Posts filter


«ለአንዳንድ የቃላት አጠቃቀሜ ትላልቅ ሰዎች እና ህፃናት ሲሰሙት ስለሚከብድ ለቃላት አጠቃቀሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ! ከዛ ውጪ ያጠፋውት ነገር የለም። በግልፅ ክርስትናን የሚሳደቡ ግለሰቦችም ይቅርታ እንዲጠይቁ ይደረግ!» በቲክቶክ ስሙ "እፎይ"


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በጥላቻ ንግግር ግጭት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው

ኢትዮጵያ ብዝሃ ሀይማኖት የሆነች ሀገር እንደ መሆኗ የተለያየ እምነት ተከታዬች ለዘመናት ተፈቃቅደውና ተከባብረው ኖረውባታል። እየኖሩባትም ይገኛሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በተለይም የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም ይህንን በጎ እሴት በመሸርሸር ውዝግብና ግጭት ለመፍጠር የሚሰሩ አካላት እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡

በተለይም የእስልምናን መልካም እሴቶች እና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር በመዳፈር ህዝበ ሙስሊሙን የሚያስቆጡ የጥላቻ ንግግሮች በስፋት እየተሰራጩ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ተረድቷል።

ጠቅላይ ም/ቤቱ እነዚህ አካላት ከዛሬ ነገ ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸው ከጥፋታቸው ይታረማሉ በሚል ቀና እሳቤ ጉዳዩን በትዕግስት ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ጠቅላይ ም/ቤቱ ችግሩን ከዚህ በላይ በትዕግስት መመልከት ውጤቱ የከፋ በመሆኑ የኢስላምንና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር የሚነኩ አካላት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ ከየትኛው አይነት ተግባር ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሰራ ይሆናል፡፡ የጥላቻ ንግግር በየትኛውም ወገን ቢሰነዘር ጠቅላይ ም/ቤቱ በጽኑ እንደሚያወግዝና ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንደሚሰራም ማወቅ ይገባል፡፡

በመሆኑም በተደጋጋሚ ተከስቶ በቸልታ እየታለፈ ያለው የኢስላምንና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብርየሚነካ የጥላቻ ንግግር ያደረጉ ግለሰቦች አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው የፍትህ፣ የፀጥታና የደህንነት አካላት የህግ ተጠያቂነትን ለማምጣትና መሰል ጥፋቶች እንዳይደገሙ ከመቼውም ጊዜ በላይ በልዩ ትኩረት እንዲሰሩ ም/ቤቱ ያሳስባል።

በመሆኑም፡-
1. የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጉዳዩ ከዚህ በላይ ከመክረሩ በፊት የጋራ አቋም በመያዝ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲያገኝ አስቸኳይ ውሳኔ እንዲወስን።

2. ይህ በአደባባይ የተላለፈ የጥላቻ ንግግርና ሀይማኖታዊ ትንኮሳ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የፈጠረውን ህመም በአግባቡ በመረዳት የሚመለከታቸው የፀጥታና የህግ አካላት ተጨማሪ ጥፋት ከመከተሉ በፊት አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱ፤

3. የሰሞኑ የጥላቻ ንግግር ምንጩ የተራ ግለሰብ ቢመስልም ከጀርባ የአጀንዳና የሃሳብ ተጋሪዎች ያሉት በመሆኑ ህዝባዊ ቁጣ ከመቀስቀሱ በፊት የሀገርና የህዝብ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ ከጠቅላይ ም/ቤቱ ጋር በመቆም ትንኮሳውን እንዲያወግዙ፤ እንዲሁም

4. ወቅቱ በሙስሊሞች እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች የፆም ወቅት እንደመሆኑ እንዲህ አይነት ከሀይማኖትና ከኢትዮጵያዊነት እሴት ያፈነገጡ የጥላቻ ንግግሮች የሚገሰፁበትና የሚታረሙበት የፅሞና ወቅት እንዲሆን ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ጠቅላይ ም/ቤቱ የእስልምና አንኳር እሴቶችን በተለይም የፈጣሪያችንን አሏህ፣ የነቢያትን፣ የመለኮታዊ መፃህፍትንና የደጋግ ተከታዮችን ክብር የሚያጎድፉ ማንኛውም አይነት የጥላቻ ትንኮሳና ድርጊት በህግ አግባብ እንዲታረሙ ተቋማዊ ኃላፊነቱን የሚወጣም ይሆናል፡፡

