FastMereja.com


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic



Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ሸገር ከተማ አስተዳደር የመንግስት መስሪያ ቤቶች እስከ ምሽቱ 4:00 ሰዓት መስራት ጀመሩ
#FastMereja
በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ የምትገኘው ሸገር ከተማ ህብረተሰቡን ለማገልገል የመንግስት መስሪያ ቤቶች እስከ ምሽት አራት ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ መወሰኑን ፋስት መረጃ ሰምቷል። ከሚያዝያ 10/2016 ዓም ጀምሮ በሸገር ከተማ በአስራ ሁለቱም ክፍለ ከተማ ከጠዋት እስከ ምሽት 4:00 ሰዓት አገልግሎት እንሰጣለን ተብሏል። ቅዳሜ ሙሉ ቀን የስራ ቀን ሆኖ ተወስኗል።

አስተያየት ሰጪዎች እስከ ምሽት አራት ሰዓት መደረጉን ውሳኔውን ደግፈው ግን ቀን በአግባቡ ቢሰራ ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል ጠቁሟል።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


ወንድማችን ታሞ ነው በማለት ሃሰተኛ የህክምና ማስረጃ አሰርተው በመኪና ሲለምኑ የነበሩት ተያዙ
#FastMereja
ወንድማችን በከፍተኛ ህመም ታመዋል በሚል ማጨበርበር ወንጀል የተሰማሩ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ በወላይታ ሶዶ ከተማ በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

በወላይታ ሶዶ እና በተለያዩ ወረዳዎች በመዘዋወር በህመም ስም ማጨበርበር ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩ ግለሰቦች በህብረተሰቡ ጥቆማ በወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊሰ በቁጥጥር ውሏል።

በማጨበርበር ወንጀሉ የተሰማሩት ግለሰቦች ከተለያዩ አከባቢዎች በመምጣት መኪና በመከራየት ሀሰተኛ የህመም ማስረጃ በማዘጋጀት ወንድማችን በደረሰበት ህመም በሚል በማጨበርበር ወንጀል መሰማራታቸው ተገልጿል።

በዚህ የማጨበርበር ወንጀል የተሰማሩት ግለሰቦች በዚህ እኩይ ተግባራቸው ምክንያት ከአሰራ ዘጠኝ ሺህ ብር በላይ ከህብረተሰቡ በማጨበርበር መሰብሰባቸው ነው ፋስት መረጃ ከከተማው ፖሊስ ያገኘው መረጃ የሚያመለክተው።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


የአንድ አመት ልጁን ከእነ ህይወቷ ለመቅበር የሞከረው ወላጅ አባት በቁጥጥር ስር ዋለ።
#FastMereja
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቤንች ሸኮ ዞን የሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፒክተር አለማየሁ አማረ ለክልሉ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን እንደገለፁት በወረዳው ኮሶል ቀጭን መንደር ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረው ፀብ ምክንያት የወንጀል ድርጊቱን ለመፈፀም ሙከራ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡

አዛዡ አክለውም በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረ ጊዜያዊ ፀብ እናት የአንድ ዓመት ሴት ህፃን ልጅ ጥላ በመጥፋቷ ወላጅ አባት ቲቲዮስ ኪያግላስ የተባለው ተጠርጣሪ የአንድ ዓመት ህፃን ልጁ እያለቀሰች ስታስቸግረዉ በሁኔታው ተበሳጭቶ የአንድ አመት ልጁን በህይወት ለመቅበር ጉድጓድ ሲያዘጋጅ የተመለከቱ የአከባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ይሰጣሉ፡፡

ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪውን ጉድጓድ እየቆፈረ እያለ በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ህፃኗን ጉዳት ሳይደርስባት መታደግ መቻሉንና በተጠርጣሪው ላይ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

ፖሊስ የህፃኗን ወላጅ እናቷን እያፈላለገ ሲሆን ህፃኗ በአሁን ሰዓት ሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊስ እንክብካቤ እያደረገላት እንደሚገኝ የገለፀት ፖሊስ አዛዡ በቤተሰብ መካካል አለመግባባቶች በሚፈጠሩበት ወቅት ችግሩን በመነጋገር መፍታት ይገባል ሲሉ ፖሊስ አዛዡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል ፋስት መረጃ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን መረጃ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


በአሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን (የኦሮሞ እና የትግራይና ማኅበረሰብ) አባላት ጦርነት እንዲቆም የሚጠይቅ ሰልፍ አካሄዱ
#FastMereja
ዋሺንግተን ዲሲ አካባቢ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ አባላት፣ የኦነግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት የአቶ በቴ ዑርጌሳ ግድያን የሚቃወም ሰልፍ እና የሻማ ማብራት ሥነሥርዐት አከናወኑ። ኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮሞ ተወላጆች ላይ ይደርሳል ያሉትን ግድያ ተቃውመው ጦርነት እንዲቆም ጠይቀዋል። በሌላ በኩል በዚሁ አካባቢ ሰልፍ ያደረጉት ትውልደ ኢትዮጵያ የትግራይ ተወላጆች፣ ጦርነት እንዲቆም፣ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር እና ተገቢው ርዳታ ወደ ክልሉ እንዲገባ የሚጠይቅ ሰልፍ አካሂደዋል ሲል የአሜሪካ ድምፅ ዘገባ ያመላክታል።


