Ethio🇪🇹Muslim🇪🇹 Nashida - Menzuma 🎼


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


ሀሳብ አስተያየት ☞ @abm_prod

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


صلي الله عليه وسلم 😍😍😍😍😍😍
😍😍😍😍😍😍😍😍


አቦ እስኪ በኢሽቅ 😇 ሼር አድርጉት🙏 !!

#share


https://t.me/ethio_muslim_nashida


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
Amazing eid song by #humood al khuder

Share it with your family



EID MUBAREK🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳😀😀🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🥳🤩🤩🤩🤩🤩🤩🤩🤩🤩🥳🥳🥳


https://t.me/ethio_muslim_nashida


🌙🌟عيد مبارك ☪تقبل الله منا ومنكم⭐️ صالح الأعمال 🌠⭐️كل عم وأنتم بخير
@ethio_muslim_nashida


እኚህን ምርጦች ለምትወዱ ብቻ 🙌


#LIKE
#SHARE




https://t.me/ethio_muslim_nashida


👳‍♂በዚህ አመት በዓል የማንን ነሺዳ ማዳመጥ ይፈልጋሉ ?


👳‍♂Whose Neshida do you want to hear in this holiday?



በአፋጣኝ እንለቅላቿለን? 🥰

#Share



https://t.me/ethio_muslim_nashida


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
A TikToker offered a Palestinian $100 to kiss the Israeli flag…

😂😂😂😂😂😂

ይሄን ብላ!✋


#FREE PALESTINE 🇵🇸




https://t.me/ethio_muslim_nashida


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#EIDUN SA'EED RINGTONE




https://t.me/ethio_muslim_nashida


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#EIDUN SA'EED

LET's ENJOY TOGETHER !😍



https://t.me/ethio_muslim_nashida


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
IF YOU SUPPORT PALESTINE 🇵🇸
SHARE THIS 👆


ፈለስጢንን ለምትወዱ በሙሉ እንዳያልፋቹ💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪💪

#SHARE
SHARE
SHARE
SHARE



FREE PALESTINE 🇵🇸


https://t.me/ethio_muslim_nashida


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
Mesut_kurtis #MEWLAYA SELI WESELIM DAIMAN ABEDEN 😍😍


[إذا المرء لا يرعاك إلا تكلفا،
فدعه ولا تكثر عليه تأسفا !]


BEAUTIFUL AREBIC NASHEED!



https://t.me/ethio_muslim_nashida


#FREE PALESTINE 🇵🇸

😍😍😍😍😍😍

https://t.me/ethio_muslim_nashida


🔴 ሰበር ዜና


በ1445 አ/ሂ የረመዳን ወር ፣ በ27 ኛው ለሊት በትላንትናዋ ምሽት በመስጂድ አል-ሐረም 🕋 የሰጋጆች ብዛት 2.5 ሚሊየን ገደማ እንደሆነ ተዘገበ !



👳‍♂ አላህ ይቀበለን !!



https://t.me/ethio_muslim_nashida


ABM LOGO & GRAPHICS DESIGN
🔅ሎጎ (አርማ)፦
- ለተቋም
- ለድርጅት
- ለድህረ ገፅ
- ለቻናል....
🔅 እስቲከር
🔅 ባነር
🔅 ቢዝነስ ካርድ
እና የተለያዩ ስራዎችን ያገኛሉ‼️

@ABMPRO1

🔅ለበለጠ መረጃ፦
+251905895717
+251912119761

https://t.me/ethio_muslim_nashida


Ethio🇪🇹Muslim🇪🇹 Neshida- Menzuma
😍😍😍

https://t.me/ethio_muslim_nashida
@ABMPRO1


አሰላሙ አላኩም ወራህመቱላሀ ወድ የቻናሌ ተከታዮች ለእስካሁን ለጠፋሁት ይቅርታ የጠየኩ አሁን ታላቁ የራመዳን ወር የመጣ ስለሆነ በአዲስ መልኩ ተመልሰናል share share ያደረጋቹልኝ

https://t.me/ethio_muslim_nashida
https://t.me/ethio_muslim_nashida

20.9k 0 17 11 193

Forward from: 👳‍♀️RIO ISLAMIC POST🧕
Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በእርግጥም የማይቀረው ሞት መጣ‼
==========================


إنا لله وإنا إليه راجعون!

