የጭለማው አለም ሰራተኞች አዲሱ የዓለም ስርአት የሚሉትን ለማምጣት ከጠቀሟቸው እጅግ ወሳኝ ፍልስፍናዎች ውስጥ ተራማጅነት (progressivism) አንዱ ነው። ይህም በጊዜ ሂደት ሰይጣን ያቀበላቸውን ክፉ ሃሳቦች አንዱን በአንዱ ላይ እየደራረቡ በየጊዜው አዳዲስ የከፉ መርዛማ ፍልስፍናዎችን ሰዎች እንዲቀበሉ ያደረጉበት መንገድ ነው።
ይህንን የጀመሩትም በ1789 የፈረንሳይ አብዮት ጊዜ ነው። ለመጀመርያ ጊዜ ዘውዳዊ ስርአትን የገረሰሱበትና "ስር ነቀል" ለውጥ ያመጡበት ጊዜ ነበር። ጊሎቲን የሚባል መሳርያ አዘጋጅተው ንጉሱና ሚስቱን አንገታቸውን በህዝብ ፊት ቆረጧቸው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ፈረንሳይ ፍጹም የተለወጠች ሃገር ነው የሆነችው። ባህሏ፣ ቋንቋዋ፣ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ስርአቷ ጭምር ነበር የተለወጡት። እናም ሊበራሊዝም እና ተራማጅነትን/ፕሮግረሲቪዝምን እስከዛሬም እየመሩ ለዓለምም አዳርሰው አሉ። ታድያ አብዮተኞቹ አዲስ ያልተለመዱ ስራቶችን እና ፍልስፍናዎችን ሲያመጡ ተቃውሞ ገጠማቸው። እነዚህም የተወሰኑ የፓርላማ አባላት ነበሩ። አብዮቱን የሚመሩት የፓርላማ አባላትም ከነዚህ የአብዮቱ ተቃዋሚዎች ጋር የስልጣን ፍልሚያ ውስጥ ገቡ። ነገር ግን አሸነፉ።
ታድያ በአጋጣሚ ይሁን ወይም ታስቦበት፣ አብዮቱን የሚመሩት ሰዎች በፓርላማው በግራ በኩል ነበር የሚቀመጡት። አብዮቱን የሚቃወሙት ደግሞ በቀኝ። ከዚህም የተነሳ በግራ የሚቀመጡት "የግራው ክንፍ" (Left Wing) የሚባል ስያሜ ሲሰጣቸው በቀኝ የሚቀመጡት ደግሞ "የቀኝ ክንፍ" (Right Wing) ተባሉ። ይህ አሰያየም እኛ ሀገር ሲመጣ "ግራ ዘመም" እና "ቀኝ ዘመም" ተባለ። ዛሬ ላይ እንደ ኮሚዩኒስት፣ ማርክሲስት፣ ያሉት ቡድኖች ግራ ዘመም ተብለው ይጠራሉ።
ቀድሞ በተጠቀሰው የፖለቲካ ፍልሚያም አብዮቱን የጠነሰሱትና የመሩት ግራ ክንፎቹ አሸነፉ። ቀኝ ክንፎቹንም በጊሎቲኑ መሳርያ አርደው ገደሏቸው። ከዚያም አዲሱን የዓለም ስራት አስጀመሩ። አብዮቱንም በመላው ዓለም አስፋፉ። ወድያው አብዮቶች በብዙ ሀገራት ተስፋፉ። በአሜሪካ፣ በሩስያ፣ በአረቡ አለም፣ በኢትዮጵያ፣ በኢራን ወዘተ። አብዮተኝነት ሰዎች የሚያደንቁት የሚወዱት ተደርጎ ታየ። አብዮተኞችን እንደ ጀግናና ታላቅ ሰው ማየት ተለመደ። እነ ሌኒን፣ እነ ማኦ፣ እነ ቼጉቬራ፣ እነ የኢራኑ ኻሜኒ፣ እንደ ጀግና፣ ታላቅ ሰው፣ ታይተው ክብር አድናቆት ፈሰሰላቸው። ከዛን ጊዜ ጀምሮ ወጣቶች እንደነሱ ለመሆን የሚመኙ የሚሹ ሆኑ።
ግን እውነታው እነዚህ ሰዎች ነው ዎርልድ ኦርደርን ቀስ በቀስ ወደ ዓለማችን ያመጡ ሰዎች ናቸው። ሁሉም ደግሞ የፍሪመሶንሪ አባላት እንደነበሩ እጅግ በዙ መረጃዎችና ማስረጃዎች አሉ። ታድያ ይህን ኒው ወርልድ ኦርደርን የሚያመጡት በሂደት ስለሆነ ያንን ሂድት ደግሞ እንደ ነዳጅ ሆኖ የሚገፋላቸው አስቀድመን ያነሳነው የተራማጅነት ሃሳብ ነው። "ወደፊት እንራመድ፣ አዲስ ለውጥ እናምጣ፣ እኛን የሚቃወሙ ሁሉ እንዲህ እና እንዲያ ናቸው፣ እንዲህ እና እንዲያ የሚሉ ስሞች ለጥፈንባቸው እናሳፍራቸዋለን" እያሉ የሚያምኑበት ሁኔታ ነው።
ይህንን ደግሞ ሲፈጠር አንዱ ፍልስፍናዊ መሰረቱ ከዚህ በፊት በቻናላችን ያነሳነው የ "
