አዲስ ምልከታ🌍


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Other


+ አዲስ የሳይንስ እይታ
+ አዲስ አስተሳሰብ
+ አዲስ እውቀት
+ ሃይማኖት
+ ፖለቲካ
+ ኢኮኖሚ
+ ሙዚቃ
# የኢትዮጵያ ትንሳኤ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Other
Statistics
Posts filter


የሚያሳዝነውና የሚያናድደው ነገር ነጮች እኛን ስለ ክርስትና ማስተማር የሚችሉ አድርገው ማሰባቸው ነው። እኛ ምንም የማናውቅ፣ እነሱ እንደ አዲስ የሚያሳውቁን አድርገው የማሰብ ድፍረት መያዛቸው ነው። ይሄኛው ሰውዬ ታሪኩ ሲታይ የፕሮቴስታንት "ሪቫይቫል" እንቅስቃሴዎች ላይ በሰፊው የሚሳተፍ እንደሆን ይነገርለታል። ሪቫይቫል ማለት ምን ማለት ነው? ጠፍቶ የነበረው ቀዝቅዞ የነበረው እምነት እንደገና እንዲፋፋም እንደገና እንዲነሳ ማድረግ ነው። እነሱ እምነታቸው በአሸዋ ላይ የተሰራ ስለሆነ፣ መንፈስ ቅዱስ አብሯቸው ስላልነበር፣ በራሳቸው የስጋ ስሜት ብቻ ስለነበር የሚንቀሳቀሱት ያ ደግሞ ይከስማል። ይጠፋል። እና እንደገና የሚቀሰቅስላቸው ያስፈልጋቸዋል።

አኛ ግን ያ አያስፈልገንም። እምነታችን ጠፍቶ ወይም ከስሞ አያውቅም። ለ2000 ዓመታት ሳይጠፋ እንደነደደ እንደጋለ ይበልጥ እንደውም እየጠነከረ ነው የሄደው። ምንክያቱም መንፈስ ቅዱስ ከመጀመርያውም አብሮን ነበር። ክርስትናን መስበክ ብቻ ሳይሆን መኖርን በህይወት መተግበርን የለመደ፣ በባህል ደረጃ የያዘ ባህሉን በክርስትና ዙርያ የገነባ ማህበረሰብ ነው ያለን። ዛሬ መድሃኒአለም ነው፣ ዛሬ ስላሴዎች ናቸው ብሎ ስራውን የሚገታ፣ በቅዱሳኑ ስም ዘክሮ ደግሶ መንገደኛውን ሁሉ፣ የኔቢጤውን ሁሉ የሚያበላ፣ እረ እባካችሁን ብሉልኝ ጠጡልኝ የሚል ማህበረሰብ፣ ሰላምታ ሲሰጥ "እግዚአብሔር ይመስገን" የሚል፣ ሲያመሰግን "እግዚአብሔር ይስጥልኝ" "እግዚአብሔር ያክብርልኝ" የሚል በእምነት በተግባራዊ ክርስትና የዳበረ፣ ተግባራዊ ክርስትናን ከቤተሰቦቹ ከአያት ቅድመ አያቶቹ የወረሰ ማህበረሰብ፣ ልክ እንደ አብርሃም እንግዳን ተቀብሎ መግቦ የሚያሳርፍ፣ እንደ ክርስቶስ እግሩን ሁሉ የሚያጥብ ማህበረሰብ።

ይህንን ማህበረስብ "መለኮታዊ ጉብኝት" አደረኩልት ማለት ትንሽ አይከብድም? መለኮትማ ቀድሞም ጎብኝቶታል እኮ። አሁን ወዴት ነው የሚጎበኘው? ታሪክን ስነመኮትን ትውፊትን፣ መጻሕፍትን እስክ አፍንጫው የተጫነ የታጠቀ ማህበረስብ ጋር መጥተህ አይ እኔ እንደ አዲስ ላስተምርህ መንፈስ ቅዱስን ወዳንት ላምጣ ማለት ትንሽ ንቀት አይሆንም? ኧር እንዲያውም ትንሽ ንቀት ሳይሆን እጅግ ትልቅ እጅግ ከባድ ነቀት እንጂ። መጽሃፍ ቅዱስን ሙሉ ብልት አድርጎ አያንዳንዷን ምዕራፍና ቁጥር ከነ አንድምታ ትርጓሜው የሚተነትኑ ሊቃውንትና መምህራን የሞሉበት ሃገር መጥቶ እኔ እንደ አዲስ ከእግዚአብሄር ጋር ላስተዋውቃችሁ ማለት ትልቅ ምጸት፣ ትልቅም ዘበት ነው።

ግን ነገሩ ይህ ብቻ አይደለም። ይህ ሂደት ግሎባላይዜሽንን ወደኛ ሀገር የማስገባት ሂደትም ስለሆነ፣ የነሱን የስለላ መረቦች መላክያም ስለሆነ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ የነሱን የስለላ ድርጅቶች በደምብ መሬት ለማስያዝ ስር ለመስደድም ጭምር ነው። እንዲሁም የነሱን አዲሱን እምነት የሚቀበሉትን ሰዎች በሙሉ የሃገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበረሰባዊ ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎች ላይ ለማስቀመጥ፣ ኢሊቶችን በዛ መልኩ የመፍጠር ሂደትም ለመጀመር ጭምር ነው። ያን ካደረጉ ኮሎናይዜሽንን በደምብ አስፈጸሙ ማለት ነው። ለዘመናት የቋመጡላትን ኢትዮጵያን በግላጭ አግንተዋታል፣ እናም በደምብ ይዘነጣጥሏታል ማለት ነው። ነባሩን የተዋህዶ እምነት የያዘው ክፍል ቀስ በቀስ እየተገለለ፣ እየተገለለ፣ ማይኖሪቲ እየሆነ እንዲሄድ ይደረጋል። የሃብትና ስልጣን መንገድን ለማግኘት ወይ እምነቱን መቀየር፣ ወይ ዋሽቶና ቀርጥፎ እንደ ዘመኑ ነገር ተሃድሶ ነኝ ማለት፣ ወይ እነ ሄኖክ ሃይሌ በቀደዱት ቦይ ገብቶ የሚስጥር ካቶሊክ መሆን፣ አልያም ደግሞ ከነ አካቴው እግዚአብሔርን ክዶ እምነት የለኝም ማለት ነው። ያ ሲሆን ነው ነባሩን የኢትዮጵያ እምነት ባህልና ማንነት የያዘው ህብረተሰብ ወደ ሃብትና ስልጣን መንገድ የሚመጣው። በነሱ እቅድ መሰረት ማለት ነው። ታድያ ይሄ በዘር አይወሰንም፣ አማራም ይሁን ትግሬም ይሁን ኦሮሞ፣ ወላይታም ይሁን ተዋህዶን ከያዘ እጣ ፈንታው ያ ይሆናል። ይህ ገና የሚፈጠር እንዳይመስላችሁ፣ ጀምሯል። ከጀመረ ሰናባብቷል።

