መሪጌታ አምደብርሃን የባህል ህክምና መስጫ ማዕከል 🌿🌿🌿


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Esoterics


☑ ከጥንት አባቶቻች በተቸረን ሰሎሞናዊ ጥበብ ተፈጥሮ ያበቃላቸው የእፅዋት መድሀኒቶችን በመጠቀም ክፉ ዓይነ ጥላ ፣ በቤተሰብ ወይም በዘር የሚተላለፉ መናፍስት መፍትሔዎቻቸው ይተነተናሉ።
☑ አድራሻ ቁጥር 1 ምዕራብ ጎጃም ቡሬ ቁጥር 2 አ/አ እንዲሁም በተለያዩ የክልል ከተሞች እንልካለን
📞#0918834904
📞#0915310455
መልዕክት ካለዎት @merigetaamedeberhan

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Esoterics
Statistics
Posts filter


🌿🌿ዕፀ ደብዳቤ🌿🌿
▶️ #ለደከመ_አይን ፦ የእንስላል ቅጠል ጨቅጭቀህ ውሃውን አጥለህ አይንህን ብታጥብ ጥሩ አድርጎ ያሳይሃል ።
▶️#ለነስር ፦ የልት ስር በክርስትና ስምህ ቆርጠህ በ 3 አጽቅ ከርክመህ በግራ ፈትል ከግንባሩ ከግራና ከቀኝ ጆሮ ግንዱ ስር እሰር ወዲያው ይድናል ።
▶️#ለችፌ_ለቆዳ_በሽታ_ለማድያት _ለቋቁቻ ፦የተነጠረ ድኝ ከብርብራ ፍሬ ጋር አገናኝተህ በጣም ሰልቀህ በቅቤ ለውሰህ ብትቀባው ይድናል
▶️#ለሳንባና_ለጉበት ፦ በሶብላ ፣ ዘቃቅቤ በወተት ዘፍዝፈህ ወይም በብርዝ ውሀ በባዶ ሆድ ቢጠጡት በሆድ አንጀት ያለውን ትል በሙሉ ያስወግዳል ።
▶️#ለምቀኛ ፦ የቀጠጥና ስር በወይራ አንካሴ ቆፍረህ የዕገሌን ቁመኛ በስሙ እንዲህ ቁረጥ ብሎ ልጡን ጥሎ በጥሬ ጨው አብሮ ጎርሶ እንደመሟጫ መምጠጥ ነው ። የሚቆረጠው ዓርብና ረዕቡ ነው ።
▶️#ለምች_ለወስፋት_ለሳል_ለልብ_ደዌ_እንደ_ሀሞት_ለሚመረው_ለሚአዞረው_ለሚያንቀጠቅጠው_ለስራይ ፦ ጣዝማ ማር ፣ ንጥር ቅቤ ፣ተልባና ኑግ ፣ ሴቴ ሬት ቡጡን 7 ቀን በማሰሮ አዋህዶ የረጋውን ቢበላ ቅራሬውን ቢጠጣ ይድናል ።
▶️#አንድ_ሰው_ቡዳ_መሆኑን_ለማወቅ ፦ ቅንጭብና ዋጊኖስ ከቤት በጎዘጉዙ ቡዳው ከቤት አይቀመጥም ።
▶️#ለድምፅ ፦ እፀ ተከዜ ፣ መሬንዝ ፣ ጊዜዋ ስራቸው በቅቤ አንጥረህ 7 ዕለት ቀብረህ የምድር እንቧይ 14 ፍሬ ከንጥሩ አግባ ውሃውን እንዘረዘይና አቱች ደምሮ በቶፋ በጣዝማ ማር ጠጣ ፍቱን ልብ ያበራል ይከፍታል ።
▶️#ጆሮው_ለደነቆረ ፦ የቀጠጥና ፣ የሰሌን ፍሬ በአንድነት አዋህዶ ደቁሶ አንጥሮ በጆሮው መጨመር ነው 7 ቀን በ7ኛው ቀን ይሰማኛል ።
▶️#ሌሊት_አልጋ_ላይ_ለሚሸና ፦ የፍልፈል አፈር አንተርሰኸው ካሳደርከው በሃላ ጧት ሳይሸና ሳይፀዳዳ ሳይነጋገር የፍልፈል አፈሩን በኩበት አድርገህ ቢሸናበት ወዲያውኑ ይድናል  ።
▶️#ለአስም ፦ እንጭብር ስርና ቅጠሉን ልምጭ ቅጠሉን የሁለገብ ስርና ቅጠል ጦስኝ ኮሽም ስር በአንድ ለይ ቀቅለህ በጠርሙስ አጥለህ ጠዋት ጠዋት በባዶ ሆድ አንዳንድ ብርጭቆ እስከ 7 ቀን ብትጠጣ ትድናለህ ።
▶️#ለነቀርሳ፦ የፍህሶ ስሩን አድርቀህ አልመህ ሰልቀህ ውሀ ባልነካው ቅቤ ለውሰህ ብትቀባ ትድናለህ ።
▶️#ዓይኑን_ለሚበላው ፦ የሜዳ እንስላል ስር አክስሎ አልሞ 7 ቀን አይኑን ይኳል ይድናል ።
▶️#ለሰላቢ ፦ የምድር እንቧይ ስር የጊዜዋ ስር በወይራ አንካሴ ምሶ በቀንድ ቢለዋ ቆርጦ ከቤት በራፍ ቢሰቅሉት ሀብትን አያስነካም ።
▶️#ሀብቷ_ላልቀና_ልጅ_አገረድ ፦ የቀጋና የእንጆሪ ቅጠል ዘፍዝፎ በአዲስ ሸክላ 3 ቀን ትታጠብ ስሩንም ትታጠነው ታገባለች ሀብቷም ይቀናል ።
▶️#ከማንኛውም_ሰው_ወይም_ከሴት_ሚስጢር_እንዳይሰወርብህ ፦ ዕፀ ፋሪስ የረኛ ቆሎ አብሾ ፍሬአቸውን አድርቆ ደቁሶ በጉራይማሌ ወፍ ደም ለውሶ ያሮጊት ፈስ የጠለንጂ ስር የአስተናግር ፍሬ የእንቁራሪት ምላስ ጨምረህ በቀይ ከፋይ ጨርቅ ጠቅልለህ በቀይ ሀር ተብትበህ ብትይዝ አይደብቁህም ።
▶️#ኮሶ_የሚያጠፋ ፦ የጠንበለል ቅጠል የወገርት የመጭ የገብር እንቧይ የጫቅማ ወይም የጉሎ የቀጠጥና የነዚህን ስራቸውን ወቅጠህ በሱፍ ውሀ ብትጠጣ ትድናለህ ።
▶️#እብድ_ውሻ_ለነከሰው ፦ የምድር እንቧይ ስር ማክሰኞ በወይራ አንካሴ ምሰህ በቀንድ ቢለዋ ቆርጠህ በጣትህ ክርክር ልክ አድርገህ ከለከፈው ከ 10 ቀን ወይም 5 ቀን ቢሆን ጀምሮ ደቁሰህ በውሀ 3 ወይም 4 ቀን ማቅመስ ነው ።
▶️#አፍንጫው_ለሚገማ_ጆሮው_ለሚመግል ፦ ዕፀ ዘዌ ስሩን ደቁሶ በቅቤ ለውሶ አውሎ አሳድሮ በፀሀይ አቅልጦ አጥሎ መጨመር ነው ይድናል ።
▶️#የደረት_ሳል_መድሀኒት ፦ አብሽ ቀቅሎ አጠንፍፎ አድርቆ ፈጭቶ ማር ጨምሮ በወተት አገንፍሎ በባዶ ሆድ ቢበላ ይነቅልለታል ።
▶️#ግማሽ_እራሱን_እየከፈለ_ለሚያመው ፦ ቀይ ሽንኩርት ይብላ ይድናል ።
▶️#ለሆድ_በሽታ_ሁለ ፦ የሮማን ቅርፊት ከዝንጅብል ጋር 7 ቀን ቢያውጡት ባፉ መግል ያወጣለታል ።
▶️#ለተመለጠ_ፀጉር ፦ የኑግ እና የዋጊኖስ ቅጠል ወቅጦ ጨምቆ ቢቀቡት መልሶ ይበቅላል ።
▶️#እግሩን_እስከ_ባቱ_እስከ_ጭኑ_እከክ_ቢወርሰው_ ፦ የሴት በግ ሀሞት ብትቀባው ይድናል 
▶️#ደምና_መግል_ለሚያስቀምጠው ፦ የፍየል ወተት አንፍረህ አብርደህ ተልባ ጨምረህ ብታጠጣው ይድናል
▶️  #ዛር_ዉላጅ_ሌሊት_በሴት_እየተመሰለች_ለሚገናኘው_ወንድ_በወንድ_እየተመሰለ_ለሚገናኛት_ሴት
የሎል ቅርፊት ወደ ምስራቅ በኩል ቀርፍተህ ማታ እሳት ላይ አድርገህ ታጠነህ ተኛ ከምኝታህ ስትነሳ ያደረ ሽትህን ብትሸናበት ይለቃል ።
▶️    #ሰው_መድሀኒት_ቢያበላህ_እንዲያስታውክህ ፦የግራዋ የሰሌን ስራቸውን በአንድነት ሰፍተህ ያዝ
▶️#ለድምፅ ፦ ዕፀ መናሂ በጥሩ ጠጅ ዘፍዝፈህ 7 ቀን ጠጣ
▶️#ለመሰወር_ለግርማ_ሞገስ ፦ የላንቁሶ ተቀጽላ በበግ ሀሞት ለውሰህ ሰፍተህ ያዝ
▶️#ልቡ_ለሚፈራና_ለሚያበሳጨው_
ዕፀ ልቡና ሁለመናዋን አልመህ በማር ለውሰህ ማቅመስ ነው ።
▶️#ለአቃቤ_ርእስ ፦ የቀጠጥናውን አበባ ከትክል ዕብን ላይ ሰልቀህ ውሀ ባልነካው ቅቤ ለውሰህ ገፅህን ተቀባ እስከ አመት ከጥይት ከዱላ ከፀር የአቅበከ ።
▶️#አልሸጥ_እንስሳ_እና_ለማንኛውም_ንብረት
የቀጠጥና ስር ነቅለህ በግራ እጅህ ይዘህ ሂድ ይሸጣል
▶️#ለገበያ ፦ የቀጠጥናውን ስር የዘረጭ እንቧይ የጭቁኝና የአስተናግር ስራቸውን ታጠን ።
▶️#ለመፍትሄ_ሀብት ፦ የቀጠጥናውን አበባ የአመራሮ ፍሮ የአደይ አበባ አንድነት ቀምመህ አምጽኡን ወይከስት አእዋመ ድረስ 49 ጊዜ ደግመህ አምሳያ እላም ወተት ቅቤ ለውሰህ እራስህን ተቀባ ለሹመትም ይከውናል ።




