FastMereja.com


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


#የሞቱት አሕዮች ጭንቅላት ተቀያይሮ ቢገጠምም…

በቅድስት ቤተ ክርስቲያችን ትልቅ ስራ ከሰሩና ትልቅ ተጋድሎ ካላቸው ቅዱሳን አባቶች አንዱ ቅዱስ ቶማስ ዘመራስ ነው፡፡ መራስ የትውልድ ሀገሩ ናትና በዚያው ይጠራል፡፡

ዲዮቅልጥያኖስና መክስሚያኖስ በክርስቲያኖች ላይ መከራ ባጸኑበት ዘመን ለ22 ዓመታት የተጋደለው ይህ ድንቅ ሰማዕትና ሐዋርያ ገና በወጣትነቱ መንኖ ገዳም የኖረ፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊትም በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የኖረ ነበር፡፡

በጨካኞቹ ነገስታት ዘመንም ለጣኦት እንዲሰግድ የደረሰበትን መከራ ታግሶ በክርስቶስ ፍቅር በመጽናቱ በ22 ዓመታት የመከራ ጊዜው ጨለማ ውስጥ ጥለውት አካሉን እየቆራረጡ ለጣዖታቸው ያጥኑ ስለነበር 2 እግሮቹ፣ 2 እጆቹ፣ 2 ጀሮዎቹ፣ አፍንጫውና ፪ ዐይኖቹ አልነበሩም፡፡ የተጣለበትን ስፍራ የምታውቅ አንዲት ሴትም በስውር እየገባች ትመግበው ነበር፡፡

እኛ በዘመናችን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፍቅር የትኛውን አካላችን እንድንሰዋ አልጠተየቅንም፤ ወይም በረሀብ አልተቀጣንም፡፡ ይልቁንም በነጻነት የምናመልክበት እድል እነዚህ ቅዱሳን አባቶቻችን መከራውን ታግሰው ባቆዩልን እምነት መጽናትና ቤተ ክርስቲያናችንን በተሰጠን ስጋዊና መንፈሳዊ ሃብት ማገዝ ብቻ ነው የሚጠበቅብን፡፡

የቤተክርስቲያን የመከራ ዘመን አልፎ ንጉስ ቆስጠንጢኖስ ስልጣን ከተረከበ በኋላ በኒቂያ ጉባኤ አርዮስን ለማውገዝ ከተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት አንዱ ቅዱስ ቶማስ ዘመራስ ነበር፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ስጋዊ አካሉ የጎደለውን ቅዱስ ሰማዕት በቅርጫት አድርገው በአሕዮች ጭነው ለቀናት ተጉዘው ነበር ወደ ኒቂያ የወሰዱት፡፡ በመንገድ ላይ ሳሉም ካደሩበት ቦታ የአርዮስ ተከታዮች የአሕዮቹን ራስ ቆርጠው ገድለዋቸው ሔዱ፡፡

ምንም እንኳን ሁለት አይኖቹ ቢጠፉም መንፈሳዊ ምጥቀቱ ከፍ ያለ ነበርና በሌሊት ገስግሰው ሊጓዙ ሲነሱ የአሕዮቹን ሁኔታ ደቀ መዛሙርቱ ሲነግሩት ቀድሞ አውቆት ነበርና ጭንቅላታቸውን ከአካላቸው ጋር እንዲገጥሙት አዘዛቸው፡፡

ከዚያም ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት አሕዮቹ እደገና ነፍስ ዘርተው ተነስተው መንገዳቸውን ቀጥለዋል፡፡ አስገራሚው ነገር በጨለማው ምክንያት አንዱን ከአንዱ መለየት ስላልቻሉ የነጩን አሕያ ጭንቅላት ለጥቁሩ፣ የጥቁሩንም ለነጩ እንደገጠሙላቸው ጠዋት በብርሃን አዩት፡፡

