ግጥም ለኢየሱስ ️️️📖✍


Channel's geo and language: Ethiopia, English
Category: Other


እንኳን ወደ ግጥም ቤታችሁ በደህና መጣችሁ ይህ የገጣሚ #አማኑኤል ነጋሽ እና የለሎች ገጣሚያን ግጥም የሚቀርብበት ነው
አዘጋጅ✍️AMANUEL NEGASH(Abu)
ግጥሜን ለኢየሱስ
10,000 members 🏃🏃‍♂️
ለአስተያየት👇
@AbuGitimBot
@abu_ND8
🛑YOUTUBE🛑
https://www.youtube.com/@gitim_alem
Telegram
@gitim_alem

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Category
Other
Statistics
Posts filter


እዮብ ገላው ቴተልትሎ ፤ ንብረቱ ሁሉ አልቆ፤ ምስቱ ከድታው፤ ልጆቹ ሞተውበት፤ ገላውን በድንጋይ እያኬከ ፤ምስቱ እግዚአብሔርን ሰድበህ ሙት እያለችው አንተ ገብተህ እንደት አደርክ ብትለው
እግዚአብሔር ይመስገን ነው መልሱ


እንደት አደራችሁ?

እኔ🗣 እግዚአብሔር ይመስገን

@gitim_alem @gitim_alem


ኢየሱሴ😍
የጸለይኳቸውን ጸሎት ባትመልስልኝ እንኳ😌 ፤ ካንተ ጋር ለመቆየት ብቻ ስባል ጸሎቴን አላቋርጥም🤲
ካንተ ጋር መኖር ማለት ለኔ ዓለሜ ነው🤌

ጸሎት🤝እኔ

ሳትጸልዩ እንዳት ተኙ

መልካም ምሽት🫣


ይቅርታዬ......

አልፈልግም ብዬ፤ ወጥቼ ነበረ
ላልመለስ ምዬ፤ ከቤትህ አምርሬ
ወጥቼ ነበረ.....
በእውነት በውሸት፤ ልብህን ሰብረ
ካንተ ጋራ ኑሮ ፤ብመስለኝ መገመድ
የዓለምን ንክክ፤ ራሰን በማስለመድ
መርጬ የራሰን፤ ያ ስመቴን ሸጋይ
ወጥቼ ነበረ... ፤ዳግም አንተን ላላይ
አሚጬ ደፍሬ፤ ቃልህን አለፍኩኝ
ትዕዛዝህን ትቼ ፤ የራሰን ሰማሁኝ
አንተ ስትጠራኝ ፤ ባልሰማ ወጣሁኝ
የዓለም ጥቃቅን፤ ልቤን ማረከብኝ
ስምህን ሰደብኩኝ፤ በቃልህ አላገጥኩ
የድፍረት ሀጢአትን ፤ በፍትህ አደረኩ
ስጋህን ግደለው፤ ብለህ አስተምረሄኝ
ስጋዬን ላወፍር ፤ መንፈሴን ገደልኩኝ
ታዲያ እኔ በርግጥ ፤ ሞት አይገባኝም!?
ላጠፋሁት ጥፋት፤ ያንሳል መስቀልም
ግን አንተ ምረሄኝ፤ ይቅርታ አልከኝ
ላጠፋሁት ጥፋት፤ ምረትህን ላክልኝ
እልሃለሁ እኔም ፤ አንተን ይቅርታዬ
የዳንኩብህ አንዱ፤ መማጸኛ ከተማዬ
በአንተ ተምሬ፤ ህይወትን አገኘሁ
ሀጢአቶቸን ክጄ፤ ወደ አንተ መጣሁ
አንተ ይቅርታዬ....
አንተ ፈላግግዬ....
አንተ መዳኛዬ
አንተ መጽናኛዬ
........ኢየሱስዬ....
........እወድሃለሁ....

✍Æmanuel Negash (abu


ማንባችሁን
በreaction ግለጹልኝ  ❤  👍    😍  🙏  🥰

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ዛሬም አንድ ግጥም አዘጋጅቼ አምጥቸላችኋለሁ በዚህ ግጥም እግዚአብሔር ልባችሁን እንድያገኝ ምኞቴ ነው።
ልባርካችሁ👐👐
እግዚአብሔር ግጥሙን ከማንበብ በላይ አልፎ ልባችሁን ያግኘው


reaction 🥰 👍 🙏 ❤ እየሰጣችሁ ጠብቁ


ሰላም ቤተሰቦቼ እንደምን አመሻችሁ በውሏችሁ እግዚአብሔር እንደከበረ ተስፋ አደርጋለሁ ።
እስት ውሏችሁን በ reaction ግለጹልኝ