ለእውነተኛ ሰላምና አብሮነት የሚቆረቆሩ አካላት ሁሉ ድርጊቱን እንዲያወግዙና ለፍትህ እንዲሰሩም ጠቅላይ ም/ቤቱ በድጋሚ ጥሪውን ያቀርባል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ




ኦክሎክ ሞተርስ ከማህበራት ጋር እርቅ መፈፀሙን አስታወቀ።

#FastMereja I ኦክሎክ ሞተርስ ከማህበራት ጋር እርቅ መፈፀሙን ዛሬ መጋቢት 01/2017 ዓም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገለፀ።

ኦክሎክ ሞተርስ ለ65 ማህበራት ተሽከርካሪ ለማቅረብ ውል ፈፅመው ወደ ስራ ገብተው የነበረ ሲሆን በኦክሎክ እና በማህበሩ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት 16 ማህበራት በድርጅቱ ላይ ክስ መስርተው የነበረ ሲሆን ዛሬ በተሰጠ ጋዜጣዊ ስድስት ማህበራት ክስ አቋርጠው እርቅ መፈፀማቸውን አስታውቋል።

በእርቁ መሰረት የማህበሩ አባላት መኪና የሚፈልጉ በሶስት ወራት ውስጥ መኪና ማስረከብ፣ ለቅድመ ክፍያ የከፈለው ክፍያ ተመላሽ እንዲደረግለት የፈለገ ደንበኛ በ45 ቀናት ውስጥ ገንዘቡ ተመላሽ እንዲደረግ ተግባብተን ወደ ትግበራ ስራ ገብተናል ብሏል።

ባለፈዉ ዓመት 800 የሚጠጉ ተሽከርካሪዎችን ለደንበኞች ማስተላለፋቸውን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ታመነ ካሳሁን ገልጸው በያዝነዉ የበጀት ዓመት 400 ገደማ ተሸከርካሪዎችን ማስተላለፋቸውን ተናግሯል።

#ቢዝነስ


#መምህሩን በሃይማኖት የመሰለው አብሪ ኮከብ 

ቅዱሱ ታላቅ የሃይማኖት ጠበቃ ሲሆን የተወለደው ግብጽ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው፡፡ ሲሆን በምግባሩ፣ በትምሕርቱ ለምዕመናን ጥቅም ሆኗቸዋል፡፡ ቅዱስ እለእስክንድሮስ ገና ልጅ ሳለ ምሥጢረ ክርስትናን ይማር ዘንድ ወደ ተፍጻሜተ_ሰማዕት ቅዱስ_ዼጥሮስ ሔዷል፡፡ ቅዱስ ዼጥሮስ የግብጽ 17ኛ ፓትርያርክና ሊቅ ሲሆን በታሪክ የዘመነ ሰማዕታት መጨረሻ ተብሎ ይታወቃል፡፡ እርሱ ያስተማራቸው ብዙ አርድእት ቢኖሩም 3ቱ ግን ተጠቃሽ ነበሩ፡፡ አኪላስ ውዳሴ ከንቱ ወዳጅ፣ ሆዱ ዘመዱ፣ አርዮስ ደግሞ ወልድ ፍጡር ያለ የቤተ ክርስቲያን ጠላት ሆኑ፡፡ አኪላስ ስለ ምንም የማይጨንቀው ሰው ነበር፡፡ ደጉ ቅዱስ እለእስክንድሮስ በሃይማኖት በመመሰል በጾምና በጸሎት እየተጋ መምሕሩን ቅዱስ ዼጥሮስን ለመተካት ለመምሰል ይጥር ነበር::

ወቅቱ ዘመነ ሰማዕታት እንደ መሆኑ ቅዱሱ ከመምሕሩ ጋር ብዙ ነገሮችን አሳልፏል፡፡ አርዮስ ክዶ ቅዱስ ዼጥሮስ ካወገዘው በሁዋላ እንደ ባልንጀራ ገስጾ ሊመልሰውም ሞክሮ ነበር፡፡ ነገር ግን የአርዮስን ክፋት ከጌታ ዘንድ የተረዳው ቅዱስ ዼጥሮስ ደቀ መዝሙሩን እለእስክንድሮስን ጠርቶ መከረው፡፡ "እኔ ከሞትኩ በሁዋላ አኪላስ ይተካል:: ከአርዮስ ጋር ስለሚወዳጅ በ6 ወሩ ይቀሠፋል:: አንተ ግን ከአርዮስ መርዝ ተጠበቅ" አለው:: ይህንን ካለው በሁዋላ ወታደሮች የቅዱስ ዼጥሮስን አንገት ቆረጡ:: ይህ የተደረገውም እ.ኤ.አ በ311 ዓ/ም ነው:: ወዲያውም አኪላስ ተሾመ:: እንደ ተባለውም ከአርዮስ ጋር ስለተወዳጀ በ6 ወሩ ተቀሰፈ:: በዚያው ዓመትም ቅዱስ እለእስክንድሮስ የእስክንድርያ ወይም ግብጽ 19ኛ ፓትርያርክ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሾመ::

