EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Medicine


ETHIOPIAN FOOD AND DRUG AUTHORITY /EFDA/
This is EFDA'S official Telegram Channel
For more updates please visit
Free call 8482
join the Channel
t.me/ethiopianfoodanddrugauthority

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Medicine
Statistics
Posts filter


የተመጣጠነ የምግብ ችግርን ለመቅረፍ የተመረጡ ምግቦችን በንጥረ ነገሮች ለማበልፀግ አስገዳጅ መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ

መጋቢት 23/2017፡- የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በንጥረ ነገሮች የበለፀጉ የዘይትና ዱቄት ምርቶችን ለመመዝገብ የሚያስችል አስገዳጅ መመሪያ ማዘጋጀቱን ተከትሎ በመመሪያው ላይ አስተያየት እንዲሰጡበት በሐዋሳ ቅርንጫፍ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቅርንጫፉ የምግብ ተቋማት ህግ ማስፈፃምና ኢንስፔክሽን ዴስክ ኃላፊ አቶ ብሩህ አለማየሁ እንደተናገሩት የተመጣጠነ የምግብ እጥረተ የህብረተሰብ ጤና ችግር መሆኑን ገልፀው መንግስት የህዝብን የአመጋገብ ስርዓት ለማሻሻል የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

እንደአቶ ብሩህ ንግግር ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሰረት ምግቦችን በማዕድን፣ ቫይታሚን እና ሌሎች ንጥረ ነገሮች ለማበልፀግ አስገዳጅ መመሪያ ማዘጋጀቱንና ይህ መድረክም ባለድርሻ አካላት በዋነኝነት የዘይትና የዱቄት አምራቾች አስተያየት እንዲሠጡበት የተዘጋጀ ነው ብለዋል፡፡

በመድረኩ በምግብ ማበልፀግ አስፈላጊነት እና የዱቄትና የዘይት አምራች ተቋማት ሊዘረጉት ስለሚገባው የዉስጥ ጥራት ዝርጋታ ፅሁፎች የቀረቡ ሲሆን ባለስልጣኑ ያዘጋጀው አስገዳጅ የምግብ ማበልፀግ መመሪያ ለውይይት ቀርቦ ሠፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በውይይቱ በሐዋሳ ቅርንጫፍ ዱቄትና ዘይት ማምረቻ ፈቃድ ወስደው እየሰሩ ያሉ ተቋማት የተሳተፉ ሲሆን ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሐዋሳ ቅርንጫፍና ከዋናው ቢሮ በተገኙ ባለሙያዎች ማብራሪያ ሲሰጥ የቅርንጫፉ  ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ንማኔ እንደተናገሩት የምግብ ማበልፀጉን ተግባራዊ የማያደርጉ ተቋማት ላይ እርምጃ መውሰዱ ይቀጥላል ብለዋል።












Forward from: EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን
#Join the #Ethiopian #Food and #Drug #Authority #community!
Addressed up-update regulatory information about the safety,quality,efficacy, rational use and performance of regulated health product. Follow us on all social media links below for all the latest updates.
Follow Us

Facebook:
https://web.facebook.com/p/Ethiopian-Food-and-Drug-Authority-EFDA-100064606425124/
Telegram:
https://t.me/ethiopianfoodanddrugauthority
LinkedIn:
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-food-and-drug-authority
YouTube:
https://www.youtube.com/@FDAEthiopiaMedia
Twitter (@efda (@EfdaMedia) on X)
https://x.com/EfdaMedia?t=CLTetULx-FBOA2Ef344B-Q&s=35
Website
WWW.efda.gov.et
Online service / eRIS - Electronic Regulatory Information System/
https://eris.efda.gov.et

For report any suspicious, substandard, or falsified medicinal products:
Email pharmacovigilance@efda.gov.et
Calling the
Toll-free 8482


ከፋብሪካዎች የሚወጡ የምግብ ዘይትና የዱቄት ምርቶች በንጥረ ነገር እንዲበለፅጉ የሚያስገደድ ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ

መጋቢት 18/2017 አዳማ፡- የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የበለፀጉ የምግብ ዘይቶችና የዱቄት ምርቶችን ለመመዝገብ የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀቱን ተከትሎ በመመሪያው ላይ ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሠጡበት የሚያስችል የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የባለስልጣኑ የምግብ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ነጋሽ ስሜ እንደተናገሩት ደቂቅ ንጥረ ምግቦች ለሠው ልጆች የሚያስፈልጉ ወሳኝ ንጥረ ምግቦች ሲሆኑ እነዚህ ንጥረ ነገሮች ለጤናማ የሰውነት እድገት፣ የበሽታ መከላከል አቅምን የሚያጎለብቱና የምግብ መፈጨትን የሚያፋጥኑ ቫይታሚንና ማዕድናትን እንደሚጨምር ገልጸው ይህ መመሪያ ህዝባችን በሚመገባቸው የዱቄትና የምግብ ዘይት ምርቶች አማካኝነት ወሳኝ ንጥረ ምግቦች እንዲያገኝ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ረቂቅ መመሪያው በባለስልጣኑ የምግብ ምዝገባና ፈቃድ መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ አስፋው ቀርቦ ሠፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን ባለድርሻ አካላቱ በመመሪያው ላይ ግልፅ ሊደረጉ የሚገባቸው ባሏቸው ጉዳዮች አስተያየታቸውን አቅርበው ከመድረኩ ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡


በመድኃኒትና ክትባት ደህንነት ክትትል ስራ የአፍሪካ ሕብረት የልማት ኤጀንሲ እያከናወን ያለው ስራ የአጉሪቱን መፃኢ የጤና ክብካቤ ለችግር የማይበገርና አስተማማኝ እንደሚያደርገው ገለፁ፡፡
የአፍሪካ ሕብረት የልማት ኤጀንሲ -አዲስ አጋርነት ለአፍሪካ ልማት 6ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመድኃኒትና የክትባት ክትትል አስተባባሪ ኮሚቴ ስብሰባላይ የጤና ሚኒስቴር ምንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ሲከፍቱ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የኮቫክስ ክትባት ወደ አፍሪካ ከሚገባበት ሁለት አገራት አንዷ መሆኗ ኩራት እንደሚሰማቸው ገልፀው አገሪቷ በአፍሪካ በመድኃኒትና ክትባት ደህንነት ክትትል አስተባባሪ ኮሚቴ ውስጥ መግባቷ ለዚህ ትልቅ አስተዋፆ ማድረጉን አውስተዋል፡፡
ይህም የዲጂታል ፈጠራን በመድኃኒት ደህንነት ክትትል ለመጠቀም ማስቻል፣በእውነተኛ ጊዜ ሪፖርትና ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም አሉታዊ ክስተቶችን የመከላከል አቅም በእጅጉ ማሳደጉን ነው ዶ/ር መቅደስ ጠቁመው ኢንሼቲቩ በርካታ ውጤቶች መሰረት የጣለ ብቻ ሳይሆን የአጉሪቱን መፃሂ የጤና ክብካቤ ለችግር የማይበገርና አስተማማኝ እንደሚያደርገው አብራተዋል፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት የመድኃኒት ደህንነት ክትትል አስተባባሪ ሆና መስራት ከጀመረች ወዲህ እንደ አገር በዘርፉ አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቧን ገልፀው አገሪቱም በኢንሼቲቩ የሙከራ ወቅት /በኮቪድ ክትባት በርካታ የደህንነት ሪፖርት በማቅረብ አስተዋፆ አድርጋለች ብለዋል፡፡
በአህጉር ደረጃ የተናበበና የተቀናጀ የመድኃኒት ደህንነት ክትትል ኢንሼቲቪ ከተጀመረ አምስት ዓመት ወዲህ አገራዊ የመድኃኒት ተቆጣጣሪ ተቋማትን ማጠናከር ዲጂታላይዜሽንን በመጠቀም እውነተኛ መረጃን በመቀበልና በመላክና አገራት ወጥ የሆነ የክትትል ስርዓት እንዲዘረጉ አድርጓል ብለዋል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram












የገበያ ፈቃድ ባለቤቶች የመድኃኒት ጎጂ ክስተት ግኝትን ቀጣይነት ባለው መልኩ ሪፖርት ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ገለፁ