❤ 2ኛ/ መተት ፦

አንድ ሰው በአንድ ሰው በመቅናት የሚያደርገው የምቀኝነት የአጋንንት ሥራ ነው፡፡ መተት በትዳር ዕድል በልጅ በባል/በሚስት በመቅናት የሚደረግ ክፉ አሠራር ነው፡፡ በትዳር ላይ መተት ከተደረገ ፈጣን የባሕርይ ለውጥ ማምጣትና ሰላም ማጣት ከዛም እስከ መለያየት የሚደርስ መጠላላት በመሃላቸው ሊፈጥር ይችላል፡፡ ታዲያ ሁለቱም በተለይም የተጋቢዎች ወገን የአጋንንቱን አሠራር ባለመረዳት ፍቺን እንደ አማራጭ በማየት በችኮላ፣ ትዕግሥት በማጣት አጋንንቱን ይተባበራሉ፡፡

የቤተሰብ ጣልቃ መግባት ለአጋንንቱ ጥሩ ከለላ ስለሚሆንና ቤተሰብን በጐ በመሰለ ሐሳብ በመደገፍ ይገባባቸውና በእነርሱ አድሮ የመለያየትን ሥራ ይሠራል፡፡ የሚያሳዝነው ሁለቱ ተፋቺዎች ምክንያት ያለው በሚመስል ባልታወቀ ምክንያት ተለያይተው ሌላ ቢያገቡ ትዳራቸው ከድጡ ወደ ማጡ ነው የሚሆንባቸው፡፡ ቀድሞ አጋንንት ስላፋታቸው ሁለተኛው ትዳር ውስጥ ጣልቃ በመግባት ማበጣበጥ ሰላም መንሳት ይጀምርና ያለያያል፡፡

በዚህም ተፋቺው ‹ትዳር› የሚባለው ነገር ሲነሳ ግፍግፍ በማለት ለልጆቻቸውና ለወዳጆቻቸው የትዳርን መጥፎ ገጽታ ብቻ በመናገር ቤተሰብን ተጽዕኖ ውስጥ በመክተት ታናናሾችንና ልጆችን ‹ትዳር ከእርሷ ወዲያ ላሳር› በማለት ትዳርን እንዲፈሩ ፈርተውም እንዳያገቡ በማድረግ ቆሞ ያስቀራል፡፡

ለዚህ መፍትሔው በትዳር ያልተጠበቀ ክሥተት ሲፈጠር መጸለይና አባቶችን በጸሎት እንዲረዱ ማድረግ፣ በተቻለ አቅም ጠበል መጠመቅ፣ ችግሩን ማወቅና ለችግሩ መፍትሔ ማግኘት ይቻላል፡፡

ወዳጆቼ በትዳር በመቅናት የሚመተት መተት ልክ እንደ ዛር እና ዓይነ ጥላ ፅንስ ሊያጨናግፍ እና ፅንስን በማኅፀን ውስጥ ሊያጠፋ ይችላል፡፡ በተለይ እርጉዝ ሴት ሆና የመተት አጋንንት ከተላከባት በማሕፀኗ ውስጥ ያለውን ፅንስ ስለሚመታውና ስለሚያድርበት ፅንሱ ሊጨናገፍ እና ሊጠፋ ይችላል፡፡
አንዳንዴ ሊወልዱ ጥቂት ወራት እና ጥቂት ቀናት ብሎም ዕለቱን ለፅንስ ክትትል ምርመራና ለመውለድ ሆስፒታል ሲሄዱ በሐኪሞች ‹‹ፅንሱ ልክ አይደለም፣ ጠፍቷል›› ተብሎ ጆሮ ጭው፣ ልብ ክው የሚያደርግ መርዶ የሚሰሙት በዛር፣ በዓይነ ጥላና በመተት ድግምት በሚፈጠር አሳዛኝ ክሥተት ነው፡፡

ልብ ካላችሁ እህቶቼ ብዙ ፅንሱ ከመጨናገፉ በፊት አንዳንዶች ሕልም ያያሉ፡፡ የሆነ ጥቁር ሰው ሲታገላችሁ፣ ማኅፀናችሁን ሲረግጣችሁ፣ ሲመታችሁ፣ የምትወዱትን ነገር ታግሎ ሲነጥቃችሁ፣ የሆነ ሰው እላያችሁ ላይ ሲከመርባችሁ፣ ሲያንቃችሁ እና ሲተናነቃችሁ ወዘተ ታልማላችሁ፡፡

ይህ የሚሆነው ከእርግዝናችሁ የቀና የቤተሰብ ዛር፣ ዓይነ ጥላ እና በተለይ በትዳራችሁ፣ በእርግዝናችሁ የሚቀናባችሁ ሰው የመተት አጋንንት ሲያስልክባችሁ እና ክፉ መናፍስቱ ሲዋጋችሁ ነው፡፡ ይህን ሕልም ስታዩ የዛኑ ቀን አልያም በጥቂት ቀናት ውስጥ ምንም ሳትሆኑ በድንገት ደም ይፈሳቹኃል ከዛም ፅንሱ ይቋረጣል፡፡
መፍትሔው ???????


❤ 2ኛ/ ዛሮች፦

ከሁለት አንዳቸው ዛር እና የዛር ውላጅ፣ ወንድ ወይም ሴት ዛር ካለባቸው ትዳራቸው አደገኛ ችግር ውስጥ ይገባል፡፡ ዛሩ ስለሚቀና ባልና ሚስትን ለማተራመስ ኩርፊያን፣ ንትርክን ጭቅጭቅን፣ ብስጭትን፣ አለመግባባትን፣ አለመተዛዘንን፣ ጥላቻን እንደ ግብዓት በመጠቀም ፍቅርን በማቀዝቀዝ ትዳሩን በፍቺ መንገድ እንዲጓዝ ይዳርጋል፡፡

ባስ ሲልም ደም የለመደ ዛር ከሆነ ጸብ በማንሳት ደም ያፋስሳል ከተቻለም ነፍስ ያዋድቃል፡፡ ዛሩ በአባትና በእናት ላይ ካለ በግንኙነት ወቅት ከዘር ጋር በመዋሐድ በማኅፀን ከፅንሱ ጋር አድጐ በመወለድ ደባል ሆኖ ያድጋል፡፡ ዛር እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ በመውረድ ቤተሰብን በማፈራረስ ሰላማቸውን በመደምሰስ ቤተሰብን ይዘበራርቃል፡፡

ዛር ልጆች ከተወለዱ በኋላ በልጆች እእምሮ በማደር አእምሮአቸውን በመዝጋት ትምህርት እንዳይገባቸው በማድረግ ቤተሰብንና ተማሪውን ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ በዚህም ልጁ በቤተሰብ እንዲጠላ ያደርገዋል፡፡ ፍራቻን እያስተማረ ያሳድገውና በራስ መተማመኑን በማጥፋት ለቤተሰቡ ለሀገሩ ደንታ ቢስ በማድረግ ውድ ሕይወቱን በመውረስ ለራሱ ለጥፋት ዓላማ ይጠቀምበታል፡፡

ሌብነትን፣ ወንጀልን፣ ክፉ ሱስን፣ መጠጥን፣ ዝሙትን፣ ጠበኛነትን እና ነውጠኝነትን በማስለመድ ምግባረ ቢስነትን በማላበስ የእርግማን ትውልድ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ወላጆች ሆይ ልጆች የሚታነጹት በእናንተ መልካምና እኩይ መሠረት ላይ ስለሆነ ዛሬ እንደ ቀልድ የዘራችሁትን ነገ መከመር እስኪያቅታችሁ ድረስ ስለምታጭዱ ልትጠነቁና በእውነተኛው መንገድ ልትሄዱ ይገባል፡፡ ዛሬ ‹‹የተረገመ ያልተባረከ›› እያላችሁ የምትረግሙት ልጅ ትላንት የናንተ ወይም የቤተሰባችሁ ጠንቅ ተርፎት ነውና ልታዝኑላቸው ይገባል፡፡

የዛር መንፈስ አንዱ መጥፎ መገለጫው በዓል በመጣ ቁጥር ለምሳሌ በዘመን መለወጫ፣ በገና እና በትንሣኤ በዓላት የቤተሰቡን ደስታ ለማጥፋት እና ሰላም ለመንሳት የማይረባ እና ውኃ የማያነሳ አለመግባባትንና ጠብን ተጠቅሞ ቤተሰቡን በማተራመስ፣ የበዓሉን ዐውድ ያጠፋባቸዋል፡፡

ወዳጆቼ በባል ወይም በሚስት ላይ የራሳቸው  አልያም የዛር መንፈስ ካለ ካላወቁበት እና ካልነቁበት መቼም ቢሆን በዓል በመጣ ቁጥር መጣላታቸው፣ በዓልን በኩርፊያ ማሳለፋቸው አይቀርም፡፡ እንዲሁም ከሁለት አንዳቸው ላይ በሕመም ተመስሎ በመቀመጥ ለበዓል የደስታ መዋያ ያሰቡት ገንዘብ የሐኪም ቀለብ ያደርጋል፡፡

ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ በተለይ የወንድ ዛር በሴቷ ላይ ካለ ከባሏ ጋር ሩካቤ ሥጋ መፈጸም ቀርቶ አብሮ መተኛት እና ማውራት ያስጠላታል፡፡ ሌሊት ከባሏ አጠገብ ተኝታ በእንቅልፍ ልቧ የወንድ ዛሩ ይገናኛታል፡፡ በደመ ነፍስም በተኛችበት የሚጫናት፣ የሚነካት፣ ሰውነቷን የሚዳስሳት ሰው መሰል ነገር ይሰማታል፡፡