ሊቁ ሲሾም መልካም አጋጣሚ የነበረው ያ የመከራ ዘመን ማለፉ ሲሆን በጣም ከባዱ ግን የአርዮስ ተከታዮች ከተገመተው በላይ መበብዛታቸው ነው፡፡ ቅዱሱ በዽዽስ መንበሩ ለ17 ዓመታት ሲቆይ ዕንቅልፍና ዕረፍትን ትቶ እየጾመ፣ እየጸለየ፣ ምዕመናንን ከአርዮስ የኑፋቄ መርዝ ለመታደግ በቃልም በደብዳቤም መሸ ነጋ ሳይል ሕዝቡን እያስተማረ ታግሏል፡፡ በመጨረሻም በ325 ዓ.ም በንጉሡ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አዋጅ በተዘጋጀው የኒቂያ ጉባኤ ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ መከራ ካሳለፉ ከ318 ሊቃውንት ጋር አውግዞታል ለይቶታል፡፡ በጉባኤው መጨረሻም ጸሎተ ሃይማኖትን ሠርተው፣ መጽሐፈ ቅዳሴ ደርሰው፣ 20 ቀኖናወችን አውጥተው፣ አሥራው መጻሕፍትን ወስነው፣ ቤተ ክርስቲያንን በዓለት ላይ አጽንተው ተለያይተዋል:: የዚህ ሁሉ መሪ ደግሞ ቅዱስ እለእስክንድሮስ ነው::

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወልድ ዋሕድ፣ አምላክ ወልደ አምላክ፣ የባሕርይአምላክ፣ መሆኑን መስክሮ ክብርን አግኝቷል፡፡ የእምነታችንም መሠረቱ ይሔው ነው፡፡ ክርስቶስን ከአባቱ ጋር በመለኮቱ የሚተካከል ብለው ካላመኑ እንኩዋን ድኅነት ክርስትናም አይኖርም፡፡ ከጉባኤ ኒቅያ በሁዋላ ቅዱስ እለእስክንድሮስ በመልካሙ ጐዳና ሲጋደል ምዕመናንንም ሲያጸና ኑሯል፡፡ ዘወትር ወንጌልን በፍቅር ያነብ ነበርና ሲጸልይ የብርሃን ምሰሶ ይወርድለት ነበር፡፡ ስለ ውለታውም ቤተ ክርስቲያን በግብጽ ካበሩ 5ቱ ከዋክብት ሊቃውንት እንደ አንዱ ታከብረዋለች፡፡ ቅዱሱ ሊቅ በ328 ዓ.ም ዐርፎ በክብር ተቀብሯል፡፡


ገዳማዊያን በዓለም ላለነው ለኛና ለቅድስት ቤተክርስቲያን ለሀገራችንም ይጸልያሉ፡፡ ገዳማቸውን በመርዳት፣ በዓታቸውን በማጽናት ከበረከታቸው እንሳተፍ፡፡ 


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




የኬኒያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ለJesus Winner Ministry ለተሰኘ እምነት ተቋም የሰጠው 20 ሚሊዮን ሽልግ በናይሮቢ ተቋሞ አስነሳ።


የኮሪደር ልማት መብራቶችን የሰረቀው ተከሳሽ በ5 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ

#FastMereja I ወንጀሉ የተፈጸመው የካቲት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 8:00 ሠዓት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዋሬ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።

ተከሳሽ ሄኖክ መኮንን በኮሪደር ልማት ላይ የተገጠሙ መብራቶችን ቆርጦና ነቅሎ በመውሰድ ሊያመልጥ ሲል በወቅቱ ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር መዋሉን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

ተከሳሽ ላይም ተገቢው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች በማደራጀት ምርመራ ተጣርቶበት በአቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶበታል፤

የተከሳሽን መዝገብ የተከታተለው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የካ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ሄኖክ መኮንን ጥፋተኛ መሆኑን በማስረጃ በማረጋገጥ ተከሳሽን ያርማል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስተምራል በማለት በ5 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል።

