Posts filter




እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ባህልን ከመጠበቅና ከማልማት አንጻር በርካታ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑ ተገለጸ፡፡
--------------
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከለያቸውና በትምህርት ሚኒስቴር ከጸደቁት አራት የትኩረት መስኮች መካከል አንዱ የአገው ባህል ቋንቋ እና ታሪክ ሲሆን ባህልን ለማልማትና ለመጠበቅ በዩኒቨርሲቲው በኩል በርካታ ሥራዎች እየተከናኑ እንደሚገኙ የዩኒቨርሰቲው የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን(ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

ከእነዚህም መካከል በየዓመቱ የሚከበረውን የአገው ፈረሰኞች ማህበር በዓለም አቀፍ ደረጃ የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ማስተዋወቅ ሲሆን አስፈላጊ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ “የአገው ፈረስ ባህል” በሚል ብሄራዊ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ ማድረግ ተችሏል፡፡
በዚህ ዓመት በተከበረው 85ኛው የአገው ፈረሰኞች በዓል ዋዜማ በተዘጋጀው ሲምፖዚየም ላይ የአገው ፈረሰኞች በዓል በዓለም አቀፍ ቅርስነት በማስመዝገብ ሂደት ያለበትን ሁኔታ የሚያሳይ ዳሰሳ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጋርዳቸው ወርቁ (ዶ/ር) የቀረበ ሲሆን “አሱሪቴ” በተሰኘው ባህላዊ ትውን ጥበብ ላይ በመ/ር ብርሃኑ አሳየ እና በመ/ር ብርሃኑ ማተቤ እንዲሁም የባኩሳ ብሔራዊ ፓርክ ያለበትን ሁኔታ የሚያሳይ ጥናት ደግሞ በመ/ር እውነቱ ታዘበው (ዶ/ር) ቀርቧዋል።
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0GTaQNkyDVVFDFd2EUe1bNveGtatMy9G961fFQVnurthTohYEfCkN7AsGC9Uwqfxxl/?app=fbl


የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በታላቅ ድምቀት ተጠናቀቀ።

ጥር 27/2017 ዓ፣ም፤አዲስ አበባ

"ስፖርት ለአንድነት እና ለጋራ ዕድገት"በሚል መሪ ቃል አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከጥር 17-27 /2017 ዓ፣ም ሲካሄድ የቆየው የኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የስፖርት ፌስቲቫል ዛሬ ሲጠናቀቅ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ  በአጠቃላይ ውጤት 9ኛ ሆኖ አጠናቋል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በዚህ ፌስቲቫል በ4 የስፖርት አይነቶች ማለትም በእግር ኳስ፣በአትሌቲክስ፣በወርልድ ቴኳንዶ እና በባህላዊ ስፖርት ተሳትፎ በባህላዊ ስፖርት ቡብ ጨዋታ ዋንጫ እና ማዳሊያ በማግኘት አንጋፋ እና ነባር ዩኒቨርሲዎችን በመፎካካር በውድድሩ  ከ49 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች 9ኛ ሆኖ በማጠናቀቅ ስኬታማ ውድድር አሳልፏል።
ይህ ውጤት ከ4ኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች ቀዳሚ ሲያደርገው በአማራ ክልል ከሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ከወልዲያ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲዎች በቁጥር 3ተኛ ደረጃ ላይ ሆኖ አጠናቋል  ።
የዚህ ስፖርት ፌስቲቫል አጠቃላይ አሸናፊ እና የዋንጫ ተሸላሚ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን የፀባይ ዋንጫ አዲግራት ዩንቨርሲቲ ወስዷል ።
በፌስቲቫሉ በባህላዊ ስፖርት ቡብ ጨዋታ ሴት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፣በቡብ ወንድ ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ፣በገበጣ ሴት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፣በገበጣ ወንድ ወልዲያ ዩንቨርሲቲ ፣ ፣በወርልድ ቴኳንዶ  ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ፣በእግር ኳስ ወሎ ዩንቨርሲቲ፣በቼዝ ሴት አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣በቼዝ ወንድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣አትሌቲክስ ወንድ ሀረሚያ ዩኒቨርሲቲ እና አትሌቲክስ ሴት የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ  የዋንጫ አሸናፊ ሆነዋል።


ያለህን ዕምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!


“የኢትዮጵያ ህብረብሔራዊ አንድነት ግንባታ ተሞክሮና ተግዳሮት” በሚል ርዕስ ሴሚናር ተካሄደ፡፡

ጥር 27/2017 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በታሪክና ቅርስ አስተዳደር ትምህርት ክፍል “የኢትዮጵያ ህብረብሔራዊ አንድነት ግንባታ ተሞክሮና ተግዳሮት” በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሴሚናር ውይይት ተካሄዷል፡፡

የውይይት መነሻ ጽሑፉን ያቀረቡት የወሎ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ አለማየሁ እርቅይሁን (ዶ/ር) ሲሆኑ ኢትዮጵያ በመንግስት መዋቅር ስትመራ ቀደምት ሀገር መሆኗን ጠቅሰው ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ብሔርን ያማከለ መንግስት ለመገንባት በሚደረገው ሂደት የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመጠቀም የአንዳንዶችን መብት የሚጥስ ድርጊት ይፈጸማል ብለዋል፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ብዝሀነትን የምታስተናግድበት መንገድ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን አንስተው በህብረ ብሄራዊ አንድነት እና ግንባታ ሂደት መፍትሄ ያሏቸውን ሃሳቦችንም ጠቁመዋል፡፡

በሴሚናሩ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) የኢትዮጵያን ህረብሔራዊ አንድነት ግንባታ በአተገባበር ላይ የምሁራን ድርሻ በእንዲህ አይነት ትምህርታዊ ጉባኤዎች የኢትዮጵያዊያን አንድነትን የሚያጠነክሩ ጉዳዮችን ማምጣት ይጠበቃል ብለዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት ውይይትና ምሁራዊ እይታን ወደ መድረክ ማምጣት ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ ነውም ብለዋል፡፡

በሴሚናሩ መምህራን እና ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በቀረበው መነሻ ጽሑፍ ላይ አስተያየት እና ጥያቄ ተነስተው ማብራሪያ እና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡



5 last posts shown.