ወጥ የእምነት ስራት" እሳቤ ነው። በዚህም መሰረት አንድ ሰው አንድን ሃሳብ እንደ ትክክለኛ ከተቀበለ አስተሳሰቦቹና እምነቶቹ ወጥ ይሆኑ ዘንድ የዛን ሃሳብ ምክንያታዊ ድምዳሜም መቀበል ይኖርበታል። ይህንንም እሳቤ እንደ ምሳሌ ለማየት ምድር በቢሊዮን አመታት የአጋጣሚ ሂደት ተፈጠረች፣ ሰውም በሚሊዮን አመታት አጋጣሚዎች ሂደት ከዝንጀሮ መጣ ብሎ ያመነ ሰው፣ የዚህ እምነቱ ምክንያታዊ ድምዳሜ የሆነውን "አስቦና አቅዶ ዓለምን የፈጠረ አካል የለም" የሚለውን ሃሳብም ለመቀበል ይገደዳል። ሰዎች ግን ያንን ሳያደርጉ ይቀሩና የተጣረሱ እምነቶችን ይይዛሉ። ብለን አንስተን ነበር። የዚህም አንዱ መፍትሄ ቀድሞውኑ መነሻ ሃሳቡ ሃሰት እና ስህተት መሆኑን መረዳት እንደሆነ አይተናል።
በተመሳሳይ መልኩም ተራማጅነት እና ሊበራሊዝም ሃሰት እና ከፊል እውነት የሆኑ ሃሳቦችን እየያዘ ይነሳና በሱ ላይም ሌሎች የተሳሳቱ ሃሳቦችን እየጨመር ይመጣል። ለምሳሌ ሁሉም ሰው በኢኮኖሚ እኩል መሆን ይችላል የመደብ ልዩነት መጥፋት አለበት ይልና። ከዚያ ደግሞ አሁን ያለውን የመደም ልዩነት ለማጥፋት ድሃውን ከማሰራት ይልቅ ሃብታሙን ቀምተን እንዳይሰራ ከልክለን ደሃ እናድርገው የሚል ድምዳሜ ላይ ይደርሳል። በሌላ ምሳሌ ደግሞ፣ በጣም አደገኛ የሆነው፣ የሴቶች መብት ነጻነት ይከበር ብለው ይጀምራሉ። ሴቶች አናሳ ቡድን (ማይኖሪቲ) ናቸው የሚል የተሳሳተ ሃሳብ ይዘው ይነሳሉ። ሴቶች አናሳ ቡድን አደሉም፣ እንዲያውም አሁን ዓለም ላይ 55 በመቶ ሴቶች ናቸው። ነገር ግን ተራማጆቹ ይህንን እንደ እውነት ይዘው ይነሱና በዙ ጊዘ ወስደው የሴቶች መብት መከበር ሲጀምር፣ አሁን ደግሞ ግብረሰዶማውያንም አናሳ ቡድን ናቸው የነሱም መብት ነጻነት ይከበር ይላሉ። የመጀመርያውን ሃሳብ የተቀበለ ሰው ወጥ የእምነት ስራት እና የአመክንዮ ስራት (logical consistency) እንዲኖረው በማሰብም እንደ እውነት ይቀበልና (ልክ እግዚአብሄር የለም የሚሉ ሰዎች እንደሚያደርጉት)፣ ከዚያም ግብረሰዶማውያን ተጨቁነዋል ከሌሎቹ እኩል ይሁኑ፣ ጭራሽ የነሱን የተበላሽ ባህሪ ወደ ሌላው እንዲያስተላልፉ ይፈቀድላቸው ይላሉ። ከዚያም አለፍ ይሉና ትራንስጀንደር የተባሉትም እንዲያው ናቸው እነሱም ይፈቀድላቸው ይላሉ። እናም አሁን ያለንበት ላይ ደርሰናል።
ግራ ዘመሞቹ በሚዲያ፣ በትምርት ስራት ውስጥ የበላይነት እንዲኖራቸው፣ ምሁራን ሁሉ ተጠርገው ወደዚያ እንዲገቡ ስለተደረገ፣ ምሁራኑና የሚዲያ ሰዎች ደግሞ ማህበረስብን የሚመሩት እነሱ ስለሆኑ፣ በዚህ መንገድ የጭለማው ሰራተኞች መላውን ዓለም ሙልጭ አርገው ወስደዋል። ይህንን የሚቃወሙ ደግሞ፣ አይ ልክ አደለም የምሉ ደግሞ ስም ተለጥፎባቸው፣ "ወግ አጥባቂ"፣ "አድሃሪ" ወዘተ እየተባሉ። ባሉበት የሚረግጡ፣ ኋላ ቀር እየተባሉ። እንደኛ ደግሞ የነሱን ሴራ የሚያቃልጡት "ሴራ ተንታን" /ኮንስፓይሪሲ ትዮሪስት እየተባልን ስም ተለጥፎብን፣ "በስይማቸው አሳፍራቸው" መርህ ብዙሃኑ ህዝብ የኛ ተቃዋሚ እንዲሆን ተደርጓል። ስዎች በተለይ ብዙሃኑ ከሎጂክ ይልቅ ትርክትን (narrative)፣ ለማብራራት ረጅም ሰአት ከሚወስድ እውነት ይልቅ በአጭር ሰከንድ የሚነገር ውሸትን ስለሚወዱ የጭለማው ሰራተኞችም በዚሁ ተጠቅመው ዓለምን በጃችው አስገብተዋል፣ ተቃዋሚዎቻቸውንም አንድ በአንድ አጥፍተዋል። ነገር ግን በዚሁ አይቀጥልም። የእውነት አምላክ አንድ ቀን ይበቀላቸዋል። ትክክለኛውንም ስርአት በዓለም ላይ ይመልሳል። እነሱንም ስር መሰረታቸው፣ ምልክታቸው እንዳይታይ አድርጎ ከምድር ገጽ ያጠፋቸዋል። ይህ ይሆናል። አይቀርም።