Via: ብስራት ሬዲዮ

#ችሎት


ተወዳጇ ድምጻዊት ትዕግስት አፈወርቅ በሞት ባጣነው ወንድሟ ተወዳጁ ድምጻዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ስም 100 ሺህ ብር የለገሰች ሲሆን አንዲሁም በየአመቱ የድምጻዊውን ሙት አመት በማስመልከት 100 ሺህ ብር ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብታለች፡፡


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመቄዶንያ የአረጋውያን እና አዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል 30 ሚሊዮን ብር አበረከተ።

አቶ አቤ እንዳሉት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች እና ማኔጅመንት አባላት የተሰበሰበ 18 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ባንኩ 12 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በድምሩ 30 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአሁኑን ድጋፍ ሳይጨምር ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ለማዕከሉ 205 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉ ይታወቃል።


" ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል።" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ከሰሞኑ በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች ድምበር የሚያልፉ ግለሰቦችን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የፉሪ ክፍለ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ከኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር በመተባበር የተዘጋጀ የዳዕዋ መድረክ በርካታ ሙስሊሞች በተገኙበት መልዕክት ያስተላለፉት ኡስታዝ አቡበከር አህመድ "ከነፍሳችን በላይ አብልጠን በምንወዳቸው ውዱ ነብያችን ክብር የማንደራደር መሆኑን ሁሉም ሊያውቅ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።

"እኛ እምነታችን በምናስተምርበት ወቅት ፈፅሞ የሰዎች እምነት ላይ ድንበር አናልፍም እስልምናም ያንን አያዘንም ያሉ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ድንበር የሚያልፍ ግለሰቦችን ተው ሊሉ ይገባል" ብለዋል።

"እንደ ተቋም በህግ መሄድ እስካለብን ጥግ ድረስ እንሄዳለን ያሉ ሲሆን ሙስሊሙ ማህበረሰብ በተለይ ወጣቱ በሰላማዊ መንገድ እምነቱን ማስከበር አለበት" ሲሉ ገልፀዋል።

ዘገባው የሀሩን ሚዲያ ነው

6.3k 0 3 13 122

ለ4 አመታት በየሩብ አመቱ ጭማሬ አደርጋለሁ

#FastMereja I ዛሬ የወጣውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሚያዝያ ወር ጭማሪ ሊያደርግ ነው የሚለውን መረጃ ያስተባበለው ተቋሙ ከመስከረም 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ4 ተከታታይ አመታት በማኅበረሰቡ ላይ ጫና እንዳይፈጠር በየሩብ አመቱ ተከፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የታሪፍ ማስተካከያ ከማስፈፀም ውጪ አዲስ ተግባራዊ ያደረገው የታሪፍ ማሻሻያ አለመኖሩን ገልጿል።


ተወዳጁ ዘማሪ አቤል መክብብ ከዳናይት መክብብ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ምን ያዝናናሃል? ኳስ የማን ደጋፊ ነህ? ተብሎ ለቀረበለ

ተወዳጁ ዘማሪ አቤል መክብብ ከዳናይት መክብብ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ምን ያዝናናሃል? ኳስ የማን ደጋፊ ነህ? ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ የአርሰናል ደጋፊ እንደነበር እና አሁን አርሰናልን መደገፍ ሙሉ በሙሉ እንዳቆመ ኳስ ማየት እራሱ ማቆሙን አርሰናል ተሸነፈ፣ አሸነፈም ምንም እንደማይመስለው ተናግሯል።

https://youtu.be/jv0w3cP4ZX0?si=orgfkeLRej8i_8T7

#ሾውቢዝ #FastMereja


የኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያዝያ ወር ጀምሮ የፍጆታና የአገልግሎት ታሪፍ ጭማሪ ሊያደርግ ነው

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ የፍጆታ የአገልግሎት ታሪፍ ተመን ጭማሪ ሊያደርግ መሆኑ ታወቀ፡፡

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ በመኖሪያ ቤት ታሪፍ ላይ 0.50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ታሪፍ 0.60 ሳንቲም እንዲከፍሉ የሚደረግ ሲሆን፣ የአገልግሎት ክፍያ ተመንን በተመለከተ ለድኅረ ክፍያ አሥር ብር ከ95 ሳንቲም ሲከፍሉ፣ ለቅድመ ክፍያ አራት ብር ከ18 ሳንቲም እንደሚከፍሉ ሪፖርተር ያገኘው ሰነድ ያሳያል፡፡

