ማህበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Religion


The channel of mahibere kidusan

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Religion
Statistics
Posts filter


ለመሆኑ ክህነት ምንድን ነው?

ክህነት በቤተ ክርስቲያናችን ‹‹ተክህነ›› ተሾመ፤ አገለገለ፤ ዲቁና፣ ቅስና፣ መንፈሳዊ ሥልጣን ተቀበለ›› የሚል ትርጉም አለው፡፡ ለአገልግሎት መመረጥን፣ መሾምን ሹመቱም መንፈሳዊ እንደሆነ ሲያመለክት ነው፡፡ (ኪዳነ ወልድ፣ ገጽ ፭፻፳፪)

ካህን፡- ማለት ደግሞ የሕዝብ መሪ፣ አስተማሪ አባት፣ አገልጋይ ተብሎ ይተረጎማል፡፡ ክህነት መንፈሳዊ አገልግሎት ሲሆን ሰውን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት የማቅረብያ፣ ከእግዚአብሔር የተገኘ ስጦታና ሥልጣን ነው፡፡ ይህ ሥልጣን ስለፈለግን የምናገኘው ስለወደድን የምንሾመው ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ ለተመረጡት ከሚሰጣቸው ሀብታት አንዱና ትልቁ ነው፡፡

ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹መንፈስ ቅዱስ አንድ ሲሆን ስጦታው ልዩ ልዩ ነው…፤ ለሁሉም ጌታ እየረዳ እንደሚገባውና እንደሚጠቅመው ለእያንዳዱ በግልጥ ይሰጠዋል›› በማለት እንደገለጸው ክህነት የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ እንጅ ብዙ ገንዘብ፣ ዘመድና ሀብት ስላለን የምናገኘው አይደለም፡፡ (፩ኛቆሮ.፲፪፥፬)

ሥልጣነ ክህነት በማናቸውም ሥጋዊ ደማዊ መመዘኛዎች የሚሰጥ አይደለም፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን ሲያስረዳ ‹‹መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ›› በማለት እንደገለጸው አገልግሎቱ ፍጹም መንፈሳዊ መሆኑን ከዓለማዊ ሥልጣን እና ሹመት መንገዱም ተግባሩም የተለየ እንደሆነ ይነግረናል፡፡ (፩ኛጴጥ.፪፥፭)

በአጠቃላይ ክህነት ማለት አገልግሎት ማለት ሲሆን በእግዚአብሔርና በምእመናን መካከል ተገኝተው የእግዘዚአብሔርን ፈቃድና ትእዛዝ ለመፈጸምና ምእመናንን ለመጠበቅ፣ ለማስተማር፣ ለማስታረቅና ለማጽናት እንዲሁም ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ለመፈጸም እንዲችሉ ለማድረግ ለተመረጡ ሰዎች የሚሰጥ ሥልጣን ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያን ምሥጢራት ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ናቸው፡፡ እነዚህን ምሥጢራት ስናስብ ያለ ክህነት የሚከወኑ ወይም የሚፈጸሙ አይደሉም፡፡ ያለ እነርሱ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንንም ክርስትናንንም በማሰብ አገልግሎቱን ማሟላት አይቻልም፡፡

