[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ!
በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ!
ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ!
ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የፍቅረኛሞች ወይስ የዝሙተኞች ቀን?!
—————
"መልከ ጥፉ በስም ይደግፉ" እንደሚባለው ዝሙትን አሰማምረው ስሙን ቀይረው ያበረታታሉ። ነጭ ነጩን ስናወራ ቅር አይበላችሁ!። ሺርኩን ሺርክ ነው፣ ቢድዓውን ቢድዓ ነው፣ ሀራሙ ስሙን ቀያይሮ ሲመጣም ሀራም ነው ስንል ቅር ሊላችሁ አይገባም!፣ እውነታውን መቀበል ነው። የዝሙተኞችን ቀን ስሙን ቀያይረው የፍቅረኛሞች ቀን ቢሉ ያው በኒካህ ያልተሳሰሩ ተቃራኒ ፆታዎች  “ያለ ኒካህ የተፋቀርንበትን ቀን ታሳቢ አድርገን አብረን እንዝናና አብረን እንደር” ተብሎ ዚና የሚሰራበት በዚህ አመለካከት ለተዘፈቁ ሰዎች የዝሙተኞች ቀን እንጂ የተለየ ነገር የለውም።

ምናልባትም አንዳንድ ሰዎች “የዚና ቀን ለማለት ይከብዳል” በማለት ድክም ያለች ምክንያት ያነሳሉ፣ ምክንያታቸውም "ተፋቅረው ወደ ኒካህ የሚሄዱ አሉ፣ ስለዚህ ያንን ቀን ቢያከብሩት ምንችግር አለው?!" የሚሉና ሌሎችንም መሰል ምክንያቶች የሚያነሱ አይጠፉም። ሲጀመር ከኒካህ በፊት መፋቀር ሚባል ነገር የለም!። እስቲ የሚከተሉትን ነጥቦችን እንመልከት:-

①, ቀኑ ስያሜውን ያገኘውና መከበር የጀመረው በማን እና መቼ ነው? ካልን፣ ያው በከሀዲ ፈረንጆችና በዝሙተኞች ከሚል መልስ የተለየ ነገር አናገኝለትም። ሌሎችም በነሱ ቀንተው ነው “ፍቅረኛዬ” ወይም ሴትና ወንድ ሆነው እያለ “ጓደኛዬ” በሚል ስም በዝሙት ሲንዘላዘሉ ቆይተው መጀመሪያ የተገናኙበት ቀን ታሳቢ በማድረግ ይህን ቀን የሚያከብሩት። ይህ ታዲያ የዝሙተኞች ቀን ለመሆኑ ዋና ማሳያ ነው።

②, በእለቱ በተለየ መልኩ ወጣቱን ለዝሙት ይበልጥ የሚያነሳሱ ተግባሮች ይከናወኑበታል። በማህበራዊና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች የተለያዩ አጋጣሚዎችን እያነሱ ወጣቱን ትዳር ከሚባለው ነገር አርቀው “ፍቅረኛሞች” በሚል የዝሙት ህይወት እንዲኖር ያበረታቱታል።

③, በስርኣቱ ሸሪዓ እንደሚያዘው ኒካህ አድርገው ቢሆን ኖሮ የኒካህ ቀን ብለው ነበር የሚሰይሙት እንጂ የፍቅር ቀን ብለው አይሰይሙትም ነበር፣ ምክንያቱም በእስልምና መፋቀር ከኒካህ በኋላ ነው። ይህም ቢሆን እስልምና እውቅና ያልሰጠው ሌላኛው የቢድዐ ተግባር ሆኖ ሀራም ይሆናል።

④, ሌላው የጀመሩት አይሁዶች እና ክርስቲያኖች ናቸው። በአይሁድና ክርስቲያን መመሳሰል ደግሞ ወንጀሉ የከፋ ነው። ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) "በሰዎች የተመሳሰለ ሰው እርሱ ከነርሱ ነው" ብለዋል። ሰዎች ማለት አይሁድና ክርስቲያኖች ማለት ነው።

⑤, ሰዎች ከትዳር ርቀው "ፍቅረኛዬ፣ ወንዱ ሴት ጓደኛዬ፣ ሴቷም ወንድ ጓደኛዬ" እየተባባሉ በዝሙት እንዲቆዩ ለዝሙትና ለዚህ ሸሪዓን ለጣሰ ግንኙነት እውቅና መሰጠትም ነው። በሸሪዓችን ያለ ኒካህ የተቃራኒ ፆታ ጓደኝነት የሚባል ነገር ሀራም (ክልክል) ነው!!

