት ተግባራዊ ይኾናል የተባለ ሲኾን፣ በቅድሚያ ግን የአገሪቱና የግዛቶቹ ፓርላማዎች ሰነዱን ማጽደቅ ይጠበቅባቸዋል።

5፤ የሱዳን ግጭት አደራዳሪዎች አሜሪካ እና ሳዑዲ ዓረቢያ ሁለቱ ተፋላሚ ወገኖች ባለፈው ሳምንት የደረሱበትን የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያራዝሙት በጋራ ጠይቀዋል። ለሰብዓዊ ዓላማ ሲባል ባለፈው ሰኞ የተደረሰው ተኩስ አቁም፣ ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ከ45 ደቂቃ ላይ ይጠናቀቃል። ተኩስ አቁሙ ግን ከጅምሩም ሙሉ በሙሉ ባለመከበሩ፣ ግጭቱ እስካሁንም እንደቀጠለ ነው። [ዋዜማ]

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ነባር መንደሮችን በማፍረስ የሚከናወኑ የልማት ስራዎች የተጠኑ እና የከተሜነት መርህን የተከተሉ አይደለም ተባለ

መንግስት በኮንዶሚኒየም ግንባታ እና በሌሎች የልማት ፕሮጀክቶች በተለይም በአዲስአበባ እና በዙሪያዋ ነባር መንደሮችን በማፍረስ የሚከናወኑ ስራዎች የከተማ ልማት መርህን የተከተሉ አለመሆናቸውን የፍሊንት ስቶን ሪልስቴት ም/ል ስራ አስኪያጅ አቶ ብሩክ ሽመልስ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል።

ፍሊንት ስቶን ፤ ከአመታት በፊት በተለይም በአዲስአበባ የሚገኙ ነባር መንደሮችን በዘመናዊና የከተማዉን ደረጃ በሚጠብቅ መልኩ አፍርሶ ነዋሪዉ ከቀዬዉ ሳይፈናቀልና ወፈ ሌላ ቦታ ሳይዘዋወር ግንባታ ለማድረግ እቅድ ይዞ የነበረ ቢሆንም በአዲስአበባ ከተማ መስተዳድር በኩል ትብብር ባለማግኘቱ ተግባራዊ ሳይደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።

ከተማዋን ማስተዳድሩ ከስርዓት ስርዓት ቢለዋዋጥም አሁንም በአዲስአበባ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ነዋሪዉን ወደ ሌላ አካባቢ እንዲፈናቀል የሚያስገድዱ ሆነዉ ዘልቀዋል። በተለይም በመኖሪያ ቤት ግንባታ ላይ ይህ ችግር በስፋት ይስተዋላል። ይህንንም እቅድ ተግባራዊ ለማድረግ ከግንባታ ፈቃድ ጋር በተያያዘ በአንድ ካርታ ላይ ብቻ ግንባታ መፈቀዱ እና ተጨማሪ መመሪያዎች በማስፈለጋቸዉ ፣ የቀበሌ ቤቶች ባለቤትነት ፣ በግል የመሬት ይዞታ ላይ የቀበሌ ቤቶች መገኘታቸዉ ዉስብስብ እንዳደረገዉና እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ መቸገሩን አንስተዋል።

እንደ አቶ ብሩክ ገለጻ ፤ ከተማ ፈርሶ ነዋሪዉም አንዲበተን ሲደረግ የማህበረሰቡ ማንነትን የሚያጠፋ እና የከተማዉን መገለጫ የሚያሳጣ መሆኑን ጠቅሰዋል። ለዚህም ምክኒያቱ  የከተማ አመሰራረትና ግንባታ ላይ መሰረታዊ ግንዛቤ የጎደለዉ አካሄድ ነዉ ብለዋል።

ፍሊንት ስቶን ፤ በአዲስአበባ ተግባራዊ ለማድረግ ያልቻለዉን እቅድ ወደ በኦሮሚያ ፣ አማራ እና ትግራይ ክልሎች ከተማና ከተሜነትን ተግባራዊ ለማድረግ የራሱን እቅድ አሰናድቶ በተለይም በገጠሩ ክፍል የሚገኘዉን ሰፊ የገበሬ ማህበረሰብ በማዘመንና የግብርና ስራዉን ጎን ለጎን እንዲያስኬድ የሚያስችል መንገድ ቢቀይስም ብቻዉን ግን ተግባራዊ ሊያደርገዉ አልቻለም ሲሉ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል። (ዳጉ_ጆርናል)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን በድጋሚ የቱርክ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ!!

ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን በቱርክ ለሁለተኛ ዙር የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በማሸነፍ በድጋሚ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ከ20 ዓመታት በላይ ቱርክን የመሩት ኤርዶኻን በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሁለተኛ ዙር ምርጫ ብርቱ ተፎካካሪያቸው የነበሩትን ከማል ኪሊዳሮግሉን በማሸነፍ ነው ሀገሪቱን ለቀጣይ አምስት ዓመታት መምራታቸውን ያረጋገጡት ሲል አልጀዚራ የሀገሪቱን ሚዲያ ጠቅሶ ዘግቧል።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


#Update

ዛሬ በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በድጋሜ ህዝቡ ድምፁን ሲሰጥ ውሏል።

በአሁን ሰዓት የድምፅ ቆጠራው እየተካሄደ ይገኛል።

እስካሁን ባለው 96.01 በመቶ የድምፅ ሳጥን ተከፍቶ በተካሄደ ቆጠራ ፦

- ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን 52.28 % 
- የኤርዶጋን ዋነኛ ተቀናቃኝ ክሊክዳርጎሉ 47.72 % ድምፅ አግኝተዋል።

በቱርክ ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው ምርጫ ተወዳዳሪዎች የሚፈለገውን ያህል  ድምጽ (ከ50 በመቶ በላይ) ማግኘት ባለመቻላቸው ምርጫው በድጋሚ እንደሚደረግ መገለፁ የሚዘነጋ አይደለም።

@sheger_press
@sheger_press


በቦረና እና ሱማሌ የድርቁ ተፅዕኖ ተባብሶ ቀጥሏል ተባለ!

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እንዲሁም በሱማሌ ክልል ያለው የድርቅ ተፅዕኖ ተባብሶ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ኮሚሽኑ በኦሮሚያና ሱማሌ ክልሎች የተከሰተው ድርቅ ባስከተላቸው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዙሪያ ባለፈው ሐምሌ ወር ባቀረባቸው ምክረ ሐሳቦች አተገባበር ላይ ሲያደርግው የቆየውን ክትትል አስመልክቶ ሪፖርት አውጥቷል፡፡ በዚሁ ሪፖርት በቦረና ዞን በሦስት ዓመት ውስጥ ባሉ አምስት የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ባለመዝነቡ የድርቁ ተፅዕኖ መጨመሩን አመላክቷል፡፡

በዞኑ 870 ሺሕ ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ እና 900 ሺሕ የሚጠጋ የኅብረተሰቡ ክፍል ደግሞ አስቸኳይ የውሃ ምላሽ ያስፈልዋል ተብሏል፡፡በተጨማሪም ከምግብ እጥረት የሚመነጩ የጤና እክሎች በሕጻናት፣ በእርጉዝና በሚያጠቡ ሴቶች እንዲሁም በአረጋዊያን ላይ መከሰታቸውን አስገንዝቧል፡፡

በቦረና ዞን 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚሆኑ የቤት እንስሳት በድርቁ ሳቢያ የሞቱ ሲሆን፤ ይህም በገንዘብ ሲተመን ወደ 33 ቢሊዮን ብር ይሆናል ተብሏል፡፡ ይህን ተከትሎም 60 ሺሕ የሚሆኑ አባወራዎች እንስሶቻቸውን ሙሉ በሙሉ ያጡ መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡ኮሚሽኑ አክሎም በዞኑ የድርቁ ተፅዕኖ በመባባሱ ወደ 69 ሺሕ የሚሆኑ አባወራዎች ወይም ከ378 ሺሕ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን በመጥቀስ፤ በዚሁ ሳቢያ ሴቶች ለጾታዊ ጥቃቶች ይበልጥ ተጋላጭ ሆነዋል ነው ያለው፡፡