ተማሪዋን በመጥለፍ አስገድዶ የደፈረው በ10 አመት እስራት ተቀጣ!!
#FastMereja
ከትምህርት ቤት እየተመለሰች የነበረችውን ተማሪ በመጥለፍ አስገድዶ የደፈረው በ10 ከ9 ወር አመት እስራት ተቀጣ! በቄለም ወለጋ ዳሌ ሰዲ ወረዳ አለማየሁ ታረቀኝ የተባለ ተከሳሽ ከትምህርት ቤት እየተመለሰች ያለች ተማሪን አገባሻለሁ በማለት በጉልበት ይዟት ከሄደ በኋላ አስገድዶ ደፍሯታል።

የወንጀል ድርጊቱ በፖሊስ ተመርምሮ በወረዳው አቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት ቀርቦ ፍርድ ቤቱ በ10 አመት ከዘጠኝ ወር እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ለፋስት መረጃ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደ
#FastMereja
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ፡፡

የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ በአካል ቀርበው ሀሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመያዝ ለ3 ግለሰቦች እና ለአንድ የግል ድርጅት ሒሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ በአፍሪካ ህብረት ሴኪዩሪቲዎች ተይዘው ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ተላልፈው መሰጠታቸውን ጠቅሶ የጥርጣሬ መነሻውን ለችሎቱ አቅርቧል።

በዚህ መነሻ መሰረትም መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ሥራ ለማከናወን የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

ተጠርጣሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ድርጊቱ መፈጸሙን አምነው፤ ይሁን እንጂ ወንጀል አለመፈጸማቸውን አስረድተዋል፡፡

ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።

ዘገባው የፋና ነው።


የውጭ ባለሀብቶች በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቀደ
#FastMereja
ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ ተደረገ፡፡

በዚህም መሰረት የውጭ ባለሀብቶች በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላከ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጉዳዩ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫው ላይ እንደተገለፀው፤ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሟሉ የውጭ ባለሃብቶች ከማዳበሪያ እና ነዳጅ በስተቀር በሁሉም የገቢ ንግድ ኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ፡፡

የጅምላ ንግድን በተመለከተ ከማዳበሪያ ጅምላ ንግድ በስተቀር በሁሉም አይነት የጅምላ ንግድ መስኮች መሰማራት ይችላል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች ቅድመ ሁኔታዎችን ሲያሟሉ ለአገር ውስጥ ባለሃብት በተከለሉ ሁሉም የችርቻሮ ንግድ ስራዎች መሳተፍ እንዲችሉ መፈቀዱም ተጠቅሷል።

በጉዳዩ ላይ በባለድርሻ አካላት የተካሄዱ ዝርዝር ጥናቶች ላይ በመመርኮዝ መሠረታዊ የፖሊሲ ለውጥ ያደረገው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድም አዲስ የአፈፃፀም መመሪያ አፅድቋል።

ዘገባው የኢቢሲ ነው።


የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ የነበሩት የረ/ፕ ጸጋዬ ቱኬ ባለቤትና ቤተሰቦቹ የተፋጠነ ፍትህ አጣን አሉ።
#FastMereja
ሐዋሳ ከተማን ለሶስት አመታት በከንቲባነት ሲመሩ የነበሩት ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ቢቆዩም ላለፉት 6 ወራት ህክምና ተከልክለው በፍርድ ቤት ጊዜ ቀጠሮ ብቻ እየተመላለሱ በፍትህ እጦት እየተሰቃዩ እንደሆነ ቤተሰቦቹ ተናገሩ።

እዉነት እንድትወጣ የምትሹ ኢትዮጲያዊያን በሙሉ ፍትህ እንዲያገኝ ድምጽ ሁኑን ሲሉ ቤተሰቦቹ ጠይቀዋል።

ሰኞ ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም የነበረውም ቀጠሮ ለ15 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ፍርድ ቤቱ ሰጥቷል።


በሸገር ከተማ አስተዳደር በከባድ የማታለል ወንጀል ሲፈለግ የነበረውን ግለሰብ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ተጠርጣሪዉ በሸገር ከተማ አስተዳደር በመልካ ኖኖ ክፍለ ከተማ በተለያዬ አራት ሀሰተኛ ስሞችን በመጠቀም በ15 ግለሰቦች ላይ በከባድ የማታለል ወንጀሎች በመፈፀም ክስ ተመስርቶበት በፖሊስ ሲፈለግ መቆየቱን ፖሊስ ኮሚሽኑ ገልጿል።

የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ተጠርጣሪውን በተገኘበት እንዲያዝ ከፍርድ ቤት መያዣ ጋር በመላካቸው  የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መረጃ ኢንተለጀንስ እና የወንጀል ምርመራ ክትትል አባላት አሰማርቶ ግለሰቡን በመከታተል በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን  አመልክቷል፡፡

ማንም ሰው ወንጀል ፈፅሞ ለጥቂት ጊዜያት ሊደበቅ ይችል ይሆናል እንጂ ፈፅሞ ከህግ ሊያመልጥ እንደማይችል የግለሰቡ በቁጥጥር ስር መዋል ማሳያ ነው ያለው ፖሊስ ኮሚሽኑ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ሲውል ፤የቤት ፕላን፤የተለያዬ የባንክ ደብተሮች፤አንድ ላፕቶፕ፣የመኪና ቁልፍ እና የእጅ ስልኩ መያዙን ነው ፖሊስ ያመለከተው፡፡

በአንድ ክልል ወንጀል ፈፅሞ ሌላኛው ክልል በመሄድ መደበቅ እንደማይቻል እና ወንጀልን ለመከላከል ሁለቱ ክልሎች በጋራ ተቀናጅተው እየሰሩ መሆኑን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡ተጠርጣሪዉን ለሸገር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስረክቧል፡፡

