EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Medicine


ETHIOPIAN FOOD AND DRUG AUTHORITY /EFDA/
This is EFDA'S official Telegram Channel
For more updates please visit
Free call 8482
join the Channel
t.me/ethiopianfoodanddrugauthority

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Medicine
Statistics
Posts filter






አሠራሮችን በሕግ አግባብ በመቃኘት የተሻለ ተቋማዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የአመራሩ ሚና ከፍ ያለ በመሆኑ  በስነምግባራዊ አመራር እና በሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007 ድንጋጌዎች ዙሪያ ግንዛቤያቸውን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
በሚያዚያ 5/2016 ዓ.ም በአዳማ ከተማ በተደረገው  ከማዕከል ፣ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሁም በመግቢያና መውጫ  ኬላዎች  ለሚገኙ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የስራ አስፈጻሚና ዴስክ ኃላፊዎች በተዘጋጀው ስልጠና በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የምግብ ዘርፍ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ነጋሽ ስሜ ባስተላለፉት መልክት እንደገለጹት ስነምግባራዊ አመራር ውቀቶች፣ክህሎቶች፣መርሆችን የሙስና ወንጀሎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የተደነገጉ ህጎችን   ከስልጠናው በመገብየት እና በመረደት ያሉ አሰራሮችን በመፈተሽ የተሻለ አገልግሎትና መልካም አስተደዳርን ለማስፈን በየደረጃው ያለው አመራር ለመስራት ሚናውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡ባለስልጣን መስሪቤቱ የተሻሻለ አገልግሎት ከመስጥትና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን አሰራሮችን ቀይሶ በመስራት ላይ ነው ብለዋል ይሄውም ለአብነት ያህል የሚሰጡ አገልግሎቶችን በቴክኖሎጂ፣ በህግና አሰራሮች የተደገፉ በማድረግ  ግንባር ቀደም  በመሆኑ ይሄን አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊነው ብለዋል፡፡
በስልጠናው የስነምግባራዊ አመራር መርሆች እና  የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007  ድንጋጌዎች ቀርበው ገለጻ  የተደረገባቸው ሲሆን ባለስልጣን መስሪያቤቱም ተገልጋዮች ለባለስልጣን መስሪቤቱ  በባር ኮድ የታገዘ ጥቆማ እና አስተያየት መሰጫ  ለሰልጣኞች ያስተዋወቀ ሲሆን ቴክኖሎጂው ዳብሮ ለተገልጋዮች ይፋ እንደሚሆንና በስፋት እንደሚተዋወቅ  ተገልጿል


አዲስ አበባ ሚያዚያ3/2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የማኔጅመንት አባላት በሲቪል ሰርቪስ ፓሊሲ ጉዳዮች እና የትኩረት መስኮች፣የሪፎርም ፅንሰ ሀሳቦች ትግበራ እና ሪፎርሙን በዕቅድ ከመምራት አንጻር መተግበር በሚያስፈልጉ መሠረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።


Video is unavailable for watching
Show in Telegram








የመገናኛ ብዙኃን አካላት ምግብና የጤና ግብአቶችን ሲያስተዋውቁ ሕግና ስነምግባር አክብረው ሊሰሩ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በጋራ አሳሰቡ፡፡
መጋቢት 30/2016 ዓ.ም አዳማ በተካሄደው በምግብና የጤና ግብዓቶች የማስታወቂያ ድንጋጌዎችን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ  ስልጠና ሲጀመር የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ለመገናኛ ብዙኃንና ኃላፊዎችናባለሙያዎች የተዘጋጀው ስልጠና ላይ እንደተናገሩት የስልጠናው ዋና ዓላማ የሚዲያ አካላትና የማስታወቂያ ባለሙያዎች ከዚህ ስልጠና ግንዛቤውን ካገኙ በኃላ በአግባቡ ሕግና ስነምግባርን ተከትለው እንዲፈፅሙ ነው፡፡
ህፃናትን ትኩረት ያደረጉ የምግብ ማስታወቂያዎች በገፍ በመደበኛውም ሆነ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተዋወቁ እንደሚገኙ የጠቆሙት ዋና ዳይሬክተሯ በእነዚህ ማስታወቂያዎች የሚተላለፉት መረጃዎች የተጋነኑ አንዳንዶቹም በማስታወቂያው የሚጠቀሱት ግብዓቶች በምግቦቹ ውስጥ በተጨባጭ የሌሉ መሆናቸው በጥናት ጭምር የተረጋገጠ በመሆኑ ማስታወቂያ በተለየ ሁኔታ ቁጥጥር ሊደረግበት ይገባል ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የማስታወቂያ ክትትል ዴስክ ኃላፊ አቶ ዮናስ ፋንታዬ በአስተላለፉት መልዕክት የሚዲያና የማስታወቂያ ባለሙያዎች ቁጥጥር የሚደረግባቸውን የጤና ግብዓቶችን በሚያስተዋውቁበት ወቅት ሕግና ስርዓትን ተከትለው እንዲያስተዋውቁ ይህ የአቅም ግንባታ ስልጠናው ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ሰልጣኞች ከስልጠናው የሚያገኙትን ግንዛቤ በተግባር ሊሰሩበት እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ሁለቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቶች በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ሰምምነት ተፈራርመው ወደ ስራ ከገቡ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ የተገኙ ውጤቶች መኖራቸውን ገልጸዋል

9 last posts shown.