ወላሂ! እኚህ ሸይኽ ለታደለ ሰው የሚኻደሙ እንጂ በጭካኔ ሽጉጥ የሚመዘዝባቸው አባት አልነበሩም። በዓይን ራሱ ለማየት ይከብዳሉ እኮ።

አላህ ይዘንላቸው።

@alahu_akber1


የተባረከው የፍልስጤም ምድር     2
—————————————————

     እ.አ.አ. በ1907 በወቅቱ በእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ባሔንሪ ካምፕቤል የተቋቋመ ኮሚቴ ወደ ሥራ መግቢያ ጥናቱን አቀረበ፡፡ በጥናቱ መሠረት ከዐረቦች በኩል በማንኛውም ጊዜ ሊመጣ የሚችለውን አደጋ ለመከላከል በመሀከላቸው የኖረውን ታሪካዊ፣ መንፈሳዊና ዝምድናዊ ትስስር እንደመነሻ እያደረገ የሚፈጠረውን አንድነት መስበርና ህብረታቸውን ጨርሶ ማድከም አስፈላጊ መሆኑ ተሰመረበት፡፡

ይህም በተሳካ መልኩ ሊከናወን የሚችለው የክልሉን አፍሪካዊና እስያዊ ክፍል ለሁለት በመክፈልና መሀል ላይ ለምዕራቡ ወዳጅ ታማኝ ለዐረቡ ጠላት ባላንጣ የሆነ ሰብዐዊ ጋሬጣ ማቆም ሲቻል መሆኑንም አያይዞ ግልጽ አደረገ፡፡ የአፍሪካና የእስያ አገናኝ መሬት ፍልስጤም ናት፡፡ የአፍሪካና የእስያ ሙስሊሞች ታላላቅ ጦርነቶችን ትከሻ ለትከሻ ገጥመው የተዋጉበት ምድር ቢኖር ፍልስጤም ቅድሚያ ተጠቃሽ ናት፡፡ ይህ ደሞ ከሁለት አህጉራት አገናኝነቷም በተጨማሪ በኢስላም ካላት የላቀ ደረጃና የተከበረች የተባረከች ሥፍራ ከመሆኗም አንፃር ነው፡፡ ከሙስሊሙ ዓለም የምዕራብ በር ላይ መገኘቷንም ልብ ይሏል፡፡ 

   እናም ይህን ሥፍራ መያዙና ከአካባቢው ህዝብ ጋር የጎሪጥ የሚተያይ ባዕድ ኃይል መሀል ላይ ሰንቁሮ ማስጠበቁ ከሙስሊሙ ዓለም በኩል ሊመጣ የሚችለውን አደጋ በመከላከል ረገድ ሁነኛ ብልኃት መሆኑን ነው የሄንሪ ካምፕቤል ኮሚቴ ጥናት የሚያትተው፡፡ በ1917 ኖቬምበር 2 ይፋ የሆነው የባልፎር ሠነድ መሠረታዊ ይዘትም ይኸው ነበር- በፍልስጤም ምድር ላይ አይሁዳዊ ሀገር ቤት መመሥረት፡፡ 

   በተለያዩ ዘገባዎች፣ ጥናቶችና የአቋም መግለጫዎች እየተጠናከረ የመጣው የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታ ከተሠነደና ይፋ ከተደረገ በኋላ በ1917 ዲሴምበር 11 ቀን የብሪትሽ ጦር ሠራዊት በጀነራል አለንቢ እየተመራ ኢየሩሣሌም ገባ፡፡ በወቅቱ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሥም በአርተር ባልፎር የተሰየመውና Balfour Decleration የተሰኘውን ፍርደ-ገምድል ሠነድ መሬት ላይ የማዋሉ ሥራም አንድ ተባለ፡፡ ይህንኑ ተከትሎ በነዋሪው ዐረብ ማኅበረሰብና በመጤ የአይሁድ ሠፋሪዎች መካከል አስፈሪ ውጥረት ነገሠ፡፡ 

