FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ማስታወቂያ


የመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በጎንደር ከተማ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌዴራል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በጎንደር ከተማ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችንና የኢንቨስትመንት ስራዎችን ጎብኝተዋል፡፡ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) እና የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ(ዶ/ር)ን ጨምሮ የፌዴራል ከፍተኛ አመራር አባላት ከጎበኙት መካከል በክልሉ መንግስትና ባለሀብቶች በጋራ የተቋቋመው የአባይ ጋርመንት የአልባሳት…

https://www.fanabc.com/archives/283589


የኢትዮጵያ አየር መንገድ “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” ዕውቅና ተቀዳጀ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት በኬኒያ በተካሄደው የ2025 የአየር ዕቃ ጭነት አገልግሎት ልሕቀት ሽልማት መርሐ-ግብር “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ዕውቅና ተቀዳጀ።

በተጨማሪም “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት ኤርፖርት” እና “ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ያለ የዓመቱ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ተደራራቢ ዕውቅና እና ሽልማት ማግኘቱን አየር መንገዱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አስታውቋል፡፡

https://www.fanabc.com/archives/283584


ሀገር አቀፍ የሕዝብ ኮንፈረንስ ከነገ ጀምሮ በ25 ከተሞች ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገር አቀፍ የሕዝብ ኮንፈረንስ ከነገ ጀምሮ በ25 ዋና ዋና ከተሞች መካሄድ እንደሚጀምር ተገልጿል፡፡ ሀገር አቀፍ የሕዝብ ኮንፍረንሱ በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና ም/ቤት አባላት የሚመራ መሆኑን የፓርቲው መረጃ ያመላክታል፡፡

https://www.fanabc.com/archives/283579


ታጂኪስታን የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ሽግግር አደነቀች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በፓኪስታን የኢትዮጵያ አምባሳደር ጀማል በከር ከታጂኪስታን የኢኮኖሚ ልማትና ንግድ ሚኒስትር ዛቭኪዞዳ ዛቭኪ አሚን ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም አምባሳደር ጀማል÷ኢትዮጵያ ወደ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ያደረገችውን ስኬታማ ሽግግር አስመልክተው ለሚኒስትሩ ገለጻ አድርገዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለማረጋገጥ በርካታ ተነሳሽነቶች መጀመሯንም አብራርተዋል፡፡ በዚህም በግብርና፣ በውሃ እና በሃይል…

https://www.fanabc.com/archives/283573


ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኮሚሽን ም/ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ምክትል ፕሬዚዳንት ካጃ ካላስ ጋር በጆሃንስበርግ ተወያይተዋል፡፡ ከቡድን 20 የሚኒስትሮች ጉባኤ ጎንለጎን በተደረገው ውይይት ሁለቱ ወገኖች በሁለትዮሽ፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት÷ ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር…

https://www.fanabc.com/archives/283564


የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያስተላለፈው መልዕክት

‹‹ከህዝብ በሚቀርቡ የቅሬታና አቤቱታዎች በየደረጃው የተሰጡ ምላሾች በሚመለከት በስድስት ወሩ የተከናወኑ ተግባራት በሱፐርቪን በማረጋገጥ የቀጣይ የትኩረት መስኮች ላይ ማህበረሰባችንን ጥያቄ መመለስ በሚያስችሉ አሰራሮች ዙርያ ከክልል እና ፌደራል ተቋማት ጋር በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አዘጋጅነት የግብረ መልስ መስጫ ውይይት ተካሂዷል ። የማህበረሰባችንን ጥያቄ ለመመለስ ይበልጥ የምንተጋ ይሆናል።››


ኢትዮጵያ በቀጣናው እየተወጣች ያለው የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ይደነቃል- የተባበሩት መንግሥታት