እንዲህ ያሉ ከባባድ ወንጀሎችን ምንም ያህል ስማቸውን እየቀያየሩ የተፈቀዱ በማስመሰል ሙስሊሙ ዘንድ ቢያቀርቧቸውም፣ ያው ወንጀል ከመሆናቸውና ሀራም ከመሆናቸው የሚቀየሩ ነገር የለም።

የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ስለ አስካሪ መጠጥ ሲናገሩ "ያለ ስሙ ይጠሩታል…" ብለው ነበር፣ እንዳሉትም አስካሪ መጠጦች ስማቸው እየተቀያየረ ብቅ ሲሉ ዓሊሞች ደግሞ "ስሙ ቢቀያየርም እውነታውን አይቀይርም" እያሉ ሀራምነቱን ለአማኙ ማህበረሰብ ግልፅ እያደረጉ ሙስሊሙም እየተጠነቀቀ ቀጥሏል። ልክ እንደ አስካሪ መጠጡ ሌሎች ከባባድ ወንጀሎችንም ስማቸውን እየቀያየሩ ያለ ስማቸው ቢጠሯቸውም ልንሸነገል አይገባም።

የእስልምና እና የሙስሊሙ ጠላቶች ሙስሊሙ ማህበረሰብ ፈፅሞ የማይደራደርባቸውና እውቅና ሊሰጣቸው የማይችልባቸውን ከባባድ ወንጀሎችን ስማቸውን ቀያይረው እያመጡ በእስልምና ዘንድም እንደ ሀላል (የተፈቀዱ) ለማስመሰል ይሞክራሉ። ይህን ጊዜ ሙስሊሙ ነቅቶ "የስም መቀያየር እውነታን ሊቀይር አይችልምና" ሀራሙን ሀራም ነው እምነታችን አይፈቅደውም ሊላቸው ይገባል።

በምንም አቅጣጫ ከሀዲዎች ቆሻሻና የሸሪዓችን እሴቶችና ድንቅ የሆኑ ስነ-ምግባሮችን ሊንዱብን የሚችሉ ባህላቸውን እኛ ላይ እንዲጭኑብን ልንፈቅድ አይገባም!። በተቃራኒ ፆታዎች ግኑኙነት ዙሪያ የሙስሊሙ ትክክለኛው እምነት፣ ባህልና እሴት ሴትን ልጅ ፍቃደኝነቷ ከተረጋገጠ በኋላ በኒካህ ከሀላፊዎቿ ወስዶ በማግባት በትክክለኛ ውዴታ ተንከባክቦ እያኖሩ ጥሩ ትውልድን ማፍራት ነው።

አላህ ዝሙትን ከሌሎች ከባባድ ወንጀሎች በተለየ መልኩ "ዝሙትን አትቅረቡት!!" ብሎ በሩቁ ነው ያስጠነቀቀው። ይህ ማለት ወደ ዝሙት መጓዝ ይቅርና ጭራሹኑ ወደ ዝሙት መዳረሻ የሆኑ ነገሮች በጠቅላላ የተከለከሉ (ሀራም) ናቸው ማለት ነው።

የዝሙተኞችን (የፍቅረኛሞችን) ቀን እንጠየፍ‼
ሙስሊም የዝሙተኞችን ቀን አያከብርም‼
ለዝሙተኞች ቀንም እውቅና አይሰጥም‼።
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join አድርገው ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


Forward from: [ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]
እውቀት ከመፈለግ የምንብቃቃው መች ነው?
———
ኢማሙ አሕመድ (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይሉ ነበር:-

«እኔ ቀብር እስከምገባ ድረስ እውቀትን እፈልጋለሁ።» [መናቂቡል ኢማሙ አሕመድ 1/37]

ኢማሙ አሕመድ (ረሂመሁላህ) ይህን ካሉና ከዒልም ካልተብቃቁ እኔስ? አንተስ? ማን ነህ?? ማነሽ??