    ጽዮናዊያን ዕለቱን እንደ አንድ የድል ቀን ሊያከብሩት ሲሞክሩ ከዐረቦቹ በኩል ደሞ የአይሁዶችን ሤራ የሚቃወሙ ኮሚቴዎችን በማዋቀርና የአቋም መግለጫዎችን በማውጣት በፍጥነት የተገዳዳሪ ሠልፍ ጥሪ ተላለፈ፡፡ ገና ከውጥኑ አንስቶ የሤራው አባሪ ተባባሪ የነበሩት እንግሊዞች ከዐረብ ፍልስጤሞች በኩል እየተጠነሰሰ የመጣውን አመፅ ባጭሩ ለማስቀረት ሲሉ በተቃውሞ ሠልፉ የሚገኝ እያንዳንዱ ዐረብ ተይዞ ዘብጥያ እንደሚወርድ በማስጠንቀቅ በብሪትሽ ከፍተኛ ኮሚሽነር ሐርበርት ስሜል በኩል እንዲተላለፍ አደረጉ፡፡ 

    ሜይ 1920 የእንግሊዝ መንግሥት በፍልስጤም ላይ ሙሉ ማንዴት ተሰጠው፡፡ ባለ ሙሉ ሥልጣን ሆነ፡፡ ከማንዴቱ መታወጅ ሶስት ቀናት በኋላ የእንግሊዞች ልዩ ተልዕኮ የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታ መሆኑንም እራሳቸው እንግሊዞች ይፋ አደረጉ፡፡ በእንግሊዝ ዘቦችና ዐረቦች መካከል ለመጀመሪያ ጊዜ የለየለት ግጭት ተካሄደ፡፡ በኢያሪኮ ከተማ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የፍልስጤሞች ሁለተኛ ጉባኤም በዚሁ ሰበብ ታገደ፡፡ 

    እንግዲህ!
  የእንግሊዝና የአይሁድ ጽዮናዊያን ሤራ ከ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ጀምሮ ሲውጠነጠን እንደነበረ ግልጽ ነው፡፡ በመሠረቱ የፍልስጤም መከራና ሥቃይ የተጠነሰሰው መላውን ሙስሊም ዓለም በሥሩ ሲያስተዳድር የነበረው የቱርክ ዑስማንያ ኢስላማዊ መንግሥት በምዕራባዊያን እጅ ሲሸነፍና ጨርሶም በ1924 እንዲያበቃለት ሲደረግ ነው፡፡ የውድቀቱ ቀጥተኛ ውጤት ሆነና ባንድ መንግሥት ጥላ ሥር ተማክሎ ይኖር የነበረው ሙስሊሙ ዓለም ዛሬ በሚታየው መልኩ በምዕራባዊያን እቅድና ፍላጎት የተከፋፈለ ጭፍራ ሆነ፡፡ እያንዳንዱ ራሱን ’ነፃ መንግሥት´ እያለ አወጀ፡፡ 

     ምዕራባዊያን ይሄን ነገር እንደምን አሳኩት? 
  ኢስላማዊውን መንግሥት ለመከፋፈል የተጠቀሙበት ዘዴ የቱርክና የዐረብ ብሔርተኛ ስሜትን በመጫር ነበር፡፡ በኢስላም መለኮታዊ ዓርማ “ላ ኢላሀ ኢልለላህ ሙሐመዱን ረሡሉልላህ” በሚለው ሥር ወንድማማች ሁኖ ባንድ ዱንያዊና ዲናዊ ዓላማና ግብ ተሳስሮ የኖረውን ህዝብ ገዢና ተገዢ አድርገው በመሳል አቃቃሩት፡፡ ቱርኮችን እንደገዢ፡፡ ዐረቦቹን እንደ ተገዢ፡፡ በዚህም ዐረቦች ከቱርክ ነፃ መውጣት አለባችሁ ተባሉ፡፡ እነሱም በየፊናቸው የተነገራቸውን ተቀብለው ዐረብ ብሔረተኝነትን በማራገብ ተጠመዱ፡፡ ያቺ የታሪካቸውና የሃይማኖታቸው ሞገስ የሆነችው ፍልስጤም ክብሯን ስትገፈፍና በባዕዳን ስትመዘበር እነሱ የእንግሊዝ መንግሥት በሰጣቸው የቤት ሥራ ተጠምደው አይሰሙም አይለሙም፡፡

