በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ እየተካሄደ ባለው ቤቶችን የማፍረስና በግዳጅ የማስነሳት ሂደት የጸጥታ አካላት ተመጣጣኝ ያልሆነ የሃይል እርምጃ መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ፡፡
ኮሚሽኑ ቤቶቻቸው የፈረሱባቸውን ሰዎች በግልና በቡድን ለኮሚሽኑ ያቀረቡትን አቤቱታ ተከትሎ ከየካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ ቆይቶ አርብ መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ. ም አመሻሹ ላይ ሪፖርት አውጥቷል፡፡
በአንዳንድ ቦታዎች ቤት የማፍረስና በግዳጅ የማስነሳቱ ሂደት ለሁከት፣ እንግልት፣ ለአካልና ሥነ ልቦና ጉዳትና ለእስር ምክንያት መሆኑኑን፤ ቤታቸው እንዳይፈርስባቸው የተቃወሙ፣ መንገድ የዘጉ፣ ጩኸት ያሰሙ ሰዎች በጸጥታ አስከባሪዎች ተመጣጣኝ ያልሆነ የኃይል እርምጃ መደብደባቸውን ተረድቻለሁ ሲል ኢሰመኮ አስታውቋል፡፡
ሪፖርቱ እንደሚመላክተው ፊሊዶሮ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገው የቤት ፈረሳ የሰው ሕይወት ማለፉን መረጃ እንደደረሰውና ኮሚሽኑ ይህንን እያጣራ ስለመሆኑ እንዲሁም በከተማ አስተዳደሩ በጊዜያዊነት የታሰሩ ሰዎች እንዳሉ ለማወቅ ችያለሁ ብሏል፡፡
በተፈጠረው ክስተት ተማሪዎች ከትምህርታቸው ለማቋረጥ ተገደዋል፤ በርካታ ቤተሰቦች የእለት ተእለት ተግባራቸውን ማከናወን የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ በርካቶች ተፈናቅለው ወደ ሌሎች ቦታዎች ለመሄድ ተገደዋል፤ከፊሎቹ መንገድ ላይ ወድቀዋል በተለያዩ የሀገር ውስጥ መጠለያ ጣቢያ በመሰብሰብ የመንግሥት እርዳታ ለመጠባበቅ መገደዳቸውን በሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ የኦሮሚያ ክልል ውስጥ በቅርቡ በአዲስ መልክ በተደራጀው የሸገር ከተማ አስተዳደር የቤቶች ፈረሳ እና በግዳጅ ማስነሳት የመኖሪያ ቤት አልባነትን ማባባሱን የገለጸው አሲመኮ ቤቶች እየፈረሱት ያሉት በቡራዩ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ መነ አብቹ እና በዙሪያው የሚገኙ አካባቢዎች ናቸው ብሏል፡፡
የነዋሪዎችን ቅሬታ ተከትሎ የሚመለከታቸውን የከተማ አስተዳደርና የጸጥታ አካላት በማነጋገር፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ቤቶችን የማፍረስና በግዳጅ የማስነሳት ሂደቱ የሚከናወንበትን ሁኔታ እንዲሁም ቀደም ሲል የፈረሱ ቤቶችን የመስክ ምልከታ በማድረግ መረጃና ማስረጃ ማሰባሰቡን አስታውቋል፡፡
ይሁን እንጂ ኮሚሽኑ አሰባሰብኩት ባለው መረጃ እርምጃው ተገቢ ልየታ ያልተደረገበት መሆኑን፤ እርምጃው ያለ በቂ የቅድመ ማስጠንቀቂያ የተከናወነ ስለመሆኑ፣አድሎአዊ እርምጃ ስለመኖሩ፣እስር፣ የአካልና ሥነ-ልቦና ጉዳት እና እንግልት ስለመድረሱ አደረኩት ባለው ጥናት አመላክቷል፡፡
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
ኮሚሽኑ ቤቶቻቸው የፈረሱባቸውን ሰዎች በግልና በቡድን ለኮሚሽኑ ያቀረቡትን አቤቱታ ተከትሎ ከየካቲት 27 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ ቆይቶ አርብ መጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ. ም አመሻሹ ላይ ሪፖርት አውጥቷል፡፡
በአንዳንድ ቦታዎች ቤት የማፍረስና በግዳጅ የማስነሳቱ ሂደት ለሁከት፣ እንግልት፣ ለአካልና ሥነ ልቦና ጉዳትና ለእስር ምክንያት መሆኑኑን፤ ቤታቸው እንዳይፈርስባቸው የተቃወሙ፣ መንገድ የዘጉ፣ ጩኸት ያሰሙ ሰዎች በጸጥታ አስከባሪዎች ተመጣጣኝ ያልሆነ የኃይል እርምጃ መደብደባቸውን ተረድቻለሁ ሲል ኢሰመኮ አስታውቋል፡፡
ሪፖርቱ እንደሚመላክተው ፊሊዶሮ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገው የቤት ፈረሳ የሰው ሕይወት ማለፉን መረጃ እንደደረሰውና ኮሚሽኑ ይህንን እያጣራ ስለመሆኑ እንዲሁም በከተማ አስተዳደሩ በጊዜያዊነት የታሰሩ ሰዎች እንዳሉ ለማወቅ ችያለሁ ብሏል፡፡
በተፈጠረው ክስተት ተማሪዎች ከትምህርታቸው ለማቋረጥ ተገደዋል፤ በርካታ ቤተሰቦች የእለት ተእለት ተግባራቸውን ማከናወን የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል፤ በርካቶች ተፈናቅለው ወደ ሌሎች ቦታዎች ለመሄድ ተገደዋል፤ከፊሎቹ መንገድ ላይ ወድቀዋል በተለያዩ የሀገር ውስጥ መጠለያ ጣቢያ በመሰብሰብ የመንግሥት እርዳታ ለመጠባበቅ መገደዳቸውን በሪፖርቱ አስታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ የኦሮሚያ ክልል ውስጥ በቅርቡ በአዲስ መልክ በተደራጀው የሸገር ከተማ አስተዳደር የቤቶች ፈረሳ እና በግዳጅ ማስነሳት የመኖሪያ ቤት አልባነትን ማባባሱን የገለጸው አሲመኮ ቤቶች እየፈረሱት ያሉት በቡራዩ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ መነ አብቹ እና በዙሪያው የሚገኙ አካባቢዎች ናቸው ብሏል፡፡
የነዋሪዎችን ቅሬታ ተከትሎ የሚመለከታቸውን የከተማ አስተዳደርና የጸጥታ አካላት በማነጋገር፤ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር ቤቶችን የማፍረስና በግዳጅ የማስነሳት ሂደቱ የሚከናወንበትን ሁኔታ እንዲሁም ቀደም ሲል የፈረሱ ቤቶችን የመስክ ምልከታ በማድረግ መረጃና ማስረጃ ማሰባሰቡን አስታውቋል፡፡
ይሁን እንጂ ኮሚሽኑ አሰባሰብኩት ባለው መረጃ እርምጃው ተገቢ ልየታ ያልተደረገበት መሆኑን፤ እርምጃው ያለ በቂ የቅድመ ማስጠንቀቂያ የተከናወነ ስለመሆኑ፣አድሎአዊ እርምጃ ስለመኖሩ፣እስር፣ የአካልና ሥነ-ልቦና ጉዳት እና እንግልት ስለመድረሱ አደረኩት ባለው ጥናት አመላክቷል፡፡
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news