EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Medicine


ETHIOPIAN FOOD AND DRUG AUTHORITY /EFDA/
This is EFDA'S official Telegram Channel
For more updates please visit
Free call 8482
join the Channel
t.me/ethiopianfoodanddrugauthority

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Medicine
Statistics
Posts filter








የበርበሬ ምርትን ከበዓድ ነገር ጋር ሲቀላቅል በተገኘ ተቋም ላይ እርምጃ ተወሰደ

ሚያዚያ 9/2017ዓ.ም ምግብን ከባዕድ ነገር ጋር መቀላቀል በህብረተሰብ ጤናና ኢኮኖሚ ላይ ከፍ ያለ ጉዳት የሚያደርስ አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣንም ለህብረተሰቡ የሚቀርቡ የምግብ ምርቶች ጥራትና ደህንነታቸው ይጠበቅ ዘንድ የቁጥጥር ስራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከፊታችን የሚከበረውን የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በሻሸመኔ ከተማ ባዕድ ነገርን የበርበሬ ምርት ጋር በመቀላቀል ለህብረተሰቡ ሊያሰራጭ የነበረ ተቋም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሐዋሳ ቅርንጫፍ ከጉምሩክ ኮሚሽን ሐዋሳ ቅርንጫፍ ኢንተለጀንስ ባለሙያዎች፣ ከኦሮምያ ጤና ቢሮ ጤና ጤና ነክ ግብዓት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት እንዲሁም ከሻሸመኔ ከተማ ጤና መምሪያና ከሻሸመኔ ከተማ ፖሊስ ጋር ባካሄደው በሰርቬይላንስ በታገዘ  ምርቱ ከመሰራጨቱ በፊት በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል፡፡

በርበሬን ከበዓድ ነገር ጋር ሲቀላቅል የተገኘውን ተቋም ለመያዝ በተደረገው ኦፕሬሽን ተቋሙ በርበሬውን ለማቅለም ሲጠቀምበት የነበረው ቀሰም ቀለም፣ የበርበሬ ተረፈ ምርት የሆነ ፎሼ እንዲሁም ሌሎች ግብዓቶችን መያዝ የተቻለ ሲሆን በኦፕሬሽኑ ወቅት የሻሸመኔ ህዝብ ህገወጥ ተግባር ላይ የተሰማራውን ተቋም ለመያዝ በተሰራው ኦፕሬሽን ላደረገው ትብብር ምስጋናችንን እየገለፅን ህብረተሰቡ ተመሳሳይ ድርጊቶችን ሲመለከት በ8482 ነፃ የስልክ መስመር አልያም በአቅራቢያው ለሚገኝ የተቆጣጣሪ አካል ጥቆማ እንዲሰጥ የአደራ መልዕክት እናስተላልፋለን፡፡

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን






ጋዜጣዊ መግለጫ /Press Release
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ ህገወጥ የጤና ግብዓቶችና የምግብ ምርቶች ዝውውርን ለመግታት የኢንተለጀንስና ህገወጥ ንግድ መከላከል መሪ ስራ አስፈፃሚ በማቋቋም ከብሔራዊ ደህንነት፣ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከኢንተርፖል፣ ከጉምሩክ ኮሚሽን፣ ከክልል የጤና ተቆጣጣሪ አካላትና ከየክልሉ ፖሊስ ኮሚሽኖች ጋር በመሆን የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

በተለይ ሕገወጥ መድኃኒቶች ወደ ገበያ ሲገቡ ጥራታቸው፣ድህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው ባለመረጋገጡ በህብረተሰብ ላይ ሁለተናዊ ሊባል የሚችል የጤና፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ጉዳትን ያስከትላሉ፡፡ በተለይ የጤናው ጉዳት ብቻ ነጥለን እንኳን ብናይ ሕገወጥ መድኃኒቶች ከአካል መጉደል እስከ ህልፈተ ሕይወት ሊያድርስ የሚችል ስጋትን ይጥላል፡፡
ከዚሁ የሕገወጥ የመድኃኒት ዝውውር ጋር በተያያዘ ባሳለፍነው ሳምንትም ከብሔራዊ ደህንነት፣ ከፌዴራል ፖሊስ፣ ከኢንተርፖል፣ ከጉምሩክ ኮሚሽን፣ ከአዲስ አበባ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣንና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመሆን በአዳማ እና በአዲስ አበባ ከተሞች በ23 ቦታዎች በተሰራ የቁጥጥር ስራ ግምታዊ ዋጋቸው 118 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የወባ፣ የካንሰርና ከመንግስት ጤና ተቋማት ተሰርቀው የወጡ የፕሮግራም መድኃኒቶች እንዲሁም ጥቅም ላይ የማይውሉ የህክምና መሳሪያዎች ግምታዊ ዋጋቸው 150 ሚሊየን ብር በተጨማሪም ተገቢው የጥራት ምርመራ ተደርጎላቸው አገልግሎት ላይ የሚውሉ ግምታዊ ዋጋቸው 70 ሚሊየን የሚያወጡ የህክምና መሳሪያዎች በአጠቃላይ ግምታዊ ዋጋቸው ከ338 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ ህገወጥ ምርቶች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ከሕገወጥ ተግባሩ ጋር በተያያዘም 19 ተጠርጣሪ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛሉ፡፡






ለህብረተሰቡ የሚቀርቡ መድኃኒቶች ላይ የሚደረገው የጥራት ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ

ሚያዚያ 2/2017፡ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የመድኃኒት ምርት ጥራት ጉድለት ምርመራ ላይ ለሚሰሩ የስራ ክፍሎችና የቅርንጫፍ ቢሮዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የመድኃኒት ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ስዩም ወልዴ እንደተናገሩት ህብረተሰቡ የሚጠቀማቸው መድኃኒቶች ተገቢውን የጥራት፣ ደህንነት እና ፈዋሽነት መስፈርቶች አሟልተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ የቁጥጥር ስራ እንደሚሰራ ገልፀው መድኃኒቶች ገበያ ላይ በሚውሉበት ጊዜ የጥራት ጉድለት ሪፖርቶች ለባለስልጣኑ ይደርሳሉ በዚህም መሰረት የመድኃኒቶች የጥራት ጉድለት የማጣራት እና የምርመራ ስራ እየሰራ የሚገኝ ሲሆን የመድኃኒቱ የጥራት ጉድለት የማጣራት እና የምርመራ ስራ በተቋም ደረጃ አንድ ወጥ የአሰራር መመሪያ በማዘጋጀት እየተሰራ መሆኑንና የአቅም ግንባታ ስልጠና የተዘጋጀውም በመድኃኒት ጥራት ጉድለት ላይ የማጣራት እና የምርመራ ስራ ለሚሠሩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶችና የስራ ክፍሎች በብቃት ለመስራት እንዲሁም ተቀናጅተው እና ተናበው የሚሰሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የባለስልጣኑ የመድኃኒት ደህንነት ክትትልና የህክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ አስናቀች አለሙ በበኩላቸው ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠና ከስልጠናነቱ ባሻገር የስራ ክፍሎችና ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች በመድኃኒት ጥራት ጉድለት ሪፖርቶች መሰረት የመድኃኒቱ የጥራት ጉድለት የማጣራት እና የምርመራ ስራዎች ዙሪያ የእርስ በእርስ ተሞክሮዎች እንዲለዋወጡ እድል ያመቻቸ መድረክ መሆኑን ገልፀዋል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram

11 last posts shown.