እንዲህ.... ነበርኩ

ያኔ... ጥንት ያኔ ድሮ
መድኔ የሌለበት መራራውን ኑሮ
በጢቂት በጥቂቱ ላስቃኛችሁ
ስለ ኢየሱስም ላጭውታችሁ

እንዲህ.... ነበርኩ
በሀጥያት የሞሽሽኩ
የመርገም ጨርቄ ከርፍቶ
ስንከላወስ መንገዴ ጠፍቶ
ለጥያቄ ጥያቄ መልሱም ጥያቄ
ከሆኑ መላምት እራሴን ደብቄ
አንድ ሁለት የሌለውን እማነባ
ከለላ የሌላት ከእቅፉ የሚያገባ

እንዲህ ...ነበርኩ
እምነቃ ከሞት እየተፋለምኩ
ህይወት የሆነብኝ መና የሰመመን የጣር
እምል አልብሰኝ ከፈኑን ይጫነኝ አፈር
እምናፍቅ  በምፃት መዳን አሊያም ሞት
ሁነቴን በቅጡ የማልለይ ሆኖብኝ ትንግርት
እምተነፍስ ቁና
ሆኜ ኦና
እር ብዙ... እንዲህ እንዲያ
አጀብ ..እልፍ ወዲህ ወድያ...
ተረሱ እንደ ዋዛ የሆኑብኝ ትንግርት
አሁንማ ዳንኩ ጌታን ያገኜሁ እለት
አልልም እንዲያ በማያጠግብ ቃል አፌን ሞልቼ
በገዛ እጄ ከጠፋሁበት በእርሱ በፍለጋ ተገኝቼ
         
ወዳጆቼ የተጣልን ሳለን ያገኘን ጌታ ይባረክ
           ተባረኩልን🙋🙋
 


        ✍️Siyana

ማንባችሁን
በreaction ግለጹልኝ  ❤  👍    😍  🙏  🥰

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ዕምነቴ ወዴት ነው......?

እየሱስ ሲናገር....
ከእዚያ ባህር ማዶ እንሂድ ተሻግረን
ባህሩን እንቅዘፍ በልጀባው ለይ ወተን
ደቀመዛሙርቱ...
እሺ እንሂድ አሉ በቶሎ ተስማምተው
ጉዞውን ጀመሩ ቦታ ቦታ ይዘው
እየሱስም ገብቶ ሸለብ እንዳረገው
አለም ተናወጠች አምላኳ ሲደክመው
ጌታ...ሆይ ጌታ...ሆይ ኧረ ልንጠፋ ነው
እባክህ ተነስተህ ማዕበሉን አስቁመው
ጌታም ተነሳና ንፋሱን ገሰፀው
ነፋስንና ማዕበልን ያዛል😱
እነርሱም ይታዘዙታል😃
ለመሆኑ ይህ ሰው ስሙ ማን ይባላል 🤔
ኢየሱስ ሲናገር.........
ዕምነታችሁ ወዴት ነው ?
አብረን ምንጓዘው በኔ ሳታምኑ ነው ?
ቃሌን የምትሰሙኝ እንዲሁ በከንቱ ነው ?
ስሜ እሳት አለው ይገድላል ያድናል
ስሜ መንሽ ይባላል
ስንዴና ገለባን መለየት ይችላል
መነገጃ መስሎት ገንዘብ መሰብሰቢያ
በኔ ውስጥ የሚኖር ለመሰለው ለዚያ
እውነተኛ መስሎ በከንቱ ለሚኖር
ይሄንን ሰው እኔ አላውቅህም ከምር
ብዬ ሳልናገር.......
ይነሳ ይታጠቅ ወገቡንም ይሰር
ደህንነትን ይድፋ ልክ እንደ እራስቁር
ፍላፃን ለማጥፋት ይመክት ጋሻ ጦር
ዕምነቱና ቃሌን በአንድ ለይ ይዞ
እኔ ያለሁበትን ይከተል ያን ጉዞ።

ማንባችሁን
በreaction ግለጹልኝ  ❤  👍    😍  🙏  🥰

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ሰላም እንደት ናችሁ ዛሬም አንድ ግጥም ስለሚለቅ ማበረታታችሁን እንዳትተው
እስት Online ያላችሁ ሁላችሁም
በ reaction ግለጹሉኝ
❤ 🙏 😍 👍 🥰
እወዳችኋለሁ 🥰


