Ministry of Education Ethiopia


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


የኢትዮጵያ ዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በመካሄድ ላይ ይገኛል ፤ በወርልድ ቴኳንዶ 12 ተወዳዳሪዎች ወርቅ አግኝተዋል ፡
----------------------------------------------
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጁ ዩኒቨርስቲ አዘጋጅነት ጥር 17/2017 ዓ.ም የተከፈተው የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲዎች ስፖርት ውድድር ቀጥሎ በመካሄድ ላይ ነው።

በወርልድ ቴኳንዶ በወንዶች በተደረጉ ውድድሮች በ80 ኪ.ግ ምድብ ፋሲል ላቀው ከደብረብርሃን ፣ በ74 ኪ.ግ ግዛቸው ደምሴ ከወልቂጤ ፣ በ68 ኪ.ግ አማኑኤል ዳንኤል ከባህር ዳር፣ በ63 ኪ.ግ. ፍቃዱ ዳንኤል ከሀዋሳ ፣ በ58 ኪ.ግ ተከታይ አደራው ከወላይታ ሶዶ ፣ በ54 ኪ.ግ ድሪባ ደበላ ከጅማ ዩኒቨርስቲ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝተዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1CKojKRhZ9/


ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ።
---------------------------------------
(ጥር 21/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲን በመጎብኘት ከተቋሙ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።

በጉብኝቱ ወቅትም ዩኒቨርሲቲው ከተቋቋመ ጀምሮ በአካዳሚክ፣ በምርምርና በማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎቶች የሰራቸውን ሥራዎች እና ድጋፍ የሚሹ ጉዳዮችን ለአመራሮቹ ገለጻ ተደርጎላቸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፣ https://www.facebook.com/share/p/18DdMBQaXC/


የትምህርት ሚኒስቴር የሚያከናውናቸውን አዳዲስ የለውጥ ስራዎች የሚደግፍ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡
--------------------------------------
(ጥር 20/2017 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር እና በኢንፎ ማይንድ ሶሊሽን መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በትምህርት ሚኒስቴር እየተተገበሩ ያሉ አዳዲስ የለውጥ ስራዎችን በመደገፍ ተቋማትና ተማሪዎች በየጊዜው አቅማቸውን እንዲገነቡ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።

የኢፊዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በፊሪማ ስነስርዓቱ ላይ እንደገለጹት ስምምነቱ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ማዕከላትን በማቋቋም እንዲሁም የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በመሳተፍ ተማሪዎች የተሻለ አቅም እንዲፈጥሩ የሚያግዝ በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ቁርጠኛ መሆን ይገባል ብለዋል።

ስምምነቱ ተማሪዎች በህይወት ጉዞአቸው ወዴትና እንዴት መሄድ እንዳለባቸው የሚያመላክት ስራዎችን ከማከናወን ባለፈ ትምህርታቸውን ጨርሰው ወደ ስራው አለም በሚቀላቀሉበት ወቅት የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ከወዲሁ ለመቅረፍ የሚያስችል መሆኑን ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል፡፡

የኢንፎ ማይንድ ሶሊሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ የሱፍ ረጃ በበኩላቸው በሰጡት ማብራሪያ የስምምነቱ መፈረም የተማሪዎችን አቅም ከመገንባት ባለፈ ሚኒስቴር መስያ ቤቱ በቀጣይ ለሚያከናወናቸው የጥናትና ምርምር ስራዎች መረጃዎችንም ጭምር ለማግኘት የሚያስችል ነው ብለዋል ፡፡




የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅ በተዘጋጀው የጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደረገ።
----------------------------------------------
(ጥር 18/2017 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ በውይይቱ መክፈቻ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት ቁልፍ መልእክት የትምህርት ስርዓቱ ፍትሃዊ፣ አካታች፣ ተደራሽነት ያለውና ችግር ፈቺ ለማድረግ በሚደረጉ ጥረቶች ውስጥ የባለድርሻ አካላትና አጋር ድርጅቶች ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ቀጣይነት ያለውና እየተሻሻለ የሚሄድ የውስጥ ጥራት አጠባበቅ ስርዓት የመዘርጋት፣ ስታንደርዶችን የማውጣትና ተግባራዊነታቸውን የማረጋገጥ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ሚንስትር ዴኤታው አያይዘው ገልጸዋል።