በሶማሌ ክልል ያለው ወቅታዊው የድርቁ ተፅዕኖም በኹሉም የክልሉ 11 ዞኖች ጨምሮ ይገኛል ብሏል፡፡ለሦስት ተከታታይ የዝናብ ወቅት ዝናብ ባለመዝነቡ የድርቁ ተፅዕኖ በዳዋ፣ በሊበን፣ በአፍዳር፣ በኮራህይ እና በጀረር ዞኖች ይበልጥ የጸና መሆኑን ኮሚሽኑ ጠቅሷል፡፡ አያይዞም በክልሉ ኹለት ሚሊዮን የሚደርሱ የቤት እንስሳት መሞታቸውን እና በሸበሌ ዞን ብቻ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 50 ሺሕ የሚሆኑ የቤት እንስሳት በድርቁ ምክንያት እንደሞቱ አመላክቷል፡፡

በክልሉ 3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የውሃ ምላሽ እንዲሁም 4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ የምግብ ድጋፍ የሚፈልጉ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡እንዲሁም ከ112 ሺሕ በላይ ሕጻናት ለምግብ እጥረት የተጋለጡ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ አኃዝ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ14 በመቶ ጭምሯል ነው የተባለው፡፡

የክልሉ ማኅበረሰብ አስቸኳይ እርዳታ ፍለጋ ይበልጥ ተፈናቅለው ወደ መጠለያ ጣቢያዎች እየገቡ እንደሚገኝ እንዲሁም በድርቁ የተነሳ ከ600 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል በመዘጋታቸው ከ90 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ተጎጂ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡ሆኖም በኹለቱም ክልሎች በድርቁ ጉዳት ለደረሰባቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እየቀረበ ያለው ሰብዓዊ እርዳታ ከደረሰው መጠነ ሰፊ ጉዳት ጋር ተመጣጣኝ አለመሆኑ ተጠቅሷል፡፡

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_new
s


"የመከላከያውን ሸክም እናቅል። ሰልፍ እና መፈክር ይቁም"
(ታዬ ደንደአ አሬዶ)

እስቲ እንነጋገር እውነት የሀገር መከላከያን እንወዳለን....? አዎን እንወዳለን ሁሉም ወንድሞቻችን እና ልጆቻችን ናቸው።በሰላም ወተን መግባታችን በነሱ ነው እና ልንጠላቸው አንችልም እናከብራቸዋላን።ነገር ግን የሀገር መከላከያን ትክክለኛ ትርጉም ማወቅ እንጅ ሰልፍ እና የመፈክር ጋጋታ አያስፈልግም።

የእውነት መከላከያችንን የምንወድ ከሆነ ያለባቸውን ሸክም ልናቀል ይገባል። ይሄ ደሞ የሚሆነው እውነተኛ ሰላም እና እርቅ በመፍጠር የህዝብን ሰላም ስናረጋግጥ ነው።ከዛ በተረፈ ንፁሀንን እየገደሉ እና ጦርነት ከዚም ከዛም እያሞቁ "መከላከያን እንወዳለን" ማለት አይቻልም።

እውነት መከላከያን እንወዳለን ከሆነ ህዝብን በሰልፍ ማድከም አስፈላጊ አይደለም።ሰላም እና እርቅ በማውረድ ላይ እናተኩር። ከህወሃት ጋር ያደረግነውን ንግግር ከኦነግ ጋርም እናድርግ።የቤት ውስጥ ፀብ እናቁም ከጎረቤት ጋርም አንጋጭ።መከላከያ በቴክኖሎጂ እናዘምን የተጎዱትን እንካስ።

እናም እንዲህ እንላላን መከላከያ የመላው ህዝብ ሆኖ ሳለ በኦሮሚያ ብቻ ሰልፍ የሚደረገው ለምንድነው.??? እውነት እላቹሀለው ይህ ለኦሮሞ ህዝብም ለመከላከየውም ጥሩ አይደለም።
ሰላም ሰላም ሰላም ለሀገራችን!
Taye Dendea Aredo

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_new
s

10k 0 14 16 127

በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ እየተካሄደ ነው‼

በቱርክ በድጋሚ እየተካሄደ ባለው ፕሬዘዳናታዊ ምርጫ ቱርካውያን ፕሬዝዳንታቸውን እየመረጡ ነው።

በቱርክ ባለፈው ግንቦት 14 በተካሄደው ምርጫ ፕሬዝደንት ኤርዶጋን እና ዋና ተቀናቃኛቸው ክሊክዳርጎሉ አብላጫ ድምጽ ማግኘት ባለመቻላቸው ምርጫው በድጋሚ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመጀመሪያ ዙር ምርጫ ላለፉት 20 ዓመታት ቱርክን የመሩት ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን 49.5 በመቶ እንዲሁም ተቀናቃኛቸው ክሊክዳርጎሉ ደግሞ 44.9 በመቶ ድምጽ ማግኘታቸው ይታወሳል።