ማቴዎስ 7 ፡ 12፤ እንግዲህ ሰዎች ሊያደርጉላችሁ የምትወዱትን ሁሉ እናንተ ደግሞ እንዲሁ አድርጉላቸው፤ ሕግም ነቢያትም ይህ ነውና።

ይሄ ሀሳብ በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ እንደት ከሰው ጋር መኖር እንዳለብ የሚያስተምር ክፍል ነው

ወንድማችንን እንደ ራሳችን ማሰብ❤❤ ይሁንልን

መልካም ምሳ


ቅርህ ነክቶኛል

        የልቤን የሚታውቅ እኔ ሳልነግርህ
       ሳልመርጥህ የመረጥከኝ ፍቅሬ ልበልህ
  ፍቅር እልሀለሁ ፍቅር አንተ አኮ ነህ
  በዛ ቀራኒዮ ለፈሰሰው ደምህ
           ፍቅር ያስያዘኝ የመስቀል ላይ ስራህ
           ፍቅርህ ትዝ ይለኛል አለብኝ ውለታህ
ልበልህ ፍቅሬ አንተ የኔ ፍቅር ላብዛልህ ምስጋና
  ውለታህ አለብኝ ልበል ጎንበስ በና
               ከያዙ ማይለቁት እነዛ እጆችህ
               ዘወትር ሚያዮኝ እነዛ አይኖችህ
                           በፍቅርህ እነድወድቅ
                           ከጉያህ እንዳልርቅ
                           እዚህ እዚያ እንዳልል
                           ይዘው አስረውኛል
ይኸው...ፍቅሬ እያልኩ መኖሬን ቀጠልኩት
ይኸው...አይኔ በርቶ ገባኝ አንድ እውነት
        ፍቅርህ አስሮኛል የልቤን ልናገር
        ፍቅርህ ይነግረኛል አንድ ልዩ ነገር
መኖር እንደ ማልችል ከቶ ያለ ፍቅሩ
በምድር እንደሌለ እንደእሱ ሩህሩ

       ጌታ ይባርካቹ
ማንባችሁን
በreactin ግለጹልኝ ❤ 👍 😍 🙏 🥰

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ሰላም እንደት ዋላችሁ ውዶች እናንተን ለእኔ እኔን ደግሞ ለእናንተ የሰጠው አባታችን እግዝያብሔር ስሙ ለዘላለም የተበረከ ይሁን፤
እግዚአብሔር እናንተን በአደራ እንደሰጠኝ አ
ይነት ነው የሚሰማኝ ምክንያቱም እናንተን እንዳገለግል ነው እግዚአብሔር ይህንን ራዕይ የሰጠኝ።
ሁለም እወዳችኋለሁ ተባረኩልኝ😍❤🙏
አማኑኤል (አቡ) ነኝ❤❤❤


የማለዳ መልዕክት


ማቴዎስ 6 : 25፤ ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን?
.
.
.
33፤ ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።

የኔ ጌታ ሁሉ ነገሬ በአንተ እጅ ነው ታዲያ እኔ ለምን ሊጨነቅ
አንተ ነገዬን ታውቃለህ በኢየሱስ ስም

🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶
ነገሬ ያለው በእርሱ እጅ ነው 2*
የሚያስፈራኝ የሚያሰጋኝ እስት ማነው

react ❤ 🙏 👍 😍 🥰


የዘገየው ነገሬ🚶‍♂‍➡️

ድሮ ድሮ ገና ያኔ በጥዋቱ
ሲሰግዱልኝ ያየሁ ፀሀይ ከዋክብቱ
ደግመው ሲሰግዱልኝ ጨረቃና ነዶ
ራዕይን ሰነቀ ልቤ በነጋታው ማልዶ
ቀኑ እየገፋ አመታት ነጎዱ
ታዲያ የታል ያኔ ለኔ የሰገዱ
ከህልሜ ልጣላ ወይስ ልክ አልነበረም
የዘገየው ነገሬ ገና አልተፈጠረም
የት ጋ ነው ስህተቴ ያጨለመው ተስፋ
ደስታን ስጠብቅ ሌተቀን ልከፋ

እያልኩ ሳጉረመርም ከብዶኝ መንዱ
ያላሰብኩት ሆነ ዘመናት ነጎዱ
.........ታዲያ
ቀን ይማይለውጥው ቃሉን የማይበላ
ከበደኝ አቃተኝ ብሎ ማይመለስ ኋላ
ለመልካም አድርጎ ጎርባጣ መንገዴን
በእሳት ፈትኖ አዳናት ህይወቴን
ልክ ነበር ህልሜ ያየሁት ትላንት
ለመፍተሄ ሰዶኝ ለክፉ ቀናት
ማዳኑን አሳየኝ ጥብቃውን አብዝቶ
ምሽቴ አማረ ጌታ ቤቴ መጥቶ
እንኳንም ዘገየ የዘገየው ነገሬ
በረከት ሆኖልኛል ሁሉ አልፎ ዛሬ