ይልቅ የተማርከውን አስተምር እንጂ ከዒልም የሚብቃቃ እንደሌለ እወቅ!!

✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join ያድርጉና ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


Forward from: مدرسة الإصلاح (አል ኢስላሕ መድረሳ)
🚎  ሀገር አቀፍ ታላቅ የዲን ኮንፈረንስ የፊታችን ጁመአ ጀምሮ  በሚደረገው ፕሮግራም ላይ
ከአዲስ አበባ ብቻ መሳተፍ ለምትፈልጉ በነዚህ ስልክ ቁጥሮች በመደወል ፕሮግራም መያዝ ትችላላቹ

✅ ፉሪ ፣ ኬንቴሪ ፣ ሰበታ  ለምትገኙ 0941058157

✅ አለም ባንክ ፣ ስልጤ ሰፈር ፣ ቤተል ለምትገኙ +251936985302

✅  መላው አዲስ አበባ  ለምትገኙ

0935008988

👉 ማሳሰቢያ ቀለል ያለ የማደሪያ ልብስ  መታወቂያ መያዣቹን አትርሱ


🔴 የመነሻ ሰአት ጁመአ ከቀኑ 3 :00 ይሆናል

https://t.me/medresetulislah


🏝 ልዩ ሀገር አቀፍ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም

👉 በአላህ ፈቃድ የዲን ትምህርት ድግስ ከቀን 07/06/2017 የጁመዓ ኹጥባ እና ሶላት ጀምሮ  ለተከታታይ 3 ቀናቶች ተዘጋጅቷል።

 🏞 ቦታሌራ ከተማ በኢማሙ አህመድ መስጂድ እና መድረሳ ተሰናድቶ ይጠብቃችኋል።

🪑 በዝግጅቱ ላይ ከሚገኙ ውድና ብርቅዬ መሻይኾች መካከል፦
🎙 አሸይኽ ዐብዱልሐሚድ  ያሲን (ከለተሞ)
🎙 አሸይኽ ሙሐመድ ሀያት (ከወሎ ሐራ)
🎙 አሸይኽ ሙሐመድ ጀማል (ከኮምቦልቻ)
🎙 አሸይኽ ሙባረክ አልወልቂጢይ (ከቀቤና)
🎙 አሸይኽ አብድል ከሪም (ከኦሮሚያ ጅማ)
🎙 አሸይኽ መህቡብ (ከሳንኩራ)     
🎙 አሸይኽ አህመድ ወሮታ (ከጎንደር)
🎙 አሸይኽ አወል (ከዳሎቻ)

በተጨማሪም በቀጥታ ስርጭት
🎙 አሸይኽ ሁሴይን መሀመድ (ከሳዑዲ አረቢያ)
🎙 አሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን (ከሳዑዲ አረቢያ)
🎙 አሸይኽ ሀሰን ገላው (ከባህር ዳር)
🎙 አሸይኽ ዩሱፍ አህመድ (ከባህር ዳር)

👉 እንዲሁም የተለያዩ በርካታ ኡስታዞች ከየ አቅጣጫው የሚታደሙበት ደማቅ ፕሮግራም ነው።

👉 ከሚሰጡ ኮርሶች መካከል፦
📚 شُروطُ الصَّلاةِ وَواجِباتُها وَأركانُها
📚 የሶላት መስፈርቶች ማዕዘናቶቿ እና ግደታዎቿ

📝 للشـيخ محمد بن عبد الوهاب النجدي
🎙 በሸይኽ አብዱልሐሚድ ብን ያሲን አል`ለተሚይ
       
የሀቅ ወዳጆች ሁሉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል እንዳትቀሩብን!

ማሳሰቢያ፦ ሁላችሁም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ እና የማታ ልብስ እንዳትዘንጉ።

አላህ ካለ ሩቅ ላላችሁ 𝙡𝙞𝙫𝙚 ላይ እናካፍላችኋለን
         ➘➘➘➘ 
https://t.me/AbuImranAselefy

https://telegram.me/IbnShifa

🔎 ሸር በማድረግ ለሰለፍዮች በሙሉ የማድረስ ሀላፊነታችንን እንወጣ


Forward from: Sheik Abuzar Hassen Abu tolha
ስለ ፆም 7⃣0⃣ ጠቃሚ ነጥቦች.pdf
481.5Kb
↪️ ስለ ፆም 70 ጠቃሚ ነጥቦች
↩️ سبعون مسألة في الصيام

