Ethiopian Press Agency/አማርኛ /


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ባህርዳር የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን ወደከፍታ በሚወስድ ሥራ ላይ ትገኛለች
****
(ኢ ፕ ድ)

ባህርዳር የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን ወደከፍታ በሚወስድ ሥራ ላይ ትገኛለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለፁ ።

ምክትል ተቅላይ ሚኒስትር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፣ ባህርዳርን ወደ ስማርት ሲቲ ለማሸጋገር ከሚረዱ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነው የኮሪደር ልማት በፍጥነት ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል።

የኮሪደር ልማት ሥራዎች የጣና ሐይቅና የዓባይ ወንዝ መናገሻ የሆነችውን ባህርዳርን የውበት ግርማ የሚያላብሱ፣ የቱሪዝምና ኢንቨስትመንት መዳረሻነቷን ከፍ የሚያደርጉ ናቸው ብለዋል።

ለኮሪደር ልማት እየዋሉ ያሉ አስፈላጊ ግብዓቶች በአብዛኛው በክልሉ የሚመረቱ መሆናቸው ይበል የሚያሰኝ ነው ብለዋል።

የካቲት 24 ቀን 2017 ዓም


ከዛሬ ጀምሮ መንገደኞች የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት ብቻ መቁረጥ ይጠበቅባቸዋል

👉 ደንበኞች የብሔራዊ መታወቂያ ከሌላቸው የተቋሙ አገልግሎት ማግኘት አይችሉም፣
****
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ከዛሬ የካቲት 24 ጀምሮ መንገደኞች የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት ብቻ መቁረጥ እንደሚጠበቅባቸው አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር ከፍተኛ የኮሙኒኬሽን ባለሞያ ወይዘሮ እስራኤል ወልደመስቀል ለኢፕድ እንደገለፁት፤ የመንገደኞችን እንግልት ለመቀነስና ለጋራ ደህንነት መንገደኞች የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት በመቁረጥ አገልግሎቱን ማግኘት እንዲችሉ ተደርጓል።

ማህበሩ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን ዲጂታላይዝድ ማድረጉን የገለፁት ወይዘሮ እስራኤል፤ ከዛሬ የካቲት 24 ጀምሮ መንገደኞች የጉዞ ትኬታቸውን በቴሌብር አማካኝነት ብቻ መቁረጥ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።

ደንበኞች የብሔራዊ መታወቂያ ከሌላቸው የተቋሙ አገልግሎት ማግኘት አይችሉም። ይህንንም ለደንበኞች የማሳወቅ ስራው ከአንድ ወር በፊት ጀምሮ ሲሰራ እንደነበርና ከብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር መታወቂያውን እንዲያገኙት እየተደረገ እንደነበር አስታውሰዋል።

የብሔራዊ መታወቂያ ተግባራዊነቱ ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች ብቻ ሲሆን፤ ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ ወይዘሮ እስራኤል ገልጸዋል።

በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ አገልግሎት ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ ይታወሳል።

በቃልኪዳን አሳዬ

የካቲት 24 ቀን 2017 ዓም


ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et


የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ONLF) ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ‼️

በኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) ስም "የኢትዮጵያ መንግሥት የሰላም ስምምነቱን ጥሷል" በሚል ከናይሮቢ ኬንያ የተሰጠው መግለጫ ከኦብነግ እውቅና ውጪ መሆኑን ገልጿል። መግለጫው እኤአ በ2018 ኦብነግ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በአስመራ የገባውን የሰላም ስምምነት የጣሰና ኦብነግን የማይወክል መሆኑን አበክረን እንገልፃለን።

የአስመራው የሰላም ስምምነት ተከትሎ በሶማሌ ክልል የተፈጠረው ሰላምና ልማት ጥሩ ጅምር ላይ መሆናቸውንና የህዝባችን የልማት፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች መልስ እያገኙ ሳለ ዛሬ በድርጅቱ ስም የወጣው መግለጫ በጅምር ላይ ያለውን ልማት እውቅና መንፈጉ የሚያሳዝን ነው።

በመሆኑም በጉዳዩ ላይ ኦብነግ የሚከተሉትን ሶስት የአቋም መግለጫ ነጥቦችን ማስተላለፍ ይፈልጋል፤

👉 በናይሮቢ ከተማ "በኦብነግ ስም የወጣው መግለጫ የድርጅቱን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ ሥራ አስፈፃሚና የኦብነግ ምክትል ሊቀመንበር አብዱልከሪም ሼህ ሙሴ እውቅና ውጭ በተወሰኑ ግለሰቦች ፍላጎት የወጣ በመሆኑ ድርጅቱን የሚወክል አይደለም።