ክህነት የሚያገለግሉበት እንጅ የሚገለገሉበት ሹመት አይደለም፡፡ በኦሪትም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሙሴ ‹‹የተቀደሰውንም ልብስ አሮንን ታለብሰዋለህ፤ በክህነትም ያገለግለኝ ዘንድ ቀብተህ ትቀድሰዋለህ›› በማለት ነግሮታል፡፡ (ዘጸ.፵፥፲፫) በዚሁ በኦሪት መጽሐፍ ላይም ‹‹ካህን ሆኖ እንዲያገለግለኝ አሮን ቅዱስ ይሆን ዘንድ ልብስ እንዲሠሩለት የጥበብ መንፈስ ለሞላባቸው በልባቸው ጥበበኛ ለሆኑት ሁሉ ተናገር›› በማለት እንኳንስ የተሾመው ካህኑ የእርሱን ልብስ እንኳን የሚያዘጋጁት የጥበብ መንፈስ በልባቸው የሞላባቸው ጥበበኞች እንደሆኑ፣ የተሾመው ካህንም ቅዱስ ሆኖ ቅዱሱን እግዚያብሔር የሚያገለግል ካህን እንደሆነ መመረጡ፣ መሾም መሸለሙም ለአገልግሎት መሆኑን እንረዳለን፡፡ (ዘጸ.፳፰፥፫) በዘመናችን ክህነት ይህን ትርጉም ይዞ ይገኛል ወይ? የሚለው ጥያቄ እንደተጠበቀ ሆኖ አገልግሎቱም ማስተማር፣ መምከር፣ መገሠፅ፣ መሥዋዕትን በመሠዋትና ጸሎትን በመጸለይ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ከላይ ከቀረበው ትርጉም ስንነሣ በአብዛኛው የሚያመለክተው ካህን/ቄስ/የምንለውን የሚገልጽ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ይሁን እንጅ ክህነት ሦስት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን የሹመቱ ባለቤቶችም እንዲሁ ሦስት ደረጃዎች አሏቸው፡፡ ዲቁና/ዲያቆን/፣ ቅስና/ቄስ/ እና ኤጲስ ቆጶስነት/ኤጲስ ቆጶስ/ ናቸው፡፡

ሁሉም ግን የክህነት ባለቤቶች ሲሆኑ የስማቸው ትርጉምም “አገልጋይነት” ነው፡፡ እነዚህ የክህነት ደረጃዎች የክርስትናችን የአምልኳችን መሠረቶች ናቸው፡፡ ክብረ ክህነት ስንል ስለ ሁሉም ማለትም ስለ ክብረ ዲቁና፣ ስለክብረ ቅስና እንዲሁም ስለ ክብረ ኤጲስ ቆጶስነት (ጵጵስና) እየተናገርን ነው፡፡ ክብረ ዲቁና፣ ክብረ ቅስና፣ ክብረ ጵጵስና ትናንትና ዛሬ ምን መልክ አለው? ነገስ ምን ሊሆን ይችላል? ምንስ ሊሆን ይገባዋል? የሚሉ ጥያቄዎችን መጠየቅና ጥያቄዎቹን መመለስ ትርጉም ያለው ጉዳይ ነው፡፡

የነገዋን ቤተ ክርስቲያን ጽንዕ ለማድረግና ቤተ ክርስቲያን በምድር ያላትን ሐዋርያዊ ተልእኮዋን እንድትወጣ ክብረ ክህነት መሠረታዊ ከሆኑ ነገሮች አንዱ መሆኑን እኛ የዚህ ዘመን የቤተ ክርስቲያን ባላደራዎችና የነገው ትውልድ አስረካቢዎች መረዳት ብቻ ሳይሆን ክብረ ክህነት የገጠመውን ተግዳሮት አስወግደን የተሟላ ማንነት ያላት ቤተ ክርስቲያን ለነገ ማሸጋገር ግዴታችን ነው፡፡ የዚች ቤተ ክርስቲያን መሠረት ክህነት በመሆኑ ከተግባባን ክብረ ክህነት በዘመናችን ምን ሁኔታ ላይ ነው? በትናንትና በዛሬ መካከልስ ምን ለውጥ ታይቶበታል? አሁን ላይ ክብረ ክህነት በብዙ መልኩ እየተፈተነ ነውና ከዚህ እንዴት ልንወጣና ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን የቅድስና፣ የንጽሕና፣ የመልካም አስተዳደርና የክብር መገለጫ፣ የምእመናን ኩራትና ክብር ሆኖ ይቀጥል? የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተን መወያየት ያስፈልጋል፡፡

ክህነት ትናንትና የሚያገለግሉበት እንጅ የሚገለገሉበት፣ የሚያበለጽጉበት እንጅ የሚበለጽጉበት፣ ሌሎችን የሚያከብሩበት እንጅ ራስን የሚያከብሩበት አልነበረም፡፡ በክህነት ብዙዎች ምግበ ሥጋ ምግበ ነፍስ አግኝተዋል፤ የታመሙ ተፈውሰውበታል፤ ያዘኑ ተጽናንተውበታል፤ የተሰበሩ በሥጋም በመንፈስም ተጠግነውበታል፤ የተበተኑ ተሰብስበውበታል፤ የራቁ ቀርበውበታል፤ ለብዙዎች የንጽሕና፣ የቅድስና፣ የመታደስ እንዲሁም የተሰደዱ የተመለሱበትም ምክንያት ነበር፡፡