ቅዱስ ቶማስ ዘመራስም አርዮስን አውግዞ ወደ ሀገሩ ስብከቱ ተመልሶ ጸሎተ ሃይማኖት የተባለውን ጸሎት ለሕዝቡ አስተምሯል፡፡ በተጨማሪም ለ40 ዓመታት በጵጵስና አገልግሎ አልፏል፡፡ ቅዱሳን አባቶች በትልቅ መስዋዕትነት ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተው ያቆዩዋትን እምነት ለመጠበቅ እጃችንን እንድንዘረጋ መጠየቅ በራሱ ከበረከታቸው መካፈል ነውና ገዳማትን እንርዳ፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


ክኖር “ምርጡ ጉርሻ” ሲል የሰየመውን የንቅናቄ ዘመቻ ታላላቅ እንግዶች በተገኙበት ይፋ አደረገ።

#FastMereja I ክኖር ፤ "ምርጡ ጉርሻ" የተሰኘ አዲሱን የንቅናቄ ዘመቻውን በዛሬው ዕለት በቃና ዌርሀውስ ባዘጋጀውና በአረንጓዴ ምንጣፍ በደመቀው ዝግጅት ላይ ይፋ አድርጓል።

ይህ ዘመቻ ይፋ ከመደረጉ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ በኢትዮጵያውያን የአመጋገብ ስርዓት ውስጥ የአትክልት ምግቦችን ጠቀሜታ ለማስተዋወቅ የተነደፉ ተከታታይ አሳታፊ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን ፤ ተከታታይ ሁነቶቹም ይህን ትልቅ ተነሳሽነት በማጉላት ረገድ ተደማጭነት ያላቸውን ግለሰቦችና ታዋቂ ሰዎችን ባንድነት አስተባብሯል።

ዩኒሴፍ እና ጤና ሚኒስቴር ያደረጉት ጥናት እንደሚያሳየው በኢትዮጵያ 39% የሚሆኑት አምስት አመት በታች ያሉ ህጻናት የመቀንጨር ችግር የሚያጋጥማቸው ሲሆን ፤ ይህም ሥር በሰደደ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት የሚመጣ መሆኑ ተመላክቷል።

የ #ምርጡ_ጉርሻ ንቅናቄ ኢትዮጵያውያን የአትክልት ምግቦችን በገበታቸው ውስጥ እንዲያካትቱ ጥሪ ሲያቀርብ ፤ ልዩ የሆነውን የጉርሻ ባህል አካታች በማድረግ ነው።  ይህም ኢትዮጵያውያን ጣፋጭ የአትክልት ምግቦችን አብስለው እንዲመገቡ እና ለወዳጆቻቸው የአትክልት ምግብን በጉርሻ እንዲጋብዙ በማነሳሳት እና ውጤታማ ለውጥ በማምጣት በህብረተሰቡ ውስጥ ተጨባጭ ልዩነት ለመፍጠር ያለመ ነው።

የዩኒሊቨር አፍሪካ ኑትሪሽን ፕላትፎርም ዳይሬክተር ሰላመክርስቶስ በላይ “ምርጡ ጉርሻ’ ዘመቻ አዎንታዊ ምላሽ በማግኘቱ እጅግ ተደስተናል።” ያሉ ሲሆን ፤ አክለውም “ይህ ተነሳሽነት የአትክልት ምግቦችን የኢትዮጵያውያን ገበታ አካል ለማድረግ እና የተሻለ የአመጋገብ ባህልን አብሮ በመብላት ውስጥ ከፍ ለማድረግ ያለንን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳያል” ብለዋል።

ክኖር ንቅናቄውን ለመምራት ከታዋቂው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ጋር በጋራ እየሰራ ነው። ኮሜዲያን እሸቱ የ"ምርጡ ጉርሻ" ዘመቻ ዋና መሪ እንደመሆኑ መጠን ፤ ዜጎች የአትክልት ምግቦችን ጠቃሚነት እንዲረዱ እንዲሁም አትክልት ምግቦችን እንዲጎራረሱ አነሳስቷል።