ደግሞ እኛ ሃገር ብቻ የሆነ ነገር አይደለም። ነጮች በዓለም የፖለቲካና ኢኮኖሚ የበላይነታቸውን ለማግኘት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም። ለዚህ አንድ በጣም ጥሩ ምሳሌ እንይ። ይህንን ተመልከቱ።
https://openamericas.org/2018/06/11/the-de-catholicization-of-latin-america/

የላቲን አሜሪካ ህዝቦች ድሮ ወደ 90 በመቶ ካቶሊክ ነበሩ። እናም እንደ ሜክሲኮ ያሉት በደቡብ በኩል የአሜሪካ ጠባቂ ጋርድ ተደርገው ስለሚቆጠሩ፣ የላቲን አገራት ዜጎችም አሜሪካ ውስጥ ከታች ያሉትን የግንባታ፣ የአትክልተኝነት፣ የጽዳት ስራዎች በሰፊው ስለሚሰሩና ኢኮኖሚውም በነሱ ስለቆመ፣ እነሱን መቆጣጠር ለአሜሪካ ፖለቲካ ወሳኝ ተደርጎ ነው የሚታየው።እናም እነሱ የአሜሪካ ደጋፊዎች እንዲሆኑ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች ይደረጋሉ።

ታድያ የአሜሪካ ፖለቲካ በፕሮቴስታንቲዝም የተቃኘ ስለሆነ፣ እነዚህ ላቲን አሜሪካውያንም የአሜሪካ ደጋፊዎች ይሆኑ ዘንድ ፕሮቴስታንት መሆን አለባቸው ተብሎ ስለታመነ፣ እነሱን ወደ ፕሮቴስታንት የመቀየር ስራ በ ሲ አይ ኢ ተመርቶ ይካሄዳል። እናም ባለፉት 50 አመታት በላቲን አሜሪካ የካቶሊክ ቁጥር ከ90 በመቶ ወደ 69 በመቶ ሊወርድ ችሏል። ይህንንም አሜሪካውያኑ አጠናክረው ይቀጥሉታል። አሜሪካውያን፣ ላቲን አሜሪካዎቹ ገና ድሮ አሜሪካ ራሷ ሳትመሰረት ካቶሊክን የተቀበሉ መሆናቸው አይመለከታቸውም። ደፋሮች ስለሆኑ፣ አኛ ከመላው ዓለም በላይ ነን ብለው ስለሚያስቡ፣ የኛ እምነት ነው ከሁሉም የሚበልጠው፣ ዓለምም የኛን እምነት፣ የኛን ባህል የኛን አስተሳሰብ መቀበል አለበት ብለው ስለሚያስቡ ያንን ይፈጽማሉ። ይህንንም ሂደት እኛ "ግሎባሊዝም" ብለን እንጠራዋለን፣ ነገሩ ግን የኢንግሊዞች ባህል በዓለም የመስፋፋት ሂደት ነው። እነዚህን የኢንግሊዝ ቡድድን ነጭ አንግሎ-ሳክሰን ፕሮቴስታንት ወይም White Anglo-Saxon Protestant የሚባሉት ናቸው። ከነ ሉተር በፊት ከካቶሊክ ቤትክርስትያን የተገነጠሉ፣ የቤተክርስትያናቸው የበላይ አካል፣ መንፈስ ቅዱስ መሆኑ ቀርቶ፣ እንደ ካቶሊክ ፖፑም መሆኑ ቀርቶ፣ ንጉሳቸውና ንግስታቸውን ያደረጉ ሰዎች ናቸው። ባህሪያቸውም እጅግ ክፉ መሰሪ፣ ሌሎች ነጭ አውሮፓውያንም ጭምር የነሱን መሰሪነት የሚመሰክሩላቸው ሰዎች ናቸው። እናታቸው እንግሊዝም ጀርመኖች በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ደራሻቸውን ካጠፏት በኋላ ልጅየው አሜሪካ የባሰ ብልጥ፣ የባሰ መሰሪ ሆና፣ አውሮፓውያኑ በኮሊኒያሊዝም እንደዘረፉት እሷም ከነሱ ጭምር ዘርፋ፣ መላው የዓለም ነዳጅ በሷ ገንዘብ እንዲሸጥ አድርጋ በዚያም ሃገራት ላይ ማዕቀብ የመጣል ስልጣንን ለራሷ አጎናጽፋ፣ በመላው አለም ሊበራሊዝምን፣ ፌሚኒዝምን፣ ግብረሰዶምን የምታስፋፋ ሆናለች።

ያንንም ደግሞ ለዘመናት በከፊልም ቢሆን ተጠብቃ የነበረችው ኢትዮጵያ፣ በጣም በጥቂቱ ተከፍቶ የነበረው በሯ አሁን ብርግድግድ ብሎ ተከፍቷል። በግላጭም አግኝተውናል። ልክ በጊቷን ለብቻዋ እንዳገኛት አውሬ ይገነጣጥሉን ጀምረዋል። በፍጹም አይራሩልንም። ፍጹም ባርያ ነው የሚያደርጉን። ብቻ እግዚአብሄር ይፍረድ።


"መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ" ምፀት ነው።
===========================
(ከሆነ አሜሪካ በUSAID በኩል ብትጎበኘን የተሻለ ነበር!)
መለኮታዊ ጉብኝት ይኸ ፈረንጃዊ ምፀት(irony) ነው። አሁን በሞቴ እኛ መቼ አነቃቂ ተናጋሪ ወይም እምነት ቸግኖን ያውቃል? እንደ ፕሩፍ ገለጻ ዋናው የሙሴ ፣ የኢየሱስና የነብዩ መሐመድ ዕጣን ለሺ ዓመታት በአንድ ላይ ሲጤስባት በኖረች ሀገር ላይ ከጌይና ሌዝብያን ሃገር የመጣ ሰው መለኮት ሊያድላት ? መለኮትን ከየት ሊያመጣልን ይሆን ? ከሰማይ ወይስ ከሉሳንጀለስ?
-------------------
እኛም እኮ የከፍታ ዘመን ፣ የብልፅግና ጊዜ ብለን ለፍፈን ፎክረን ነበር ዳሩ ግን የተረፈን የማያቋርጥ ጦርነት ፣ የሕጻናት ዋይታ ፣ የራሀብ ሲቃ ነው ። በእውኑ ኢትዮጵያ ከምዕራብ የሚያስፈልጋት የአውሮፓ ኢየሱስ ነው? ወይስ እነሱ ጡረታ ያወጡትን የማሽን አሰራር? ሰማይ ዝቅ መሬት ከፍ ቢል 18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ተሰርቶ expired ያደረገ በእነሱ ሀገር ጥቅም የሌለው ቴክኖሎጅ አይሰጡህም። እኛ ለእናንተ ያዘጋጀንላችሁን ኢየሱስን ግን በኃይልና በሞገስ እንካችሁ እያሉ ቢሊዮን ዶላር ይበጅታሉ ። ይኸ ፈለካዊ ምጸት ይባላል! በኢየሱስ ስም የማደንዘዝ አባዜ !
------------------
የአሜሪካ ህዝብ በእግዚአብሔር እያላገጠ ፣ ቸርቾች ወደ ቡቲክና ጭፈራ ቤት እየተቀየሩ ፣ እጅግ ጸያፍ ኃጢአት በዐደባባይ እየተፈጸመ ባለበት ጊዜ መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ ብሎ መምጣት አስቂኝ ነው ። ጎበዝ ከሆኑ መጀመሪያ የራሳቸውን ሕዝብ አያስተምሩም ነበር ? ደግሞ ጥቁር ገነት እንዲገባ አዝነው ? ይኸን ግን ፈለካዊ ምፀት ብለን እናልፈዋለን!'


Forward from: አዲስ ምልከታ🌍
በዚህች ዓለም ላይ አዲስ ነገር የለም። ጠቢቡ ሰሎሞን እንዳለው ከፀሐይ በታች አዲስ ነገር የለም። አዲስ ሀሳብ የለም። ከዚህ በፊት ሰዎች ያላሰቡት ሀሳብ፣ አሁን እኛ የፈጠርነው የለም። ድሮ የነበሩ ሀሳቦች ናቸው ዛሬም ያሉት።

ስለ ህዋና ፕላኔቶች ወዘተ ያሳመኑን በዋናነት ፊልም ሰርተው ነው። ሰዎች ፈጣን መንኩራኩሮች ሰርተው ሲሄዱ፣ ሌሎች ዓለማትን ሲያገኙ፣ በዛ ላይ ኤሊየኖችን ሲያገኙ ወይም እነዛ ኤሊየኖች ሲመጡ የተሰሩ እጅግ በርካታ ፊልሞችን አይተናል። በዚህም ነው ስለ ስፔስ ለማመን የበቃነው።

ነገር ግን እነዚህ ፊልሞች አዲስ ሀሳብ፣ ወይም አዲስ ምናብ (imagination) አላመጡም። ከጥንት የሰው ልጅ ታሪክ የነበሩ ሀሳቦችና ክስተቶችን ነው ቀይረው የስፔስ ፊልም የሰሩበት። እንዴት? የሚለውን እንይ።

👉በፊልሞቹ ሁሌም ሰዎች ፈጣን መንኩራኩሮች ሰርተው እጅግ ሰፊ በሆነው ህዋ ውስጥ ይሄዳሉ።
እነዚህን መንኩራኩሮች ምን ብለው ነው የሚጠሯቸው? Space ship
ship ምንድን ነው? መርከብ። ልክ መርከቦች በሰፊው ውቂያኖስ/ባህር እንደሚሄዱ ሁሉ እነዚህም space-ships "በሰፊው ህዋ" ይሄዳሉ የሚለው ሀሳብ ከሱ ይወሰዳል።

👉 ነጮች በመርከብ እየሄዱ ዓለምን "explore" ሲያደርጉ ወይም ሲያስሱ እንደነበረው ሁሉ እነዚህ ፊልሞች ላይም "space"ን "explore" ያደርጋሉ (ያስሳሉ)።

👉 በመርከብ ሲሄዱ የተለያዩ ደሴቶችን እንደሚያገኙ (discover እንደሚያረጉ) ሁሉ፣ በዚያም የተለያዩ ከነሱ (ከነጮች) የተለየ መልክ አለባበስ፣ አነጋገር ያላቸው ህዝቦች ያጋጥሟቸው እንደነበረ ሁሉ፣ በፊልሞቹ ላይም የተለያዩ ፕላኔቶችን ያገኛሉ (discover ያረጋሉ) በነዚህም ላይ ከነሱ (ከሰው ልጆች) የተለዩ "ኤሊየኖች"ን ያገኛሉ።

👉 በሌላ ጊዜ ደግሞ ሌሎች ህዝቦች መርከብ ሰርተው፣ ባሕር ተሻግረው መጥተው እንደሚወሯቸው ሁሉ፣ በፊልሞቹ ላይም፣ የተለያዩ "ኤሊየን" ወይም "UFO"ዎች "space-ship" ሰርተው በመምጣት ምድርን ይወራሉ።

👉 ከዚህም በላይ፣ ኤሊየኖቹ (UFOዎቹ) ሁሌም ሰውነታቸው አካሎቻቸው የሰው አይነት መልክ ያላቸው ናቸው። እንደ ሰው አይነት ቁመና፣ ሁለት ዓይም፣ ፊታቸው እንደ ሰው ያለ፣ እጅና እግራቸውም ከሞላ ጎደል ከሰው ጋ የተመሳሰለ ነው። እንጂ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ፣ መልኩና ቅርጹ የተለየ፣ በምናባችንም በሀሳባችንም አስበነው የማናውቀውን አይነት ፍጡር አሳይተው አያውቁም።

እንደውም እነዚህ ኤሊየኖች ሰው መምሰላቸው በዙ የሳይንስ ፊክሽን ወዳጆች ያሳስባቸዋል። እናም ኤሊየኖች የሰው መልክ የመምሰላቸውን ክስተት ስም ሰጥተውታል፦ Anthropomorphism ብለው። ቃሉ ሌሎች ክስተቶችንም የሚወክል ቢሆንም ለዚህኛው ዓውድም ይጠቀሙታል።


