የፍቅረኛሞች ወይስ የዝሙተኞች ቀን?!—————
"
መልከ ጥፉ በስም ይደግፉ" እንደሚባለው ዝሙትን አሰማምረው ስሙን ቀይረው ያበረታታሉ። ነጭ ነጩን ስናወራ ቅር አይበላችሁ!። ሺርኩን ሺርክ ነው፣ ቢድዓውን ቢድዓ ነው፣ ሀራሙ ስሙን ቀያይሮ ሲመጣም ሀራም ነው ስንል ቅር ሊላችሁ አይገባም!፣ እውነታውን መቀበል ነው። የዝሙተኞችን ቀን ስሙን ቀያይረው የፍቅረኛሞች ቀን ቢሉ ያው በኒካህ ያልተሳሰሩ ተቃራኒ ፆታዎች “
ያለ ኒካህ የተፋቀርንበትን ቀን ታሳቢ አድርገን አብረን እንዝናና አብረን እንደር” ተብሎ ዚና የሚሰራበት በዚህ አመለካከት ለተዘፈቁ ሰዎች የዝሙተኞች ቀን እንጂ የተለየ ነገር የለውም።
ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች “
የዚና ቀን ለማለት ይከብዳል” በማለት ድክም ያለች ምክንያት ያነሳሉ፣ ምክንያታቸውም "
ተፋቅረው ወደ ኒካህ የሚሄዱ አሉ፣ ስለዚህ ያንን ቀን ቢያከብሩት ምንችግር አለው?!" የሚሉና ሌሎችንም መሰል ምክንያቶች የሚያነሱ አይጠፉም። ሲጀመር ከኒካህ በፊት መፋቀር ሚባል ነገር የለም!። እስቲ የሚከተሉትን ነጥቦችን እንመልከት:-
①, ቀኑ ስያሜውን ያገኘውና መከበር የጀመረው በማን እና መቼ ነው? ካልን፣ ያው በከሀዲ ፈረንጆችና በዝሙተኞች ከሚል መልስ የተለየ ነገር አናገኝለትም። ሌሎችም በነሱ ቀንተው ነው “ፍቅረኛዬ” ወይም ሴትና ወንድ ሆነው እያለ “ጓደኛዬ” በሚል ስም በዝሙት ሲንዘላዘሉ ቆይተው መጀመሪያ የተገናኙበት ቀን ታሳቢ በማድረግ ይህን ቀን የሚያከብሩት። ይህ ታዲያ የዝሙተኞች ቀን ለመሆኑ ዋና ማሳያ ነው።
②, በእለቱ በተለየ መልኩ ወጣቱን ለዝሙት ይበልጥ የሚያነሳሱ ተግባሮች ይከናወኑበታል። በማህበራዊና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን እያነሱ ወጣቱን ትዳር ከሚባለው ነገር አርቀው “
ፍቅረኛሞች” በሚል የዝሙት ህይወት እንዲኖር ያበረታቱታል።
③, በስርኣቱ ሸሪዓ እንደሚያዘው ኒካህ አድርገው ቢሆን ኖሮ የኒካህ ቀን ብለው ነበር የሚሰይሙት እንጂ የፍቅር ቀን ብለው አይሰይሙትም ነበር፣ ምክንያቱም በእስልምና መፋቀር ከኒካህ በኋላ ነው። ይህም ቢሆን እስልምና እውቅና ያልሰጠው ሌላኛው የቢድዐ ተግባር ሆኖ ሀራም ይሆናል።
④, ሌላው የጀመሩት አይሁዶች እና ክርስቲያኖች ናቸው። በአይሁድና ክርስቲያን መመሳሰል ደግሞ ወንጀሉ የከፋ ነው። ነቢዩ (
ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) "
በሰዎች የተመሳሰለ ሰው እርሱ ከነርሱ ነው" ብለዋል። ሰዎች ማለት አይሁድና ክርስቲያኖች ማለት ነው።
⑤, ሰዎች ከትዳር ርቀው "
ፍቅረኛዬ፣ ወንዱ ሴት ጓደኛዬ፣ ሴቷም ወንድ ጓደኛዬ" እየተባባሉ በዝሙት እንዲቆዩ ለዝሙትና ለዚህ ሸሪዓን ለጣሰ ግንኙነት እውቅና መሰጠትም ነው። በሸሪዓችን ያለ ኒካህ የተቃራኒ ፆታ ጓደኝነት የሚባል ነገር ሀራም (ክልክል) ነው!!