  የነቢያት አገር ቤት፣ የኢስራእ ወል ሚዕራጅ ጉዞ መነሻ፣ አቅሷ የኸሊል ምድር፣ የስንት ሙጃሂዶች ደም የፈሰሰባት ቅድስት ሀገር ከሐዲያን ሲያረክሷት ዐረቦች እዚያው ግድም ሆነው አንድ ነገር ማድረግ አልቻሉም፡፡ ክብርና ሞገሳቸው ከነበረው ኢስላማዊ አንድነት ይልቅ እስከዛሬ ተዋራጅ ሆነው ያሉበት ብሔራዊ ልዩነት ይሻለናል በሚል የዘቀጠ እምነት ጎራ ለዩ፡፡ ወደ ፍልስጤም ዞረው ለማየትና ተቃውሞ ለማደራጀት ጊዜ አልነበራቸውም፡፡ ለዘላለም ከክብር ሰገነት የወረዱበት ጎሠኛ ስሜት ዛሬ ወደሚገኙበት የውርደት አዘቅት እያንደረደራቸው ምንም ቢባሉ የሚያዳምጡ አልነበሩም፡፡

ኢራቅ፣ ሶሪያ፣ ግብጽ፣ ሳዑድ ዐረቢያ … ተብለው እንደተለያየ አገር መታወጅን ቀዳሚ አጀንዳ አድርገው መሽቀዳደም ይዘዋል፡፡ ምዕራባዊያን ውጥናቸው በዐረቦች እጅ ሲፈፀም እያዩ ባደባባይ ይስቃሉ፡፡ ዛሂድ ዑለሞች ተደብቀው ያለቅሳሉ፡፡ 

    ፍልስጤም የዐረብ ወገኖቻቸውን እገዛ በመሻትም ጭምር አገራቸው የታላቁ ሶሪያ (ቢላዱ ሻም) አንድ አካል መሆኗን አበክረው ለማስረዳት ቢሞክሩም ለነሱ የተደገሠላቸው ሌላ ነገር ስለነበረ ሰሚ አላገኙም፡፡ እንደሌሎቹ ሁሉ ለነሱም አገራዊ ነፃነት እንዲከበርላቸው ቢጠይቁም አልተደመጡም፡፡ እነሱ እስከመኖራቸውም እውቅና ሊሰጣቸው አልተፈለገም፡፡ በነሱ ላይ የአይሁድ አገር ቤት ተመሥርቶ እንደ መንግሥት እንዲታወቅ ነበር የተፈለገው፡፡ “የምን ፍልስጤም ብሎ ሀገር” ሌሎቹ ዐረብ አገራት በመሬታቸው ላይ የአይሁድ ሠፋሪ ሳይኖርባቸው ብሔራዊ ተብዬውን ነፃነት ሲሰጡ ፍልስጤም ግን ባዕድ ሠፋሪም ሠፍሮባት ብሔራዊ ተብዬውን የይስሙላ ነፃነትም ተነፍጋ ህልውናዋን ለማስቀጠል ትታገል ጀመር...
               ይቀጥላል

https://t.me/ethio_muslim_nashida
https://t.me/ethio_muslim_nashida


የተባረከው የፍልስጤም ምድር    ክፍል 1

   የተባረከው የፍልስጤም ምድር መቼም ቢሆን የአይሁድ ይዞታ ሆኖ አያውቅም፡፡ ለዚህ አንዱ ማስረጃ ለአይሁድ የተለየ አገር (separate homeland) የመፍጠሩ ሀሳብ ሲንሸራሸር በነበረበት ወቅት ከፍልስጤም ውጭ ሌላም ቦታ ታስቦ የነበረ መሆኑ ነው፡፡