መጋቢት 12/2017፡- የመድኃኒት ጎጂ ክስተት ሲያጋጥም የመድኃኒት ገበያ ፈቃድ ባለቤቶች ሪፖርት ማድረግ በሚችሉባቸው መንገዶች ዙሪያ ከየገበያ ፈቃድ ባለቤቶቹ ለተወከሉ ብቁ የመድኃኒት ጎጂ ባህሪያት ስርዓት ላይ ኃላፊነት ለሚወስዱ ባለሙያዎች በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የባለስልጣኑ የመድኃኒት ደህንነት ክትትልና የህክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አስናቀች አለሙ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በምግብ እና መድኃኒት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1112/2011 አንቀጽ 71 ንዑስ አንቀጽ (2) በተሰጠው ስልጣን መሰረት የመድኃኒት ጎጂ ባህሪያት ክትትል ሥርዓት መመሪያ ከዚህ ቀደም እንዳዘጋጀ ገልፀው ብቁ የመድኃኒት ጎጂ ባህሪያት ስርዓት ላይ ኃላፊነት የሚወስዱ ባለሙያዎች የመድኃኒትን ደህንነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ሚና እንዳላቸው አስረድተዋል፡፡

በውይይት መድረኩ ብቁ የመድኃኒት ጎጂ ባህሪያት ስርዓት ላይ ኃላፊነት የሚወስዱ ባለሙያዎች ስላለባቸው ኃላፊነቶችና ግዴታዎች ፅሁፍ ቀርቦ ሠፊ ውይይት ከተካሄደ በኋላ በጋራ መግባባት መድረኩ ተጠናቋል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Video is unavailable for watching
Show in Telegram




የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ብቁና ተወዳዳሪ ለማድረግ አዲስ ተቋሙን የተቀላቀሉ ሠራተኞች ተቋሙን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋገር ጠንክረው እንዲሰሩ ተጠየቀ፡፡
መጋቢት 11/2017 ዓ.ም አዳማ ከተማ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ከተለያዩ ተቋማት በዝዉዉር ለተቀላቀሉ አዲስ ሠራተኞች ባለስልጣ መስሪያ ቤቱ የሚሠራቸውን የቁጥጥር ስራዎችን የሚያስተዋወቅና ገለፃ የሚሰጥ ስልጠናን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሲከፍቱ እንደተናገሩት አዲስ ተቋሙን የተቀላቀሉ ሠራተኞች ራሳቸውን ከጥቅም ግጭት በፀዳና በመልካም ሥነ ምግባር ታንፀው የተቋሙን ራዕይና ተልዕኮ እንዲያሳኩ ጠይቀዋል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ባለፉት 15 ዓመታት በሕግ ማዕቀፍ፣ በአደረጃጀት ክለሳ እና በጥራት መሠረተ ልማት ዝርጋታ ዙሪያ በበርካታ የለውጥ ሂደቶች ውስጥ ያለፈ መሆኑን ያብራሩት ዋና ዳሬክተሯ እነዚህ የለውጥ አጀንዳዎች እርስ በእርስ ተሳስረው ለመሄድ የሰው ኃይሉን በቅጥርና በአቅም ግንባታ ማጠናከር ወሳኝ ነው ብለዋል፡፡
ለአዲስ ሠራተኞች በተዘጋጀው ተቋሙን የማስተዋወቅ ስልጠና ላይ ከዋናው መስሪያ ቤትና ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የመጡ 34 ሰራተኞች እየተሳተፉ ሲሆን በስልጠናው ላይ የተቋሙን መዋቅራዊ አደረጃጀት፣ የፌደራል ሠራተኞች አስተዳደር አዋጅ 1350/2017 ፣ የተቋሙን ሕግና ፖሊሲ፣የተቋሙ ስትራቴጂዎችና ኢንሼቲቮች እንዲሁም ተግባቦት፣ የደንበኞች አያያዝ፣ ስነባህሪና የጥቅም ግጭት የመሳሰሉ ርዕሰ ጉዳዮች ቀርበው ሰፊ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡

20 last posts shown.