የጭለማው አለም ሰራተኞች አዲሱ የዓለም ስርአት የሚሉትን ለማምጣት ከጠቀሟቸው እጅግ ወሳኝ ፍልስፍናዎች ውስጥ ተራማጅነት (progressivism) አንዱ ነው። ይህም በጊዜ ሂደት ሰይጣን ያቀበላቸውን ክፉ ሃሳቦች አንዱን በአንዱ ላይ እየደራረቡ በየጊዜው አዳዲስ የከፉ መርዛማ ፍልስፍናዎችን ሰዎች እንዲቀበሉ ያደረጉበት መንገድ ነው።

ይህንን የጀመሩትም በ1789 የፈረንሳይ አብዮት ጊዜ ነው። ለመጀመርያ ጊዜ ዘውዳዊ ስርአትን የገረሰሱበትና "ስር ነቀል" ለውጥ ያመጡበት ጊዜ ነበር። ጊሎቲን የሚባል መሳርያ አዘጋጅተው ንጉሱና ሚስቱን አንገታቸውን በህዝብ ፊት ቆረጧቸው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ፈረንሳይ ፍጹም የተለወጠች ሃገር ነው የሆነችው። ባህሏ፣ ቋንቋዋ፣ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ስርአቷ ጭምር ነበር የተለወጡት። እናም ሊበራሊዝም እና ተራማጅነትን‌/ፕሮግረሲቪዝምን እስከዛሬም እየመሩ ለዓለምም አዳርሰው አሉ። ታድያ አብዮተኞቹ አዲስ ያልተለመዱ ስራቶችን እና ፍልስፍናዎችን ሲያመጡ ተቃውሞ ገጠማቸው። እነዚህም የተወሰኑ የፓርላማ አባላት ነበሩ። አብዮቱን የሚመሩት የፓርላማ አባላትም ከነዚህ የአብዮቱ ተቃዋሚዎች ጋር የስልጣን ፍልሚያ ውስጥ ገቡ። ነገር ግን አሸነፉ።

ታድያ በአጋጣሚ ይሁን ወይም ታስቦበት፣ አብዮቱን የሚመሩት ሰዎች በፓርላማው በግራ በኩል ነበር የሚቀመጡት። አብዮቱን የሚቃወሙት ደግሞ በቀኝ። ከዚህም የተነሳ በግራ የሚቀመጡት "የግራው ክንፍ" (Left Wing) የሚባል ስያሜ ሲሰጣቸው በቀኝ የሚቀመጡት ደግሞ "የቀኝ ክንፍ" (Right Wing) ተባሉ። ይህ አሰያየም እኛ ሀገር ሲመጣ "ግራ ዘመም" እና "ቀኝ ዘመም" ተባለ። ዛሬ ላይ እንደ ኮሚዩኒስት፣ ማርክሲስት፣ ያሉት ቡድኖች ግራ ዘመም ተብለው ይጠራሉ።

ቀድሞ በተጠቀሰው የፖለቲካ ፍልሚያም አብዮቱን የጠነሰሱትና የመሩት ግራ ክንፎቹ አሸነፉ። ቀኝ ክንፎቹንም በጊሎቲኑ መሳርያ አርደው ገደሏቸው። ከዚያም አዲሱን የዓለም ስራት አስጀመሩ። አብዮቱንም በመላው ዓለም አስፋፉ። ወድያው አብዮቶች በብዙ ሀገራት ተስፋፉ። በአሜሪካ፣ በሩስያ፣ በአረቡ አለም፣ በኢትዮጵያ፣ በኢራን ወዘተ። አብዮተኝነት ሰዎች የሚያደንቁት የሚወዱት ተደርጎ ታየ። አብዮተኞችን እንደ ጀግናና ታላቅ ሰው ማየት ተለመደ። እነ ሌኒን፣ እነ ማኦ፣ እነ ቼጉቬራ፣ እነ የኢራኑ ኻሜኒ፣ እንደ ጀግና፣ ታላቅ ሰው፣ ታይተው ክብር አድናቆት ፈሰሰላቸው። ከዛን ጊዜ ጀምሮ ወጣቶች እንደነሱ ለመሆን የሚመኙ የሚሹ ሆኑ።

ግን እውነታው እነዚህ ሰዎች ነው ዎርልድ ኦርደርን ቀስ በቀስ ወደ ዓለማችን ያመጡ ሰዎች ናቸው። ሁሉም ደግሞ የፍሪመሶንሪ አባላት እንደነበሩ እጅግ በዙ መረጃዎችና ማስረጃዎች አሉ። ታድያ ይህን ኒው ወርልድ ኦርደርን የሚያመጡት በሂደት ስለሆነ ያንን ሂድት ደግሞ እንደ ነዳጅ ሆኖ የሚገፋላቸው አስቀድመን ያነሳነው የተራማጅነት ሃሳብ ነው። "ወደፊት እንራመድ፣ አዲስ ለውጥ እናምጣ፣ እኛን የሚቃወሙ ሁሉ እንዲህ እና እንዲያ ናቸው፣ እንዲህ እና እንዲያ የሚሉ ስሞች ለጥፈንባቸው እናሳፍራቸዋለን" እያሉ የሚያምኑበት ሁኔታ ነው።

ይህንን ደግሞ ሲፈጠር አንዱ ፍልስፍናዊ መሰረቱ ከዚህ በፊት በቻናላችን ያነሳነው የ "ወጥ የእምነት ስራት" እሳቤ ነው። በዚህም መሰረት አንድ ሰው አንድን ሃሳብ እንደ ትክክለኛ ከተቀበለ አስተሳሰቦቹና እምነቶቹ ወጥ ይሆኑ ዘንድ የዛን ሃሳብ ምክንያታዊ ድምዳሜም መቀበል ይኖርበታል። ይህንንም እሳቤ እንደ ምሳሌ ለማየት ምድር በቢሊዮን አመታት የአጋጣሚ ሂደት ተፈጠረች፣ ሰውም በሚሊዮን አመታት አጋጣሚዎች ሂደት ከዝንጀሮ መጣ ብሎ ያመነ ሰው፣ የዚህ እምነቱ ምክንያታዊ ድምዳሜ የሆነውን "አስቦና አቅዶ ዓለምን የፈጠረ አካል የለም" የሚለውን ሃሳብም ለመቀበል ይገደዳል። ሰዎች ግን ያንን ሳያደርጉ ይቀሩና የተጣረሱ እምነቶችን ይይዛሉ። ብለን አንስተን ነበር። የዚህም አንዱ መፍትሄ ቀድሞውኑ መነሻ ሃሳቡ ሃሰት እና ስህተት መሆኑን መረዳት እንደሆነ አይተናል።