ዛሬ ዓለምን ለማደናገር እንደሚሞከረው የፍልስጤም ምድር ከድሮም የአይሁድ ይዞታ የነበረ ቢሆን ኖሮ፣ ለነሱ አገር ቤት በመፍጠሩ ሀሣብ ውስጥ አርጀንቲናና ዑጋንዳ ታሳቢ ባልተደረጉ ነበር፡፡

   ለአይሁድ የብቻ አገር ቤት የመፍጠሩ ሀሣብ የአውሮጳን ቡራኬ አግኝቶ በዋናነት ፍልስጤም ተመረጠች፡፡ ዓላማውን እውን የማድረጉ እንቅስቃሴም ተጀመረ፡፡ ጊዜው በ8ኛው መቶ ሂጅሪያ ማብቂያ ላይ ነበር፡፡ ይህ ወቅት ደሞ የምዕራብ የኩ#ፍ..ር ኃይላት የዑስማንያ ቱርክን ኢስላማዊ መንግሥት ለመጣል የተጠናከረ ርብርብ እያደረጉ የነበረበት ወቅት ነው፡፡

አይሁዶችም ይህንኑ ሁኔታ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀምና ገፀ-በረከት በማስያዝ አንድ ከማኅበረ-አይሁድ የተውጣጣ የልዑካን ቡድን በአውሮጳ ድጋፍ ሰጪነት ወደ ወቅቱ የዑስማኒያ ኸሊፋ ሡልጣን ዐብዱልሐሚድ ላኩ፡፡ ልዑኩም በሡልጣኑ ቤተ-መንግሥት ተገኝቶ አይሁዳዊያን በፍልስጥኤም መሬት ላይ መሥፈር እንዲችሉና የመግቢያ ፈቃድም እንዲሰጣቸው ተማጽኖ አቀረበ፡፡

   ሡልጣን ዐብዱልሐሚድ ግን በጊዜው መንግሥታቸው ላይ እየተደረገ በነበረው አሉታዊ ጫና ሳይበገሩ፣ በቀረበላቸው ገፀ-በረከትም ሳይደለሉ የአይሁዶችን ጥያቄ ውድቅ አደረጉ፡፡ አይሁዶች አንዴ እንደምንም ብለው ፍልስጤም መሬት ላይ እግር መትከል ከቻሉ አገሪቱን ከተቀረው ኢስላማዊ ግዛት በቀላሉ በመነጠል የግላቸው ሊያደርጓት ይችላሉ የሚል ስጋት ነበራቸው፡፡ ቀድሞ ከታያቸው ከዚህ ሥጋት በመነሳትም ይመስላል ሡልጣኑ በ1900 እና በ1901 መካከል በነበረው አጭር ጊዜ ውስጥ ተጨማሪ ደንቦችን በማስረቀቅ ማንኛውም የአይሁድ መንገደኛ ከሶስት ወር ባለፈ ፍልስጥጤም መሬት ላይ ውሎ ማደር እንደሌለበት የደነገጉት፡፡ ከዚህም ሌላ ምንም ዐይነት የመሬት ሽያጭ ከአይሁድ ጋር እንዳይፈፀም ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ 

    የአይሁዶች ጥረት ግን በቀላሉ የሚቆም አልነበረም፡፡ ሰላሳ አምስት ሚሊዮን የወርቅ ዲናሮችን በከረጢት ቋጥረው እንደገና በ1920 ወደ ሡልጣኑ ቤተ-መንግሥት አመሩ፡፡ በጊዜው የዑስማኒያ ኢስላማዊ መንግሥት ካዝና በብዙ ወጪዎች ተራቁቶ ባዶ እንደነበረም ያውቃሉ፡፡ እንደዛም ሁኖ ግን የኢስላማዊውን መንግሥት ይሁንታ በወርቅ ሳንቲሞች ለመግዛት ያደረጉት ጥረት በሡልጣኑ ዘንድ ተቀባይነትን አላገኘም፡፡ ሡልጣኑ የጉዳዩ ዋና አስተባባሪ ለነበረው ለቴዎዶር ሄርዞል በላኩት ማስታወሻ ግልጽ አደረጉ