በዝግጅቱ አስደሳች የጉርሻ ሁነቶች የታዩበት ሲሆን፣ ተሳታፊዎች የአትክልት ማዕድ ተጋርተዋል። በዚህም ዝግጅቱ የኢትዮጵያን ባህል እና የምግብ አሰራር ልምድን ያጎላ ሆኖ ታይቷል። ይህ አስደናቂ መስተጋብር ታዳሚዎችና ሰፊው ማህበረሰብ ከአትክልት ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያስታውሳቸው ሁነቶቹ በልዩ ልዩ ፎቶግራፎች ተከትበዋል።

በዘመቻው  ተሳታፊዎች ሲጎራረሱ ፎቶዎችን የተነሱ ሲሆን በዚህም #ምርጡ_ጉርሻ ለብሩሕ ኢትዮጵያ! በሚል አትክልት ምግቦችን የገበታችን ኩራት የሚደረግን ቅስቀሳ አበረታተዋል።




#የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውላለሁ…


ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ባኮስ የታላቋ ንግስት ሕንደኬ የግዛቷ ሁሉ አዛዥና በገንዘቧም የሰለጠነ ነበር፡፡ ጃንደረባው እንደዘመናችን ሕትመት ባልተስፋፋበት በዚያ ዘመን በ34 ዓ.ም ወደ ኢየሩሳሌም ሊሰግድ ሔዶ ሲመለስ ትንቢተ ኢሳይያስን ያነብ ነበር፡፡

በሐዋርያት ስራ 8÷26 ጀምሮ እንደተጻፈው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ ሀዋርያው ቅዱስ ፊሊጳስ በመምጣት ጃንደረባውን እንዲያገኘው አዘዘው፡፡ ሐዋርያውም መጥቶ ባኮስን “በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን?” አለው፡፡ እርሱም “የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውላለሁ?” ሲል መለሰለት፡፡

ባያስተውለውም፣ ባይገባውም፣ እንደ ዘመናችን ሕትመት ባይስፋፋም ጃንደረባው ግን በሞላው በተረፈው የንግስቲቱ ሃብት ላይ አዛዥ ሆኖ ሳለ ኢየሩሳሌም ሔዶ መስገድና ትንቢተ ኢሳያስን ማንበብ ነበር ምርጫው፡፡ በዚህ ዘመን እግዚአብሔር በሃብት የባረከን ሰዎች በገንዘባችን፣ የት መሔድ፣ ምን ማንበብ፣ ምን ማድረግ፣ ምንስ መስራት ይሆን የምንፈልገው?

የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “በጉዞ ላይ ሆኖ ያውም በሠረገላ ላይ ተቀምጦ ማንበብ አለማቋረጥ ምን ያህል ትጋት የሚጠይቅ እንደሆነ እንድታስተውሉ እጠይቃችኋለሁ በቤታቸው እንኳን ቁጭ ብለው ማንበብን ለማይፈልጉ ሰዎች ይህ ታሪክ ሊስተዋል ይገባዋል፤ ይልቁንም መጻሕፍትን ማንበብን ጊዜን እንደማጥፋት የሚቆጥሩ ወይም የተለያየ ምክንያት የሚሰነዝሩ ሰዎች ቅዱሳት መጻሕፍትን የማንበብ ጠቀሜታ አይታያቸውም” የሐዋርያት በማለት ሥራን በተረጎመበት መጽሐፉ አድንቆ ተናግሯል፡፡


ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስም ሲያነበው የነበረውን “እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፣ የበግ ጠቦትም በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ። ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና። ትውሉዱንስ ማን ይናገራል።” የሚለውን በትንቢተ ኢሳይያስ 53÷7 የሚለውን ቃል መነሻ አድርጎ ስለ ጌታችን የሰው ልጅን ማዳንና ፍቅር አስተማረው፡፡ በፈቃዱም አምኖ ተጠመቀ፡፡

ስጋዊ ሃብታችንን የነፍሳችንን ድህነት የምንሰራበት መሳሪያ አድርጎ ሰጥቶናል፡፡ እንደ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የቅዱሳን መካናትን በረከት ለማግኘት እንትጋ፡፡

በዘመናችንም ቅዱሳን ገዳማውያንና አባቶች ያሉባቸውን ገዳማት እናግዝ፣ በፍጹም ልግስና ከሚያልፈው ገንዘባችን ሰጥተን ከማያልፈው የጸሎታቸውን በረከት እንካፈል፡፡ የቅዱስ ፊሊጶስና የጃንደረባው በረከት ይደርብን!!!         