በተመሳሳይ መልኩም ተራማጅነት እና ሊበራሊዝም ሃሰት እና ከፊል እውነት የሆኑ ሃሳቦችን እየያዘ ይነሳና በሱ ላይም ሌሎች የተሳሳቱ ሃሳቦችን እየጨመር ይመጣል። ለምሳሌ ሁሉም ሰው በኢኮኖሚ እኩል መሆን ይችላል የመደብ ልዩነት መጥፋት አለበት ይልና። ከዚያ ደግሞ አሁን ያለውን የመደም ልዩነት ለማጥፋት ድሃውን ከማሰራት ይልቅ ሃብታሙን ቀምተን እንዳይሰራ ከልክለን ደሃ እናድርገው የሚል ድምዳሜ ላይ ይደርሳል። በሌላ ምሳሌ ደግሞ፣ በጣም አደገኛ የሆነው፣ የሴቶች መብት ነጻነት ይከበር ብለው ይጀምራሉ። ሴቶች አናሳ ቡድን (ማይኖሪቲ) ናቸው የሚል የተሳሳተ ሃሳብ ይዘው ይነሳሉ። ሴቶች አናሳ ቡድን አደሉም፣ እንዲያውም አሁን ዓለም ላይ 55 በመቶ ሴቶች ናቸው። ነገር ግን ተራማጆቹ ይህንን እንደ እውነት ይዘው ይነሱና በዙ ጊዘ ወስደው የሴቶች መብት መከበር ሲጀምር፣ አሁን ደግሞ ግብረሰዶማውያንም አናሳ ቡድን ናቸው የነሱም መብት ነጻነት ይከበር ይላሉ። የመጀመርያውን ሃሳብ የተቀበለ ሰው ወጥ የእምነት ስራት እና የአመክንዮ ስራት (logical consistency) እንዲኖረው በማሰብም እንደ እውነት ይቀበልና (ልክ እግዚአብሄር የለም የሚሉ ሰዎች እንደሚያደርጉት)፣ ከዚያም ግብረሰዶማውያን ተጨቁነዋል ከሌሎቹ እኩል ይሁኑ፣ ጭራሽ የነሱን የተበላሽ ባህሪ ወደ ሌላው እንዲያስተላልፉ ይፈቀድላቸው ይላሉ። ከዚያም አለፍ ይሉና ትራንስጀንደር የተባሉትም እንዲያው ናቸው እነሱም ይፈቀድላቸው ይላሉ። እናም አሁን ያለንበት ላይ ደርሰናል።

ግራ ዘመሞቹ በሚዲያ፣ በትምርት ስራት ውስጥ የበላይነት እንዲኖራቸው፣ ምሁራን ሁሉ ተጠርገው ወደዚያ እንዲገቡ ስለተደረገ፣ ምሁራኑና የሚዲያ ሰዎች ደግሞ ማህበረስብን የሚመሩት እነሱ ስለሆኑ፣ በዚህ መንገድ የጭለማው ሰራተኞች መላውን ዓለም ሙልጭ አርገው ወስደዋል። ይህንን የሚቃወሙ ደግሞ፣ አይ ልክ አደለም የምሉ ደግሞ ስም ተለጥፎባቸው፣ "ወግ አጥባቂ"፣ "አድሃሪ" ወዘተ እየተባሉ። ባሉበት የሚረግጡ፣ ኋላ ቀር እየተባሉ። እንደኛ ደግሞ የነሱን ሴራ የሚያቃልጡት "ሴራ ተንታን" /ኮንስፓይሪሲ ትዮሪስት እየተባልን ስም ተለጥፎብን፣ "በስይማቸው አሳፍራቸው" መርህ ብዙሃኑ ህዝብ የኛ ተቃዋሚ እንዲሆን ተደርጓል። ስዎች በተለይ ብዙሃኑ ከሎጂክ ይልቅ ትርክትን (narrative)፣ ለማብራራት ረጅም ሰአት ከሚወስድ እውነት ይልቅ በአጭር ሰከንድ የሚነገር ውሸትን ስለሚወዱ የጭለማው ሰራተኞችም በዚሁ ተጠቅመው ዓለምን በጃችው አስገብተዋል፣ ተቃዋሚዎቻቸውንም አንድ በአንድ አጥፍተዋል። ነገር ግን በዚሁ አይቀጥልም። የእውነት አምላክ አንድ ቀን ይበቀላቸዋል። ትክክለኛውንም ስርአት በዓለም ላይ ይመልሳል። እነሱንም ስር መሰረታቸው፣ ምልክታቸው እንዳይታይ አድርጎ ከምድር ገጽ ያጠፋቸዋል። ይህ ይሆናል። አይቀርም።


የቅዱስ ጊዮርጊስን ታቦት ተሸክመዉ አድዋ ድረስ በእግራቸዉ ከተጓዙት አባቶች ዉስጥ መምህር ካሳሁን እንግዳ አንዱ ነበሩ!!!