“… የግል ንብረቴ አይደለምና ከፍልስጤም መሬት ስንዝር ቆርሼ መስጠት አልችልም፡፡ ባለመብቱ ህዝቡ ነው፡፡ ህዝቦቼ ለዚህ መሬት ሲሉ የህይወት መሥዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ ደማቸውን አፍሰውበታል፡፡ ስለዚህ አይሁዶች የወርቅ ዲናሮቻቸውን ለራሳቸው ያድርጉት፡፡ ምናልባት መንግሥቴ ቢፈርስ ያን ጊዜ ፍልስጤምን በቀላሉ ነጥሎ መያዝ ይቻላቸው ይሆናል፡፡ እኔ በአፀደ ሥጋ እያለሁ ግን ከሰውነቴ ላይ በስለት ተቆርጦ ቢወሰድ ይቀለኛል - ፍልስጤም ከኢስላማዊው መንግሥት ተነጥላ ስትሄድ ከማይ፡፡ ይህ ደሞ ከቶም ሊሆን የማይችል ነው” በማለት ያላቸውን ቁርጠኛ አቋም ግልጽ አደረጉላቸው፡፡ 

   እንደሚታወቀው ቴዎዶር ሄርዞል ዋነኛ የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታ አቀንቃኝ የነበረ ሰው ነው፡፡ ሠፈራን መሠረት ያደረገ ቅኝ ግዛት እንዴት ሊቋቋም እንደሚችል ቀድም ሲል ጀምሮ ከሮዲዚያ የዛሬዋ ዚምባውቤና መሠል ሀገራት ልምድ በመውሰድ የአይሁድ አገር ቤት ምሥረታም በተመሳሳይ መንገድ ሊከናወን እንደሚችል የፀና እምነት ነበረው፡፡

   ከዚህ በኋላ አይሁዶች በቀጥታ ወደ ፍልስጤም ለመግባት ያደረጉት ሙከራ እንዳልተሳካ እየገባቸው ሲመጣ አሳቻ መንገዶችን መጠቀም ጀመሩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜም ተሳክቶላቸው ´Union & progress society’ የተሰኘ ቱርካዊ ሥያሜ በመያዝ ሙስሊም ነን በሚሉ አንድ የአይሁድ ጎሣ ድርጅት በኩል ቀስ በቀስ ወደ ፍልስጤም መግባት ቻሉ፡፡ ይህን ያህል መግቢያና እግር መትከያ ክፍተት ካገኙም በኋላ ወደ ፍልስጤም የሚያደርጉትን ንቅናቄ በድርጅቱ አባላት በኩል የበለጠ በማጠናከር እስከ 1924 የኸሊፋው ይፋ ውድቀት ድረስ ቀጠሉ፡፡

    ከ1917 ጀምሮ ኢየሩሣሌም የገባውና ቁጥጥሩን የዘረጋው የእንግሊዝ ጦር በሚሰጣቸው ከለላ አንዳንድ እያሉ በፍልስጤም መሥፈር የጀመሩት አይሁዶችም ዋል አደር እያሉ ድንበር እየገፉ አጥር ማጠራቸውን ተያያዙት፡፡ ድርጊቱ ነዋሪዎቹን ዐረቦች እያስቆጣ ሲመጣ የእንግሊዝ ጦር ከሠፋሪ አይሁዶች በስተጀርባ በመሆን ይተኮስባቸው ጀመር፡፡ በዚህ ዐይነት ሤራ የአይሁድ በፍልስጤም ምድር ላይ መሥፈርና ብሎም መስፋፋት ከእንግሊዞች በኩል ያልተቆጠበ ድጋፍ እየተቸረው የብረት ሽፋንም እየተደረገለት ቀጠለ።