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


«የኢትዮጵያ ሴቶች በጣም ውብ ናቸው ባለቤቴም ትስማማለች ነገርግን ባለቤቴ ትበልጣቸዋለች።» የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪክ ሞትስፔ


አርቲስት ናርዶስ አዳነ የሎዛ የስነምግብ አማካሪ ድርጅት አምባሳደር ሆነች

አርቲስት ናርዶስ አዳነ የሎዛ የስነ ምግብ ማማከር ህክምና ተቋም የብራንድ አምባሳደር በመሆን ስምምነት አደረገች።

ሎዛ የስነ ምግብ ማማከርና ህክምና ተቋም በዘርፉ የካበተ የስራ ልምድ እና እውቀት ባላቸው ባለሙያዎች የስኳር ፣ የኮሌስተሮል መጨመር ፣ የደም ግፊት ፣ የስትሮክ ፣የልብ በሽታ ፣ ሪህ ፣ የሰውነት ክብደት መጨመር(መቀነስ) ተጋላጭነት ስጋት ውስጥ ለሚገቡ ሰዎች መፍትሔ ለመስጠት የተቋቋመ መሆኑን የተቋሙ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ሙሉቀን ፈቃደ (ረ/ኘ) የብራንድ አምባሳደር ሰምምነት አስመልክቶ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጸዋል።

አርቲስት ናርዶስ አዳነ በበኩላ የኀብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት ላይ በብራንድ አምባሳደር በመሳተፌ ደስተኛ ነኝ ብላለች።


#የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውላለሁ…


ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ባኮስ የታላቋ ንግስት ሕንደኬ የግዛቷ ሁሉ አዛዥና በገንዘቧም የሰለጠነ ነበር፡፡ ጃንደረባው እንደዘመናችን ሕትመት ባልተስፋፋበት በዚያ ዘመን በ34 ዓ.ም ወደ ኢየሩሳሌም ሊሰግድ ሔዶ ሲመለስ ትንቢተ ኢሳይያስን ያነብ ነበር፡፡

በሐዋርያት ስራ 8÷26 ጀምሮ እንደተጻፈው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ ሀዋርያው ቅዱስ ፊሊጳስ በመምጣት ጃንደረባውን እንዲያገኘው አዘዘው፡፡ ሐዋርያውም መጥቶ ባኮስን “በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን?” አለው፡፡ እርሱም “የሚያስረዳኝ ሰው ሳይኖር እንዴት አድርጌ አስተውላለሁ?” ሲል መለሰለት፡፡

ባያስተውለውም፣ ባይገባውም፣ እንደ ዘመናችን ሕትመት ባይስፋፋም ጃንደረባው ግን በሞላው በተረፈው የንግስቲቱ ሃብት ላይ አዛዥ ሆኖ ሳለ ኢየሩሳሌም ሔዶ መስገድና ትንቢተ ኢሳያስን ማንበብ ነበር ምርጫው፡፡ በዚህ ዘመን እግዚአብሔር በሃብት የባረከን ሰዎች በገንዘባችን፣ የት መሔድ፣ ምን ማንበብ፣ ምን ማድረግ፣ ምንስ መስራት ይሆን የምንፈልገው?

የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “በጉዞ ላይ ሆኖ ያውም በሠረገላ ላይ ተቀምጦ ማንበብ አለማቋረጥ ምን ያህል ትጋት የሚጠይቅ እንደሆነ እንድታስተውሉ እጠይቃችኋለሁ በቤታቸው እንኳን ቁጭ ብለው ማንበብን ለማይፈልጉ ሰዎች ይህ ታሪክ ሊስተዋል ይገባዋል፤ ይልቁንም መጻሕፍትን ማንበብን ጊዜን እንደማጥፋት የሚቆጥሩ ወይም የተለያየ ምክንያት የሚሰነዝሩ ሰዎች ቅዱሳት መጻሕፍትን የማንበብ ጠቀሜታ አይታያቸውም” የሐዋርያት በማለት ሥራን በተረጎመበት መጽሐፉ አድንቆ ተናግሯል፡፡


ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስም ሲያነበው የነበረውን “እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፣ የበግ ጠቦትም በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ። ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና። ትውሉዱንስ ማን ይናገራል።” የሚለውን በትንቢተ ኢሳይያስ 53÷7 የሚለውን ቃል መነሻ አድርጎ ስለ ጌታችን የሰው ልጅን ማዳንና ፍቅር አስተማረው፡፡ በፈቃዱም አምኖ ተጠመቀ፡፡

ስጋዊ ሃብታችንን የነፍሳችንን ድህነት የምንሰራበት መሳሪያ አድርጎ ሰጥቶናል፡፡ እንደ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የቅዱሳን መካናትን በረከት ለማግኘት እንትጋ፡፡

በዘመናችንም ቅዱሳን ገዳማውያንና አባቶች ያሉባቸውን ገዳማት እናግዝ፣ በፍጹም ልግስና ከሚያልፈው ገንዘባችን ሰጥተን ከማያልፈው የጸሎታቸውን በረከት እንካፈል፡፡ የቅዱስ ፊሊጶስና የጃንደረባው በረከት ይደርብን!!!         

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


ከ500 በላይ የዌብሳይት ቴፕሌት አበልፃጊዎችን አወዳድሮ ሊሸልም መሆኑን አሸዋ ቴክኖሎጂ አስታወቀ።

#FastMereja I አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አ.ማ ሲሰራበት የቆየዉን የቴክኖሎጂ ዉጤት ከ500 በላይ አበልፃጊዎችን በማሳተፍ ዘርፉን ለማበርታታት ፕሮጀክት ቀርፆ መንቀሳቀስ መጀመሩን በዛሬዉ ዕለት ጥቅምት 12/2017 ዓ.ም ቦሌ በሚገኘዉ ዋና መስሪያቤቱ ሪያሊቲ ሀንፃ 9ኛ ፎቅ በተሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ አስታዉቋል።

የአሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽን አ.ማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዳንኤል በቀለ ይሀንን የፈጠራ ዉድድር በዘጠና ቀን ዘመቻ ወደስራ ስናስገባ የኢትዮጵያን ብሎም የአፍሪካን የቴክኖሎጂ እድገት ካለበት ደረጃ በአጭር ጊዜ የከፍታ ማማላይ ለማድረስ አልመን ነዉ ሲሉም ተናግረዋል፡፡

በመርሀ ግብሩም በቅድሚያ የተወዳዳሪዎች ምዝገባ የሚካሄድ ሲሆን ምዝገባዉም እስከ ኖቬምበር 8 ድረስ የሚቆይ ሲሆን በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚገኙ የቴክኖሎጂ ዘርፍ ተማሪዎችን እንዲሁም በዘርፉ በግላቸው የሚንቀሳቀሱ ከ500 በላይ ዌብሳይት አበልፃጊዎችን አወዳድሮ እንደሚሸልም እና ለወጣቶች የስራ ፈጠራ ሃሳባቸውን ይዞ መምጣቱን ገልፀዉ፤ ዉድድሩ በአምስት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚካሄድ እንደሆነና የዌብ ዲዛይነሮች ይህ እድል ሳያመልጣቸዉ እንዲመዘገቡ ጥሪ ያቀረቡት ሀላፊዉ፤ አቅማችሁን በማዉጣት የተሻለ ነገር በመሥራት ብሎም በፍሪላንሰርነት በጋራ እንሥራ የሚል ጥሪ በማቅረብ ለበርካቶች የሥራ ዕድል የሚፈጥር እንቅስቃሴ መሆኑን በጋዜጣዊ መግላጫ መረሀ ግብሩ ወቅት ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የዌብ ዲዛይኑ ትኩረት አድርጎ የሚሰራባቸው የስራ ዘርፎች ኢኮሜርስ፣ ቱሪዝም፣ ሆስፒታሊቲ፣ የሄልዝ ኬር፣ የተማሪዎች ሰርቪስ፣ የማህበረሰባዊ ትስስር ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ማወቅ ተችሏል።