እንዲሁም ሴት ዛር በወንዱ ላይ ካለች በተለይ በስንፈተ ሩካቤ ይጠቃል፡፡ በሕልመ ሌሊትም እጅጉን ይመታል፡፡ ጠባዩ እየተቀያየረ በውኃ ቀጠነ ይጨቃጨቃል፣ እንደ ሕፃን ይነጫነጫል፡፡ ሚስቱ ታስጠላዋለች፡፡ አብሯት ቢተኛም ሩካቤ ሥጋ ለመፈጸም እጅጉን ይቸገራል፡፡ በባል ላይም ሴት ዛር ካለች በሚያውቃት እና በማያውቃት፣ በቤተሰብ እየተመሰለች ሌሊት በተኛበት ትገናኘዋለች፡፡


❤ 1ኛ/ ዓይነ ጥላ

ዓይነ ጥላ ገርጋሪ ምቀኛ ክፉ መንፈስ ነው፡፡ ይህ ክፉ መንፈስ አድብቶ በመተናኮል ዕድላችንን በመዝጋት እጃችን ገባ ያልነውን ነገር በማሳጣት ይተናኮላል፡፡ ዓይነ ጥላ አብረውን ከሚወለዱና ተወልደን ከጊዜ በኋላ ከሚጠናወቱን ክፉ መንፈስ አንዱ ነው፡፡

ዓይነ ጥላ ያለባቸው ባል ወይም ሚስት በትዳራቸው ሰላም፣ ፍቅር፣ መግባባት በመሃላቸው በፍጹም አይኖርም፡፡ በተለይ በሩካቤ ሥጋ አይስማሙም፣ አይጣጣሙም፣ አይግባቡም፡፡

የዓይነ ጥላ መንፈስ ተጠቂ ከሆኑ እንኳን ሩካቤ ሥጋን በመፈቃቀድ ሊፈጽሙ ቀርቶ አብሮ መተኛት መተቃቀፍ አይወዱም፡፡ መንፈሱ የባልን ሰውነት ወይም የሚስትን ሰውነት እንደ ባዕድ አካል በማሳየት እንዲቀፈው/እንዲቀፋት በማድረግ ምክንያት የሌለውን ጥላቻ በመሃላቸው ይዘራል፡፡ በሩካቤ ሥጋም ደስታ የሚባል ያሳጣቸዋል፡፡ ሩካቤ ሥጋን የሚፈጽሙት ስለተጋቡ ብቻ እንጂ ወደውና ፈቅደው አይደለም፡፡ ደመ ቀዝቃዛ ያደርጋቸዋል፡፡

ከትዳር በፊት ወደ ሕይወታቸው ሰተት ብሎ የገባው መንፈስ በትዳራቸው ውስጥ ራሱን በተለያየ ጠባይና መልክ በመግለጥ፣ ለትዳራቸው መበጣበጥ እና መናወጥ ምክንያት ይሆናል፡፡ በማግባታቸው የተበሳጨው ዓይነ ጥላ በትዳር ኑሮአቸው ውስጥ የበቀል መርዙን እየረጨ፣ ትዳሩን እያቀጨጨ ለፍቺ ይዳርጋል፡፡

ዓይነ ጥላ በትዳር ሕይወት ሰላም በመንሳት እና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ስሜት በማጥፋት፣ የሩካቤ ሥጋ ደስታን በማበላሸት የተካነ ስለሆነ የመንፈሱን ጠባይ አውቃችሁ ልትነቁበት እና በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ልትዋጉት እንዲሁም በቅዱስ ቁርባን ጸጋ ከሕይወታችሁ ልታርቁት ይገባል፡፡ ምክንያቱም መንፈሱ ሸፍጠኛና ከጠባይ ጋር የሚመሳሰል በመሆኑ የብዙዎችን ትዳር ለፍቺ አብቅቷል፡፡
መፍትሔው ????????


የዳዊት ገቢር.pdf
4.9Mb
ገቢሩ ከመጨረሻው ወደ መጀመሪያ የሚመጣ ነው !!


የዳዊት ገቢር
#ለአቃቤ_ዕርስ
❤️መዝሙር፭ #ቃልየ፧አጽምዕ፧እግዚኦ፧ወለቡ፧ጽራሕየ.... ከሚለው ጀምሮ ሙሉውን መድገም
#ገቢሩ..በየብስም,ባሕርም,በመንገድም እህል ሳትቀምስ በቅባ ቅዱስ ,በሜሮን,ውሀ ባልነካው ቅቤ ..በማንኛውም ቅባት ላይ ፯ ጊዜ ደግመህ ተቀባ #ከሞት ይጠብቅሀል
እንዲሁ #ለራስ_ምታት በቅቤ ፯ ጊዜ ደግመህ ተቀባ ።
#አይኑን_ለታመመ
❤️መዝሙር ፮
#እግዚኦ፣በመዓትከ፣ኢትቅሥፈኒ፣ወበቅሠፍትከ፣ኢትገሥጸኒ.... ከሚለው ጀምሮ ሙሉውን መድገም
#ገቢሩ .. መዝሙሩን ፯ ጊዜ ደግሞ ፅፎ መያዝ እንዲሁ በቅቤ ፯ ጊዜ ደግሞ የታመመውን አይን መቀባት ያድናል ።
#ደግሞም ለምትፈራው ነገር ሁሉ ከቤት ሳትወጣ ማንኛውንም ሽት ቤት ሳትጠቀም ከሰው ሳትነጋገር የምትፈራውን ሰው ስም ከነእናቱ  ስም እየጠራህ ፯ ጊዜ ድገም ከእሱ ትድናለህ ።

#አስማት_ለተዋለበት_የአጋንንት_ቁራኛ_ለያዘው_ሰው
❤️መዝሙር ፯
#እግዚኦ፣አምላኪየ፣ብከ፣ተወከልኩ፣ኢትግድፈኒ....ከሚለው ጀምሮ ሙሉውን መድገም ።
#ገቢሩ .. ፀሀይ ከማታየው ጉድጓድ ውሀ ቀድተህ ከዕለቱ ከዕለቱ ሐፁረ መስቀል ፣ አርድእት ፣ ባርቶስ ጋር ፰ ቀን ፯ ፯ጊዜ ደግመህ አጥምቀው በእግዚአብሔር ቸርነት ይድናል ።  ይህንንም ስታደርግ ደርግ ልጅና ከብት ማንኛውንም ሰው ከሌለበት ሜዳ ነው ።  ከቤትም ከመንገድም አትድገም
#እንደዚሁ ባሏ ለጠላት ሴት በቅቤ ፯ ጊዜ ደግመህ ሰውነቷን ትቀባ ባሏ ይወዳታል ።

#ለታመሙ_ሕፃናት
❤️መዝሙር ፰
#እግዚኦ፣እግዚእነ፣ጥቀ፣ተሰብሐ፣ስምከ፣በኩሉ፣ምድር..ከሚለው ጀምሮ ሙሉውን መድገም ።
#ገቢሩ መዝሙሩን ጽፈህ አሲዘው ይፈወሳል ።
#እንዲሁ ለታሰረ ሰውም በኅብስት ላይ ጽፈህ ስጠው በእግዚአብሔር ቸርነት ይፈታል
#እንዲሁ በዝርግ ሳህን ላይ ጽፈህ በዓሣ መረብ ከተህ ከባህር ብትጥለው ብዙ አሳ ይያዝልሃል ። 
#እንዲሁ ለገበያ በእንቧጮ አርጩሜ ፯ ጊዜ ደግመህ የምትሸጠውን  እቃ ፯ ጊዜ ብትመታው ይሸጣል
#እንዲሁ ጥሬ ጨው በማር ለውሰህ ፯ ጊዜ ደግመህ ብትበላ ከሰው ጋር በፍቅር እና በሰላም ለመኖር ያስችልሃል ።

#ጠላት_በበረታብህ_ጊዜ
❤️መዝሙር ፱
#እገኒ፣ለከ፣እግዚኦ፣በኩሉ፣ልብየ ... ከሚለው ጀምሮ ሙሉውን መድገም ።
#ገቢሩ .. የራሱን የእናቱን ስም እየጠራህ ፫ ፫ ጊዜ ብትደግም ይታገስሃል ።
#እንዲሁ ሀገር ቢጠላህ ፯ ጊዜ በሊት ውሀ ደግመህ በ፬ቱ ማዕዘን እርጭ ሰው ሁሉ ይወድሃል።
እንዲህ እያለ እስከ መዝሙር ፻፳፭ ድረስ ይቀጥላል ለዛሬ ምሽት እነዚህን ፃፍኩላችሁ !!!
የዳዊቱን ሙሉ ገቢር የምትፈልጉ ሰዎች ካላችሁ ከታች pdf የምለቅላችሁ ይሆናል ።




አንዳንዴ ሊወልዱ ጥቂት ወራት እና ጥቂት ቀናት ብሎም ዕለቱን ለፅንስ ክትትል ምርመራና ለመውለድ ሆስፒታል ሲሄዱ በሐኪሞች ‹‹ፅንሱ ልክ አይደለም፣ ጠፍቷል›› ተብሎ ጆሮ ጭው፣ ልብ ክው የሚያደርግ መርዶ የሚሰሙት በዛር፣ በዓይነ ጥላና በመተት ድግምት በሚፈጠር አሳዛኝ ክሥተት ነው፡፡

ልብ ካላችሁ እህቶቼ ብዙ ፅንሱ ከመጨናገፉ በፊት አንዳንዶች ሕልም ያያሉ፡፡ የሆነ ጥቁር ሰው ሲታገላችሁ፣ ማኅፀናችሁን ሲረግጣችሁ፣ ሲመታችሁ፣ የምትወዱትን ነገር ታግሎ ሲነጥቃችሁ፣ የሆነ ሰው እላያችሁ ላይ ሲከመርባችሁ፣ ሲያንቃችሁ እና ሲተናነቃችሁ ወዘተ ታልማላችሁ፡፡

ይህ የሚሆነው ከእርግዝናችሁ የቀና የቤተሰብ ዛር፣ ዓይነ ጥላ እና በተለይ በትዳራችሁ፣ በእርግዝናችሁ የሚቀናባችሁ ሰው የመተት አጋንንት ሲያስልክባችሁ እና ክፉ መናፍስቱ ሲዋጋችሁ ነው፡፡ ይህን ሕልም ስታዩ የዛኑ ቀን አልያም በጥቂት ቀናት ውስጥ ምንም ሳትሆኑ በድንገት ደም ይፈሳቹኃል ከዛም ፅንሱ ይቋረጣል፡፡