በመጨረሻም በክትትል ሂደቱ መረጃ እና ጥቆማ በመስጠትና ድጋፍ ላደረጋችሁ የህብረተሰብ ክፍሎች እና የፖሊስ አባላት ምስጋናችንን እያቀረብን በቀጣይም ወንጀልን በጋራ መከላከል የሁሉም ኃላፊነትና ግዴታ በመሆኑ ህዝቡ ከፖሊስ ጎን እንዲቆም ኮሚሽኑ ጥሪውን አቅርቧል።

ዘገባዉ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ነዉ።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja




«ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ህወሓት ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል» ሲል የአማራ ክልል መግለጫ ሰጠ
#FastMereja

ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል፡፡

ጀንበር ጠልቃ በወጣች ቁጥር ከጦርነት ውጭ ማሰብ የማይችለው የህወሓት ቡድን ከዉጭ እና ከዉስጥ ጠላቶቻችን ጋር ተናቦና ተቀናጅቶ በእርካሽ ፖለቲካዊ ብያኔና ፍረጃ በጊዜያዊ አሥተዳደሩ ካቢኔ አማካኝነት መጋቢት 16/2016 ዓ.ም የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት ማወጁና መቀስቀሱ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ ይህን የመላ ኢትዮጵያ ጠላትና የደኅንነት ስጋት የሆነውን የህወሓት ቡድን ባለፉት ሦስት ዙሮች ከተደረገው ደም አፋሳሽ ጦርነት ትምህርት ሊወስድ ይችል ይሆናል በሚል ጭላንጭል ተስፋ የፌዴራል መንግሥት እጅግ እልህ አስጨራሽ ትዕግስት ተላብሶ ውይይቶች እንዲካሄዱ ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደረግ ቆይቷል፡፡

የአማራ ክልል መንግሥትም በተደጋጋሚ ከትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር ጋር በፌዴራል መንግሥት አማካኝነት ውይይት ለማድረግ በርካታ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም ህወሓት ይህን የሰላም አማራጭ ወደ ጎን በመተው የማንነት ጥያቄ ያለባቸውን የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ አካባቢዎች ላይ ወረራ ፈፅሟል፡፡

ህወሓት ወረራ የፈፀመባቸው የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት አካባቢዎች የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመፅደቁ በፊት በነበሩ አሥተዳደራዊ መዋቅርና አደረጃጀት በኀይል ጠቅልሎ ከመውሰድ ጀምሮ የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከመፈፀም ድረስ አሰቃቂ ጥፋት የፈፀመባቸው አካባቢዎች ናቸው፡፡ እነዚህ አካባቢዎች ስቃይ በተሞላበት ችግር ውስጥም ሆነው በወቅቱ ለነበረው መንግሥት የማንነትና ራስን በራስ የማሥተዳደር ጥያቄዎችን በማንሳት፣ መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ መሆኑ በበርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች የተረጋገጥ ጉዳይ ነው፡፡

ተቸንካሪነት ዋና መለያ የሆነው የህወሓት የጥፋት ቡድን ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የፈፀመውን አሰቃቂና ታሪክ ምንጊዜም የማይዘነጋው የባንዳነት ተግባር ተከትሎ በተቀሰቀሰው ጦርነት በመላ ኢትዮጵያዊያን እና በጀግኖች የፀጥታ ኀይሎች አማካኝነት የሽንፈት ፅዋን ከመጎንጨቱ ባሻገር የማንነትና የራስ አሥተዳደር ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች በጉልበት ተገፎባቸው የነበረውን ራሳቸውን የማሥተዳደር ነጻነት መቀዳጀት ችለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ይህ ሁኔታ ያልተመቸው ተቸንካሪው የህወሓት ቡድን በሦስት ዙሮች ከተደረገው ጦርነት ማግሥት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በማክበር በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የድርሻውን ከመወጣት ይልቅ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የተለያዩ ጥፋቶችን ሲፈጽም ቆይቷል፡፡አሁንም እየፈጸመ ይገኛል፡፡

ስለሆነም የአማራ ክልል መንግሥት ይህን መሰሉን የህወሓትና የግብረ አበሮቹን ፖለቲካዊ ግልሙትና እና ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀብና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በማክበር በአጭር ጊዜ በወረራ የያዛቸውን አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ እየጠየቅን ይህ የማይሆን ከሆነ የአማራ ክልል መንግሥትና ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ በመሆን ሀገርን ከማፍረስ መታደግና ሕዝባችንንም ከጥቃት ለመከላከል የምንገደድ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

የተከበራችሁ በክልላችን በየደረጃው ያላችሁ የፖለቲካና የጸጥታ መዋቅር አባላት፡- ከሰሜን ዕዝ ጥቃት በኋላ ትህነግ በቀሰቀሰው ጦርነት ሕዝባችን ቀጥተኛ ተጠቂ በመሆኑ ምክንያት ለበርካታ ችግሮች ተዳርጎ የነበረ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን በየደረጃው የሚገኙ የመዋቅር አባላት ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ጥምር የጸጥታ ኃይሎችና ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመሆን ሀገር አፍራሽ የጥፋት ኀይሉ ላይ የተቀዳጀው ድል ታሪክ አይዘነጋውም፡፡ ዛሬም እንደ ትናንንቱ በፅናትና በቁርጠኝነት ሕዝቡን በማደራጀት አካባቢያችሁን በመጠበቅ ታሪካዊ ኀላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