ትርጉም፦
📖 በሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን አቡ ጦልሃ አላህ ይጠብቃቸው
📚 للشيخ أبي طلحة أبي ذر بن حسن الولوي «حَفِظَهُ اللَّهُ»

በዚች መልዕክት የሚከተሉት ነጥቦች ተዳሰዋል:-
✔️ የፆም ትሩፋት

✔️ የፆም ስርዓቶች እና ሱናዎች

✔️ የፆም ህጎች
  => ጉዞ ላይ መፆም
  => የበሽተኛ ፆም
  => የሽማግሌ የደካማ እና የአዛዉንት ፆም
  => ለመፆም ኒያ ማድረግ
  => ማፍጠር እና መከልከል
  => ፆምን የሚያበላሹ ነገሮች
  => ሴቶችን የሚመለከቱ የፆም ህጎች

አንብቡት ትጠቀሙበታላችሁ!!!

https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha


🔰አዲስ🔰

አስደሳች ዜና
አሰላሙ ዐለይኩም ወረህመቱሏሂ ወበረካቱሁ
ውድና የተከበራችሁ ስለዚህ ርዕስ መች ነው ሚወራው ስትሉ የነበራችሁ ሀቅ ፈላጊያን በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ፣
እነሆ ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ልዩ የኮርስ ፕሮግራም ተደግሶና ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል
ስለሆነም ከአሁኑ ጀምራችሁ ወደ ግሩፑ ገብታችሁ ጆይን በማለትና ለሌሎችም በማካፈል ማስታወቂያውን በመልበስ ይህንን የመሰለ ፕሮግራም ለመላው ሙስሊም ማድረስ ይጠበቅባችኋል

📡ርዕስ የሙመዪዖች ጥመትና ድሮ የነበሩበት ሀቅ

🎙ተጋባዡ እንግዳችን ተወዳጁና ታላቁ ሙብተዲዖችን በማንኮታኮት የሚታወቁት ሸይኻችን ሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን ኮምቦልቻ

📡በኢሞ ሩም የሩሙ ስም የአህባሾች ጥመት
🔷هدم جماعة الأحباش
🔷ጀማዐተል አህባሽን ማፍረስ"

ሊንኩ ያልሰራላችሁ ይህንን ቁጥር ሴቭ በማድረግ ከውስጥ ሊንኩን መጠየቅ ትችላላችሁ
👇
0954682617

⏰ የሚጀመርበት ሰዓት በኢትዮ 3:00 በሱዑዲያ 9:00 በኢማራት ዱባይ 10:00

የኢሞው ሊንክ👇
https://imo.onelink.me/RAdY?af_dp=imo%3A%2F%2Fuser.voiceroom.join%2Fmy.0f2q1mmec4yw8iew%3Fentry_type%3Dshare&af_web_dp=https%3A%2F%2Fimo.im&from=copy_link


Forward from: Abu abdurahman
ልዩ የዳዕዋ እና የኮርስ ፕሮግራም

    ነገ እሮብ የካቲት 5/2017 በስልጤ ዞን በሲልጢ ወረዳ በአንሸቤሶ ቀበሌ በፉፋሌ መንደር ለየት ያለ የሙሐደራ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል ።
    
በእለቱ የሚቀርበው ፕሮገራም

① ተውሒድ ትልቁ የአሏህ ሀቅ

② ሱና እና ፀጋዎቿ

③ ወጣትነት በኢስላም

④ ሰላት እና አሳሳቢነቷ

⑤ረመዷንን እንዴት እንቀበለው


በተጨማሪ (ዛዱ አዳኢያቲ ኢለሏህ) በሚል ኮርስ የሚቀርብ ይሆናል ኢንሻአሏህ

https://t.me/abuabdurahmen


Forward from: የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ
አጅዊበቱል_ሙፊዳህ_በሸይኽ_ዩሱፍ_አህመድ.apk
592.5Mb
「📲አዲስ አፕ | ተለቀቀ