👉 የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) የአስመራው የሰላም ስምምነት እንደሚደግፍና የጀመረውን ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል አጠናክሮ በመቀጠል ስምምነቱን በተሻለ መልኩ ተፈፃሚ የምናደርግ ሲሆን፣ እስካሁንም የፌዴራልና የሶማሌ ክልል መንግሥት ለአስመራው ስምምነት ተግባራዊነት ላደረጉት አስተዋጽኦ እውቅናን እንሰጣለን።

👉 የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ደንብ አማካኝነት በቅርቡ ጉባኤ የሚናካሄድ ሲሆን፣ በጉባኤው ሰላማዊ ትግሉን የሚያጠናክሩ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል።

በኦብነግ ጉዳይ ዙሪያ በተወሰኑ ግለሰቦች የሚሰጡ የተሳሳቱ መግለጫዎች ህብረተሰቡ እንዳይደናገርና ግለሰቦቹም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እናሳስባለን።

ዘላለማዊ ክብር ለሰማዕቶቻችን!!
የኦብነግ ማዕከላዊ ኮሚቴ
የካቲት 24 ቀን 2017 ዓም
ጅግጅጋ




የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል
******
(ኢ ፕ ድ)

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በየካቲት ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

የነዳጅ ማደያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በታማኝነት እንዲያገለግሉ ለኢፕድ በላከው መረጃ አመላክቷል።

የካቲት 23 ቀን 2017 ዓም


ከዓድዋ ጀግኖች የድል ዕሴትን የወረሰው የመከላከያ ሠራዊት ጥቃትን መመከት የሚያስችል አስተማማኝ ቁመና ገንብቷል" - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
********
(ኢ ፕ ድ)

ዓድዋ የቅኝ ገዥዎችን ውጥን ያመከነ፣ ሁሉም የሰው ልጅ እኩል መሆኑን እንዲገነዘቡ ያደረገ፣ በባርነት ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ህዝቦች ለነጻነት ትግል እንዲነሱ ማድረጉን የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ።

129ኛ የዓድዋ ድል በዓል "ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሀሳብ በዓድዋ ድል መታሰቢያ በመከበር ላይ ይገኛል።

ትናንትም፣ ዛሬም፣ ወደፊትም ኢትዮጵያ ጠላቶቿን እያንበረከከች ሉዓላዊነቷን አስከብራ የምትቀጥል ሀገር ናት።

ባለንበት ዘመን ከጠላቶቻችን ተልዕኮ በመቀበል የሀገርን ጥቅም ለመጉዳት የሚሞክሩ ባንዳዎች መኖራቸውን ገልጸው ህልማቸው የማይሳካ በመሆኑ ህዝባቸውን ይቅርታ ጠይቀው የበደሉትን ለመካስ እንዲነሱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ኢትዮጵያን ጠላት አንበርክኳት አያውቅም፤ የዓድዋ ጀግኖችን የድል ዕሴትና ጀግንነት የወረሰው ጀግናው መከላከያ ሰራዊት ኢትዮጵያን ይጠብቃታል፤ ሀገሩን ከውስጥና ከውጭ ጠላት ለመከላከል ከመቼውም ጊዜ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።

ሠራዊቱ ውስጣዊ አንድነቱ የጠነከረ፣ የሀገር ፍቅር ስሜቱ እጅግ ከፍ ያለ፣ ወታደራዊ ብቃቱ የዳበረ ወኔው የጋለ መሆኑን ገልፀው በየትኛውም የስነልቦና ጦርነት የማይደነገጥ ሠራዊት መሆኑን አረጋግጠዋል።

መከላከያ ሠራዊቱ የኢትዮጵያን ጠላት አደብ እያስገዘ የኢትዮጵያን ከፍታ ለማረጋገጥ እንደሚተጋ ተናግረዋል።

በክብረአብ በላቸው አማን ረሽድ

የካቲት 23 ቀን 2017 ዓም


"ዓድዋ ኢትዮጵያ ታሪኳን በወርቅ ቀለም የፃፈችበት ነው"- ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን
*****
(ኢ ፕ ድ)

የአድዋ ድል ኢትዮጵያ ታሪኳን በወርቅ ቀለም የፃፈችበት መሆኑን የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን ገለፁ።

የ129ኛው የአድዋ ድል በዓል ''ዓድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል" በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ ይገኛል።