ዓድዋ ከአጼ ምኒሊክ ጎን ሳይለዩ ጦርነቱን በብርታት ቤተክርስቲያንን ወክለው በጸሎት የመሩት ግብጻዊው አቡነ ማቴዎስ።


... የንጉሡ የሣህለ ማርያም (የምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ ለሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይል ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር።

በእውነትም ለተመለከታት ሁሉ እንደ ኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበር እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር። የንጉሡም ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ። ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና የፍየል መንጋ እንዳየ ነብር እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፋት ነበር።

መጽሐፍ ሹመትን ሽልማትን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ አያፈገፍግም ብሎ ተናግሯልና፡፡ በዚያም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ ጳጳሱ አባ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኰሳትና ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምህላ ያደርሱ ነበር።

ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል (እቴጌ፡ጣይቱም) በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር። የጽዮን አገልጋዮችም በእግዚአብሔር የሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር።


የዐድዋ ጦር አሰላለፍ


እንኳን ለአድዋ የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!! አባቶቻችን ትልቅ ዋጋ ከፍለው ነፃ ሀገር ለኛ ያስረከቡበት፣ በየትኛውም ዓለም ፊት ወተን ደረታችንን ነፍተን የምናወራበትን ክብር የሰጡን ቀን ነው። በእምነት በጸሎት በቅዳሴ፣ እግዚአብሔርን ይዘው፣ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተገን አድርገው፤ እርሱም ረድቷቸው ኢትዮጵያን ነፃነቷን ያስጠበቁበት ቀን፤ ለመላው ጥቁር ህዝብ ኩራትና ምሳሌ እንድንሆን፣ በነጮቹም ዘንድ እንደንከበር ያደረጉጓት ቀን ነው።

አንዳንዶች ግን ዛሬ ከንቱ ሆነው፣ የተከፈለውን ዋጋ ዘንግተው ምነው ጣልያን ቀኝ በገዛን ይላሉ። ባርነትን ስለማያውቁ ይመኙታል። ሌላው አፍሪካምኮ ቀኝ ተገዝቷል። ግን ምን የተሻለ ነገር አገኙ? ከኛ የተሻለ ሀብት እድገት የላቸውምኮ። ግን ሀገራቸው ሀብታቸው ሁሉ የነጮች ነው። በእጃችን ያለው ነገር ምን ያህል ዋጋ እንዳለው ስለማይገባን ግን ለፈረንጅ ባርያ መሆንን እንመኛለን። ያሳዝናል።

ግን እኛ የተሰጠንን ክብር እናድንቅ። ቦታም እንስጠው። የተራዳንን እግዚአብሔርን፣ የርሱን አገልጋይ ሰማዕቱን ጊዮርጊስንም እናመስግን። የተከፈለልን ዋጋ እጅግ ውድ ነውና ከልባችን እናስበው።


እስቲ ትንሽ ስለ አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ እናውጋ።

አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ ምንድን ነው ዓላማው? ብዙ ሰዎች እንደ ሰው የሚያስብ አልፎም ከሰው የማሰብ አቅም በላይ ያለው ማሽን ለመፍጠር ነው ይላሉ። ግን አስተውሎ ላሰበ ሰው ይህንን የሚፈጥሩበት በቂ ምክንያት የለም። ግን በሳይንስ ፊክሽን ላደገ ትውልድ ትልቅ ግኝት ወይም የስልጣኔ ጥግ መስሎ ሊታይ ይችላል። ነገር ግን አሁን ያሉ ትላልቅ ይህንን የሚሰሩ ድርጅቶች የሰውን የማሰብ ችሎታ በከፊሉ ለመስራት እንኳ በቢሊዮን እና ትሪሊዮን የሚቆጠር ፈንድ ሲጠይቁ ይታያል። ቃል የገቡትን ውጤት በተግባር ሲያሳዩ ግን አይታይም። ይህ ለምን ይሆን? ብለን መጠየቅ አለብን።

በመሰረቱ አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ እንዴት ነው የሚሰራው? ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ዳታ ሰብስበው "ሞዴል" የሚባለውን ያሰለጥኑታል። ከዚያ ሌላ ዳታ አምጥተው ደግሞ ሞዴሉ በትክክል ይገልጸዋል ወይ‌ ማለትም ምንነቱን በትክክል ለይቶ ያውቃል ወይ የሚለውን ቼክ ያደርጋሉ። ታዲያ መጀመሪያ የሚገባለት ዳታ በበዛ ቁጥር የሞዴሉ ጥንካሬም በዚያው ልክ ይጨምራል። ለዚህ ነው ቻት ጂ ፒ ቲ ጠንካራ የሆነው። መላው ኢንተርኔት ላይ ያለውን፣ እያንዳንዱ ሰው ዌብሳይት ላይ የጻፈውን እና የተናገረውን ሁሉ ሰብስበው በዛ ዳታ ላይ ስላሰለጠኑት ነው አሁን ላይ የሚገርም ብቃት ያየንበት። ከቴክኒካል ነገሮች እስከ ፈተና መልስ፣ እስከ የህይወት ምክር ድረስ ሲሰጥ የታየው ቀድሞውኑ ለነዚህ ነገሮች ሌሎች ሰዎች በኢንተርኔት ላይ ያሰፈሩትን አምጥቶ ስለሚያሳይ ነው። ከኮምፒውተር የሚለየው ደሞ ከዚያ ከባህር የሰፋ መረጃ ውስጥ ለይቶ ሰዎች በጠየቁት ልክ መመለስ መቻሉ ነው።

ይህንን ስናስብ ነው አርቴፍሻል ኢንተልጀንስ ምናልባትም ለምን እንደተፈለገ የሚገባን። አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ ሚሊዮን እና ቢሊዮን ሰዎች ካስቀመጡት ዳታ ውስት አንድ ልዩ ጥያቄ ሲጠየቅ ለዛ መልስ የሚሆውን ከዚያ እንደ ባህር ከሰፋው ዳታው ውስጥ አውጥቶ መመለስ መቻሉ ነው። ልክ አንድ ሰው በአመታት እድሜው ካወቀው እና ከተማርው ውስጥ ሰዎች የጠየቁትን መርጦና ለይቶ እንደሚናገር ማለት ነው። ታዲያ ኮምፒውተሮች ይህ ችሎታ ሲቸራቸው እጅግ አደገኛ ያደርጋቸዋል። እንዴት?