የመኖሪያ ቤት ታሪፍን በተመለከተ ከ51 እስከ 100 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች አንድ ብር ከ49 ሳንቲም፣ ከ101 እስከ 200 ኪሎ ዋት ሁለት ብር ከ67 ሳንቲም፣ ከ201 እስከ 300 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች ሦስት ብር ከ84 ሳንቲም እንደሚከፍሉና በየኪሎ ዋቱ መጠን ክፍያው የሚለያይ እንደሆነ ሰነዱ ያስረዳል፡፡

የአገልግሎት ክፍያ ተመንም እንደ ኪሎ ዋቱ የሚለያይ እንደሆነና ለድኅረ ክፍያ ከፍተኛው 45 ብር ከ80 ሳንቲም ሲሆን፣ ለቅድመ ክፍያ 15 ብር 97 ሳንቲም እንደሆነ በነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን የወጣው ሰነድ ይጠቁማል፡፡

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን የኢነርጂ አቅርቦት ሥርጭት ሬጉሌሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ባህሩ ኦሊጅራ እንደገለጹት፣ በየሦስት ወራት በፍጆታና በአገልግሎት ታሪፍ ላይ ከሚያዝያ ወር ጀምሮ ጭማሪ ይደረጋል፡፡

የመኖሪያ ቤት፣ የንግድ፣ የአነስተኛ ኢንዱስትሪ፣ የመካከለኛ ኢንዱስትሪዎችና የመንገድ መብራቶች ላይ እንደ ኪሎ ዋቱ ልዩነት ጭማሪ የሚደረግ መሆኑን አክለው ገልጸዋል፡፡

ከጥር እስከ መጪው መጋቢት ወር ድረስ 0.50 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ የመኖሪያ ቤት ደንበኞች 0.52 ሳንቲም እንዲከፍሉ የተደረገ ሲሆን፣ የአገልግሎት ክፍያ ተመን ለድኅረ ክፍያ ደግሞ 10 ብር 71 ሳንቲም እንዲከፍሉ ሲደረግ፣ ለቅድመ ክፍያ ደግሞ 4 ብር 01 ሳንቲም እንዲከፍሉ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ የንግድ፣ የአነስተኛ ኢንዱስትሪ፣ የመካከለኛ ኢንዱስትሪዎችና የመንገድ መብራቶች በተቀመጠላቸው አኃዝ መሠረት እንዲከፍሉ እየተደረገ መሆኑን ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡

በተለይ ማኅበረሰቡ ላይ ጫና እንዳይፈጠር በየሦስት ወራት የፍጆታና የአገልግሎት ታሪፍ ተመን ጭማሪ እንዲደረግ ውሳኔ መተላለፉን፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሙዩኑኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ታዬ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ 

የኃይል ማመንጫ ዋጋ በመጨመሩ ብቻ የተጨመረው ታሪፍ (Cost Reflection Tariff) በአንድ ኪሎ ዋት ሰዓት ከአራት ዓመታት በኋላ 6.01 ብር እንደሚሆን ከዚህ በፊት መዘገባችን አይዘነጋም፡፡ 

ዘገባው የሪፖርተር ነው።




#ምኩራብ፣ የቤትህ ቅናት በላኝ

በቅድስት ቤተክርስቲያናችን የዐቢይ ጾም ሶስተኛ ሣምንት ምኩራብ ተብሎ ይጠራል፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምኩራብ የገባበትና ያስተማረበት ነው፡፡ ምኩራብ ማለትም ቀጥተኛ ፍቺው ኮረብታ፣ ተራራ የሚያህል ታላቅ ሕንጻ ማለት ነው። የዮሐንስ ወንጌል 2÷12-ፍጻሜው ይነበባል፡፡ “የአይሁድም የፋሲካቸው በዓል ቀርቦ ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን÷ ርግቦችንም የሚሸጡትን፣ ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፡፡ የገመድም ጅራፍ አበጀ፤ በጎችንና በሬዎችን፣ ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣ፤ የለዋጮችንም ገንዘብ በተነ፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡ ርግብ ሻጮችንም÷ “ይህን ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም÷ “የቤትህ ቅናት በላኝ” የሚል ቃል በመዝ. 68÷9 ተጽፎ እንዳለ ዐሰቡ፡፡”