ክህነት ትናንት የብዙዎች አንደበት ነበር፤ የተጣሉ ታርቀውበታል፤ የተበደሉ ተክሰውበታል፤ አምባገነኖችና ክፉዎች ተገሥፀውበታል፤ እግዚአብሔርም ሰውም ከብሮበታል፤ አጋንንትና የአጋንንት ማደሪያ የሆኑ ሁሉ ተዋርደውበታል፡፡ በአማናዊ ክህነት ዓይኑ ያልበራለት፤ የድንቁርና ጨለማን ያላስወገደ በክብረ ክህነት ያልከበረ ማንም አልነበረም፡፡

መጠራታቸውን ያወቁ፣ መመረጣቸውን ያጸኑ፣ ራሳቸውን አክብረው ክብረ ክህነትን ያስከበሩ በክብረ ክህነት በአርአያ ክህነትና በመታፈር በመከበር የነበሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ለአገልግሎታቸው ሰማያዊ ዋጋን እንጅ ምድራዊ ደመዎዝን የማያስቡ፣ እውነተኛ አገልጋዮች የአገልግሎትን ዋጋ የሚያውቁ፣ የክህነትን ታላቅነትና የተልእኮውን ክብደት የተረዱ ለማገልገል ቅድመ ሁኔታ ያልነበራቸው፤ አገልግሎታቸው በቦታና በሁኔታ ያልተገደበ የክህነት ሰዎች ነበሩ፡፡

ባሉበት በተሾሙበት አጥቢያ ቀርቶ መንገድ ሲጓዙ በመንገድ ምናልባት ቅዳሴ ሊታጎል ይችላል ብለው ምግብ ሳይበሉ የሚጓዙ ጸጋቸውን በውል የጠበቁ ክህነትን ተከብረው ያስከበሩ አባቶች የነበሩባት ቤተ ክርስቲያን ስለነበረች በወዳጆቿ ተከባሪ በጠላቶቿ ተፈሪ ሆና ዘመናትን ተሻግራለች፡፡

ውድ የዚህ ጽሑፍ ተከታታዮች! “ክብረ ክህነት ዛሬስ ምን ደረጃ ላይ ነው? ነገስ ምን መሆን አለበት?” የሚሉ ጉዳዮችን በቀጣይ ክፍል ይዘንላችሁ እንቀርባለን፡፡ እስከዚያው ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን!


‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ››

ክፍል ሦስት


ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ባለፉት ሁለት ክፍሎች ‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ›› በሚል ርእስ ጽሑፍ አድርሰናችኋል፡፡ አንብባችሁ ቁም ነገር እንዳገኛችሁ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ አሁን ደግሞ ክፍል ሦስትን ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!

ቤተ ክርስቲያን አሁን የገጠማትን ዘርፈ ብዙ ተግዳሮት አሸንፋ ለመጩ ትውልድ ከእነ ሙሉ ክብሯና መታፈሯ መሻገር አለባት፡፡ በየዘመኑ ከክፉዎች ጋር ታግላ አሸንፋለች፤ ተዋግታ ድል አድርጋለች፤ ጠላቶቿን ሁሉ አሳፍራ ከዚህ ዘመን ደርሳለች፡፡ ምክንያቱም የዚህች ቤተ ክርስቲያን የቅድስና፣ የመከበርና የመታፈር፣ የአሸናፊነትና የድል አድራጊነት ምሥጢር ክብረ ክህነትና ክብረ ምንኩስና ስለ ነበሩ ነው፡፡