የተከበርከው የክልላችን ሕዝብ፡- በተደጋጋሚ ጥቃት የፈፀመብህ የጥፋት ኀይል ዛሬም እንደ ትናንቱ ወረራ ፈፅሟል፡፡ በመሆኑም መላ የክልላችን ሕዝብ ከሀሰት ፕሮፓጋንዳ እና ሠርጎ ገቦች ራስህን በመጠበቅ ከክልል መንግሥትና በየአካባቢው ከሚገኙ አሥተዳደሮች ጋር የጠበቀ ቁርኝት በመፍጠር ጠላቶቻችን የከፈቱብንን ጥቃት ለመመከት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከመንግሥት ጎን በመሰለፍ የድርሻህን እንድትወጣ የከበረ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት፡- የፌደራል መንግሥት ህወሓት የቀሰቀሰው ደም አፋሳሽ ጦርነት በሰላም እንዲቋጭ ማድረጉን ሳናደንቅ አናልፍም፡፡ ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተደረገውን ጥረት በሙሉ ልብ በመደገፍ ለውጤታማነቱ የድርሻችንን ስንወጣ ቆይተናል፡፡ ሆኖም ግን ህወሓት በተደጋጋሚ የተሰጠውን ዕድል ባለመጠቀም የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሲያፈርስ ቆይቷል፡፡ አሁንም በሙሉ አቅሙ ወደ ጦርነት ገብቷል፡፡ ይህን እኩይ ድርጊቱን የአፍሪካ ሕብረትና የዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በቦታው ተገኝተው አረጋግጠዋል፡፡በመሆኑም ይህን እብሪተኛ ቡድን በአጭር ጊዜ ከወረራቸው አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ በማድረግ ሕዝባችንን ከጥፋት መታደግና የሀገራችንን ሉዓላዊነት ማስከበር ይገባል፡፡

ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ
ህወሓት ከምስረታዉ ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ባለው ሥር የሰደደ ጥላቻ ምክንያት በአማራ ሕዝብና በመላ ሀገሪቱ ሕዝብ ላይ የማያባራ ደም አፋሳሽ ጦርነትን ሲቀሰቅስ ኖሯል፡፡ ለዚህም ነው ህወሓት የኢትዮጵያም ሆነ የአፍሪካ ቀንድ አለመረጋት ምንጭ ነው የምንለው፡፡

ሆኖም በአሳሳች የፕሮፖጋንዳ ሥራዎቹ ምክንያት የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተደጋጋሚ በህወሓት ጉዳይ ላይ የተሳሳተ አቋም ሲይዝ ተስተውሏል፡፡ ዛሬ ግን ለዚህ አሳሳች ፕሮፖጋንዳው ያልተመቼ ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ በጠራራ ጸሐይ የአፍሪካ ሕብረትና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በተገኙበት ወቅት ወረራ መፈጸሙ በገሃድ ታይቷል፡፡

በመሆኑም ከዚህ ቀደም እንዳደረገው በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ማወናበድ አይችልም፡፡ የአማራ ክልል መንግሥትና ሕዝብ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ህወሓት የፈጸመብንን ወረራ በጥብቅ እንዲያወግዝና ከጎናችን እንዲቆም የከበረ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
ሚያዚያ 08 /2016 ዓ‹ም
ባሕር ዳር


አላማጣ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆኗን የከተማዋ ከንቲባ ተናገሩ

ካለፈው ሳምንት ቅዳሜ ጀምሮ የተኩስ ልውውጥ ሲካሄድባቸው በነበሩ የራያ አላማጣ አካባቢዎች አቅራቢያ የምትገኘው አላማጣ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆኗን የከተማዋ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ ለቢቢሲ ተናገሩ።

የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው መገደላቸውን እና ሌሎች የወረዳው እና የከተማዋ ኃላፊዎች አካባቢውን ለቅቀው ወደ ሌሎች የራያ ወረዳዎች መሄዳቸውንም ገልፀዋል።

ካለፈው ሳምንት መጨረሻ አንስቶ በራያ አላማጣ ወረዳ የተለያዩ አካባቢዎች ለተከታታይ ቀናት በተካሄደው የተኩስ ልውውጥ ስጋት ውስጥ ገብታ የነበረችው አላማጣ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የሆነችው ከትላንት ሰኞ ሚያዝያ 7/2016 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን የከተማዋ ከንቲባ ተናግረዋል።

የራያ አላማጣ ባለሥልጣናት ለተኩስ ልውውጡ ምክንያት የሚያደርጉት በትግራይ ኃይሎች “ተከፍቷል” ያሉትን ጥቃት ሲሆን፣ የትግራይ ክልል ደቡብ ትግራይ ዞን ደግሞ የወረዳ አስተዳደሩ ታጣቂዎች ተኩስ መክፈታቸውን በመጥቀስ ሌላውን አካል ተጠያቂ ያደርጋል።

ለቀናት በቀጠለው ግጭት ውስጥ የትግራይ ኃይሎች “ክፍለ ጦሮችን ማሰለፋቸውን” የሚናገሩት የራያ አላማጣ ወረዳ ባለሥልጣናት፤ ታጣቂዎቹ ሌሎች የወረዳውን አካባቢዎች መቆጣጠራቸውን እና ወደ አላማጣ ከተማ እየተጠጉ መሆኑን ሰኞ ለቢቢሲ ተናግረው ነበር።

ቢቢሲ በዛሬው ዕለት ያነጋገራቸው ሁለት የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ከሰኞ ከሰዓት ጀምሮ በርካታ ነዋሪዎች ወረዳውን እና ከተማውን ለቀው በመውጣት ወደ አጎራባች አካባቢዎች መሸሻቸውን ተናግረዋል። ነዋሪዎች “ሸሽተውባቸዋል” ከተባሉ አጎራባች አካባቢዎች አንዱ ቆቦ ከተማ ሲሆን፣ አንድ የቆቦ ከተማ ኃላፊ ከትናትን ጀምሮ በርካታ ወደ ከተማዋ እየገቡ መሆኑን ገልፀዋል።