ጌታችን ከጥምቀቱ በፊት ወደ ቤተመቅደስ የመጣባቸው በርካታ አጋጣሚዎች ቢኖሩም ሁለቱ ግን ተለይተው ይታወቃሉ፡፡ የመጀመሪያው ሉቃስ 2÷22-40 በሥርዓተ ኦሪት መሰረት በተወለደ በአርባኛው ቀን ወደ ቤተመቅደስ መምጣቱ፣  ሁለተኛ በሉቃ 2÷41-47 እንደምናገኘው ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው ከዮሴፍና ከእመቤታችን ጋር ለበዓል ወደ ኢየሩሳሌም በሄዱ ጊዜ ከእነርሱ ተለይቶ በቤተመቅደስ በመቅረት የኦሪት ሊቃውንትን ሲጠይቃቸውና ሲሰማቸው የነበረበት አጋጣሚ ናቸው፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ወደ ቤተ መቅደስ ሲመጣ አገልጋዮቹ በሥጋዊ ፍላጎታቸው ምክንያት በቤተመቅደሱ የማይገባ ሥራ እየሰሩ ቢያይም አምላክነቱን ገልጦ የሚያስተምርበት፣ የሚገስጽበት ጊዜ አልደረሰምና በዝምታ አልፏቸው ነበር፡፡

ከጥምቀቱ በኋላ ግን በሁለት አጋጣሚዎች ቤተ መቅደሱን አጽድቷል፡፡ ቀዳሚው በመጀመሪያው ፋሲካ አገልግሎቱን ሲጀምር ያደረገውና ከላይ በዮሐንስ ወንጌል የገለጽነው በምኩራብ ሣምንት የሚነበበው፣ የሚተረጎመው ነው፡፡ ጌታችን ለሁለተኛ ጊዜ ቤተመቅደሱን ሊያነፃ የሄደው ለመከራና ለሞት ተላልፎ ከመሰጠቱ አስቀድሞ በዕለተ ሆሳዕና፣ በማቴ 21÷12-17 የሚገኘው ነው፡፡ በዚህም ወቅት በተመሳሳይ ገዥዎችንና ለዋጮችን፣ እንዲሁም የቤተመቅደስ አለቆችን “ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፣ እናንተ ግን የሌቦችና የወንበዴዎች፣ ቀማኞች ዋሻ አደረጋችኋት” በማለት የገሰጸበት ነው፡፡ ስለሆነም ትንቢተ ነቢያትን የፈጸመ ጌታ በአገልግሎቱ መጀመሪያና ፍፃሜ ላይ ወደ ቤተመቅደስ የመጣው ቤተመቅደሱን ለማንፃት ነበር፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተመቅደስ ሲመጣ በቤተመቅደሱ እንስሳት የሚሸጡ የሚለውጡ ሰዎች እንደ ብሉይ ኪዳን ሥርዓት ለኃጢአት ማስተስረያ መስዋእትነት የሚቀርቡ ነበሩ፡፡ የካህናት አለቆችና ግብር አበሮቻቸውም በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እንስሳት ለመስዋእት ብቁ መሆናቸውን የሚያሳይ ማስረጃ በመስጠት በምትኩ ገንዘብ እየተቀበሉ አገልግሎቱ መልኩን ቀይሮ ንግድ ሆኖ ነበር፡፡ እንስሳቱን የሚሸጡት ሰዎችም ስለሚያገኙት ትርፍ እንጂ ስለ መስዋእቱ ንጽህና አይጠነቀቁም ነበር፤ ከጌታ የሚገኝ ሰማያዊ ጸጋን በመሸጥና በመለወጥ በሚያገኙት ትርፍ የቀየሩ ነበሩ፡፡

ታዲያ ወደ ቤተመቅደስ የመጣው ለፍርድ ሳይሆን ለማንፃት ነበርና ሻጮችና ለዋጮችን ሰዎች ሳይሆን የሚሸጡትንና የሚለወጡትን ርግቦችን፣ በጎችን፣ በሬዎችን፣ የሰዎቹን የሚለወጥ ገንዘብ ከቤተ መቅደስ አስወጣ፡፡ የቤተ መቅደሱ ባለቤት ዳግም ይመጣል፡፡ የሚመጣው ግን እንደቀደመው ለማንፃት ሳይሆን ለፍርድ ነውና በምግባር በሃይማኖት ጸንተን፣ በጸሎትና በምጽዋት ተግተን እንጠብቀው፡፡


ገዳማዊያን በዓለም ላለነው ለኛና ለቅድስት ቤተክርስቲያን ለሀገራችንም ይጸልያሉ፡፡ ገዳማቸውን በመርዳት፣ በዓታቸውን በማጽናት ከበረከታቸው እንሳተፍ፡፡ 


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




ኢትዮጵያ መረጃ ለመሰብሰብ፣ ለመከላከል አቅም እንዲሁም ለማጥቃት የሚውሉ ድሮኖችን ማምረት መጀመሯ ምን ተሰማችሁ?