የነገዋ ቤተ ክርስቲያንና ክብረ ክህነት፡-

ክብረ ክህነት ሲከበር ሲኖዶሳዊ ልዕልና ይከበራል፡ ፡ክብረ ክህነት ሲኖር ቤተ ክርስቲያን የታፈረችና የተከበረች ትሆናለች፤ ክብረ ክህነት ሲኖር የምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ያድጋል፤ ክብረ ክህነት ካለ ሃይማኖት ይጸናል፤ ምግባር ይቀናል፤ ትውልዱ ሰላማዊና ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው ይሆናል፡፡ ክብረ ክህነት ካለ መልካም አስተዳደር በቤተ ክርስቲያን ይሰፍናል፤ የምእመናን አንድነት ይጸናል፤ ክፉ ሠራተኞች ቦታ ያጣሉ፤ የቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ይሳካል፤ ሰላም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ፣ ሰላም በአባቶች መካከል፣ ሰላም በምእመናን ሕይወት ዘንድ ይሰፍናል፤ አልፎ ተርፎ ትሩፋቱ ለሌላም ለሀገር ይተርፋል፡፡ ድኃ ተበደለ ፍርድ ተጓደለ የሚል መሪ ይመጣል፡፡ በዘመናችን ትልቁ የቤተ ክርስቲያን ተግዳሮት የክብረ ክህነትና የገዳማዊ ሕይወት ወይም ክብረ ምንኩስና መዳከምና ቅቡልነት መቀነስ ነው ብለን ስለምናምን ነው፡፡


የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት እና የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርእይ ተከፈተ።

በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር አዘጋጅነት " መጽሐፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በሕዝባችን ሕይወት እናሥርጽ" በሚል መሪቃል የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት እና የቅዱሳት መጽሐፍት ዐውደ ርእይ እየተከናወነ ይገኛል።

በስካይ ላይት ሆቴል እየተከናወነ በሚገኘው በዚህ መርሐ ግብር ላይ ብፁእ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስን ጨምሮ በርካታ እንግዶች ተገኝተዋል።

መርሐብ ግብሩ እስከ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ የተነገረ ሲሆን በማጠናቀቂያው ዕለትም የመጽሐፍ ቅዱስ ቀን እንደሚከበር ተጠቁሟል

5k 0 16 2 72

The Sabbath known as “synagogue” is the day that Our Lord rebuked the changers, threw out those who made the temple cattle drive and sells of gold along their things, taught about the temple which is Abode of God, presentation of Scarification, place of prayer and Sanctuary of Saints. His words were not only preached on that age. But also told to us and thus shall return back to Him before His whip us. “He found in the temple those who sold oxen and sheep and doves, and the money changers doing business. When He had made a whip of cords, He drove them all out of the temple, with the sheep and the oxen, and poured out the changers’ money and overturned the tables.” (John 2:14-15)

In order to be saved from the coming whip in this world, it is relevant to have faith and deed. “What does it profit, my brethren, if someone says he has faith but does not have works? Can faith save him? If a brother or sister is naked and destitute of daily food, and one of you says to them, “Depart in peace, be warmed and filled,” but you do not give them the things which are needed for the body, what does it profit? Thus also faith by itself, if it does not have works, is dead.” (James 2: 14 up to the end)

This day’s psalm is from Saint Jared’s Book locally known as “Tsome Degwa”- “Our Lord Jesus went into the synagogue. He thought word of religion.”

Epistles: - (Colossians 2:16 up to the end) (James 2:14 up to the end)
Gospels, (John 2:12 up to the end)
(Acts 10:1-8)
“Mesebak” Prophets David’s words in rhyme; “for the zeal of thine house has eaten me up; and the reproaches of them that reproached thee are fallen upon me.” (Psalm 68:9)
May God’s mercy be upon us and Glory be to Him!


Unfortunately, King Nebuchadnezzar destroyed the synagogue of Jews whilst capturing Israeli and the people fled to Babylon. (2 Kings 24-25, Jeremiah 4:7, 39:1-10, 52:1-30) Onwards, the Jews build house for their prayer ever else. On that era, if there were ten house owners present on that place, they were allowed to build synagogues. (Talmud Mishnah, Responsa literature, Jewish Encyclopedia, Academic Scholarly Works.) When Our Lord and Savior Jesus Christ visited Jerusalem and their synagogues. In the New Testament, they served as stages for preaching Gospel for the Apostles.