ከ500 በላይ ቤተሰብ በማፍራት በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ የሰፈሩት አባ ዳሉ ጃርሶ ማረፋቸዉ ተሰማ

#FastMereja I ከ500 በላይ ቤተሰብ በማፍራት በአፍሪካ ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ የሰፈሩት አባ ዳሉ ጃርሶ ማረፋቸዉን የናነሰቦ ወረዳ አስተዳደር አስታወቀ፡፡

የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ ዑመር ቴና ለኦቢኤን ሳይበር ሚዲያ እንደተናገሩት የእድሜ ባለጸጋዉ አባ ዳሉ ጃርሶ ዊርቱ ማረፋቸዉን ገልጸዋል፡፡


እሳቱን መቆጣጠር ተችሏል።
#FastMereja
መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። የእሳት አደጋዉን በቁጥጥር ስር በማዋል ርብርብ ያደረጉ ፤ በርካታ ሎጀስቲክ በማቅረብ ለደገፉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።


#ሌብነት
አሁን ላይ በመርካቶ ሸማ ተራ ላይ የተከሰተው እጅግ ከባድ የእሳት አደጋ ይኸንን ይመስላል ። የእሳት አደጋ ሰራተኞች እና ቅን የሆኑ ነዋሪዎች (ሕዝቡ) እሳቱን ለማጥፋት እያደረጉ ላለው ድካም ክብር ይገባቸዋል ።

አጋጣሚውን በመጠቀም የሰው ንብረት እየዘረፉ ያሉ ምናምንቴ ሰዎች ሌላ አገር አላቸው ወይ !? የትስ ነው ሸጠው የሚበሉት !?
ከሰውስ አልተፈጠሩም ወይ !? ምን ያክል ተጣመው ቢያድጉ ነው ሰው ትልቅ መከራ ደርሶበት እያለቀሰ ባለበት ሰዓት ላይ ለመስረቅ የሚሯሯጡት !?

Via: ዘካሪያስ ኪሮስ


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
በመርካቶ የደረሰው የእሳት አደጋ እጅግ ከባድ ነው


#ትዝብት

#ትዝብት
ሁለት የእሳት አደጋ መኪናዎች ላንቃቸውን ከፍተው እየጮሁ እና መብራታቸውን እያንቦገቦጉ ይመጣሉ።

ይመስለኛል መርካቶ ላይ ለተከሰተው የእሳት አደጋ ይመስለኛል

መንገድ ማን ይልቀቅ?

ጭራሽ ከመኪናዎቹ ጋር እሽቅድድም : የመኪናዎቹን ሁኔታ ከቁብም የቆጠረ ያለ አይመስልም።

በምን የአእምሮ ልኬት ነው ግን ሰው ከአንቡላንስ እና እሳት አደጋ መኪና ጋር መንገድ ያለመልቀቅ ግብ ግብ ውስጥ የሚገባው?

Via: ዘመላክ ኢንድሪያስ


መርካቶ ሸማ ተራ

መርካቶ ሸማ ተራ ከጃቡላኒ የንግድ ማዕከል ጀርባ ወይም ሽንኩርት በረንዳ የሚባለው ሥፍራ ላይ ከበድ ያለ የእሳት አደጋ ተከስቷል ። የእሳት አደጋ ሰራተኞች እሳቱን ለማጥፋት የሰውንም ሕይወት ለማትረፍ ንብረትም እንዳይወድም ጥረት እያደረጉ ነው ።

Via: ጌች ሐበሻ፣ ናርዶስ ክፍሌ

17 last posts shown.