ቢክ እስኪብርቶ በኢትዮጵያ ውስጥ ሊመረት ነው።

#FastMereja I ቢክ እስኪብርቶ በኢትዮጲያ ከንጉሱ ጊዜ ጀምሮ በዋናነት አገልግሎት ላይ ውሎ የነበረ ሲሆን አልሳም ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበርም ከሃያ አመታት በፊት ጀምሮ ቢክ እስኪብርቶን በብቸኛ አስመጪነትና አከፋፋይነት በኢትዮጲያ ውስጥ ለገበያ ሲያቀርብ ቆይቷል፡፡

ምርቱንም ያስመጣ የነበረው ከኬንያ አገር ለረዢም ጊዜ ሃኮ ኢንደስትሪስ ከሚባል ኩባንያ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ከቢክ ኢስት አፍሪካ ሊሚትድ ከሚባለው ተቋም እንደሆነ ተገልጻል።

አልሳም ቢክ እስኪብሮቶን በኢትዮጵያ ውስጥ ለማምረት ዛሬ የካቲት 29/2017 ዓም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል ከኢስት አፍሪካ ሊሚትድ ጋር የአጋርነት ስምምነት አድርጓል።

አልሳም ከማምረቱ በተጨማሪ የምርቱ ስርጭትም ለምስራቅ አፍሪካ አገሮች ኢትዮጲያን ጨምሮ ለጅቡቲ፣ ለሶማሊያና ለኤርትራ የሚያከፋፍል ይሆናል።

የቢክ እስክብርቶ በኢትዮጲያ መመረት በአከባቢው ካለው የገበያ ስፋት አንፃር ለአገራችን የቴክኖሎጂ ሽግግር ይፈጥራል፣ የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል፣ ለዜጎች የሥራ እድል ይፈጥራል ተብሏል።

በቀጣይ በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ፕሮጀክቱን ተግባራዊ እንደሚሆን ነው የተገለጸው።

አልሳም ኃላ/የተ/የግል ማህበር ከተመሰረተ 25 ዓመታት ያለፉት ሲሆን በአስመጪነት፣ በላኪነት፣ በአገር ውስጥ ንግድ፣ በሪል እስቴትና በማኑፋክቸሪንግ የሥራ ዘርፎች ተሰማርቶ ይገኛል።

#ቢዝነስ


# በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን...


በ4ኛው መቶ  ክ/ዘመን የነበሩት ጻድቃን እንድራኒቆስና ሚስቱ አትናስያ በዘመናቸው ከልጅነት ጀምረው ቃለ እግዚአብሔርን የሚሰሙ ለወላጆቻቸው የሚታዘዙ ነበሩ፡፡

ዘመኑ ደርሶ በሚገባው የተክሊል ሥርዓት ጋብቻቸውን ፈጽመው 40 ቀን ከተጠናቀቀ በኋላ ከምንም ነገር በፊት 2ቱ ቁጭ ብለው ተወያዩ፡፡ የውይይታቸው ርዕስ ደግሞ "ፈጣሪያችን በምን እናስደስተው" የሚል ነበር፡፡ በመጨረሻም ሁልጊዜም እንግዳ በመቀበል፣ ነዳያን በቤታቸው በማስተናገድ፣ ጸሎት፣ ጾምና ስግደት ሳያቋርጡና ለሩካቤ ስጋ ሳይቻኮሉ ለመኖር ተስማሙ፡፡ መልካም ነገር አስበዋልና አምላክ የሰጣቸውን ሃብት ሲመጸውቱ ኖሩ፡፡ ከዘመናት የቅድስና ጉዞ በሁዋላ በፈቃደ እግዚአብሔር 2 ልጆች አከታትለው ወለዱ፡፡ ወንዱን ዮሐንስ ሴቷን ደግሞ ማርያም አሏቸው::