╭┈⟢
│📚አጅዊበቱል ሙፊዳህ الاجووبة المفيدة
╰─────────────────╯   
╭🎙የደርሱ አቅራቢ:-
├─┈┈┈
│✑ሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ሃፊዘሁላህ
╰──────────────
╭⧿⧿⛉
┝ለሌሎችም ሼር በማድረግ የአጅሩ
│          📲  ተካፍይ ይሁኑ!
│──────────
│    📨 መሰል ቂራአት አና ሙሀደራወቸ │ለማሰራት 
│ሚከተልውን አድራሻ ይጠቀሙ 
│              👇👇│👇👇
│     @selfy_app_developer
╰───────────
╭╼╺╼╺╼╺╼╺╼ ╺╼╺╼
┢⎘  ለመሰል ስራዎች ይቀላቀላሉን

┡🖇 https://t.me/safya_app
╰─╼╺╼╺╼╺╼╺╼╺╼╺╼


قال الشيخ الدكتور حسين بن محمد حفظه الله
نعوذ بالله من الحور بعد الكور  وهل تغير أصحاب المركز مما ذكرته هنا قبل أن تنتكس؟ بل زاد شرهم  وعداوتهم للسلفيين وهذا ظاهر لكل عاقل منصف فلله الحمد.                        وهذا جزاء الرويبضة  رويبضة الانترنت وجزاء من لم يترب على كتب السلف وعلى علماء السنة وهذا التقلب والتلون دليل على أن المميعة سفهاء الأحلام مع ضحالة العلم والتعجل وإنما ينتصرون لأنفسهم وينتقمون لأجلها .  لا سيما ابن منور حاطل ليل لا يميز الغث من السمين ونقل شبهات شيوخ المميعة علي الحلبي وأبي الحسن المأربي لكن رد الله كيده ومكره بفضله ورحمته (ولا يحيق المكر السيئ إلا بأهله) والعجب من المخدوعين بهؤلاء المميعة بل ممن يدافع عنهم من الحمقى والمغفلين.  اللهم ثبتنا على الإسلام والسنة حتى نلقاك.


💧ትናንትና ባስጠነቀቁት ነገር ላይ
ዛሬ የወደቁ ጉዶች
      ክፍል 11

👉 ኢብኑ ሙነወር ድሮ በዚህ መልኩ ሙመዪዓዎችን ያስጠነቅቅ ነበር:-
እስኪ አዳምጡት ከራሱ አንደበት


📮 ኢኽዋን ሲዘፍን ከለጨበጨብኩኝ ብሎ መነሳቱን ምን አመጣው? ምንድነው እዚህ መድረሱ?...
በልክህ አቶንም?


⚠️ ጎን ለጎን ተያይዘህ አብረህ
ምትታየው ለምንድነው?
አብረህ መፈክር ምታሰማው ምንድነው?
አብረህ አንድ ነን የምትለው ምንድነው?
አንድ ነህ? ይህ ከሆነ እዛው እነስጠጋሃለን።


ምንድነው የፈለግከው? እውነት አንድ ነህ?.. ከኢኽዋንጋ አንድ ነን?
በዲን እኮ ነው እየቀለዱ ያሉት

⚠️ ስለ ኢኽዋን ለምን ዝም አላቹ ስንል የት ነበራቹህ? ለምን ትከፋላቹህ
ከአመት አመት ሰለፊያን እያጠለሹ አይደለም ኢኽዋኖች ?

⚠️ ኢኽዋኖች አሁን እንኳ ትንሽ ቆም ብለዋል ስራቸው በሌላ አካል እየተሰራላቸው ነው ።

👉 ስለሆነም ኢኽዋን ትቶናል እኮ አሁን ....

⚠️ልክ እንደ ኢኽዋኖች ዛሬ በሰለፊያ ካባ ሆኖ ክስተቶችን ለመጠቀም አኮብኩቦ ተጠባብቆ እያንደንዷን ነገር ለመጠቀም የተዘጋጀ አካል አለ።

ይህ የኢብኑ ሙነወር አቋም ዛሬ የት አለ?
የለም ለዛም ነው ሰከን ብላችሁ ወደ ጤናችሁ ወደ ድሮው አቋማቹህ ብትመለሱ ይበጃል የምንለው ።
  ✍ አቡ ያሲር ኢብን ሙዘይን!
https://t.me/YusufAsselafy

http://t.me/aredualelmumeyia
http://t.me/aredualelmumeyia





















20 last posts shown.