የራያ አላማጣ ወረዳ እና የአላማጣ ከተማ አስተዳደር ኃላፊዎችም ከሰኞ ጀምሮ አካባቢውን ለቅቀው መውጣታቸውን በአሁኑ ሰዓት ቆቦ እንደሚገኙ የገለፁት የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ ተናግረዋል። ከትናንት ጀምሮ አላማጣ ከተማን እየተቆጣጠሩ ያሉት የመከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ አባላት መሆናቸውን ከንቲባው አስታውቀዋል።

“[አላማጣ] ከተማው መከላከያ እና ፌደራል ፖሊስ ነው ያለው። ዙሪያው የተያዘው ግን በትግራይ ታጣቂዎች ነው” ያሉት አቶ ኃይሉ፤ በከተማዋ “ውስጥ ለውስጥ የትግራይ ታጣቂዎች” አሉ ሲሉ ከስሰዋል።

“ቦታውን ከተቆጣጠሩት እዚያ እየሠራን ነው ማለት አይደለም” ያሉት አቶ ኃይሉ፤ የራያ አላማጣ አካባቢዎች በአማራ ክልል ስር ከሆነ በኋላ በተመሠረው የመንግሥት መዋቅር ውስጥ የነበሩት ኃላፊዎች በአሁኑ ሰዓት ከተማውን እያስተዳደሩ አለመሆኑን ገልፀዋል።

የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ሞላ ደርበው እና ለሌች ቁጥራቸውን ያልገለጿቸው ሰዎች በትናንትናው ዕለት መገደላቸውን ከንቲባው ተናግረዋል። የአቶ ሞላ ህልፈት ምክንያት ከትግራይ ኃይሎች ጋር በተደረገ “ውጊያ” አለመሆኑን ጠቅሰዋል።

“[አቶ ሞላ ሕይወታቸው ያለፈው] ከህወሓት ጋር በተያያዘ አይደለም። ሕግ የያዘው ነገር ስለሆነ ተጣርቶ የሆነ ነገር እስከሚባል ድረስ ዝርዝሩን [አልገልፅም]” ሲሉ ምክንያቱን ከመናገር ተቆጥበዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ትናንት ምሽት በማኅበራዊ ትስስር ገፆቻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፤ “በደቡባዊ ትግራይ እና ሌሎች የተያዙ የትግራይ ግዛቶች” ያለው ሁኔታ በፌደራል መንግሥት እና በጊዜያዊ አስተዳደሩ እንዲሁም የትግራይ እና የአማራ ክልል የተፈጠረ ግጭት እንዳልሆነ ገልፀዋል።

በአካባቢዎቹ የሚታየው ሁኔታ የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዲተገበር የማይፈልጉ “የስምምነቱ ጠላቶች ሥራ” መሆኑን በመልዕክታቸው አስፍረዋል። “ፀረ ፕሪቶሪያ” ስምምነት የሆኑ “ቅርብ እና ሩቅ የሚገኙ” አካላት “የጦርነት ቅስቀሳ” ቢኖርም ብቸኛው መንገድ “ሰላም” እና “ንግግር” መሆኑን አቶ ጌታቸው ጠቅሰዋል።

አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በበኩሉ ትናንት ባወጣው መግለጫ ህወሓት በራያ በኩል “ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት” በመክፈት “አራተኛ ዙር ወረራ ፈጽሟል” ሲል ከስሷል። አብን በመግለጫው፤ “ፌዴራሉ መንግሥት እና የአማራ ክልል መንግሥት በሕዝባችን ላይ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን” ብሏል። “በሁሉም አካባቢዎች” የሚገኘው የአማራ ሕዝብ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት ጥቃቱን እንዲመክት ጥሪ አቅርቧል።

ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያሏት የሚሊየነሮች ቁጥር በአጠቃላይ 2,700 መድረሱን በዘርፉ ላይ የተደረገ አንድ ሪፖርት አመላከተ

ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ ወደ 2,700 የሚጠጉ ሚሊየነሮች እንዳሏት የገለፀዉ ይህ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ሀገሪቷ በዚህ የስነ ህዝብ እድገት ዉስጥ ጠንካራ እንድገት እንደሚኖረዉ ትንበያውን አስቀምጧል።

በ 2024 የወጣዉ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ዘጠኛ እትሙ ላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አዳዲስ ገበያዎችን የሚይዘው የአህጉሪቱ ሚሊየነር ህዝቧ በሚቀጥሉት አስርት አመታት ዉስጥ በ 65% ከፍ ሊል እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል ።

አሁን ላይ በአፍሪካ ያለዉ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ሀብት 2.5 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱ የተነገረ ሲሆን ኢትዮጵያ በዚህ ኢኮኖሚ እድገት ዉስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጓ ነዉ ይህ ሀተታ የሚያመላክተዉ።

ዘገባው የካፒታል ነው።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


በኢትዮጵያ 56 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ምንም አይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ አንድ ጥናት አመላከተ

የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ አደረጉት ባለዉ ዓመታዊ ጥናቱ ላይ እንደገለፀው በኢትዮጵያ 56 በመቶ የሚሆኑ የ 2ኛ እና የ 3ኛ ክፍል ተማሪዎች ምንም አይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ አረጋግጫለሁ ብሏል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሲያከናዉን የቆየዉን ጥናት ይፋ አድርጓል ። በዚህም ከትግራይ ክልል በስተቀር በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ 401 ትምህርት ቤቶች እና በ 16 ሺህ ተማሪዎች ላይ በተደረገ ጥናት ዉጤቱ መገኘቱን አስታዉቀዋል ።