እንዲህ ያሉ ከባባድ ወንጀሎችን ምንም ያህል ስማቸውን እየቀያየሩ የተፈቀዱ በማስመሰል ሙስሊሙ ዘንድ ቢያቀርቧቸውም፣ ያው ወንጀል ከመሆናቸውና ሀራም ከመሆናቸው የሚቀየሩ ነገር የለም።
የአላህ መልእክተኛ (
ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ስለ አስካሪ መጠጥ ሲናገሩ "
ያለ ስሙ ይጠሩታል…" ብለው ነበር፣ እንዳሉትም አስካሪ መጠጦች ስማቸው እየተቀያየረ ብቅ ሲሉ ዓሊሞች ደግሞ "
ስሙ ቢቀያየርም እውነታውን አይቀይርም" እያሉ ሀራምነቱን ለአማኙ ማህበረሰብ ግልፅ እያደረጉ ሙስሊሙም እየተጠነቀቀ ቀጥሏል። ልክ እንደ አስካሪ መጠጡ ሌሎች ከባባድ ወንጀሎችንም ስማቸውን እየቀያየሩ ያለ ስማቸው ቢጠሯቸውም ልንሸነገል አይገባም።
የእስልምና እና የሙስሊሙ ጠላቶች ሙስሊሙ ማህበረሰብ ፈፅሞ የማይደራደርባቸውና እውቅና ሊሰጣቸው የማይችልባቸውን ከባባድ ወንጀሎችን ስማቸውን ቀያይረው እያመጡ በእስልምና ዘንድም እንደ ሀላል (የተፈቀዱ) ለማስመሰል ይሞክራሉ። ይህን ጊዜ ሙስሊሙ ነቅቶ "
የስም መቀያየር እውነታን ሊቀይር አይችልምና" ሀራሙን ሀራም ነው እምነታችን አይፈቅደውም ሊላቸው ይገባል።
በምንም አቅጣጫ ከሀዲዎች ቆሻሻና የሸሪዓችን እሴቶችና ድንቅ የሆኑ ስነ-ምግባሮችን ሊንዱብን የሚችሉ ባህላቸውን እኛ ላይ እንዲጭኑብን ልንፈቅድ አይገባም!። በተቃራኒ ፆታዎች ግኑኙነት ዙሪያ የሙስሊሙ ትክክለኛው እምነት፣ ባህልና እሴት ሴትን ልጅ ፍቃደኝነቷ ከተረጋገጠ በኋላ በኒካህ ከሀላፊዎቿ ወስዶ በማግባት በትክክለኛ ውዴታ ተንከባክቦ እያኖሩ ጥሩ ትውልድን ማፍራት ነው።
አላህ ዝሙትን ከሌሎች ከባባድ ወንጀሎች በተለየ መልኩ "ዝሙትን አትቅረቡት!!" ብሎ በሩቁ ነው ያስጠነቀቀው። ይህ ማለት ወደ ዝሙት መጓዝ ይቅርና ጭራሹኑ ወደ ዝሙት መዳረሻ የሆኑ ነገሮች በጠቅላላ የተከለከሉ (ሀራም) ናቸው ማለት ነው።
የዝሙተኞችን (የፍቅረኛሞችን) ቀን እንጠየፍ‼
ሙስሊም የዝሙተኞችን ቀን አያከብርም‼
ለዝሙተኞች ቀንም እውቅና አይሰጥም‼።
✍🏻ኢብን ሽፋ (
t.me/ibnshifa)
የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join አድርገው ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifahttps://telegram.me/IbnShifa