ብዙ ሰዎች አሁን ላይ መረጃቸውን ኢንተርኔት ላይ አስቀምጠዋል። በክፉም በደጉም ብጽሁፍም በቪዲዮም በድምጻቸውም ጭምር አስቀምጠዋል። አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ ደግሞ ይህንን ሁሉ አበጥሮ ዘርዝሮ ማስቀመጥ ይችላል። ስለዚህ ያንን የሚቆጣጠሩ ሰዎች አበበ የሚባል ሰው በጥር 2015 ምን ተናገረ ብለው ቢጠይቁት፣ "መንግስትን የሚተች ነገር ተናገረ" ወይም "ስለ ኮንስፓይረሲ ቲዮሪ እንዲህ እንዲህ ብሎ ጻፈ" ብሎ ሊመልስላቸው ይችላል። ከዚያም፣ ይህ አበበ ምን አይነት ሰው ነው? ባህሪው እንዴት ነው? ብለው ቢጠይቁት፣ "ከሚናገራቸው ነገሮች እና ከሚጽፋቸው ጽሁፎች ተነስቼ ሳይ፣ አበበ ወጣት ወንድ ነው፣ እገር ኳስ ይወዳል፣ ከሙዚቃ ይህ እና ይህ የሙዚቃ አይነት ይመቸዋል፣ የፖለቲካ እይታዎቹ እንዲህ እና እንዲህ ናቸው" ወዘተ ብሎ ሊዘረዝር ይችላል።

ይህን ከማድረግ ምን ይከለክለዋል? ምንም? ብዙ የቻት ጂፒቲ ተጠቃሚዎች ጂፒቲ እስከ ዛሬ ከሱ ጋር ካወሩት ንግግሮች ተነስቶ ስለነሱ ህይወት አብጠርጥሮ እንደሚናገር ያውቃሉ፣ ይህ የአደባባይ ሚስጥር ነው። ታዲያ መንግስታት ይህንን አይነት ቴክኖሎጂ አይጠቀሙም ብሎ ማሰብ የዋህነት አይሆንም? እነ ቻይና ገና ድሮ ይህንን እንደጀመሩ ይታወቃል። ቻይና ራሷን አልፋ መላውን አለም በዚህ አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ እንደምትሰልል ይታወቃል። የዚህ ምርጥ ምሳሌ ቲክቶክ ነው። ቲክቶክ ምን እንደምንወድ ምን እንድምንጠላ በደምብ አብጠርጥሮ ያውቃል። እነ ፌስቡክ ጉግል እና ትዊተርም እንዲሁ።

አሁን ላይ ደግሞ ሌላ አደገኛ ነገር እየተፈጠረ ነው። ትላልቅ የቴክኖሎጂ ካምፓኒዎች ከመንግስታት ጋር ሆነው ህዝብን መግዛት እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ለማሳደር መስራት ከጀመሩ ቢሰነባብቱም አሁን ላይ ግን ግልጽ እየሆነ መጥቷል። "ኦሊጋርኪ" የሚባለው የመንግስት አስተዳደር፣ ፈላስፋው ፕላቶ እንደሚነግረን ጠቂት ሰዎች ያሉበት ስብስብ ሃገርን ሲመራ ነው። አሁን ላይ በተለይ አሜሪካ ወደዛ እየሄደች ነው። እነ ኢሎን ማስክ በግልጽ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቻቸውን ይዘው ወደ ፖለቲካው ገብተዋል። ይህም የአውሬው ሰራተኞች በቴክኖሎጂ ተጠቅመው ዓለምን የመግዛት ህልማቸውን ወይም ቴክኖክራሲ የሚባለውን እያሳኩበት ያለበት መንገድ ነው።

በዚህም እንደ አርቴፊሻል ኢንተልጀንስ ባሉ የተራቀቁ ቴክኖሎጂዎች የዜጎችን እያንዳንዷን እንቅስቃሴ መቆጣጠር፣ መሰለል እና መመዝገብ ላይ ነው። አሁን ላይ ብዙ አይነት አፕሊኬሽኖች አሉ። አንድ ሰው በቀን ስንት ሰአት ተኛ፣ መች ተኝቶ መች ተነሳ፣ በቀን ስንት እርምጃ ተራመደ፣ የት ደርሶ ተመለሰ፣ ሴቶች መች ምች የወር አበባቸውን አዩ ይህንን ሁሉ የሚከታተሉ አፕሊኬሽኖች መጥተዋል። ሰዎችም በገዛ ፈቃዳቸው እንዲህ አይነት የግል መረጃቸውን እንዲሰብስብ አሳልፈው ይሰጣሉ። ታድያ ነገ ላይ ስራአቱ ሲቋቋም ማን እነሱን ይቃወማል? ምን እንደበላህ ምን እንደጠጣህ፣ ምን እንደምትወድ ምን እንደምትጠላ በምን ፍጥነት እንደምትሮጥ ሁሉ ያውቃሉ። የት ታመልጣለህ እንዴትስ ብለህ ታመልጣለህ? እድል የለህማ። ነጻነትህን ቀድመህ አሳልፈህ ሰጥተሃላ!!


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


Forward from: አዲስ ምልከታ🌍
The fact that the globe-universe-heliocentric model is based on unproven claims and explanations, meant that over time there was more and more evidence against it, and the so called scientists continued more and more "plausible" contrived explanations for them. This meant that they created lies upon lies, and that led to a point in the history of science, where only few, bright-minded people could understand it. When in reality, it should have been the opposite, anyone should be able to understand, and challenge these theories. But now they have gotten so complicated and non-common-sensical that it is simply impossible for the average person to engage with them.

Here is one example
- simple lies like newton's gravity, led to the problem of "singularity"
- this meant that the universe should come collapsing together
- but also the observations indicated that it was not the case
- so they created new concepts like dark matter and dark energy, this invisible, un-detectable mysterious thing that keeps the world from collapsing together. But there is no way to prove that it even exists

Another example
- there was a claim that earth moves through space
- but Michelson-morley experiment proved that that is wrong
- So they created new theories "length contraction", "time dilation" etc to explain away why Michelson-Morley experiment was wrong
- Not only is this non-sensical, there was no evidence for it and it was even disproven by the Sagnac Experiment
- On the other hand, Albert Einstein and others claimed that the aether, a form of matter believed to exist above earth, did not exist at all
- This created a big problem. If light is a wave, and it travels through space, then what is the medium
- And here, they created one more false theory: the "wave-particle duality". Now light is both a wave and a stream of particle, so it can move through empty space
- But now which one is it really? Wave or particle? Well it's both, kind of
- well then if it's a wave, how is it's speed constant?

There is just no answer to this. Just more and more nonsense answers that we have to just accept, because brilliant minded scientists told us.

But this is exactly what they were criticizing in religion -- that we were following the words of religious leaders, and trusting their word.

So how is this not hypocrisy?


We reject the premise. And thus the conclusion as well.

The premise is that earth is a spinning ball, flying in empty space, in a random corner of the universe, created by billion years of random events.

The conclusion is that there is no God that intentionally created and designed the world.

We reject the wrong premise, and we prove that it is wrong as well. Therefore we also reject its conclusion and show that it is wrong.