ማንበባችሁን በreaction ግለጹ
❤ 👍 🙏 😍 🥰

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ሰላም ቤተሰብ እንደምን አመሻችሁ
እኔ ሰላም ነኝ አባታችን ጌታ ኢየሱስ ስሙ ለዘላለም ይባረክ አንድ ግጥም ሊለቅ ነው።
እስት
በ reaction

ሞቅ አድርጉኝ

👍 ❤ 😍 🙏 🥰


የዛሬ አምልኮ እንደት ነበር
እግዚአብሔርን በቃሉ ተገናኛችሁት?
በ reaction ግለጹልኝ
❤ 🙏 👍 😍


እንዳትወደኝ በመልካምነቴ
ይህ አይደለም ማንነቴ
እንዳትጠላኝ ደግሞ በጥፋቴ
ፍቅር ነህ አያስችልህም አባቴ

ያለ ምክንያት ወደህ በምክንያት አትጠላም
ለምህረትህ ስፍር መለኪያ የለውም
የአንተ ፍቅር መነሺያው ከራስህ
የመውደድ ልብ የማያልቅብህ
የእኔ ጌታ

ያለምክንያት ወዶ ጌታ በኃጢአታችን ምክንያት አይተወንም
አሜን🤦‍♀️


መልካም ምሽት ይሁንላችሁ ❤️‍🩹


የወደድከኝ ሰሞን!

ከቤቴ ደጃፍ ላይ
ሲመላለስ አይተው የታዘቡት ሁሉ
'የፍቅር ደብዳቤ
በልጁ አስይዞ ልኮ ነበር አሉ'

እርሱ ግን!
ዘወትር ተመላልሶ ፥ ባያገኘኝ ላፍታ
ተስፈኛዋ ልቡ ፥ አጥታኝ ብትሄድ ለፍታ

ሰነባብቼ ግን
ከበሬ በስተ ሥር ፥ የታየኝ ወረቀት
እኔን ለማፍቀርህ ፥ የሄድክበት 'ርቀት
ምን ያህል እንደሆን ፥ በቅጡ ያስረዳል
የእውነት መውደድህ ፥ እንዲሁ ይወደዳል፤

እንዲህ ተገረምኩኝ!
በደም የከተብከው ፥ የመዳፍህ ጽሕፈት
እርማት ማያሻው ፥ ያልታየበት ግድፈት
የተጠቀምከው ቃል ፥ ብዛት ያላወቀው
አንድ እሱኑ ነው ፥ ይህ ነው ሚደንቀው

እናልህ ወዳጄ...
'ላስብበት' ብዬህ ፥ እንዳትቆም ከደጄ
እንደ ትላንትናው ፥ ላላመላልስህ
አንድ እድል ብትሰጠኝ ፥ እንዴት ልከልስህ ?
:
የእኔንስ ደብዳቤ ፥ በማን ልላክልህ
ማነው አንተን ደራሽ  ፥ የሚያካልልህ ?

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ለዛሬ ጻፍልኝ


አታቋርጥ አታቁም ጻፍልኝ ለዛሬ
ቀለምህ አይለቅ ለነገም ብዕሬ
አልረካሁምና መዳኔን መስክሬ
አልጠገብኩምና አዳኙን አብስሬ
የመስቀል ላይ ሞቱ
የፍቅሩ ጥልቀቱ
የሰማይ ክህነቱ
አማላጅነቱ
የኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆን
በመስቀሉ ስራ አባት ማግኘታችን
መች ተነግሮ ያልቅና
ይልቅስ ብዕሬ ልፃፍብህና
ለትውልድ ልናገር
በደም እንደዳንኩኝ ባንተ አሳልፌ ወረቀት ላይ ላስፍር
አደራ ብዕሬ
ጻፍልኝ ለዛሬ
አትለቅ ለነገም
ስለ እየሱሴ ፅፌብህ አልጨርስም።


#SHARE     #SHARE

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


እንደምን አመሻችሁ family እስት online ያላችሁ
በ reaction አሳዩኝ አንድ ግጥም ሊለቅ ነው
react👍 ❤ 😍 🙏 አድርጉ


ሰው የማይጠራበት ቦታ ላይ ስንቴ እግዚአብሔር ደረሰልን❤️‍🩹
አይ እግዚአብሔር 😭❤🙏

20 last posts shown.