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በቀጣናው እየተወጣች ያለውን የሰላም ማስከበር ተልዕኮ የተባበሩት መንግሥታት ምክትል ዋና ፀሐፊ እና የጸጥታና ደኅንነት ኃላፊ ጊልስ ሚቻውድ አደነቁ፡፡ የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) ከጊልስ ሚቻውድ ጋር የተወያዩ ሲሆን፤ በዚሁ ወቅትም ኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግሥታት ቁልፍ አጋር መሆኗን ምክትል ዋና ፀሐፊው አንስተዋል፡፡ መንግሥታቱ በኢትዮጵያ እና በአፍሪካ…

https://www.fanabc.com/archives/283552




የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ድልድል ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ድልድል በስዊዘርላንድ ናዮን ይፋ ተደርጓል።

በዚህ መሰረትም አርሰናል ከኔዘርላንድሱ ፒ ኤስ ቪ አይንድሆቨን እንዲሁም ሊቨርፑል ከፒ ኤስ ጂ ጋር ተደልድለዋል።

በተጨማሪም ባየርን ሙኒክ ከባየር ሊቨርኩሰን፣ ክለብ ብሩገ ከአስቶንቪላ፣ ቦሩሺያ ዶርትመንድ ከሊል፣ አትሌቲኮ ማድሪድ ከሪያል ማድሪድ፣ ፌይኖርድ ከኢንተር ሚላን እና ቤኔፊካ ከባርሴሎና መደልደላቸውን የሊጉ መረጃ ያመላክታል፡፡

የጥሎ ማለፉ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች የፊታችን የካቲት 25 እና 26 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄዱ ይሆናል፡፡


የዓድዋ ድል መታሰቢያን ከ246 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ጎብኝተዋል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዓድዋ ድል መታሰቢያ ተመርቆ ወደ ስራ ከገባ ወዲህ ከ246 ሺህ በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቱሪስቶች መጎብኘታቸው ተገልጿል፡፡ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዋና ዳይሬክተር ግሩም ግርማ÷ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ለህዝብ ክፍት ከተደረገ ጀምሮ በየእለቱ በርካታ ጎብኚዎችን እያስተናገደ መሆኑን ገልጸዋል። ኢትዮጵያውያን በጋራ በከፈሉት መስዋዕትነት የተገኘውን ድል የሚዘክር…

https://www.fanabc.com/archives/283538


ኡስታዝ አቡበከር ሁሴንን በማገት ሊብሬውን በመቀየር መኪናውን ሊነጥቁ ነበር የተባሉ 5 ተከሳሾች ጥፋተኛ ተባሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኡስታዝ አቡበከር ሁሴን የተባለ ግለሰብን በማገት ሊብሬውን በመቀየር መኪናውን ሊነጥቁ ነበር የተባሉ አምሥት ተከሳሾች ጥፋተኛ ተባሉ። የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ የጥፋተኝነት ፍርድ የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። ጥፋተኛ የተባሉት ተከሳሾች 1ኛ የሁለተኛ ተከሳሽ ወኪል የሆነው ፍፁም ተክሉ…

https://www.fanabc.com/archives/283532


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#የቅዳሜ ልዩ 90 ደቂቃ በፖድካስት

በfanafacebook ነገ ቅዳሜ ጠዋት 2 ሰዓት ላይ ይጠብቁን !


የሰላም ጥሪን ለተቀበሉ የቀድሞ የኦነግ አመራሮች ሹመት ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ክልል የመንግስትን የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦነግ አመራሮች ሹመት ሰጥቷል፡፡

በዚህ መሰረትም፡-

1. አቶ ያደሳ ነጋሳ--------- በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ

2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ --------- የኦሮሚያ ክልል ዓቃቤ ሕግ ምክትል ሃላፊ

3. አቶ ቶሌራ ረጋሳ --------- የኦሮሚያ ክልል ጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
👉የጸሀይ-2 አውሮፕላን ስኬታማ የሙከራ በረራ

👉አዲስ የኢትዮጵያ ኢ-ፓስፖርት ይፋ ሆነ


በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስና ዘመናዊ ፓስፖርት ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ፓስፖርት ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት ይፋ ሆነ፡፡

ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር÷ የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርትን ተግባራዊ ማድረጋችን የሀገርን ገጽታ ከመገንባት ባሻገር ለዜጎች የተሰጠውን ዋጋ ያሳያል ብለዋል፡፡

ፓስፖርቱ የግለሰቡን መረጃና የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረት ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተጠቅሷል።

ይህም ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገር አምራች ድርጅት እጅ የነበረውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲሸፈን አድርጓል ነው የተባለው፡፡

ከዚህ በፊት ይወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሪ በማስቀረት ገቢ ወደ ማመንጨት እንደሚያሸጋግርም ተመላክቷል።

በአሸናፊ ሽብሩ እና በወንድሙ አዱኛ


ፀሐይ-2 አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት አከናወነች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአየር ኃይል የተሰራችው ፀሐይ - 2 የስልጠና አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማከናወኗ ተገልጿል፡፡

ፀሐይ -2 አውሮፕላን ለበረራ ማሰልጠኛ እና ለሌሎች አገልግሎት መዋል የምትችል ሲሆን÷ የተሰጣትን ግዳጅ በብቃት መፈፀም የሚያስችላትን የዘመኑን የአቪዬሽን ቴክኖሎጂ ታጥቃለች ተብሏል፡፡

የአውሮፕላኗ ስኬታማ የሙከራ በረራ አየር ኃይሉ የደረሰበትን የከፍታ ጉዞ እንደሚያሳይ ነው የተመላከተው፡፡

በቀጣይነት ወደ ምርት ሂደት ለመሸጋገር ፋብሪካውን የማደራጀት፣ የመፈተሻ እቃዎችን የማሟላትና የሞያተኞችን አቅም የማጎልበት ሥራ በመከናወን ላይ መሆኑ ን የመከላከያ ሠራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ መረጃ ያመላክታል፡፡

የትራንስፖርት አውሮፕላን ስኳድሮን አዛዥና አብራሪ እንዲሁም የፀሃይ -2 የሙከራ በረራን በስኬት ያካሄዱት ሻለቃ ፍቃዱ ደምሴ ÷ አውሮፕላኗ የበረራ አቅሟ አስተማማኝና ተቋሙ ለያዘው የወደፊት ራዕይ ጉልህ አስተዋፅኦ የምታበረክት መሆኗን ገልፀዋል፡፡


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የፀሐይ -2 አውሮፕላን የመጀመሪያ ስኬታማ የሙከራ በረራ


የዕለቱ የምንዛሪ ዋጋ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ


ኢትዮጵያ የቡድን-20 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ፎረም ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ዛሬ በተጀመረው የቡድን-20 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ፎረም ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ነው።

“አንድነት፣ እኩልነት እና ዘላቂነት” በሚል ቀጥታ ፍቺ ባለው መሪ ሃሳብ እየተካሄደ ያለው የውይይት መድረክ በደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ በይፋ ተጀምሯል።

ጌዲዮን (ዶ/ር) በንግግራቸው፥ ዓለም በጂኦፖለቲካል ውጥረቶች፣ ግጭቶች እና የአየር ንብረት ለውጥ የተለያዩ ፈተናዎች ውስጥ እየገባች ነው ብለዋል።

በትብብር ትክክለኛ ሚዛን ማምጣት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፥ የቡድን-20 አባል ሀገራትን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ማህበረሰብ መካከል የጋራ ትብብር እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል፡፡

በፎረሙ በፈረንጆቹ 2025 በደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት በተዘረዘሩት የቡድን-20 የትኩረት አቅጣጫዎች ላይም ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ይህም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ልማት፣ የምግብ ዋስትና፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ እና የኢነርጂ ሽግግርን እንደሚያጠቃልልም ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኘው ፎረሙ፥ ሁለት ቀናት ይቆያል ተብሏል፡፡

20 last posts shown.