People who accept the premise are pushed/forced to slowly accept the conclusion. And that creates atheists/agnostics/deists over time. Therefore we see an epidemic of Godlessness in our world.

Why do we reject the premise? because we have proofs and evidence against it:
https://t.me/hasabochhh/6683
https://t.me/hasabochhh/6374
https://t.me/hasabochhh/6349
https://t.me/hasabochhh/6350
https://t.me/hasabochhh/6352


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የሜዲቺ ቤተሰብ


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


አበው ስለ እመቤታችን ዕረፍት እንዲህ አሉ

‹ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች 'ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

‹‹ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው … በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው … በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው … በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ … አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት የተለያየ ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ›› ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ (Homily on the Dormition)


በተረፈ ግን፣ እንኳን ለአስተርእዮ ማርያም በዐል በሰላም አደረሳችሁ!!!


ስለዚህ ጉዳይ እንዲብራራ በጠየቃችሁት መሰረት ነገሩን ይበልጥ ለማብራራት እና ረዘም ባለ ጽሁፍም ለማቅረብ ስሞክር ነበር፣ እና የደረስኩበት ነገር ቢኖር ጉዳዩ የተወሳሰበ መሆኑን ነው። በዚህ ቻናልም በኩል ርዕሱን በማስረዳት በኩል ስህተት ተፈጥሯል ስለዚህም ይቅርታ ለመጠየቅ እወዳለሁ።

እንዲሁም ከላይ ሼር የተደረገው ቪድዮ ላይ ያለው ጥንተ አብሶ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ አይደለም የሚለው ሙሉ በሙሉ ትክክል አይደለም። ጥንተ አብሶ ማለት በአጭሩ የቀደመው በደል፣ አዳም እና ሄዋን የሰሩት ሃጢአት ነው። ነገር ግን በነሱ ሃጢአት ምክንያት እኛ ልጆቻቸው የሃጢአቱን ፍዳ ወረስን ወይስ ሃጢአቱንም ጭምር ወረስን የሚለው ጋ ነው ልዩነቱ። በዚህም ካቶሊኮች ሃጢአቱንም ጭምር በውርስ እንደተቀበልን ያስተምራሉ። ይህን አስተምህሮአቸውን ዋና አነሳሽ የሆነው ደግሞ አውግስጢኖስ ነው። ነገር ግን ከአውግስጢኖስ ጋር በተመሳሳይ ጊዜ ወይም ከርሱ በፊት የነበሩት እና ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ቄርሎስ እና ቅዱስ ጎርጎርዮስን ስንመለከት የቀደመው የአዳም ሃጢአት እኛን የወደቀ የተዋረደ ባህሪ እንድንላበስ አደረገን ይላሉ እንጂ የአዳም ሃጢአት እኛም እንዳለብን ወይም እኛ እንደሰራነው ይቆጠራል፣ ወይም እኛም እንጠየቅበታለን አይሉም።

የኛ ቤተክርስቲያን እና የኢርትራ ቤትክርስቲያን አባቶች ስለ ጉዳዩ ምን ይላሉ የሚለውን የተለያዩ ጽሁፎች እንዳየሁት የሚሉት በአዳም እና ሄዋን ሃጢአት ምክንያት እኛ የሃጢአታቸው መዘዝ የሆነው ሞት፣ እና ለሃጢአት የሚያደላው የወደቀው ባህሪ ወረስን የሚለውን አቋም ነው የሚይዙት። ስለዚህ ያ ነው ከካቶሊኮች የሚለየን። ጉዳዩን ይበልጥ ከመዘዝነው ሌላም ብዙ ነገር አብሮት ይነሳል። ለምሳሌ immaculate conception የሚባለው ድንግል ማርያም ያለዚህ የውርስ ሃጢአት ነው የተወለደችው የሚለውን ያነሳሉ።

ነገር ግን ይህ አስተምህሮ በኛ ቤትክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ ውስጥ የሚገኝ አይሆንም። ምክንያቱም መጀመርያም እኛ የአዳምን ሃጢአት ወርሰናል ብለን አናምንም። ይልቁንም ስለ ድንግል ማርያም መወለድ የምናምነው ነገር ቢኖር እኛ ያለንን የጎሰቆለ ባህርይ ይዛ አልተወለደችም፣ እንዲሁም በህግ እና በስርአት፣ ያለ ዝሙት ወይም ስጋ ፈቃድ ተወለደች እንጂ።


ኦሪጂናል ሲን ወይም ጥንተ አብሶ የሚባለው የካቶሊኮች አስተምህሮ ሲሆን የሰው ልጆች በሙሉ የአዳምን እና የሄዋንን ሃጢአት ወርሰናል የሚል ነው። በዚህም ምክንያት ሁላችንም የውርስ ሃጢአት አለብን ይላል። ነገር ግን ይህ አስተምህሮ የካቶሊኮች አስተምህሮ እና የኛ ቤትክርስቲያንም ሆነ የምስራቅ ኦርቶዶክሶች የማያምኑበት የተሳሳተ አስተምህሮ ነው። ይህንን አስተምህሮ ከጀመሩት ውስጥ ደግሞ አውግስጢኖስ አንዱ ነው።

የኛ ቤትክርስቲያን የምታስተምረው አዳም እና ሄዋን በበደሉ ጊዜ ሰውነታቸው መዋቲ፣ ለሃጢአት የተጋለጠ ወይም ሃጢአት ለመስራት ቅርብ የሆነ የተጋለጠ ባህሪን ያዝን የሚለው ነው። ታዲያ ጌታችን ሲወለድ ይህንን የወደቀ ለሃጢአት የተጋለጠ ባህሪ አልያዘም፣ ምክንያቱም እናቱ ድንግል ማርያምም ለዚህ ለሃጢአት የተጋለጠ ባህሪ አልነበራትም ብለን ነው የምናምነው። ለዚህም ነው እመቤታችን ሃሳቧ ሁሉ ስለ እግዚአብሔር የሆነ፣ በስጋም በህሊና(ሃሳብም) ድንግል የሆነች ብለን የምንገልጻት።

ነገር ግን ሰዎች ይህንን አስተምህሮ ያዩና ከጥንተ አብሶ ጋር ያምታቱታል። ነገር ግን ያ ስህተት ነው። ጥንተ አብሶ የሚባለው መጽሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆነ አስተምህሮ ነው።


ምንድነው original sin?

20 last posts shown.