ይህ ቁጥር ከባለፉት አመታት ጋር ሲነፃፀር በመጠኑ መሻሻል አሳይታል የተባለ ሲሆን ከሁለት አመት በፊት የተደረገው ጥናት ምንም ማንበብ የማይችሉት 63 በመቶዎች እንደነበሩ ጥናቱ አመላክቷል ።

ዘገባው የካፒታል ነው።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


በራያ አላማጣ ወረዳ ከቅዳሜ ጀምሮ ለቀናት የዘለቀ የተኩስ ልውውጥ መደረጉ ተገለጸ

የአማራ እና ትግራይ ክልሎች ከሚወዛገቡባቸው የራያ አካባቢዎች አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ ወረዳ “የህወሓት ኃይሎች በከፈቱት ጥቃት” ከቅዳሜ እስከ ዛሬ የቆየ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን የአካባቢው ባለሥልጣናት እና ነዋሪዎች ሲናገሩ፣ የደቡባዊ ትግራይ ዞን በበኩሉ ግጭት የተፈጠረው ታጣቂዎች በትግራይ ሚሊሻዎች ላይ ተኩስ በመክፈታቸው መሆኑን ገልጿል።

ከየካቲት ወር ጀምሮ በተደጋጋሚ የተኩስ ልውውጥ እየተደረገባቸው ካሉት የራያ ወረዳዎች አንዱ በሆነ ራያ አላማጣ የተከስ ልውውጡ በድጋሚ ያገረሸው ባለፈው ቅዳሜ ሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም. ከቀኑ አምስት ሰዓት ገደማ ጀምሮ መሆነን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው እና የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ባለሥልጣናቱ “የህወሓት ኃይሎች” በማለት የሚጠሯቸው ታጣቂዎች፤ ተኩስ የከፈቱት በወረዳው አዲስ ብርሃን (በቀድሞ ስሙ ላዕላይ ድዩ) በተባለ ቀበሌ በኩል መሆኑን ገልጸዋል። ቅዳሜ፤ የነበረው ተኩስ እሁድም ቀጥሎ እንደዋለ እና ዛሬ [ሰኞ] ጠዋትም የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ እና አንድ ነዋሪ ተናግረዋል።

በትግራይ ክልል የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ሀፍቱ ኪሮስ፤ ቅዳሜ እና እሁድ የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዲተገበር የሚጠይቁ የራያ አካባቢ ተፈናቃዮች “ረጅም ርቀት በእግራቸው በመጓዝ” ሰልፍ ማድረጋቸውን አስታውሰዋል። ከመሆኒ እና ከማይጨው ከተሞች በመነሳት የተደረጉት ሰልፎች “የመከላከያ ሠራዊት ኬላ እስከሚገኝባቸው አካባቢዎች” የተደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አቶ ሀፍቱ፤ “ድምጻችንን እያሰማን ባለንበት ወቅት ታጣቂዎች፤ ታኦ ከሚባል አካባቢ ተሰባስበው የእኛ ሚሊሻዎች ወዳሉበት አካባቢ [መጥተው] ለተኩስ የተጋበዙበት ሁኔታ ተፈጠረ” ሲሉ በሁለቱ አካላት መካከል ለተደረገው የተኩስ ልውውጥ ምክንያት የሆነውን ክስተት ጠቅሰዋል።

ይህንን ተከትሎ “ግጭቶች” መፈጠራቸውን የሚናገሩት የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፤ “ከእኛ ሚሊሻዎች ጋር ግጭት ተፈጠረ፤ [ከእኛ በኩል የነበሩት] ሚሊሻ እና ፖሊስ ናቸው። ሌላ ምንም ሌላ ዓላማ የነበረው አይደለም” ብለዋል።

የዚህን ተቃራኒ የሚናገሩት የራያ አላማጣ ባለሥልጣናት በበኩላቸው፤ ተኩስ የተከፈተው “አርሚ 24” ከተባለ የህወሓት የሠራዊት ክፍል ውስጥ “ሦስት ክፍለ ጦሮች” በአካባቢው ላይ ተሰማርተው እንደሆነ ገልጸዋል። የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ በበኩላቸው አካባቢው ላይ የተሰማሩት “አክሱም፣ አልጋነሽ እና ዮሐንስ ክፍለ ጦሮች” መሆናቸውን ተናግረዋል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሞላ በበኩላቸው፤ “ሦስት ክፍለ ጦር ይዞ እኛ ላይ ኦፕሬሽን እያደረገ ያለው አርሚ 24 ነው። [አርሚ] 44 እና 24 ነበሩ፤ በታች በኩል ያለው አርሚ 44 በባላ [ወረዳ] በኩል ምንም አልተጠጋም። አርሚ 24 ግን አክሱም ክፍለጦር ከእኛ ሚሊሻ ጋር እየተጋጨ ነው” ብለዋል።

ተኩስ የከፈተው ከባድ መሳሪያዎችን በመጠቀም መሆኑንም ባለሥልጣናቱ ገልፀዋል።

የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ፤ ታጣቂዎች “ብሬል፣ ዲሽቃ እና ስናይፐር” መጠቀማቸውን የተናገሩ ሲሆን፣ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪው አቶ ሞላም “ዲሽቃ” በተባለው የቡድን መሳሪያ ተኩስ መከፈቱን ተናግረዋል። አንድ ነዋሪ በበኩላቸው ዛሬ አራት ሰዓት ገደማ ላይ “የዲሽቃ እና መትረየስ” ተኩስ ድምፅ መስማታቸውን አስረድተዋል።

የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀፍቱ ግን ይህንን አስተባብለዋል። “ይህ ነገር በሰላማዊ [መንገድ] ይፈታ እያልን ባለንበት ሰዓት፤ ሌላ ኃይል ልንጠቀም የሚያስችለን ምንም ምክንያት የለም” ብለዋል። እንደ ዲሽቃ ያሉት የቡድን መሳሪያዎች ጥቅም ላይ የዋሉት በተቃራኒ ወገን በሚገኙት የአካባቢው ታጣቂዎች መሆኑንም ተናግረዋል።

የራያ አላማጣ ባለሥልጣናት እና ነዋሪዎች፤ ከትግራይ ክልል መጥተዋል የሚሏቸው ታጣቂዎች፤ አዲስ ብርሃን የተባለውን ቀበሌ መቆጣጠራቸውን የተናገሩ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ደግሞ “ጋርጃሌ” የተባለ አካባቢ መያዙን ጠቅሰዋል።

የራያ አላማጣ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ፤ “መከላከያው ትንኮሳ እንዲፈጠር አልፈለገም፤ ‘እባካችሁ’ እያለ እንደ ልመና ነው የያዘው። እየተጠየቁ ያለው እንደ ግዴታ አይደለም። እነሱ ግን ኃይላቸውን እያጠናከሩ እያስገቡ ነው ያለው። እኛም በተለይ በትናንትናው ዕለት ጋርጃሌ ከተማ ሊይዙብን ስለሆነ የምንችለውን ኃይሉን በሙሉ አሟጠን ብዙ ሞከርን፤ አልተቻለም” ብለዋል።

“አሁን አላማጣ [ከተማ] ሊገቡ ሦስት ኪሎ ሜትር ነው የቀራቸው” ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ የአካባቢው ሚሊሻ ያለው “ኃይል ባለመመጣጠኑ ምክንያት አፈግፍጎ ተኩስ መቆሙን” ገልፀዋል።

ከቅዳሜ ዕለት ጀምሮ በነበረው የተኩስ ልውውጥ የአንድ ሰው ሕይወቱ ሲያልፍ፤ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች መቁሰላቸውን ባለሥልጣናቱ እና ነዋሪዎች ተናግረዋል። ሕይወቱ ያለፈው ግለሰብ “ሚሊሻ” እንደሆነ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀፍቱ፤ ቅዳሜ ዕለት “ተከፍቶብናል” ባሉት ተኩስ የተጎዳ ሰው ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ “በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙም አስተያየት ባልሰጥ ደስ ይለኛል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት መቀስቀሱን ተከትሎ በአማራ ክልል ስር የገቡት አወዛጋቢ አካባቢዎች ጉዳይ መፍትሔ የሚያገኘው በሕዝበ ውሳኔ እንደሆነ የፌደራል መንግሥት መግለፁ ይታወሳል። ጉዳዩን ለመፍታትም ከፌደራል መንግሥት እንዲሁም ሁለቱ ክልሎች ከፍተኛ አመራሮች ያሉበት ዐቢይ ኮሚቴ ሥራ ላይ መሆኑን የፌደራል መንግሥት አስታውቆ ነበር።

ከሁለት ሳምንት በፊት ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ፤ “በአማራ አዋሳኝ አካባቢዎች” ላይ “በትግራይ በኩል” የሚታየው “አዝማሚያ”፤ የፕሪቶሪያውን ስምምነት የሚጥስ” እንደሆነ ተናግረው ነበር።

ዶ/ር ለገሰ፤ “ወሰንን በኃይል እናስከብራለን” የሚል አካሄድ “የትግራይ ሕዝብን ለሌላኛው ዙር ስቃይ እና እንግልት የሚዳርግ ነው” ሲሉም በዚህ መግለጫቸው አሳስበው ነበር።

ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው።




ራሷን ወንድ አስመስላ ሰው ሰራሽ የወንድ ብልት በመጠቀም በተበዳይ ላይ ጾታዊ ጥቃት ስትፈጽም የቆየችው በእስራት ተቀጣች።
#FastMereja
የ19 ዓመት ዕድሜ ያላት ተከሳሽ ክህደት ዮራም ወንጀሉን የፈፀመችው በጋምቤላ ክልል ማጃንግ ብሔረሰብ ዞን መንገሺ ወረዳ በጥቅምት ወር 2016 ዓ.ም ፈጀጅ ቀበሌ ተብሎ በሚጠራበት ሰፈር እንደሆነ ተጠቅሷል።

ተከሳሿ በዚሁ በማጃንግ ብሔረሰብ ዞን መንገሺ ወረዳ ፈጀጅ ቀበሌ ተብሎ በሚጠራበት ሰፈር በጥቅምት ወር 2016 ዓ.ም በጎደሬ ወረዳ ነዋሪ የሆነችውን የግል ተበዳይ ፍሬህይወት ዮሐንስ የተባለችውን ሴት ተከሣሿ ፆታዋን በመቀየር እራሷን ወንድ በማስመሰል የጋብቻ ጥያቄ በማቅረብ ወይም እንጋባለን ብላ በማታለል ፍቃደኝነቷን ከጠየቀቻት በኋላ ተከሣሿ ወደ ምትኖርበት መንገሺ መረዳ ይዛት ሄዳለች።