❤ 5ኛ/ መስተፋቅር ፦

መስተፋቅር ማለት አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ያለ ፍላጐትዋ በአጋንንት ጥበብ እንድትወደው ማድረግ ነው፡፡ መስተፋቅር የተደረገበት ሰው ከፍተኛ ፍቅር ውስጥ በመግባት በቤተሰብ እንኳን ተው/ተይ ቢባሉ ከቤተሰብ እስከ መለያየት ተወራርደው እንቢኝ ይላሉ፡፡

በመስተፋቅር የተጀመረ ትዳር ትልቁ ችግር እግዚአብሔር የመሠረተው ሳይሆን በሰይጣን ጥበብ የተመሠረተ ስለሆነ አይጸናም፡፡ በጊዜ ሂደት ምስጢሩ ይወጣል አልያም መስተፋቀሩ ይከሽፋል፡፡ ያኔ በመናፍስት ጥበብ ያዋረሱት ፍቅር እንደ ጉም ይተንና የተደረገበት ሰው እንደ ሰመመን መርፌ ከነቃ ሁሉም ነገር ይበላሻል፡፡

በመስተፋቅር በተመሠረተ ትዳር የሚወለዱትም ልጆች የመናፍስቱ ሰለባ ይሆናሉ፡፡ ጤና ከማጣት እስከ መደንዘዝ ይደርሳሉ፡፡ በመስተፋቅር በተመሠረተ ትዳር የሚወለዱት ልጆች የአጋንንቱ ግብር ናቸው፡፡

ትዳሩ የተመሠረተው እና ልጆቹም የሚመጡበት መንገድ በእግዚአብሔር ዘንድ ስለማይወደድና ብሎም ስለማይባረኩ የእናት ወይም የአባታቸው አጋንንት እየተጠናወታቸው ለሀገር እና ለወገን በተለይም ለቤተ ክርስቲያን የማይጠቅሙ፣ ከጥቅማቸው ጥፋታቸው ያመዘነ ልጆች ይሆናሉ፡፡

❤ 6ኛ/ ቡዳ ፦

ወዳጆቼ እንደ ቀልድ የምንሰማውና የምናየው የቡዳ መንፈስ ጣጣው ብዙ ነው፡፡ አንዲት ሴት በውበቷ፣ በጸጉሯ፣ በቁመናዋ የአጋንንት ጥርስ ውስጥ ገብታ፤ በቡዳ መንፈስ ተበልታ ከሆነ በትዳር ሕይወቷ እጅጉን ልትቸገር ትችላለች፡፡

በተለይ በጸባይ እና በልጅ ማጣት ትቸገራለች፡፡ የቡዳ መንፈስ ያለባት ሴት አመሏ ንጭንጭ ይላል፣ ሆድ የሚብሳት እና ለቅሶ የሚቀድማት ናት፡፡ በተለይ መልከኛ ከሆነች ራስዋን የምትጥል፣ ለውበቷ ግድ የሌላት ዝርክርክ ትሆናለች፡፡

እንዲሁም የቡዳ መንፈሱ በማኅፀኗ ውስጥ አሸምቆ በመደበቅ ፅንስ ሊያጨናግፍባት እና ሊያጠፋባት ይችላል፡፡ በቡዳ ዓይኗን ከተበላች ዓይኗን ያቃጥላታል፣ አጥርቶ የማየት ችግር ይገጥማታል፣ ውበቷ ይበላሻል ለምሳሌ ፊቷ እንደ ማድያት ባለ ሁኔታ ይበልዛል፣ በወጣትነቷ ፊቷ የአሮጊት ፊት ይመስላል፣ ያለ እድሜዋ ፊቷ ይሸበሸባል፡፡ ማኅፀኗን ይቆርጣታል የሚገላበጥ እና ውስጡ የሆነ ነገር ያለ መስሎ ይሰማታል፡፡

ወዳጆቼ ስለ ቡዳ ካነሳን እንደው እርግዝና በቡዳ እንደሚበላ ታውቃላችሁ? ብዙዎቻችን የቡዳ መንፈስ በውበት በደም ግባት ወዘተ የሚገባ ብቻ ይመስለናል፡፡ ግን እርግዝናም በቡዳ ይበላል፡፡ እናቶቻችን ሲያረግዙ ማርገዛቸውን ለሰው የማያሳውቁት፣ እርግዝናቸውን በልብስ ደረብረብ አድርገው የሚሸፍኑት ከዓይነ ወግ ቡዳ ራሳቸውን ለመጠበቅ ብለው ነው፡፡ ልብ ካላችሁ አንዳንድ ሴቶች እርግዝናቸው ያምራል፡፡ ከቁመናቸው ጀምሮ እስከ ፅንሱ አቀማመጥ ላያቸው ለዓይን ደስ ይላሉ፡፡

የቡዳ መንፈስ ደግሞ ከዓይን ተነስቶ ወደ ሰው የሚገባ መንፈስ ስለሆነ እርግዝናቸውን በቡዳ ይበላል፡፡ ከዛማ ብዙም ሳይቆዩ አቅለሸለሸኝ፣ አመመኝ፣ ማኅፀኔን ቆረጠኝ ወዘተ በማለት ደም ሊመታቸውና ፅንሱ ሊጨናገፍ ብሎም ሊጠፋ ይችላል፡፡

ስለዚህ እባካችሁ እርጉዝ ስትሆኑ ፅንሱን ሰው ይይልኝ፣ ማርገዜን ምቀኞቼ ይወቁልኝ፣ ዓይናቸው ደም ይልበስ እያላችሁ ስስ ልብስ በመልበስ አትታዩ፡፡ በተለይ የመውለጃ ጊዜያችሁ ሲደርስ ሰው የሚበዛበት ቦታ በመታየት እና በመዝናናት ስም ዞር ዞር ከማለት ታቀቡ፡፡

ቤቢ ሻወር እያላችሁ እርግዝናችሁን በቡዳ አታስበሉ፡፡ ቤቢ ሻወር ብላችሁ እዩልኝ እንዳላችሁ በቡዳ የተበላ፣ ጤና ያጣ ልጅ ወልዳችሁ ልጄን አትዩብኝ፣ ደብቁልኝ እንዳትሉ ተጠንቀቁ፡፡

ወዳጆቼ ከላይ ያየናቸው ርኩሳን መናፍስት፣ በትዳራችን ላይ ጣልቃ በመግባት፣ ካለመግባባት እስከ መለያየት ሊያደርሱን ስለሚችሉ በትዳራችን ውስጥ የሚፈጠሩትን ነገሮች ረጋ ብሎ፣ አስተውሎ ማየት ያስፈልጋል፡፡

በተረፈ ትዳራችሁ በክፉ መናፍስትም ይሁን በሰው ተንኮል ችግር ውስጥ ከገባ፣ የወለድናቸውም ልጆች እክል ከገጠማቸው ንስሐ ገብተን፣ በጸሎት በርትተን በአምልኮት ሕይወት ፊታችንን ወደ እግዚአብሔር ከመለስን ምህረቱን፣ ቸርነቱን ወደ እኛ ይመልሳል፣ መፍትሔም ይሰጠናል፡፡

ቀናችሁን በጸሎት ጀምሩ፣ ማታ በጸሎት እደሩ!

መርጌታ አምደብርሃን ይትባረክ !!!


እንዲሁም የፅንሱን ደም በመጠጣት ልጁን ለራሳቸው ይገብራሉ፡፡ በተለይ የቤተሰባችን ባዕድ አምልኮ ካለ እንደ ዛርና ዓይነ ጥላ ያሉ መናፍስት ዘራችንን በማምከን ሴቷን ማኅፀኗን በመዝጋት፤ ብታረግዝም ፅንሱን በማጨናገፍ፤ ቢወለድም ጤናማ ያልሆነ ልጅ ለምሳሌ ንቃተ ኅሊናው የቀነሰ፣ የአእምሮ እድገት ውሱንነትና የአካል እድገት መዘግየት ያለበት፣ በተለይ ከተፈጥሮ  ውጭ የሆኑ ልጆች እንዲወለዱ በማድረግ ከፍተኛውን ሚና ይጫወታሉ፡፡

እኛም እነዚህን ክሥተቶች በሳይንሱ መንገድ በመረዳት ፈታኛችንን እንዳንዋጋ ቀድመን በሥጋ እውቀት ተመልተናል፡፡ ብናውቅም ከመረዳት ውጪ በጸሎት መዋጋትን ስለማንሻ የጨለማው ዓለም ገዢ ሰለባዎች እንሆናለን፡፡

እነዚህ የአጋንንት ፍላጻዎች እንዳይወጉን ስለ ትዳራችን ጤናማነት፣ ጽነስ ከመፈጠሩ በፊት በቡራኬ እንዲመጡ አብዝቶ መጸለይን ስላልቻልን፣ ልጀቻችንን መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ሳይሆን ርኩስ መንፈስ የተጠናወታቸው እንዲሆኑ እናደርጋለን፡፡

እኛ ወላጆች በመንፈሳዊ ሕይወት ዝለት፣ በጸሎት ድክመት ምክንያት በልጆቻችን ላይ የሕይወት ዘመን የመከራና የፈተና ጦስን እናወርሳቸዋለን፡፡

የዛር መንፈስ እየባሰ ሲመጣ በተለይ ደም የለመደ ከሆነ አባትና ልጅን፣ ልጅንና እናትን፣ ወንድምና እህትን፣ በማጣላት ደም ሊያፋስስ ይችላል፡፡ ደሙን እንደ በዓል ግብር ይጠቀምበታል፡፡ ስለዚህ ፅንስ ከአንድም ሁለቴ ሲጨናገፍ፣ በማሕፀን ውስጥ ሲጠፋ ዝም ብለን በየሕክምናው ከምንሮጥ ቆም ብለን ወደ ኋላ እናስብ፡፡

ብዙ ጊዜ የቤተሰቦቻችንን ጣጣ ችግሮቻችንና የችግሮቻችን መንስኤ ሆነው እናገኛለን፡፡ ስለዚህ ወደ ጠበሉ ወደ ጸሎቱ ፊታችንን መልሰን ወደ ፈጣሪ ብንማጸን መፍትሔ እናገኛለን ጤናማ ልጅ እንወልዳለን፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ  በሳይንሱ ስም የተሰጣቸው፣ ግን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በማኅፀን በአጋንንት ከመጨናገፍ ተርፈው ግን የአጋንንት ሰለባ ሆነው የተወለዱትን ልጆችን አጋንንት እንዴት ለከፋ ሕይወት እንደዳረጋቸው እግረ ብዕራችንን እንይ፡፡