በዚህም ከ50 በመቶ በላይ ያመጣ እጩ ባለመኖሩ ምርጫው በዛሬው እለት በድጋሚ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በቱርክ እየተካሄደ ባለው ምርጫ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ያለው እጩ ለፕሬዝደንት ኤርዶጋን ድጋፉን በመስጠት ዋና ተቀናቃኝ የሆኑት ከማል ክሊክዳርጎሉ የሚደርስባቸውን ፉክክር እንዲጠነክርባቸው አድርጓል።

የኩርዶች ደጋፊ የሆነው ኤችዲፒ ፖርቲ ክሊክዳርጎሉን የደገፈ ሲሆን የኩርዲሽ እስላሚስት ደግሞ ኤርዶጋንን ደግፏል።
ፕሬዝደንት ኤርዶጋን በመጀመሪያው ምርጫ ተቀናቃኛቸውን ክሊክዳርጎሉን ስለመሩ እድል ከሳቸው ጋር ነች የሚል ግምት ተሰጥቷቸዋል።ክሊክዳርጎሉ ስድስት ፖርቲዎችን በያዘ ጥምረትና እና የኩርድ ፖርቲ በሆነው ኤችዲፒ ፖርቲ ይደገፋሉ።(via Al ain)

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news


በሙስና ወንጀል በተከሰሱ በ49 ግለሰቦች ላይ የፍርድ ውሳኔ ተላለፈ

በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሙስና ወንጀል ከተከሰሱ 53 ግለሰቦች መካከል በ49 ተከሳሾች ላይ የፍርድ ውሳኔ መተላለፉን የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቢ ህግ አስታዉቋል ።ተከሳሾች ከሙስና ጋር በተያያዘ ስልጣንን  ያለ አግባብ በመጠቀም ወንጀል በመንግሥት ገቢ ታክስ እና በመሬት አስተዳደር በተፈፀመ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለዋል ።

ውሳኔ የተላለፈባቸው 49 ግለሰቦች ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ ለግል ጥቅማቸው ለማዋል ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን በዚህም ጥፋታቸው ከሁለት ዓመት እስከ ሰባት አመት እስራት ተቀጥተዋል። በገንዘብ መቀጮ ረገድ ከ10 ሺ እስከ 40 ሺ ብር እንዲቀጡ መወሰኑን የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቢ ህግ ጽ/ት ቤት ሀላፊ  ዳአ/ቶ ጎሹ ለገሰ ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል ።

ግለሰቦቹ 16 ሚሊዮን ብር ለግል ጥቅማቸው ለማዋል የተደራጀ የሙስና ተግባር ውስጥ ገብተው እንደነበር የተገለፀ ሲሆን በተቋቋመው የፀረ ሙስና ኮሚቴ መሰረት በተደረገ የኦዲት ምርምረ ውጤት 44 ሚሊዮን የመንግስት ገንዘብ ከብክነት ማዳን ተችሏል ። 

ከዚህም ውስጥ ከመንግሥት ካዝና ወጥቶ ያለ አግባብ እንዲከፈል የተወሰነ 30 ሚሊዮን ብር ሳይከፈል በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከስንቄ ባንክ ያለ አግባብ በብድር የወጣ 15 ሚሊዮን ብር ተመላሽ እንዲሆን ተደርጓል ።

ከመሬት ጋር በተያያዘ ከ 50 ሺ በላይ ካሬ ሜትር ቦታ ያለ አግባብ ሊከፋፈል ሲል በተደረገ ምርመራ ተደርሶበት ለመንግሥት ገቢ ሆኗል ። በተጨማሪ 660 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የተሰራ መኖሪያ ቤት በቁጥጥር ስር መዋሉ አ/ቶ ጎሹ ጨምረው ለብስራት ራዲዮ ተናግረዋል ።

@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news

20 last posts shown.