መልዕክት ያስተላለፉት የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፤ ዓድዋ ኢትዮጵያ ታሪኳን በወርቅ ቀለም የፃፈችበት ነው። ድሉ በቅኝ ግዛት የነበሩ ሁሉ የሚያከብሩት የድል ቀን ነው ብለዋል።

ዓድዋ የቅኝ ገዥዎችን ቅስም የሰበረ ድል ነው ያሉት ልጅ ዳንኤል፤ ወቅቱ ኢትዮጵያ በተለያዩ ተፈጥሯዊ ችግሮች የተፈተኑበት ቢሆንም ለነፃነታቸው የህይወት ዋጋ ከመክፈል አልተመለሱም ብለዋል።

የተለያየ ቋንቋና ባህል ያላቸው ከተለያየ የኢትዮጵያ ክፍል የተሰበሰቡ ኢትዮጵያውያን ቋንቋቸውን አንድነታቸው አድርገው ወራሪን ድባቅ መምታት መቻላቸውን ተናግረዋል።

የአሁኑ ዘመን ትውልድ የልማትና የሰላም አርበኛ በመሆንና እርስበርስ መናናቅ መገፋፋት በመተው ለኢትዮጵያ መለወጥና ዕድገት በጋራ መቆም እንደሚገባው አሳስበዋል።

በትምህርት የበለፀገ የትናንቱን ታሪክ የሚያውቅ የነገውን የሚያልም ትውልድ መፍጠር ይገባል ብለዋል።

በክብረአብ በላቸውና በአማን ረሸድ

የካቲት 23 ቀን 2017 ዓም


"ዓድዋ የጦርነት ድል ብቻ ሳይሆን የአፍሪካዊያን አይበገሬነት ማሳያ ነው" - የቀድሞው የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር
****
(ኢ ፕ ድ)
129ኛው የዓድዋ ድል በዓል በመከላከያ ሚኒስቴር አስስተባባሪነት “ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል” በሚል መሪ ሃሳብ በአድዋ መታሰቢያ ሙዚዬም እየተከበረ ይገኛል።

በዚሁ ወቅት የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማሃማት ባስተላለፉት መልዕክት፣ ዓድዋ የጦርነት ድል ብቻ ሳይሆን የአፍሪካዊያንን አይበገሬነት ማሳያ ነው።

የአድዋ ድል አንድነትና መተባበር ካለ ድል ማስመዝገብ እንደሚቻል ህያው ማሳያ እንደሆነም ተናግረዋል።

አፍሪካዊያን ራሳቸውን ከውጪ ወራሪ ሀይል ለመከላከል የከፈሉትን የህይወት መሰዋትነት የሚዘክር መሆኑን ጠቅሰው የበለጸገች አፍሪካን ለመገንባት መጠቀም እንደሚገባም ጠቁመዋል።

በአማን ረሺድ እና በክብረአብ በላቸው

የካቲት 23 ቀን 2017 ዓም


"ዓድዋ ኢትዮጵያውያን ውድ ህይወታቸውን መሰዋዕት በማድረግ ያስገኙት ድል ነው"- ኢንጅነር አይሻ መሐመድ
*
*
(ኢ ፕ ድ)

የአድዋ ድል የፅናትና የአልበገር ባይነት ማሳያ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሐመድ ገለፁ።

129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ ''አድዋ የጥቁር ህዝቦች ድል'' በሚል መሪ ሀሳብ እየተከበረ ይገኛል።

በክብረ በዓሉ ተገኝተው መልክት ያስተላለፉ የመከላከያ ሚኒስትር ኢንጅነር አይሻ መሐመድ፤ ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ፅናትና አልበገር ባይነት ማሳያ ነው። ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁር ህዝቦች ድል መሆኑን ተናግረዋል።

ድሉ ኢትዮጵያውያን ከልጅ እስከ አዋቂ አብረው ያሸነፉበትና ነፃነታቸውን የማይተካ ውድ ህይወታቸውን መሰዋዕት በማድረግ ያስገኙት መሆኑን ጠቅሰዋል።

ዓድዋ የድል ታሪክ ብቻ ሳይሆን ኃላፊነት ነው፤ የአባቶቻችንን ህልም አንድነትና ብልፅግናችንን በማረጋገጥ ማሳካት ይገባል ብለዋል።


የአባቶቻችንን የጀግንነት መንፈስ በመላበስ ፈተናዎች በፅናት ለመሻገር መሥራት ከአሁን ዘመን ይጠበቃል ብለዋል።

በክብረአብ በላቸውና አማን ረሽድ

የካቲት 23 ቀን 2017 ዓም

10 last posts shown.