FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


"የፒያኖዋ እመቤት" ን የሚዘክር መርሐግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) "የፒያኖዋ እመቤት" እማሆይ ፅጌማርያም ገብሩ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚዘክር መርሐግብር ተካሂዷል፡፡

መርሐግብሩ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተካሄደ ሲሆን ፥ ለዘርፉ ያደረጉትን አበርክቶ በማስመልከት የኮሌጁ የሙዚቃ ትምህርት ክፍል በስማቸው ተሠይሟል።

በመርሐግብሩ የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ፕሬዚዳንት ልጅ ዳንኤል ጆቴ መስፍን፣ የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሰብሳቢ አርቲስት ደበበ እሸቱ እንዲሁም አንጋፋና ወጣት የኪነጥበብ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።... https://www.fanabc.com/archives/195490


አየር መንገዱ የኢ-ኮሜርስ ሎጀስቲክስ አገልግሎት ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዕቃ ጭነት እና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኢ-ኮሜርስ ሎጀስቲክስ አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ፡፡

አየር መንገዱ የአፍሪካን የኢ-ኮሜርስ ንግድ ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱንም በመረጃው አስታውቋል፡፡ https://www.fanabc.com/archives/195462


ማስታወቂያ!

ሲቢኢ ብር - ለቀላል፣ ፈጣን፣ አስተማማኝ የነዳጅ ግብይት!
=================
ደንበኞች ወደ ነዳጅ ማደያ ከመምጣታቸው አስቀድመው
• የሲቢኢ ብር አገልግሎታቸው በአግባቡ እንደሚሠራ ቢያረጋግጡ፣
• ሲቢኢ ብርን መጠቀም ካልጀመሩም ወደ *847# በመደወል፣ ወይም የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ በራሳቸው ተመዝግበው፤ እና
• በሲቢኢ ብር አካውንታቸው በቂ ገንዘብ መኖሩን አረጋግጠው ቢመጡ የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡
ስለ ሲቢኢ ብር አገልግሎት በቂ መረጃ ለማግኘት ወደ 951 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ!
*********************
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለመጫን፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
rel='nofollow'>https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787https://t.me/combankethofficial/2907


ማይክ ሐመር በኢትዮጵያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሊያደርጉ ነው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንዳስታወቀው ልዩ መልዕክተኛው እስከ መጭው ማክሰኞ በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ ጉብኝት ያደርጋሉ።

በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታም ከመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ጋር በተደረሰው የሰላም ስምምነት አተገባበር ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የሽግግር ፍትህና ተጠያቂነትን የማስፈን ሂደትን እንዲሁም የትጥቅ ማስፈታት እና የመልሶ ማቋቋም ሂደቶችን ጨምሮ በሰላም ስምምነቱ በታዩ መሻሻሎች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩም ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ውይይቱ ከመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር የሚካሄድ መሆኑም ነው የተገለጸው።

በጅቡቲ ቆይታቸውም በአፍሪካ የአሜሪካ ወታደራዊ ዕዝ እና የምስራቅ አፍሪካ የተቀናጀ የጋራ ግብረ ኃይል በጋራ በሚያስተናግዱት የምስራቅ አፍሪካ የደህንነት ፎረም ላይ ይካፈላሉ ተብሏል።

በተጨማሪም ከጅቡቲ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽ ትብብር እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩም ነው የተገለጸው።

ከዚህ ባለፈም ከምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ዋና ፀሃፊ ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር ኢጋድ በሚያከናውናቸው ተግባራት ዙሪያም ይወያያሉ ነው የተባለው።


በሐዋሳ ከወ/ሪት ፅጌ መጠለፍ ጋር በተያያዘ 6 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰሞኑን በሐዋሳ ከተማ ወ/ሪት ፅጌ በላቸው የተባለች ወጣት በአንድ ግለሰብ የመጠለፏ ጉዳይ የማህበራዊ ሚዲያዎች አጀንዳ ሆኖ ቆይቷል።

የከተማዋ ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ዛሬ መግለጫ ያወጣ ሲሆን ፥ ከጠለፋ ወንጀሉ ጋር የተጠረጠሩ 6 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ነው ያስታወቀው።

የወንጀሉ ድሪጊት የተፈፀመው በሐዋሳ ከተማ በመናኸሪያ ክ/ከተማ መሆኑን የከተማው ፖሊስ ገልጿል፡፡

በዚህም ወ/ሪት ፅጌ በላቸው የተባለች ግለሰብ በቀን 15/9/2015 ዓ.ም ቤተሰቦቿ ተጠልፋ የት እንደደረሰች አናውቅም በማለት ለመነኸሪያ ክ/ከተማ ፖሊስ ባቀረቡት ማመልከቻ መሰረት ምርመራ መጀመሩ ተገልጿል።... https://www.fanabc.com/archives/195413


የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልፅግና ፓርቲ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ማካሄድ ጀምሯል።

ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ውይይቱን የጀመረው በቅርቡ በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወታቸውን ላጡት ለፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አባል ለአቶ ግርማ የሺጥላ የሕሊና ፀሎት በማድረግ ነው።

ኮሚቴው በሚኖረው ቆይታ በሀገራዊ እንዲሁም በፓርቲያዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት በማካሄድ ውሳኔዎችንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ለውይይት በተዘጋጁ ሰነዶች ላይ የጋራ ግምገማ በማድረግም መላውን ህዝብ በማሳተፍ የሚሳኩ የብልፅግና ጉዞ ትልሞች ላይ እንደሚመክር ከፓርቲው ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።... https://www.fanabc.com/archives/195405


በሞስኮ ከተማ የድሮን ጥቃት መሰንዘሩ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሩሲያ ርዕሰ መዲና ሞስኮ ከተማ የድሮን ጥቃት መሰንዘሩን የከተማዋ ከንቲባ ሰርጌ ሶቢያኒን ተናገሩ፡፡

ዛሬ ማለዳ ድሮኖች በሩሲያ ዋና ከተማ ጥቃት በመፈፀም በሕንፃዎች ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ነው ከንቲባው የተናገሩት።

ሶቢያኒን ነዋሪዎች ኢላማ ከተደረጉ ሁለት አፓርታማዎች እንዲወጡ ማዘዛቸው ተገልጿል።

ከንቲባው ከከተማው የህክምና አገልግሎት የተገኘን መረጃ በመጥቀስ በድሮን በተመታ ህንጻ ውስጥ ምንም አይነት ነዋሪ ላይ ከባድ ጉዳት እንዳልደረሰ ገልፀዋል።... https://www.fanabc.com/archives/195402


በሱዳን የተኩስ አቁም ሥምምነቱ ለተጨማሪ 5 ቀናት ተራዘመ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች የተኩስ አቁም ሥምምነቱን ለተጨማሪ 5 ቀናት አራዘሙት፡፡

የሱዳን ጦር እና የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይል አዲስ ስምምነት ላይ የደረሱት በፈረንጆቹ ግንቦት 20 ቀን 2023 በሳዑዲ አረቢያ መዲና ጅዳ ከመከሩ በኋላ መሆኑን ሺንዋ አል-አረቢያን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡

ሁለቱ ኃይሎች ሠላማዊ ዜጎች ከጦርነት ቀጣናው ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት መንገድ በመክፈት ለማሳለጥ ሥምምነት ላይ መድረሳቸውም ነው የተመላከተው፡፡... https://www.fanabc.com/archives/195398




ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረትና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመካለከል የቀረበው አዋጅ ጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸመውን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበውን አዋጅ አጸደቀ፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ፣ስዊዘርላንድ እና በግራንድ ዱቺ ኦፍ ሉዘምበርግ መንግስት መካከል በገቢ ላይ የሚከፈለውን ግብር በሚመለከት በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ መክሯል፡፡

በሀገራቱ መካከል ተደራራቢ ግብርን ለማስቀረት እና በታክስ ላይ የሚፈጸምን ማጭበርበር ለመከላከል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አዋጁን አጽድቋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው ከገንዘብ ሚኒስቴር የሕግ አማካሪ በተለያዩ መድረኮች በረቂቅ አዋጁ አስፈላጊነት ላይ እንደተወያየም የምክር ቤቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

የምክር ቤቱ አባላትም÷ረቂቅ አዋጁ በታክስ ማጭበርበር የሚታዩ ግድፈቶችን ለማረም የሚያስችል እና የሀገራቱን ግንኙነት የሚያጠናክር አዋጅ መሆኑን ገልጸዋል፡፡


ኢትዮጵያን ወክለው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይ ሲ ቲ ፍጻሜ ውድድር የተሳተፉ ተማሪዎች 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያን ወክለው በ7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይ ሲ ቲ ፍጻሜ ውድድር የተሳተፉት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ።

ከግንቦት 16 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ የሁዋዌ አይ ሲ ቲ ዓለም አቀፍ ውድድር የተካሄደ ሲሆን÷ ኢትዮጵያን ወክለው የተወዳደሩት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቀው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ…https://www.fanabc.com/archives/195292


በዋሽንግተንና አካባቢው ከሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ከንቲባ አዳነች ገለፁ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዋሽንግተን እና አካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ።

ከንቲባዋ በዩናይትድ ስቴትስ የተለያዩ አካባቢዎች ያደረጉትን ጉብኝት አጠናቀዋል።

በዋሽንግተንና አካባቢው ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ባደረጉት ውይይ በአዲስ አበባ ስላለው የኢንቨስትመንት አማራጮች ጠቅለል ያለ መረጃም መሠጠቱን ገልፀዋል።

"በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች ከሚሰሙት የተዛቡ መርጃዎች በላይ በከተማችን አዲስ አበባ ትላልቅ ሰው ተኮር ስራዎች እና ሜጋ ፕሮጀክቶች መሰራታቸውን ጠቅሰናል" ያሉት ከንቲባዋ፥ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑም ለመሳተፍ ያላቸውን ፍላጎት መግለፃቸውን ነው ያስታወቁት።

በውይይቶቹ ላይ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የ200 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ለማድረግና ፕሮጀክቶቹም ተገንብተው እስኪጠናቀቁ በቀጣይነት ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባታቸውን አመልክተዋል።

በአሜሪካ ለነበራቸው ቆይታ ስኬታማነት አስተዋፅኦ ለነበራቸው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የዲያስፖራ አባላት ምስጋና አቅርበዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለፕሬዚዳንት ኤርዶኻን የደስታ መልዕክት ላኩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቱርክ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ ለተመረጡት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶኻን የእንኳን ደስ ያልዎት መልዕክት አስተላለፉ።

ትናንት በቱርክ በተደረገ ምርጫ ፕሬዚዳንት ኤርዶኻን በድጋሚ ተመርጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመልዕክታቸው፥ "በድጋሚ በመመረጥዎ እንኳን ደስ ያልዎት" ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ የኢትዮጵያ እና ቱርክን ግንኙነት በቀጣይ የበለጠ ለማጠናከር በጋራ ለመሥራትም ዝግጁ መሆናቸውን ነው ያመላከቱት።


በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሊድስ ዩናይትድ እና ሌሲስተር ሲቲ ወደ ታችኛው ሊግ ወረዱ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሊድስ ዩናይትድ እና ሌሲስተር ሲቲ ወደ ታችኛው ሊግ ወርደዋል።

በሊጉ የመጨረሻ ሳምንት መርሐ ግብር ሌሲስተር ከዌስትሀም ጋር ተጫውቶ 2 ለ 1 ሲያሸንፍ ሊድስ በቶተንሀም 4 ለ 1 ተሸንፏል።

በሜዳው ከበርንማውዝ የተጫወተው ኤቨርተን ደግሞ 1 ለ 0 አሸንፏል።

ውጤቱን ተከትሎም ኤቨርተን በመጨረሻው ሳምንት በፕሪሚየር ሊጉ መቆየቱን አረጋግጧል።

በአንጻሩ ሊድስ እና ሌሲስተር ቀደም ብሎ መውረዱን ያረጋገጠውን ሳውዝሃምተንን ተከትለው ወደ ታችኛው ሊግ ወርደዋል።




አቶ ደመቀ የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ ደመቀ÷ በቻይና የኢንቨስትመንት ዋና ማዕከል በሆነችው ጉዋንግዡ በተካሄደው የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ ተሳትፋዋል፡፡

በመድረኩ ባደረጉት ንግግርም የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡


አቶ ፍቃዱ ተሰማ በኦሮሚያ ክልል ሕዝቡ ለመከላከያ ሰራዊት ላሳየው ድጋፍ አመሰገኑ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሰማ የክልሉ ሕዝብ ለመከላከያ ሰራዊት ላሳየው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

አቶ ፍቃዱ ባስተላለፉት መልዕክት÷ዛሬ በመላው ኦሮሚያ ሕዝቡ ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ያለውን ፍቅርና ክብር በሚመጥን መልኩ ድጋፉን አሳይቷል፤ጠንከር ያሉ መልዕክቶችንም አስተላልፏል ብለዋል።

መከላከያ የአንድነታችን ነፀብራቅ፣ የህልውናችን መተማመኛ፣ የክብራችን መገለጫ እና የሰላማችን ዘብ መሆኑ መላው ዓለም የሚያውቃው ደጋግሞም የመሰከረለት ሃቅ ነው ሲሉም አውስተዋል።

የክልሉ ሕዝብ መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ በፈለገባቸው ጊዜያት ሁሉ ልጆቹን መርቆ እስከመሸኘት ያለውን ጠንካራ ድጋፍ አሳይቷል ያሉት ሃላፊው÷ የሰራዊቱን ክብር በሚመጥን መልኩም ድጋፉን ቀጥሏል ብለዋል።https://www.fanabc.com/archives/195236


ለመከላከያ ሰራዊት የድጋፍ ሰልፍ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ ክልሎች ዋና ዋና ከተሞች ዜጎች ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ድጋፍ በታላቅ ሠላማዊ ሰልፍ በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።

በድጋፍ ሰልፉ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ወጣቶችና የየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች እየተሳተፉ ነው፡፡

ሰልፈኞቹ ለመከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ድጋፍ የሚገልፅ መፈክርም እያሰሙ ይገኛሉ፡፡

18 last posts shown.