ለምሳሌ በሕክምናው ‹‹ዳውን ሲንድረም›› የሚባልም ሕመም አለ፡፡ ይህም የእድገትና የአእምሮአዊ መዘግየትን የሚያስከትለው የዘረ መል ክሮሞዞም 21 ችግር ነው፡፡ ይህ ያልተለመደ የሕዋስ ክፍፍል ከክሮሞዞም 21 ተጨማሪ የዘረ መል (ንጥረ ነገር) ውጤት ሲመጣ የተከሠተ የዘር ቀውስ ነው፡፡

ዳውን ሲንድረም ያለባቸው ልጆች ከውልደታቸው ጀምሮ የተለያዩ ምልክቶች ይታይባቸዋል፡፡ እነርሱም ፡- የሰውነት ጡንቻ መልፈስፈስና አቅም ማጣት፣ ትንሽ ጭንቅላት፣ ትንሽ ጆሮ፣ ትንሽ አፍ፣ አጭር አንገትና ከአንገት ጀርባ ደግሞ ከመጠን ያለፈ የተረፈ ቆዳ፣ ሰፋፊ አፍንጫ ናቸው፡፡

የሕመሙ ምልክት ከዚህም ከፍ ሲል በቋሚነት የሚገለጥባቸው መንገዶች አሉ፡፡ ለምሳሌ ፡- የዕውቀት ጉድለት፣ ከሌሎች ሰዎች ያነሰና ሾጠጥ ያለ ራስ ቅል፣ የልብ ሕመም፣ ጆሮአቸው ድምጽ መሰብሰብ አቅሙ አናሳ የሆነና የመስማት ችግር ያለበት፣ በሽታ የመከላከል አቅም ማጣት፣ በአፍ መተንፈስ፣ ከመጠን በላይ የሆነ ውፍረት፣ የእንቅልፍ ችግር ፣ የእይታ ችግር ወዘተ …ናቸው፡፡

እንዲሁም ኦቲዝም (Autism) የተባለውን ብንመለከት ኦቲዝም በማኅበራዊ መስተጋብር እና ግንኙነት ፣ እንዲሁም በተገደበ እና ተደጋጋሚ በሆነ ባሕርይ ተለይቶ የሚታወቅ የእድገት በሽታ ነው፡፡ ኦቲዝም ያለባቸው ወላጆች በልጆቻቸው ሕይወት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ዓመታት ውስጥ ምልክቶችን ያስተውላሉ፡፡

ሌላው አልዛይመርን ብንመለከት አብዛኞቹ የሳይንስ ሊቃውንት በሰዎች ላይ አልዛይመር የሚከሠተው በአንጎል ላይ ተጽዕኖ በሚያሳድሩ የዘረ መላዊ ፣ የአኗኗር ዘይቤዎች እና አካበቢያዊ ምክንያቶች ውሕደት በመፍጠር እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ከአንድ በመቶ በታች የሆነው የአልዛይመር በሽታ የሚከሠተው በተወሰኑ ሰዎች ላይ በዘር ለውጦች ምክንያት ነው፡፡

ግን ዋና ዋና ምልክቶቹ የማስታወስ ችሎታ መቀነስ፣ ግራ መጋባት ፣ የአእምሮ ማሽቆልቆል፣ የመረዳት ችግር፣ በምሽት ሰዓታት ግራ መጋባት፣ መገለል፣ መርሳት፣ የትኩረት ማነስ፣ ትውስታዎችን አለመፍጠር፣ የተለመዱ ነገሮችን ለይቶ አለማወቅ፣ ጠብ መፍጠር፣ ብስጭት፣ ራስን በተገቢው መልኩ አለመንከባከብ፣ ትርጉም የለሽ ቃላትን መደጋገም፣ እረፍት ማጣት፣ እየተንከራተቱና ሲጠፉ መዋል፣ ሥነ ልቦናዊ ድብርት ወዘተ ናቸው፡፡

እነዚህ ከላይ ያየናቸው የሾተላይ የዳውን ሲንድረም፣ የኦቲዝም፣ የአልዛይመር  ምልክቶች ተብለው የተጠቀሱት በሙሉ ክፉ መናፍስት/አጋንንት፣ ዛር፣ ዓይነ ጥላ፣ ብዳ ወዘተ/ በሕፃናት እና በልጆች እንዲሁም በአዋቂዎች ላይ ሲያድሩ የሚታዩ ምልክቶች ናቸው፡፡ አንዳንዱ ላይ መልክአ አጋንንት ተሥሎባቸው የሚወለዱ አሉ፡፡ ያ ማለት አስፈሪ ገጽታን ተላብሰው የሚታዩ፤ ሲያዩዋቸው የሚያሳዝኑ ሳይሆን የሚያስፈሩ ልጆች ሆነው ይታያሉ፡፡

አጋንንት ከሥጋቸው ሲዋሐዱ ራሱን በሰው ገጽታ ሲገልጽ ልጆቹ አስፈሪ ገጽታን እንዲላበሱ ያደርጋል፡፡ ዛር እና ዓይነ ጥላ የልጆች ፊት ላይ ሲቀመጥ እራሱን በመሳል እራሱን በመምሰል ከተፈጥሮ ወጣ ያለ ገጽታ እንዲኖራቸው ያደርጋሉ፡፡

እነዚህ ችግሮች በጊዜ ከታወቁ በጸሎት፣ በጸበል በእምነት እና በቅብዓ ቅዱስ መፍትሔ እና ድህነት የሚገኝባቸው ናቸው እምነት ትእግስት ፅናት ላላቸው፡፡ ካልሆነ ግን ችግሩን እና በዚህ የተቸገሩትን ልጆች ይዞ መኖር ነው፡፡

❤ 4ኛ/ መተት ፦

አንድ ሰው በአንድ ሰው በመቅናት የሚያደርገው የምቀኝነት የአጋንንት ሥራ ነው፡፡ መተት በትዳር ዕድል በልጅ በባል/በሚስት በመቅናት የሚደረግ ክፉ አሠራር ነው፡፡ በትዳር ላይ መተት ከተደረገ ፈጣን የባሕርይ ለውጥ ማምጣትና ሰላም ማጣት ከዛም እስከ መለያየት የሚደርስ መጠላላት በመሃላቸው ሊፈጥር ይችላል፡፡ ታዲያ ሁለቱም በተለይም የተጋቢዎች ወገን የአጋንንቱን አሠራር ባለመረዳት ፍቺን እንደ አማራጭ በማየት በችኮላ፣ ትዕግሥት በማጣት አጋንንቱን ይተባበራሉ፡፡

የቤተሰብ ጣልቃ መግባት ለአጋንንቱ ጥሩ ከለላ ስለሚሆንና ቤተሰብን በጐ በመሰለ ሐሳብ በመደገፍ ይገባባቸውና በእነርሱ አድሮ የመለያየትን ሥራ ይሠራል፡፡ የሚያሳዝነው ሁለቱ ተፋቺዎች ምክንያት ያለው በሚመስል ባልታወቀ ምክንያት ተለያይተው ሌላ ቢያገቡ ትዳራቸው ከድጡ ወደ ማጡ ነው የሚሆንባቸው፡፡ ቀድሞ አጋንንት ስላፋታቸው ሁለተኛው ትዳር ውስጥ ጣልቃ በመግባት ማበጣበጥ ሰላም መንሳት ይጀምርና ያለያያል፡፡

በዚህም ተፋቺው ‹ትዳር› የሚባለው ነገር ሲነሳ ግፍግፍ በማለት ለልጆቻቸውና ለወዳጆቻቸው የትዳርን መጥፎ ገጽታ ብቻ በመናገር ቤተሰብን ተጽዕኖ ውስጥ በመክተት ታናናሾችንና ልጆችን ‹ትዳር ከእርሷ ወዲያ ላሳር› በማለት ትዳርን እንዲፈሩ ፈርተውም እንዳያገቡ በማድረግ ቆሞ ያስቀራል፡፡

ለዚህ መፍትሔው በትዳር ያልተጠበቀ ክሥተት ሲፈጠር መጸለይና አባቶችን በጸሎት እንዲረዱ ማድረግ፣ በተቻለ አቅም ጠበል መጠመቅ፣ ችግሩን ማወቅና ለችግሩ መፍትሔ ማግኘት ይቻላል፡፡

ወዳጆቼ በትዳር በመቅናት የሚመተት መተት ልክ እንደ ዛር እና ዓይነ ጥላ ፅንስ ሊያጨናግፍ እና ፅንስን በማኅፀን ውስጥ ሊያጠፋ ይችላል፡፡ በተለይ እርጉዝ ሴት ሆና የመተት አጋንንት ከተላከባት በማሕፀኗ ውስጥ ያለውን ፅንስ ስለሚመታውና ስለሚያድርበት ፅንሱ ሊጨናገፍ እና ሊጠፋ ይችላል፡፡


❤ #_የርኩሳን_መናፍስት_ፈተና_በትዳር_ሕይወት ❤

#_ክፉ_መናፍስት_በትዳር_እና_በሩካቤ_ሥጋ_ጣልቃ_መግባት

ወዳጆች ሆይ ክፉ መናፍስት በትዳር ሕይወታችን፣ በሩካቤ ሥጋ ደስታችን እንዴት ጣልቃ እየገቡ እንደሚበጠብጡ እና እንደሚያናውጡ በዝርዝር እናያለን። እኔ ሳልሰለች የጻፍኩትን እናንተ ሳትሰለቹ አንብቡት።

❤ 1ኛ/ ዓይነ ጥላ

ዓይነ ጥላ ገርጋሪ ምቀኛ ክፉ መንፈስ ነው፡፡ ይህ ክፉ መንፈስ አድብቶ በመተናኮል ዕድላችንን በመዝጋት እጃችን ገባ ያልነውን ነገር በማሳጣት ይተናኮላል፡፡ ዓይነ ጥላ አብረውን ከሚወለዱና ተወልደን ከጊዜ በኋላ ከሚጠናወቱን ክፉ መንፈስ አንዱ ነው፡፡