Inside the Jews synagogue, there are Manuscripts of Law and Prophet’s Books. Teachers and Priests use to teach standing on the stage so that laities could hear their voice. They teach word of God. The chiefs of the synagogue had the authority to punish guilty person. They also served by executing their order of the chiefs in teaching the servile or assistance youngsters.

All the people use to congregate in synagogue on Sabbath and receive preaching and consecration from the readings of Law and Prophet Books and worship God. Our Lord Jesus Christ was present at synagogue and taught the people. Saint Luke in his Gospel said, “So He came to Nazareth, where He had been brought up. And as His custom was, He went into the synagogue on the Sabbath day, and stood up to read.” (Luke 4:16). The Apostles word signifies their reading, learning and interpreting of Holy Scriptures also providing cohort were their daily routine. (Luke 4:16)

However, their congregation were for the following reasons as well.

1. Saying He is the true Shepherd: -
Their faith to follow Him with the hope of The Holy and Incarnated Son came down and Be born, Believing He is the world’s salvation. “And when he brings out his own sheep, he goes before them; and the sheep follow him, for they know his voice.” (John 10:4)


2. Seeking His words and miraculous: - They gathered to be healed from malady. They those also who touched His clothe, falling down and bowing, shaded by His shadow and touched by His hands and healed. (Mark 5:22- up to the end) The Gospel tells us Our Lord taught the congregation in the synagogue on Sabbath. “Then He went out from there and came to His own country, and His disciples followed Him. And when the Sabbath had come, He began to teach in the synagogue. “When He had come to His own country, He taught them in their synagogue, so that they were astonished.” (Matthew 13:54)


3. In search for food and seeing His Grace: - Our Lord Jesus Christ after bestowing few of but fed thousands by His teaching and so people attend the cohort. Christians do not worship God because He gave us food. That He already provided for pupil and gentiles without greed for He is world’s feeder. Christians is not evaluated by food. It is stated as, “Therefore do not let anyone judge you by what you eat or drink, or with regard to a religious festival, a New Moon celebration or a Sabbath day.” (Colossians 2:16 up to end)

4. There were persecuted ones: - Sakhalin Jews who seek to sew the Lord of all, in court, Arch Priests doubting Him Being God, followed Him. as it is written, “At daybreak the council of the elders of the people, both the chief priests and the teachers of the law, met together, and Jesus was led before them. “If you are the Messiah,” they said, “tell us.” (Jesus answered, “If I tell you, you will not believe me.” Luke 22:66-68, Matthew 26:59)

Todays, it is clear there exists children of Jews who only prioritizing the bodily thing, made the True Holy Church business center, sell and exchange Holy Icons and Holy Antiques for profiting, rushing for persecution on those who are still in synagogue that are shepherd of sheep. But. Lord Jesus Christ has said, “Take these things away! Do not make My Father’s house a house of merchandise!”, “‘My house shall be called a house of prayer,’ but you have made it a ‘den of thieves.’ ” (John 2:16, Matthew 21:13)


Synagogue

“I desire mercy and not sacrifice,’ you would not have condemned the guiltless. For the Son of Man is Lord even of the Sabbath. Now when He had departed from there, He went into their synagogue.” (Matthew 12:7-9)

The Ethiopian Orthodox Incarnation (Tewahedo) Church has named the third week of The Great Lent as “synagogue.” The direct meaning of the word is, “a hill, building that is as high as a mountain and shallow like hall. It was the Jewish hall for prayer and worship of God serving as their temple.


በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት "ኑ ቸርነትን እናድርግ " በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር
በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

ድጋፍ ለማድረግ

በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፦
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
በወጋገን ባንክ - 0837331610101
በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
በአዋሽ ባንክ - 01329817420400
Gofundme
https://www.gofundme.com/f/uerc8?utm_campaign=p_cp+share-sheet&utm_medium=copy_link_all&utm_source=customer&utm_term=undefined
Wegenfund
https://Www.wegenfund.com/mknu

ለበለጠ መረጃ
. +251 9 43 00 04 03
. +251 9 26 41 31 12


በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት "ኑ ቸርነትን እናድርግ " በሚል መሪ ቃል የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር
በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ነው።