በዚህም ዜጎች የሀገሪቱን ልማትና ዕድገት ለማሳለጥ የሚያስችል ዕውቀት፤ ክህሎት እና አመለካከት ይዘው እንዲወጡና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርዶች የተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።

የትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ መመሪያው ከጸደቀ በኋላ በአዲሱ የስልጠና ጥራት ኦዲት መመሪያ እና ስታንዳርድ መሠረት የሚመዘኑ መሆኑ ተጠቁሟል


ስፖርትና እውቀትን በማቀናጀት በትምህርት ጥራት ላይ የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጥል እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስታወቁ፡።
………………………………………………………………………….
(ጥር 18/2017 ዓ.ም) የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ተከፍቷል።

የትምህት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፌስቲቫሉን ሲከፍቱ ባደረጉት ንግግር ስፖርትና እውቀትን ከትምህርት ጥራት ስራዎች ጋር በማስተሳሰር የአገርን እድገት ከፍ ማድረግ ይገባል፡፡

የአእምሮ እድገትና የአካል እድገት የተሳሰሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሩ ተወዳዳሪዎች በቆይታቸው ሰላምን ወዳጅነትና አብሮነትን በማስቀደም የስፖርት ፌስቲቫሎችን ማካሄድ እንደሚጠበቅባቸውም ተናግረዋል። ለሙሉ መረጃው ይህንን ሊንክ ይጫኑ።
https://www.facebook.com/share/p/1DzHGg4X57/




ሴት ተማሪዎች በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶች በትብብር መቅረፍ እንደሚገባ ተገለጸ።
=====================
(ጥር 16/2017 ዓ.ም) የትምህርት ሚኒስቴር ሥርዓተ ጾታን መሠረት ያደረገ መማር ማስተማር ስርዓትን ለመገንባት በሚያስችሉ ጉዳዬች ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል።

በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት ቤት አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በውይይቱ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ስርዓተ ጾታን ከግንዛቤ ውስጥ ያስገባ የመማር ማስተማር ስርዓትን በማጎልበት ተማሪዎች፣ መምህራን ፣የትምህርት አስተዳደር ሠራተኞችና ወላጆች ለትምህርት ጥራት መሳካት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ማስቻል እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። https://www.facebook.com/share/1L6iaBZ9UG/


በሰሜን ማዕከላዊ፣ በምዕራብ፣ በሰሜንና በደቡብ ምዕራብ ቀጣና የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግ እንደቀጠለ ነው

----------------------------------------------
(ጥር 15/2017 ዓ.ም) እየተካሄደ በሚገኘው የ2017 ዓ.ም. የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግ በሰሜን ቀጣና የተደለደሉ የትግራይ ክልል 6 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በክላስተር ደረጃ በአትሌትክስ፣ እግር ኳስና ቮሊ ቦል ውድድሮች ማካሄድ ጀምረዋል።

በደቡብ ምዕራብ ቀጣና ጅማ ዞን በ21 ወረዳ ውስጥ በክላስተር ደረጃ በተለያዩ ስፖርት ዓይነቶች እየተካሄደ የሚገኘው ስፖርት ውድድር በትምህርት ማህብረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃትን የፈጠረ መሆኑ ታውቋል ።

በሰሜን ማዕከላዊ ቀጣና የተደለደለው የደሴ ከተማ አስተዳደርም የትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድሩን በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች መካከል በሚደረግ የእግር ኳስ ውድድር በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

በተመሳሳይ በምዕራብ ቀጣና ውስጥ የተደለደለው ቄለም ወለጋ በ11 ወረዳዎች እና በ 1 ከተማ አስተዳደር በሚገኙ 559 አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ውድድሩ እየተካሄደ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የትምህርት ቤቶች ስፖርት ሊግ በቀጣይም በአንደኛው መንፈቀ ዓመት ተማሪዎች ረፍት በሚሆኑበት ወቅት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች በክላስተርና በዲስትሪክት ደረጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከወጣው መርሀ ግብር ለማወቅ ተችሏል፡፡

9 last posts shown.