ዓይነ ጥላ ያለባቸው ባል ወይም ሚስት በትዳራቸው ሰላም፣ ፍቅር፣ መግባባት በመሃላቸው በፍጹም አይኖርም፡፡ በተለይ በሩካቤ ሥጋ አይስማሙም፣ አይጣጣሙም፣ አይግባቡም፡፡

የዓይነ ጥላ መንፈስ ተጠቂ ከሆኑ እንኳን ሩካቤ ሥጋን በመፈቃቀድ ሊፈጽሙ ቀርቶ አብሮ መተኛት መተቃቀፍ አይወዱም፡፡ መንፈሱ የባልን ሰውነት ወይም የሚስትን ሰውነት እንደ ባዕድ አካል በማሳየት እንዲቀፈው/እንዲቀፋት በማድረግ ምክንያት የሌለውን ጥላቻ በመሃላቸው ይዘራል፡፡ በሩካቤ ሥጋም ደስታ የሚባል ያሳጣቸዋል፡፡ ሩካቤ ሥጋን የሚፈጽሙት ስለተጋቡ ብቻ እንጂ ወደውና ፈቅደው አይደለም፡፡ ደመ ቀዝቃዛ ያደርጋቸዋል፡፡

ከትዳር በፊት ወደ ሕይወታቸው ሰተት ብሎ የገባው መንፈስ በትዳራቸው ውስጥ ራሱን በተለያየ ጠባይና መልክ በመግለጥ፣ ለትዳራቸው መበጣበጥ እና መናወጥ ምክንያት ይሆናል፡፡ በማግባታቸው የተበሳጨው ዓይነ ጥላ በትዳር ኑሮአቸው ውስጥ የበቀል መርዙን እየረጨ፣ ትዳሩን እያቀጨጨ ለፍቺ ይዳርጋል፡፡

ዓይነ ጥላ በትዳር ሕይወት ሰላም በመንሳት እና በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ስሜት በማጥፋት፣ የሩካቤ ሥጋ ደስታን በማበላሸት የተካነ ስለሆነ የመንፈሱን ጠባይ አውቃችሁ ልትነቁበት እና በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ልትዋጉት እንዲሁም በቅዱስ ቁርባን ጸጋ ከሕይወታችሁ ልታርቁት ይገባል፡፡ ምክንያቱም መንፈሱ ሸፍጠኛና ከጠባይ ጋር የሚመሳሰል በመሆኑ የብዙዎችን ትዳር ለፍቺ አብቅቷል፡፡

❤ 2ኛ/ ዛሮች፦

ከሁለት አንዳቸው ዛር እና የዛር ውላጅ፣ ወንድ ወይም ሴት ዛር ካለባቸው ትዳራቸው አደገኛ ችግር ውስጥ ይገባል፡፡ ዛሩ ስለሚቀና ባልና ሚስትን ለማተራመስ ኩርፊያን፣ ንትርክን ጭቅጭቅን፣ ብስጭትን፣ አለመግባባትን፣ አለመተዛዘንን፣ ጥላቻን እንደ ግብዓት በመጠቀም ፍቅርን በማቀዝቀዝ ትዳሩን በፍቺ መንገድ እንዲጓዝ ይዳርጋል፡፡

ባስ ሲልም ደም የለመደ ዛር ከሆነ ጸብ በማንሳት ደም ያፋስሳል ከተቻለም ነፍስ ያዋድቃል፡፡ ዛሩ በአባትና በእናት ላይ ካለ በግንኙነት ወቅት ከዘር ጋር በመዋሐድ በማኅፀን ከፅንሱ ጋር አድጐ በመወለድ ደባል ሆኖ ያድጋል፡፡ ዛር እስከ ሰባት ትውልድ ድረስ በመውረድ ቤተሰብን በማፈራረስ ሰላማቸውን በመደምሰስ ቤተሰብን ይዘበራርቃል፡፡

ዛር ልጆች ከተወለዱ በኋላ በልጆች እእምሮ በማደር አእምሮአቸውን በመዝጋት ትምህርት እንዳይገባቸው በማድረግ ቤተሰብንና ተማሪውን ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ በዚህም ልጁ በቤተሰብ እንዲጠላ ያደርገዋል፡፡ ፍራቻን እያስተማረ ያሳድገውና በራስ መተማመኑን በማጥፋት ለቤተሰቡ ለሀገሩ ደንታ ቢስ በማድረግ ውድ ሕይወቱን በመውረስ ለራሱ ለጥፋት ዓላማ ይጠቀምበታል፡፡

ሌብነትን፣ ወንጀልን፣ ክፉ ሱስን፣ መጠጥን፣ ዝሙትን፣ ጠበኛነትን እና ነውጠኝነትን በማስለመድ ምግባረ ቢስነትን በማላበስ የእርግማን ትውልድ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ወላጆች ሆይ ልጆች የሚታነጹት በእናንተ መልካምና እኩይ መሠረት ላይ ስለሆነ ዛሬ እንደ ቀልድ የዘራችሁትን ነገ መከመር እስኪያቅታችሁ ድረስ ስለምታጭዱ ልትጠነቁና በእውነተኛው መንገድ ልትሄዱ ይገባል፡፡ ዛሬ ‹‹የተረገመ ያልተባረከ›› እያላችሁ የምትረግሙት ልጅ ትላንት የናንተ ወይም የቤተሰባችሁ ጠንቅ ተርፎት ነውና ልታዝኑላቸው ይገባል፡፡

የዛር መንፈስ አንዱ መጥፎ መገለጫው በዓል በመጣ ቁጥር ለምሳሌ በዘመን መለወጫ፣ በገና እና በትንሣኤ በዓላት የቤተሰቡን ደስታ ለማጥፋት እና ሰላም ለመንሳት የማይረባ እና ውኃ የማያነሳ አለመግባባትንና ጠብን ተጠቅሞ ቤተሰቡን በማተራመስ፣ የበዓሉን ዐውድ ያጠፋባቸዋል፡፡

ወዳጆቼ በባል ወይም በሚስት ላይ የራሳቸው  አልያም የዛር መንፈስ ካለ ካላወቁበት እና ካልነቁበት መቼም ቢሆን በዓል በመጣ ቁጥር መጣላታቸው፣ በዓልን በኩርፊያ ማሳለፋቸው አይቀርም፡፡ እንዲሁም ከሁለት አንዳቸው ላይ በሕመም ተመስሎ በመቀመጥ ለበዓል የደስታ መዋያ ያሰቡት ገንዘብ የሐኪም ቀለብ ያደርጋል፡፡

ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ በተለይ የወንድ ዛር በሴቷ ላይ ካለ ከባሏ ጋር ሩካቤ ሥጋ መፈጸም ቀርቶ አብሮ መተኛት እና ማውራት ያስጠላታል፡፡ ሌሊት ከባሏ አጠገብ ተኝታ በእንቅልፍ ልቧ የወንድ ዛሩ ይገናኛታል፡፡ በደመ ነፍስም በተኛችበት የሚጫናት፣ የሚነካት፣ ሰውነቷን የሚዳስሳት ሰው መሰል ነገር ይሰማታል፡፡

እንዲሁም ሴት ዛር በወንዱ ላይ ካለች በተለይ በስንፈተ ሩካቤ ይጠቃል፡፡ በሕልመ ሌሊትም እጅጉን ይመታል፡፡ ጠባዩ እየተቀያየረ በውኃ ቀጠነ ይጨቃጨቃል፣ እንደ ሕፃን ይነጫነጫል፡፡ ሚስቱ ታስጠላዋለች፡፡ አብሯት ቢተኛም ሩካቤ ሥጋ ለመፈጸም እጅጉን ይቸገራል፡፡ በባል ላይም ሴት ዛር ካለች በሚያውቃት እና በማያውቃት፣ በቤተሰብ እየተመሰለች ሌሊት በተኛበት ትገናኘዋለች፡፡

❤ 3ኛ/ ፅንስን የሚያጨናግፉ እና በማሕፀን የሚገድሉ ክፉ መናፍስት/ሾተላይ ፦

ብዙዎች በተደጋጋሚ የፅንስ መጨናገፍ እና በማኅፀን ውስጥ የፅንስ መጥፋት ያጋጥማቸዋል፡፡ በተለይ በማኅፀን ውስጥ ፅንስ ሲጠፋ በሕክምናው ሾተላይ ተብሎ ስም ይሰጠዋል፡፡

ሕክምናው የሕክምናውን ጥበብ እንጂ የክፉ መናፍስቱን ተንኮል ስለማያውቅ ከቤተሰቦቻችን በወረስናቸው፣ በራሳችንም ባመጣናቸው የዛር መንፈስ እንዲሁም በዓይነ ጥላና እና በመተት በድግምት ፅንስ እንደሚጨናገፍ እና በማኅፀን እያሉ እንደሚጠፋ አያውቅም፡፡ ስለዚህ የተጨናገፈውና በማኅፀን የሚጠፋው ፅንስ ሁሉ ሾተላይ ይባላል፡፡
አጅሬም በሾተላይ ስም ራሱን ሰውሮ ሥራውን በገሃድ ይሠራል፡፡

በነገራችን ላይ ሕክምናው በተደጋጋሚ  ፅንስ የመጨናገፍ ችግር የሚገጥማቸውንና የፅንሱን የመጨናገፍ ምክንያት በውል የማያውቃቸውን ‹‹መንስኤው የማይታወቅ›› ወይም በሕክምናው ቋንቋ ‘አይድዮ ፓቲክ’ ይለዋል፡፡

በሕክምናው ሾተላይ የሚባለው አንዲት ሴት የደም ዓይነቷ አር ኤች ኔጌቲቭ /Rh-/ ሆኖ ከዚህ በፊት አር ኤች ፖዘቲቭ /Rh +/ የሆነ ደም  ወደ ሰውነቷ ሲገባ አር ኤች ፓዘቲቭ የሆኑ የደም ሕዋሶችን የሚያጠፋ ንጥረ-ነገር በደሟ ውስጥ ይመረታል፡፡ ይህ ንጥረ-ነገር አንዴ ከተመረተ በደሟ ውስጥ እስከ ሕይወት ፍጻሜ ድረስ ይኖራል፡፡

በዚህም በማኅፀንዋ ውስጥ የያዘችውን ፅንስ የደም ዓይነቱ አር ኤች ፖዘቲቭ ከሆነ የተመረተው ንጥረ-ነገር ፅንሱን እንደ ባዕድ አካል ስለሚቆጥረው ያጠቃዋል ፅንሱም ይጠፋል በማለት ይገልጻል፡፡