በአገራችን በሰው ሠራሽ እና የተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመደገፍ የሚያስችል ልዩ መርሐ ግብር በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሔደ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ በቀጥታ በማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣብያ እየተላለፈ ይገኛል።

ድጋፍ ለማድረግ

በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፦
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
በወጋገን ባንክ - 0837331610101
በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
በአዋሽ ባንክ - 01329817420400
Gofundme
https://www.gofundme.com/f/uerc8?utm_campaign=p_cp+share-sheet&utm_medium=copy_link_all&utm_source=customer&utm_term=undefined
Wegenfund
https://Www.wegenfund.com/mknu

ለበለጠ መረጃ
. +251 9 43 00 04 03
. +251 9 26 41 31 12


 
ምኵራበ አይሁድ በውስጡ የብራና የሕግ እና የነቢያት መጻሐፍት ይገኛሉ፡፡ ምእመኑ እንዲሰማቸው ከፍ ባለ መድረክ ላይ በመሆን መምህራንና ካህናት ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም  ያስተምሩ ነበር። የምኵራብ ሹማምንት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሊቀጡ ሥልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር፣ በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትእዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡
 
በሰንበት ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስቦ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፣ ስብከትና ቡራኬ በመቀበል አምልኮታቸውን ይፈጽሙ ነበር፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምኵራብ ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ”ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን  ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሣ” እንዳለ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ፣ መማር፣ መመርመር፣መተርጎም፣ጉባኤ መሥራት አዘውትረው የሚፈጽሙት ተግባር እንደነበር ያስረዳል።(ሉቃ.፬፡፥፲፮)
 
ነገር ግን በምኵራብ ሰዎች ለተለያየ ዓላማ ይሰበሰቡ ነበር፡፡
 
፩. አማናዊ እረኛ ነው ብለው፦
ወልድ ዋሕድ ብለው ሲጠብቁት የነበረው ተስፋ “ደረሰልን፤ ወረደ፤ ተወለደ፤ የዓለም መድኃኒት እርሱ ነው” ብለው አዳኝነቱን አምነው ይከተሉታል። “ነዋ በግዑ ለእግዚብሔር ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም፤ የዓለሙን ኃጢአት የሚያስተሰርይ የእግዚብሔር በግ መሆኑን አውቀው የሚከተሉት አሉ። ”በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል” እንዲል። (ዮሐ.፲፥፬)
 
፪. የቃሉን ትምህርት የእጁን ተአምራት ሽተው፦ ከደዌ ለመፈወስ ይሰበሰባሉ፤ ልብሱን ዳሰው፣ ወድቀው ሰግደው፣ ጥላውን ተጋርደው፣ በእጁ ተዳሰው የሚፈወሱ ነበሩ። (ማር. ፭፥፳፪ እስከ ፍጻሜ)። ጌታችን በዕለተ ሰንበት ሕዝብ በተሰበሰበበት በምኵራብ እንደሚያስተምር ያስረዳናል፤ ”ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፤…ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ፡፡”  (ማር.፮፥፩) “ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር።” (ማቴ.፲፫፥፶፬)
 
፫. ምግበ-ሥጋ ፈልገው ደም ግባቱን አይተው:- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከምኵራብ ጉባኤ ትምህርት በኋላ ጥቂቱን አበርክቶ እልፉን ይመግብ ስለነበር ጉባኤውን ይታደማሉ። ክርስቲያኖች እግዚአብሔርን የምናመልከው ምግበ ሥጋ ስለሰጠን አይደለም። እርሱንማ ለሕዝብም ለአሕዛብም ሳይሰስት የሚመግብ መጋቤ ዓለማት ነው። ክርስቲያን በመብል አይገመትም። “እንግዲህ በመብልም ቢሆን÷ በመጠጥም ቢሆን÷ በልዩ ልዩ በዓላትም ቢሆን÷ በመባቻም ቢሆን÷ በሰንበትም ቢሆን የሚነቅፋችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፡፡” እንዲል፡፡ (ቆላ. ፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ)
 
