FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


አቶ ሽመልስ አብዲሳ በጅማ ዞን የልማት ስራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በጅማ ዞን ጎማ ወረዳ የተለያዩ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል። በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው የሥራ ኃላፊዎች ቡድን ሰሞኑን በኢሉአባቦር እና በቡኖ በደሌ ዞኖች የተለያዩ የልማት ስራዎችን ተመልክቷል። በዞኖቹ በነበራቸው የልማት ስራዎች ጉብኝት ቆይታም የክልሉ መንግስት…

https://www.fanabc.com/archives/267763


የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ በ2028 ለአጠቃላይ ሀገራዊ ምርት 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር አስተዋጽዖ ያደርጋል ተባለ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ በፈረንጆቹ 2028 ለአጠቃላይ ሀገራዊ ምርት 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ብር አስተዋጽዖ እንደሚያደርግ ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ የተሰኘ ዓለም አቀፍ ድርጅት አመላከተ። ኢትዮ ቴሌኮም እና ግዙፍ ዓለም አቀፍ የሞባይል ኦፕሬተሮች እና መለስተኛ ኦፕሬተሮችን ጨምሮ 26 የቦርድ አባላት ያሉት ዓለም አቀፉ ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ በጋራ በመሆን የኢትዮጵያን ዲጂታል ኢኮኖሚን…

https://www.fanabc.com/archives/267752


የወባ ስርጭትን ለመከላከል የተቀናጀ ስራ ሊሰራ ይገባል- ዶ/ር መቅደስ ዳባ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የወባ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጣር የተቀናጀ ስራ ሊሰራ ይገባል ሲሉ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ገለጹ፡፡ የወባ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጣር እየተከናወነ ያለውን ስራ በሚመለከት በተደረገው የግምገማ መድረክ ዶክተር መቅደስ ዳባ በበይነ መረብ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የወባ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጣር የተቀናጀ ስራ ሊሰራ ይገባል ብለዋል። ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ…

https://www.fanabc.com/archives/267748


አቡበከር ናስር ሱፐር ስፖርት ዩናትድን ተቀላቀለ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በማሜሎዲ ሰንዳውንስ ሲጫዎት የነበረው አቡበከር ናስር ሌላኛውን የደቡብ አፍሪካ ክለብ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን ተቀላቅሏል፡፡ የፊት መስመር አጥቂው በማሜሎዲ ሰንዳውንስ ቆታው ባጋጠመው ከበድ ያለ ጉዳት ምክንያት በክለቡ ያልተሳካ ገዜ መሳላፉ የሚታወስ ነው፡፡ አቡበከር በሰንዳውንስ አለመፈለጉን ተከትሎ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን ለመቀላቀል ንግግር ሲደርግ የቆየ ሲሆን በአንድ ዓመት…

https://www.fanabc.com/archives/267741


ሀይድሮ ጂኦሎጂ ጥናት በውሃ አቅርቦትና ጥራት ላይ ለሚከናወኑ ተግባራት እገዛ ያደርጋል – ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀይድሮ ጂኦሎጂ ጥናት በውሃ አቅርቦትና ጥራት ላይ ለሚከናወኑ ተግባራት እገዛ ያደርጋል ሲሉ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ። የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከቼክ ሪፐብሊክ የልማት አጋር ጋር በሲዳማ ክልል እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦና ጋሞ ዞኖች ላይ በተዘጋጀው የጂኦሎጂና የሃይድሮጂኦሎጂ ካርታ ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ…

https://www.fanabc.com/archives/267743


ባለፉት ሦስት ወራት ከ1 ነጥብ5 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሦስት ወራት ከ1ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ፡፡ ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ÷ ዛሬ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የወጪ ንግድ አፈጻጸም ከላኪዎች ጋር መገምገሙን ገልጸዋል። አፈጻጸሙ በምርት ጭማሪም ሆነ በውጭ ምንዛሪ ዕድገት…

https://www.fanabc.com/archives/267736


ቱርክ በኩርድ ታጣቂ ቡድን ይዞታዎች ላይ ጥቃት መፈፀሟን ገለፀች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ቱርክ ትናንት ምሽት የተፈፀመውን የአንካራ ከተማ ጥቃት አቀናብሯል ባለችው የኩርድ ታጣቂ ቡድን (ፒኬኬ) ይዞታዎች ላይ ጥቃት መፈፀሟን አስታውቃለች፡፡ የቱርክ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ በፒኬኬ ላይ በተወሰደው የአፀፋ ጥቃት በኢራቅ እና ሶሪያ በሚገኙ 32 የቡድኑ ይዞታዎችን ማውደም ተችሏል፡፡ በአንካራ የደረሰውን ጥቃት ቡድኑ እንደፈፀመ የገለፀው ሚኒስቴሩ፤ ጥቃቱን የፈጸሙ…

https://www.fanabc.com/archives/267735


በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ እየጨመረ ነው - ፕሬዚዳንት ፑቲን

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በኢትዮጵያና ሩሲያ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ እየጨመረ እንደሚገኝ አስታወቁ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በካዛን እየተካሄደ ባለው 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ተገናኝተው መክረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር)፤ በሁለትዮሽ መድረካችን ወቅት ላደረግነው ጥልቅ ውይይት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲንን አመሰግናለሁ ብለዋል።

በሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ ቁርኝት ላይ የተመሠረተው የሁለትዮሽ ግንኙነት እያደገ መቀጠሉንም አመላክተው፤ የጋራ የሆነው የብሪክስ መድረክ ሰፋ ላለ የኢኮኖሚ ትብብር እንድንሰራ በር ከፍቶልናል ሲሉ ገልጸዋል።

ሩሲያ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ውስጥም ቢሆንም ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬን በማስጠበቅ ረገድ ስኬታማ መሆኗን አድንቀው፤ ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ፕሬዚዳንት ፑቲን በበኩላቸው፥ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላት ተቀባይነት እየጨመረ የመጣችው ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል መሆኗ ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለፈው ዓመት በሁለቱ ሀገራት መካከል በዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖቻችን መካከል ያለው ግንኙነት ይበልጥ መሻሻል ታይቶበታልም ብለዋል።

በዚህም ሩሲያ ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያላት ግንኙነት ላይ ትኩረት እንደምታደርግ ጠቅሰው፤ ... https://www.fanabc.com/archives/267709


የካፍ ልዑክ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ልዑክ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝታቸው ወቅት ልዑካኑ በሰጡት አስተያየት ÷የዓድዋ ድል ታሪክ በአፍሪካ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ ሊካተት ይገባል ብለዋል፡፡ እንዲሁም በአፍሪካ የሚገኙ ታዳጊ ህፃናት እና ወጣቶች የነፃነት እና የሰው ልጆች እኩልነት ፈር ቀዳጅ የሆነችውን ኢትዮጵያን እና መታሰቢያውን እንዲጎበኙ…

https://www.fanabc.com/archives/267730




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካቸው በሩሲያ ካዛን የሶስተኛ ቀን ውሎ


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የቭላድሚር ፑቲን የሁለትዮሽ ውይይት


በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ የውጭ ሀገራት ዜጎች እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ግለሰቦች ከ2 ዓመት እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጥተዋል፡፡ በ1996 የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀፅ 525 ንዑስ አንቀፅ 1(ለ) ሥር የተደነገገውን በመተላለፍ በአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉ ግለሰቦች መቀጣታቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል። የፖሊስ የወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ…

https://www.fanabc.com/archives/267715


በሁለቱ ሀገሮቻችን ታሪካዊ ቁርኝት ላይ የተመሠረተው የሁለትዮሽ ግንኙነታችን እያደገ ቀጥሏል - ጠ/ሚ ዐቢይ(ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ እና ሩሲያ ታሪካዊ ቁርኝት ላይ የተመሠረተው የሁለትዮሽ ግንኙነት እያደገ መቀጠሉን ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለፁ፡፡

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በሁለትዮሽ መድረክ ውይይት አካሂደዋል፡፡

ይህንን ተከትሎ ጠ/ሚ ዐቢይ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ÷"በሁለትዮሽ መድረካችን ወቅት ላደረግነው ጥልቅ ውይይት ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንን አመሰግናለሁ" ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሁለቱ ሀገራት ታሪካዊ ቁርኝት ላይ የተመሠረተው የሁለትዮሽ ግንኙነት እያደገ መቀጠሉንም አመላክተዋል፡፡

በተጨማሪም የጋራ የሆነው የብሪክስ መድረክ ሰፋ ላለ የኢኮኖሚ ትብብር እንድንሰራ በር ከፍቶልናል ነው ያሉት ጠ/ሚ ዐቢይ(ዶ/ር)፡፡


የዕለቱ የምንዛሪ ዋጋ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ፋናቀለማት በዚህ ሳምንት


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ዋንጫን የማስተናገድ አቅም አላት – የካፍ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 2029 የሚካሄደውን የአፍሪካ ዋንጫ የማስተናገድ አቅም እንዳላት የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የቀድሞው የቦትስዋና እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ማክሊን ኮርቴዝ ሌትሺዊቲ ገለጹ። 46ኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ትናንት በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ…

https://www.fanabc.com/archives/267684




ከደንበኛ ሒሳብ ወደ ሌላ ሰው ገንዘብ ያዛወሩ ተከሳሾች እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ከባንኩ ደንበኛ ሂሳብ ከ1 ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ ወደ ሌላ ግለሰብ አዘዋውረዋል የተባሉ ተከሳሾች እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነባቸው። ተከሳሾቹ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዓድዋ ፓርክ ቅርንጫፍ ባንክ ባለሙያ የነበሩት መቅደስ በላይ፣ በዚሁ ባንክ ንኪንግ ኦፊሰር የነበሩት ዮሴፍ ተስፋዬ፣ በዚሁ ባንክ የደንበኞች አገልግሎት…

https://www.fanabc.com/archives/267680

20 last posts shown.