ወዳጆቼ ከላይ እንዳየነው ሾተላይን ወደ መንፈሳዊው ዓለም ስናመጣው ፅንስን የሚያጨናግፍ እና በማኅፀን እንዳለ የሚያጠፋው የቅድመ አያቶቻችን፣ የአያቶቻችን፣ የእናት አባታችን ዛር እንዲሁም ዓይነ ጥላና እና መተት ድግምት ነው፡፡ አጋንንት፣ ሰይጣን፣ ዛር፣ ዓይነ ጥላ ፅንስን ተዋሕደው በማጨናገፍ ይታወቃሉ፡፡


«በቃና ዘገሊላ ከብካብ ኮነ፣ ወሰማይኒ ረስዮ ወይነ፤»

(በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር ሰርግ ሆነ፤ውኃውንም ወደ ወይንነት ለወጠው።) ዮሐ ፪፥፩-፲፩

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ አውራጃ በዳዊት ከተማ በቤተልሔም ምድረ ኤፍራታ ተወልዶ በሠላሣ ዘመኑ በሠላሣ ዓመተ ምሕረት በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ጾመ ጸለየ፤ በጠላት ዲያብሎስ ተፈተነ። ፈተናውን ድል አድርጎ ሱባኤውን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን ከእናቱ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ጋር በመሆን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር በሰርግ ቤት ተገኝቶ ቤተ ከብካቡን በትምህርቱ በተአምራቱ ባረከ።

 ኢየሱስ ክርስቶስ ይኽን ድንቅ ተአምር በቃና ዘገሊላ ያደረገው በገዳመ ቆሮንቶስ ሱባኤውን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን የካቲት ፳፫ ቀን ነው። ይሁንና አባቶቻችን ሊቃውንት «የውኃ በዓል ከውኃ በዓል ጋር መቀናጀት አለበት» በማለት በጥምቀት በዓል ማግስት ጥር ፲፪ ቀን እንዲከበር አድርገውታል። እኛም ይኽንኑ ቀን ጠብቀን በዓሉን በማክበር ላይ እንገኛለን።

በቃና ዘገሊላ የተደረገው ይኽ ተአምር በዮሐንስ ወንጌል በምእራፍ ፪ ከቁጥር ፩-፲፩ ድረስ ተጽፎ ይገኛል። በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘውና በዚህ ስም ሊጠራ የቻለው አምላካችን፣ ጌታችንናመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍልበምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈጸመው ተአምርምክንያት መነሻነት ነው። ከቅዱስ መጽሐፍ ላይ ተጽፎ የሚገኘው ሙሉ ቃል እንዲህ ይላል፦

«በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤ ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ። የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት። የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው። ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት። እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው። አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር። ኢየሱስም። ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው። አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም። አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ። ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው። ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።»

በቃና ዘገሊላ የተፈጸመው ይኽ ሰርግ ሙሽራ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንድናስብና እንድናስታውስ ያደርገናል። ሚዜው የሙሽራው አገልጋይ ነውና መጥምቁ ዮሐንስ ሙሽራ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ መደሰቱንና ሊያገለግለው የተዘጋጀ መሆኑን ሲያስረዳ ፦ «ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።» ዮሐ ፫፥፳፱-፴ ይለናል። በቃና ዘገሊላ በሰርጉ ቤት ተገኝቶ ተአምሩን የጀመረው ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ እና ከሐዋርያት ጋር አብሮ ነበርና አማላጅ እና ተማላጅ ማን እንደሆነ በልዩ ምሥጢር ተስተውሎበታል። ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ በተከታታይ ልዩ የሆነውን ብሥራት ሲያሰማ እንዲህ በማለት ጽፎልናል፦ በስድስተኛው ወር ማለትም መልአኩ ገብርኤል ካህኑ ዘካርያስን

«ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።» ካለው በኋላ ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በክብር ተገልጦ «ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ።» ብሏታል።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በአብሣሪው መልአክ በቅዱስ ገብርኤል እንደተነገራት በእውነት ጸጋን የተሞላች ናትና በሰርግ ቤት የጎደለውን የጓዳውን ምሥጢር ተረድታ የሠርጉ ሥነ-ሥርዓት በሠመረና በተዋጣለት ሁኔታ እየተከናወነ ድንገት የወይን ጠጅ በማለቁ ተጨንቀውና ግራ ተጋብተው አስተናባሪዎቹ በታወኩበት ሰዓት የጭንቅ አማላጅ ናትና ወደ ልጅዋ ወደ ወዳጅዋ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘወር ብላ «ወይን እኮ የላቸውም»በማለት አሳስባ ባዶ የሆኑት የድንጋይ ጋኖች ውኃ ተሞልተው ጣፋጭ ወይን ጠጅ ተገኝቶባቸዋል።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ«እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ። ፩ጢሞ ፫፥፲፮ በማለት እንደጻፈልን ከድንቅ በላይ ድንቅ በሆነ ተዋሕዶ በሥጋ መገለጡ ከእመቤታችን ተወልዶ ነውና በልደቱ ጊዜ አብራ እንደነበረችው እንዲሁ ደግሞ በሞቱ ጊዜ ከእርሱ እንዳልተለየች እንረዳለን።

ይኽንንም ወንጌላዊው ዮሐንስ «ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።» ዮሐ ፲፱፥፳፭ በማለት በጻፈልን መልእክት ለማወቅ ችለናል።

በመጀመርያ በልደቱ በኋላም በሞቱ ጊዜ አብራው የነበረች ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመኗን በሙሉ በፍጹም  እንዳልተለየችው ተአምሩን በጀመረበት በቃና ዘገሊላም አብራው ነበረችና ዛሬ ትውልዱ ሁሉ የሚኮራበትን የአማላጅነት ሥራ በቃና ዘገሊላ ፈጽማለች።

«አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ» በሚለው ቃል ብዙዎች ተሰናክለውበት ቢገኙም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን አምልተውና አስፍተው ምሥጢራትን የነገሯቸው የተዋሕዶ ልጆች ግን በእናትና በልጅ መካከል ያለውን የንግግር ዘይቤ ተረድተው እውነቱን ሲመሰክሩ ይኖራሉ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣውን አብሳሪ መልአክ«እንደ ቃልህ ይደረግልኝ» እንዳለችው ኢየሱስ ክርስቶስም እመቤታችንን «ከአንቺ ጋር ምን አለኝ» (እንደ ቃልሽ ይሁን) በማለት ጥያቄዋን መልሷል፤ ምልጃዋን ተቀብሏል።

«ጊዚዬ አልደረሰም» በማለት ቢናገርም ስለ እናቱ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ሲል የእናቱን ልመና ተቀብሎ ተአምራቱን ፈጽሟል። እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሳይነግሯት በልባቸው ያለውን የምታውቅ እናት ናትና የሰርጉ አስተናባሪዎችን ኃዘን ተመልክታ ከልጇ ከወዳጇ አማልዳ የጎደላቸውን እንደሞላች ለእኛም ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል ብላ በተፈጸመላት ቃል ጎዶሏችንን ትሙላልን። የሰዎችን ጭንቅ አውቃ ሳይነግሯት ያማለደች እናት ስሟን ጠርተው ለሚለምኗትማ የበለጠ ታደርጋለችና ሁላችንንም በተሰጣት ጸጋ ታማልደን።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨




ደብተራዎቻችን Vs Psychiatry

Psychiatry ከህክምና ዘርፎች አንዱ ሲሆን ትኩረት አድርጎ የሚሰራው የአእምሮ በሽታዎች ላይ ነው። ይህ የህክምና ዘርፍ ለመፈወስ ከሚሰራባቸው በሽታዎች መካከል፦ የመርሳት ችግር ፣ ከእውነታ ማፈንገጥ ፣ አስከፊ የፀባይ መለዋወጥ እና ከአስተሳሰብ ጋር ተዛማጅ የሆኑ በሽታዎች ተጠቃሽ ናቸው።

   የምእራቡ አለም ምሁራን ይህን የህክምና አገልግሎት እንደ አንድ ዘርፍ ተቀብለው በዘመናዊ መንገድ መስጠት የጀመሩት ወደ ሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን መባቻ ነበር። በተለይ በጣም አስቸጋሪ ለሆኑ የአእምሮ በሽታዎች መድሃኒት ማግኘት የጀመሩት 21 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ ቢሆንም አሁን ድረስ ፈዋሽ መድሃኒት ያላገኙላቸው በሽታዎች አሉ።

ወደኛ ስንመለስ ደብተራ (ሊቃውንት) አያቶቻችን የአእምሮ በሽታዎችን መፈወስ የጀመሩት ከአምስት ሺህ ዘመናት በፊት አንስቶ ነው። አያቶቻችን ይህን የአእምሮ በሽታዎችን የመፈወስ ጥበብ ያገኙት ከኖህ አባታቸው ነው። በመፅሐፈ ኩፋሌ ላይ እንደተፃፈው የኖህ ልጆች የአእምሮ በሽታ አጥቅቷቸው ነበር። ኖህም ልጆቹን የሚፈውስበትን ጥበብ በፀሎት ጠየቀ። እግዚአብሔርም መለሰ! መድሃኒት የሚቀምምበትን እና ለዚሁ ህክምና አገልግሎት የሚውሉትን እፅዋትና ማዕድናትን ገለፀለት። ኖህ ያገኘውን ጥበብ በመጠቀም ልጆቹን ፈወሰ። ጥበቡ ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሻገር ዘንድ በመፅሐፍ ፅፎ አለፈ።

ይህን መፅሐፍ መሰረት አርገው ኢትዮጵያውያን ደብተራዎች መፅሐፍቱን በሁለት መልኩ ከፍለው ፃፏቸው።

1. የመጀመርያ እፀ ደብዳቤ ይሰኛል። 2. ሁለተኛው እንቁ አእባን ይሰኛል።

እፀ ደብዳቤ፦ የሰባት መቶዎቹን እፅዋት ዝርዝር ፣ አቀማመማቸው፣ ለምን በሽታ ፈውስ እንደሚሰጡና ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን የያዘ ነው።   እንቁ አእባን፦ እርሱ ደግሞ የማዕድናት ዝርዝሮችን የያዘ ሲሆን ለህክምና አገልግሎት የሚውሉ ማእድናትን ዝርዝር መረጃ የያዘ ነው።