ልጆች ከወለዱ በኋላ ይህንን ላደረገላቸው ጌታ ክብር አልጋ ለመለየት ሌላ ወስነው ለ12 ዓመታት በጾምና በጸሎት ኖሩ፡፡ ልጆቻቸው ዮሐንስና ማርያም በቅንነት አድገው እድሜአቸው 12 ሲሆን 2ቱም በአንድ ቀን ታመው ሞቱ፡፡ እንድራኒቆስና ሚስቱ አትናስያ ታቅፈው ወስደው ቀበሯቸው:: ይህ እጅግ አሰቃቂ ፈተና እንድራኒቆስ ከቀብር በሁዋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ምርር ብሎ እንዲያለቅስ ቢያደርገውም “አምላከ ኢዮብ! አንተ ሰጠኸኝ፣ አንተም ነሳኸኝ፤ ስምህ ለዘለዓለም ይባረክ" ብሎ ሔደ፡፡ አትናስያ ግን ከሐዘኗ ብዛት የልጆቿ መቃብር ላይ ተደፍታ ስታለቅስ ቅዱስ መልአክ ልቡናዋን ወደ ሰማይ አሳረገው፡፡ ልጆቿ ዮሐንስና ማርያም በገነት ውስጥ ከቅዱሳን ጋር ሐሴትን ሲያደርጉም ተመለከተች፡፡ ወዲያው ወደ ቤቷ ተመልሳ ለባሏ እንድራኒቆስ ያየችውን ነገረችውና ተደሰቱ፡፡


ለዚህ የእግዚአብሔር ውለታም በምናኔ ሊኖሩ ተስማሙ፡፡ እጅግ ሃብታሞች ነበሩና ያላቸውን ሁሉ ለነዳያን አካፍለው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሔደው እርሷ ከሴቶች፣ እርሱ ደግሞ ከወንዶቹ ገዳም ገቡ፡፡ ለ12 ዓመታት በፍጹም ተጋድሎ ለፈጣሪያቸው ተገዙ፡፡ በእነዚህ ዘመናት አንዳቸው ስለ ሌላው ሰምተው ባያውቁም በጸሎት ግን ያለማቁዋረጥ ይተሣሠቡ ነበር፡፡ ከ12 ዓመታት በሁዋላ የፍቅር አምላክ በልቡና ተመሳሳይ ሐሳብን አመጣ፡፡ እርሱ ከአበ ምኔቱ ታላቁ_አባ_ዳንኤል እርሷም ከእመ ምኔቷ አስፈቅደው ከኢየሩሳሌም ከቅዱሳት መካናት ለመባረክ ጉዞ ጀመሩ፡፡ በጉዞ ላይ ሲተያዩ እርሷ ለየችው፡፡ እርሱ ግን በጥበበ እግዚአብሔር አካሏ በገድል ከመለወጡ ባሻገር የለበሰችው እንደ ወንድ መነኮሳት ለብሳ ነበርና ሊለያት አልቻለም፡፡


2ቱም እየተጫወቱ፣ እየጸለዩ በሰላም ተባርከው ወደ ግብጽ እስኪመለሱ ቅድስት አትናስያን የለያት አልነበረም፡፡ ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሲደርሱ ግን አባ ዳንኤል በጸጋ እግዚአብሔር ባልና ሚስት መሆናቸውን አውቆ “ለምን አብራችሁ አትኖሩም?” አላቸው፡፡ በደስታ ተቀብለውት እርሷ እያወቀችው እርሱ ሳያውቃት ለ12 ዓመታት አብረው በቅድስና ኖሩ፡፡ ከእነዚህ ዘመናት በሁዋላ ግን ሐምሌ 28 ቀን ቅድስት አትናስያ ታመመችና አባ ዳንኤል ሥጋውን ደሙን አቀብሏት ዐረፈች፡፡ ሊገንዟት ሲቀርቡ ቅዱስ እንድራኒቆስ ሚስቱን አወቃት፡፡ በአንድ ጊዜ ሚስቱንና የሚወደውን ባልንጀራ በማጣቱ አለቀሰ፡፡ ከቀብር መልስ "ጌታ ሆይ! ውሰደኝ?" ብሎ ጸልዮ እርሱም ተከትሏት ዐረፈ:: አባ ዳንኤል እርሱንም ቀብሮ ዜና ቅድስናቸውን ጻፈ፡፡


የቅዱሳን በረከት እንዲያድርብን ገዳማትን እንርዳ፡፡ 


ገዳማዊያን በዓለም ላለነው ለኛና ለቅድስት ቤተክርስቲያን ለሀገራችንም ይጸልያሉ፡፡ ገዳማቸውን በመርዳት፣ በዓታቸውን በማጽናት ከበረከታቸው እንሳተፍ፡፡ 


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

20 last posts shown.