፬. ለክስ የሚቀርቡ አሉ፦ ከቃሉ ግድፈት ከትምህርቱ ስሕተት የሚፈልጉ ሰቃለያን አይሁድ፣ ሊቃነ ካህናት አምላክነቱን የሚጠራጠሩ አይሁድ የሸንጎውን ጌታ ለሸንጎ ፍርድ ሊያቀርቡት ከግር በግር ይከተሉት ነበር። “ወጸቢሖ ተጋብኡ ሊቃነ ካህናት ወጸሐፍት ወሊቃናተ ሕዝብ ወወሰድዎ ውስተ ዐውዶሙ። ወይቤልዎ እመ አንተሁ ክርስቶስ ንግረነ ገሃደ ወይቤሎሙ እመኒ አይዳእኩክሙ ኢተአምኑኒ፡፡ በነጋም ጊዜ፥ የካህናት አለቆች፥ ጻፎችና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱት፡፡ “አንተ ክርስቶስ እንደ ሆንህ በግልጥ ንገረን” አሉት፡፡እርሱም እንዲህ አላቸው፥ “ብነግራችሁም አታምኑኝም” እንዲል፡፡ (ሉቃ. ፳፪፥፷፮፣ ማቴ.፳፮፥፶፱)
 
ዛሬም በአማናዊቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥጋዊ ነገር ብቻ ገዝፎባቸው ቤተ መቅደሱን ለንግድ፣ ንዋያተ ቅድሳትን ለትርፍ ብቻ አሳልፈው የሚሸጡ፣ የሚለውጡ፣ ለክስ የሚፋጠኑ ከምኵራብ ያልወጡ የበጎችን እረኛ አሳልፈው የሚሰጡ አዋልደ ይሁዳ እንዳሉ ግልጽ ነው። “ወረከበ በምኵራብ እለ ይሠይጡ አልህምተ ወአባግዐ ወአርጋበ …፤ በመቅደስም በሬዎችን፣ ላሞችን፣ በጎችን፣ ርግቦችን፣ የሚሸጡትን አገኘ …፤ “ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት፤ ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል” እያለም የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡፡ (ዮሐ.፪፥፲፮፣ማቴ.፳፩፥፲፫)
 
በምኵራብ ይሸጡ፣ ይለውጡ የነበሩትን የገሠፀበት፣ ቤተ መቅደስን የከብት መንጃ የወርቅ መነገጃ ያደረጉ ሰዎችን ከእነ ሸቀጣቸው ከቤተ መቅደስ ያስወጣበት፣ ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ የመሥዋዕቱ መክበሪያ፣ የጸሎት ሥፍራ ምስካበ ቅዱሳን መሆኗን ያስተማረበት ዕለት ነው። ቃሉ በዚያን ዘመን ተነግሮ ብቻ ያለፈ አይደለም፤ ለእኛ የተነገረን መሆኑን አውቀን የባለቤቱ ጅራፍ ሳይገርፈን ልንመለስ ይገባል። “የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡” (ዮሐ.፪፥፲፬)
 
ከሚመጣው ጅራፍ ለመዳን እምነት ከተግባር ይዞ መገኘት ያስፈልጋል።” ወንድሞቻችን ሆይ÷ እምነት አለኝ፤ ምግባር ግን የለኝም የሚል ሰው ቢኖር÷ ምን ይጠቅመዋል? በውኑ እምነቱ ልታድነው ትችላለችን? ከወንድሞቻችን÷ ወይም ከእኅቶቻችን÷ የታረዙ ወይም የዕለት ምግብ ያጡ ቢኖሩ÷ ከእናንተም አንዱ …እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።” እንዳለ። (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)
 
የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤
 
መልእክታት፦(ቆላ.፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ) (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)
ወንጌል፦ (ዮሐ.፪፥፲፪-እስከ ፍጻሜ)
(የሐዋ.፲፥፩-፰)
 
ምስባክ፦ “እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፡፡ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፡፡ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡” ትርጉም “የቤትህ ቅንዓት በልቶኛልና፥ የሚሰድቡህም ስድብ በለዬ ወድቆአልና፡፡ ሰውነቴን በጾም አደከምኋት፡፡  (መዝ.፷፰፥፱)     
 
በምሕረቱ ይታደገን፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ አሜን!!!

9 last posts shown.