አቶ ፍቃዱ ተሰማ በኦሮሚያ ክልል ሕዝቡ ለመከላከያ ሰራዊት ላሳየው ድጋፍ አመሰገኑ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ የክልሉ ሕዝብ ለመከላከያ ሰራዊት ላሳየው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
አቶ ፍቃዱ ባስተላለፉት መልዕክት÷ዛሬ በመላው ኦሮሚያ ሕዝቡ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ፍቅርና ክብር በሚመጥን መልኩ ድጋፉን አሳይቷል፤ጠንከር ያሉ መልዕክቶችንም አስተላልፏል ብለዋል።
መከላከያ የአንድነታችን ነፀብራቅ፣ የህልውናችን መተማመኛ፣ የክብራችን መገለጫ እና የሰላማችን ዘብ መሆኑ መላው ዓለም የሚያውቃው ደጋግሞም የመሰከረለት ሃቅ ነው ሲሉም አውስተዋል።
የክልሉ ሕዝብ መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ በፈለገባቸው ጊዜያት ሁሉ ልጆቹን መርቆ እስከመሸኘት ያለውን ጠንካራ ድጋፍ አሳይቷል ያሉት ሃላፊው÷ የሰራዊቱን ክብር በሚመጥን መልኩም ድጋፉን ቀጥሏል ብለዋል።
https://www.fanabc.com/archives/195236