በአከባቢው የቀበሌ አመራሮች በደረሣቸው ጥቆማ መሰረት በአንድ ቤት ውስጥም አንድ ላይ እንደ ባል እና ሚስት 2 ወር አብረው የኖሩ ሲሆን የሴትነትን ፆታዋን በመደበቅ አብራ ከግል ተበዳይ ጋር አብረው አንድ መኝታ ላይ በመተኛት ራሷን ወንድ አስመስላ በመቅረብ አንድ አይነት ፆታ እያላት ሰው ሰራሽ የሆነ የወንድ ብልት በመጠቀም የግል ተበዳይዋን በማታለል የግብርሰዶም ወንጀል በመፈፀም ክስ ተከሣለች።

ተከሳሿ በ1997 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣውን የኢ.ፌ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 629 እና 630(2)(ሀ) ስር ያለውን የህ ድንጋጌ በመተላለፍ እንዲሁም ክስ 2 በ1997 ዓ.ም ተሻሽሎ የወጣው የኢ.ፊ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 646(1)(2) ስር ያለውን የህግ ድንጋጌ በመተላለፍ የቀረበ የወንጀል ክስ ነው።

ተከሳሿ በተከሰሰችበት ወንጀል ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ የማጃንግ ብሔረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት ከተያዘችበት ቀን አንስቶ በ8 ዓመት ከ4 ወር ጽኑ እስራት እንድትቀጣ መወሰኑን ከዞኑ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ሊቨርፑል ተሸነፈ
#FastMereja
በእንግሊዝ ፕሪሚየርሊግ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ሊቨርፑል በሜዳው እና በደጋፊው ፊት በክርስታል ፓላስ አንድ ለባዶ በሆነ ውጤት ተሸነፈ።
ሊቨርፑል 0 - 1 ክርስታል ፓላስ


አሜሪካ በሀገሯ በጊዜያዊነት ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ተጨማሪ የመኖሪያ ጊዜ ፈቀደች
#FastMereja
በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በነበረበት ወቅት ወደ አሜሪካ በጊዜያዊነት የገቡ ኢትዮጵያዊያን ለ18 ወራት እንዲቆዩ የመኖሪያ ፈቃድ ሰጥታ ነበር፡፡

ለአጭር ጊዜ ቪዛ አግኝተው ለጉብኝት፣ ትምህርት እና ሌሎች ምክንያቶች ወደ አሜሪካ የገቡ ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እንደሚቸገሩ በወቅቱ አመልክተው ነበር፡፡

አሜሪካም ከኢትዮጵያዊያኑ ሀገራችን ጦርነት እና ሌሎች የፖለቲካ ቀውስ ላይ በመሆኗ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ እንቸገራለን በሚል ለቀረበላት ጥያቄ ለ18 ወራት መኖር እንደሚሉ የመኖሪያ ፈቃድ ሰጥታ ነበር፡፡

ለነዚህ ኢትዮጵያዊያን አመልካቾች የተሰጠው የ18 ወራት ጊዜ የፊታችን ሰኔ ላይ የሚያበቃ የነበረ ሲሆን እነዚህ በጊዜያዊነት ይኖሩ የነበሩ ዜጎች ለተጨማሪ 18 ወራት እንዲኖሩ እንደተፈቀደላቸው ተገልጿል፡፡

የሀገሪቱ የሀገር ውስጥ ደህንነት ቢሮ ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ አሁንም በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመኖራቸው ምክንያት ለአጭር ጊዜ ወደ አሜሪካ የመጡ ኢትዮጵያዊያን ለተጨማሪ 18 ወራት እንዲኖሩ እንደፈቀደ አስታውቋል፡፡

በአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ኢትዮጵያዊያን ከፈረንጆቹ ሰኔ 2024 እስከ ታህሳስ 2025 ድረስ የሚቆዩበት የመኖሪያ ፈቃድ እንደሚሰጡ ተቋሙ ባወጣው መግለጫ ገልጿል፡፡

ዘገባው የዐል ዐይን ነው።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja


አቶ አብነት ሼክ መሐመድን ከቦሌ ታወርስ ባለድርሻነት ለማስወጣት በመሠረቱት ክስ እራሳቸው እንዲወጡ ተወሰነ
#FastMereja
አቶ አብነት በነሃሴ 2014 ዓም አቅርበውት በነበረው ክስ የቀድሞ የቅርብ ወዳጃቸው እና አጋራቸው የሆኑት ሼክ መሃመድ ሁሴን አሊ አልአሙዲ በቦሌ ታወር ያላቸውን ድርሻ ለቀው እንዲወጡ ወይም ድርጅቱ እንዲፈርስ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም፡፡

ባሳለፍነው ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2016 የዋለው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የንግድ እና ኢንቨስትመንት ችሎት በሰጠው ውሳኔ ቦሌ ታወርስ የተባለው እና በወሎ ሰፈር አካባቢ የህንጻ ግንባታ ያለው ድርጅት እንዳይፈርስ የወሰነ ሲሆን፡፡

በተጨማሪም አቶ አብነት የሚገባቸው ድርሻ ተከፍሏቸው ከድርጅቱ ለቀው እንዲወጡ ወስኗል፡፡ ቢሊየነሩ ሼክ መሃመድ በቦሌ ታወርስ ላይ የ60 በመቶ ድርሻ ያላቸው ሲሆን ቀሪው በቀድሞ አጋራቸው የተያዘ ነው፡፡

መረጃው የካፒታል ነው።
***
በቴሌግራም መረጃ ማቅረብ ጀምረናል ተከተሉን
https://t.me/fastmereja
https://t.me/fastmereja

20 last posts shown.