ደብተራ አያቶቻችን በዚህ አላቆሙም ከላይ የጠቀስኳቸውን መፅሐፍት መሰረት አርገው የራሳቸውን ጥናትም በማካተት የተለያዩ የአእምሮ በሽታ መፈወሻ ጥበብ የያዙ የህክምና መፅሐፍትን አዘጋጁ።

ከነኚህ መፅሐፍት መካከል ዋንኛዎቹ የሚከተሉት ናቸው፦
፩ኛ. መፍትሔ ሥራይ ( በስሩ ከሰላሳ በላይ የሚሆኑ መፅሐፍትን አካቷል)                                                                                                ፪ኛ. መፅሐፈ አፍልሆ                                                                                                                                                                  ፫ኛ. መፅሐፈ ነድራ                                                                                                                                                                    ፬ኛ. መፅሔተ ሠለሞን
፭ኛ.መርበብተ ሠለሞን
፮ኛ.መጽሓፈ ባርቶስ..ወዘተ ናቸው።

እነዚህ ሁሉ ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደተዘጋጁ አሁን ድረስ ያሉ ደብተራዎች ይናገራሉ። በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት እነኚህ የህክምና መፅሐፍት የማይፈውሱት የአእምሮ በሽታዎች የሉም። ዛሬ ድረስ ሳይንስ መድሃኒት ያላገኘላቸው የአእምሮ በሽታዎች በነኚህ መፅሐፍት ይፈወሳሉ።

ያሳዝናል … እውነታው ይህ ቢሆንም ግን ይህን በደብተራ አያቶቻችን ጥረት ከዚህ ዘመን የደረሰው ይህ አገራዊ ህክምና በአገራችን “ዘመናዊ” ሀኪሞች “ባህላዊ” ተብሎ የተናቀ በማህበረሰቡም ” ጥንቆላ” ተብሎ ገሸሽ የተደረገ በመንግሥት ትኩረት ያልተሰጠው ጥበብ ነው።

እውነታው ግን  ከላይ የጠቀስኳቸው መፅሐፍት እንዳለ በጀርመን ፣ በእንግሊዝ እና ፈረንሳይ ውስጥ በሚገኙ የህክምና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ጥናት ይደረግባቸዋል። ከዚህም አልፎ በፈረንሳይኛ እና በእንግሊዘኛ ቋንቋ ተተርጉመው በትላልቅ ጥራዞችም ታትመዋል። ለማስረጃም በእጄ ላይ የሚገኙ አሉ።

የዚህ ፅሁፍ መልእክት ሁለት ነው።

፩ኛ. ለበርካታ ሺህ ዘመናት አገራዊ የሆነውን ጥበብ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማሻገር ታላቅ መስዋእትነት ለከፈሉት ደብተራ አያቶቻችን እውቅና መስጠት ሲሆን …

፪ኛ. በአገራዊ እውቀት ዙሪያ መነቃቃትን መፍጠር ነው። አገራዊ የሆኑ እውቀቶችን ከዘመኑ ጋር አስታርቀን ብንገለገልባቸው ምክሬ ነው።

መርጌታ አምደብርሃን !




የባህል ሕክምና ከዘመናዊ ሕክምና የተለየ ጥበብን እንደሚፈልግ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ በተፈጥሮና በሳይንስ መካከል ያለውን ሚዛናዊነት የማስጠበቅ ባህሪ እንዳለውም የዘርፉ ባለሙያዎች ይስማማሉ፡፡ አንድ የባህል ሐኪም ለታማሚው ፈውስ ለመስጠት የታማሚውን አካላዊ፣ አዕምሯዊና መንፈሳዊ ሁኔታ በጥልቀት ማጤን ይጠበቅበታል፡፡ ይህም የተለየ ጥበብንና ተሰጥኦን የሚጠይቅና ለተመረጡ ሰዎች ብቻ የሚሰጥ ፀጋ ተደርጎ ይታሰባል፡፡

በባህላዊ ሕክምና መድኃኒቱ ከሚቆረጥበት ዕለትና ጊዜ ጀምሮ መደረግ ያለባቸው ጥንቃቄዎች አሉ፡፡ ዕፀዋት የተፈጠሩት በዕለተ ማክሰኞ ነው ተብሎ ስለሚታመን ባህላዊ ሐኪሙ ለመድኃኒትነት የሚውሉ ዕፀዋትን የሚቆርጠው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ መድኃኒቱን ለመቁረጥ ከመውጣቱ አስቀድሞ መደረግ ያለባቸው የተለያዩ ጥንቃቄዎችም አሉ፡፡

ለምሳሌ አንድ የአፋር ብሔረሰብ የባህል ሐኪም የሚከተላቸው የመድኃኒት ዕፀዋት አቆራረጥ ሥነ ሥርዓት አሉት፡፡ የአፋር ብሔረሰብ ባህላዊ እሴቶች በሚል ርዕስ በተዘጋጀው መጽሔት መሠረት፣ ሐኪሙ መድኃኒት ለመቁረጥ ከቤቱ መውጣት ያለበት በቀን በተወሰኑና ሰው በማይበዛባቸው ሰዓታት ነው፡፡ መድኃኒት ለመቁረጥ በአካልም ሆነ በአዕምሮ ንፁህ መሆን ግድ ነው፡፡ በአዕምሮ ተንኮል እያሰላሰሉ መድሐኒት መቁረጥና ለታማሚው መስጠት ዋጋ ዋጋ የለውም ተብሎ ይታሰባል፡፡ ለዚህም በተቻለው ሁሉ ተንኮል አለማሰብ አለበት፡፡ መድሐኒቱን ከመቁረጡና ከቆረጠ በኋላ ከቅዱስ ቁርዓን ውስጥ የተወሰኑ አንቀጾችን መቅራት አለበት፡፡

አንዳንድ በምሽት ሲቆረጡ ዕርኩስ መንፈስ የማዝያስ ባህሪ ያላቸው ዕፀዋት አሉ ተብሎ ስለሚታሰብ አብዛኞቹ የብሔረሰቡ የባህል ሐኪሞች መድኃኒት መቆረጥ ያለበት በቀን እንደሆነ ይስማማሉ፡፡ በረመዳን ወር፣ በአረፋና በመውሊድ በዓላት ዕለት የመድኃኒት ዕፅ አይቆረጥም፡፡ ዝናብ በሚዘንብበት ጊዜ መድኃኒት መቁረጥም አይመከርም፡፡ የተቆረጠው መድኃኒት ቤት እስኪገባ ድረስ በምንም ዓይነት ውኃ ሊነካው አይገባም፡፡

በዚህ መለኩ መድኃኒቱ ከተቆረጠ በኋላ ሕክምናውን ለመስጠት ከታማሚው ጋር ቤተሰባዊ ግንኙት መፍጠር ያስፈልጋል፡፡ ሕክምናው ከተደረገለት በኋላ መድኃኒቱ እስኪያሽረው ከማድረግ መቆጠብ የሚገባው አንዳንድ ነገሮችም አሉ፡፡  በክልሉ የባህል ሕክምና ዕውቀት ያላቸው፣ ሕክምናውን ከአሥር ዓመት ዕድሜአቸው ጀምሮ መስጠት ይችላሉ፡፡

አንድ አንድ በኤፍራጥስ እና በጢግሮስ
ወንዞች ዳርቻ ላይ ይኖሩ የነበሩ የሱሜሪያ (በአሁኑ ኢራቅ) ሕዝቦች ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ4,000 ዓመታት በፊት፣ እንዲሁም ግብፆች ከ3,700 ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት ባህላዊ መድኃኒቶችን መጠቀም እንደጀመሩ የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፡፡

ዘመናዊ ሕክምና አስኪጀመር ድረስ ፈውስ የሚገኘውም በባህላዊ ሕክምና ነበር፡፡ ትልቅ በጀት ተይዞለት በቂ ጥናት በሚደረግበት በዘመናዊ ሕክምና የተሻለ ሕክምና ማግኘት እንደሚቻል ብዙዎች ያምናሉ፡፡ ይሁንና በአፍሪካና በእስያ የሚገኙ 80 በመቶ የሚሆኑ ሰዎች የባህላዊ ሕክምና ተጠቃሚ መሆናቸውን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ አንዳንድ ጥናቶች ደግሞ አራት ቢሊዮን የሚሆነው የዓለም ሕዝብ የባህላዊ ሕክምና ተጠቃሚ መሆኑን ያመለክታሉ፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ከሚሰጡ ባህላዊ የሕክምና ዓይነቶች፣ በቻይና ለሚሰጡ የባህል ሕክምናዎች ዕውቅና ከሰጠ ሰነባብቷል፡፡ በባህላዊ ሕክምና ቀዳሚ የሆነችው ይህች አገር እ.ኤ.አ. በ2012 በባህላዊ ሕክምና ብቻ 83 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ችላለች፡፡ ይህ እ.ኤ.አ. 2011 በዘርፉ ካገኘችው ገቢ የ20 በመቶ ብልጫ ነበረው፡፡

ከሌሎቹ አገሮች አንፃር የባህላዊ ሕክምናዎችን ብዙም እንደማይጠቀሙ በሚነገርላቸው በዩናይትድ ኪንግደም አካባቢዎች ለባህላዊ ሕክምና በየዓመቱ 230 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚወጣ የዓለም የጤና ድርጅት ከዓመታት በፊት ያወጣው ሪፖርት ያሳያል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2020 የዓለም የባህላዊ መድኃኒቶች ገበያ 115 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል የሚል ትንበያም አለ፡፡

በዚህ መጠን የአገርን ኢኮኖሚ እያንቀሳቀ የሚገኘው ባህላዊ ሕክምናን ምዕራባውያን ሰፊ ጥናት እያደረጉበት ይገኛል፡፡ በአንፃሩ ግን የበርካታ ባህላዊ መድኃኒቶች መፍለቂያ በሆነችው አፍሪካ በተለይም ኢትዮጵያ ለባህላዊ መድኃኒቶች ተገቢው ትኩረት ሳይሰጥ ቆይቷል፡

ከቻልን ለትብብር እንኳን አቅሙ ባይፈቅድልን ቀደምት የሆነው ሀገራዊ ጥበብን ስሙን ባናጠለሸው ምክሬ ነው።

አምደ ብርሃን!
ለበለጠ መረጃ 0918834904 ብለው ይደውሉ።









20 last posts shown.