    በምዕራባዊያን በኩል ፍልስጤምን ቅኝ የማድረጉ ፍላጎትና የአይሁድ የአገር ቤት ምሥረታ ጥያቄ አንድ ላይ መገጣጠሙ የራሱ ድርሻ ነበረው፡፡ ምዕራባዊያን የዑስማንያን ኢስላማዊ መንገሥት ካሸነፉ በኋላ ለዘመናት በሥሩ የቆየውን ሰፊ ኢስላማዊ ግዛት ለመቀራመት ሲከጅሉ ዐይናቸውን ከጣሉባቸው መሬቶች አንዷ ፍልስጤም ነበረች፡፡ የምዕራባዊያኑን ክጃሎት የሳበችው በታሪካዊነቷ ብቻ ግን አልነበረም፡፡ በመልክዐ-ምድራዊ አቀማመጧ በአፍሪካዊት ዐረባዊት ግብጽና በኢስያ ዐረቦች መካከል እንደ አገናኝ ድልድይ ስለሆነች በዚህ ጊዜና ከዚህም በኋላ ሊኖር በሚችለው የሙስሊሞች ድንበር ዘለል ትብብር ላይ ሣንካ ለመፍጠር ከመሀል ፍልስጤምን ነጥሎ መያዙ በምዕራባዊያን ዘንድ እንደ አዋጭ መንገድ ሆኖ ታሰበበት፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በጊዜው የግብፅ አገረ-ገዢ የነበረው ሙሐመድ ባሻ ወደ ሻም ጉዞ አደረገ፡፡ የሱ ጉዞ ግብፅና ሶሪያን ሊያስተባብር ይችላል በሚል ግምት እንግሊዞች ስጋት ገባቸው፡፡  ቀደም ሲል ጀምሮ ሲቀነቀን በነበረው መሠረት ግብጽና ሻም በሚገናኙበት ማዕከላዊ ግዛት ላይ የአይሁድን የሠፈራ ፕሮግራም መቀበልና ማጠናከር እንዳለባቸው ተማመኑ፡፡ እንቅስቃሴም ጀመሩ፡፡ ይህ ደሞ ለምዕራባዊያን ሌላ ድብቅ በረከት ነበረው፡፡ ራስ ምታት ከሆኑባቸው አይሁዶች መገላገል፡፡ እናም ፍልስጤም በእንግሊዞች እጅ ለአይሁዶች ተበረከተች፡፡ መርዛሙን እሾህ ፍልስጤም ምድር ላይ በመትከልና ተንከባክቦ በማሳደግም አውሮጳ በተለይም ኢንግልተራ (እንግሊዝ) የአንበሻውን ድርሻ ያዙ
                                        ይቀጥላል
Join join join
👇👇👇👇👇
https://t.me/ethio_muslim_nashida
https://t.me/ethio_muslim_nashida


አስተውል ...!!

ቆንጆ ሴት  ብታገባ   ቆንጆ  ልጆችን  ታገኝ  ይሆናል  ውበት   ጀነት   አያስገባም እወቅ በተርቢያ    በዲን  ግንዛቤ   የተገነቡ  ልጆች     ግን   አደብ   ባላትና    ዲን   ባላት   ሴት   እንጅ   ላታገኝ  ትችላለህ  ሞዴል  አግብተህ   ሞዴል   እንዳትወልድልህ !!  

💍=====የትዳር ትልቁ  አላማ ራስህን ወደ አላህ   የሚያቃርብ    አጋዥ ማግኘት  ነው።

ዐልይ   ረዲየላሁ ዐንሁ  እና ፋጢማ ረዲየላሁ ዐንሀ በተጋቡ ማግስት የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም  ወደ ቤታቸው በመሄድ ዐልይን  ባለቤትህን እንደት አገኘሀት ?
ሲሉ ጠየቁት እርሱም አላህን_  ለመገዛት ጥሩ ረዳት ሆና አገኘኾት ብለው መለሱ. ።

💍ትዳርን   አላህን   የማመፅ   ሳይሆን   እረሱን  የማፍቀርና    የመገዛት   ምርጡ  መንገድ   መሆኑን  ተገንዘብ !!

ምንም የሌለው ድሃ ወንድ ሷሊህ ሚስት ካለችው ከማንም በላይ ሀብታም ነው።


በቴሌግራም ይ🀄️ላ🀄️ሉን!
➢👇👇

https://t.me/ethio_muslim_nashida
https://t.me/ethio_muslim_nashida

20 last posts shown.