#ልዩመረጃ ትናንት ምሽት በደቡባዊ ኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የታየው ክስተት የሰው ሰራሽ ጠፈር ስብርባሪ ወደ ምድር ንፍቀ ክበብ ሲመለስ የተፈጠረ መሆኑን የአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ ለመሠረት ሚድያ አስታወቀ
- ስብርባሪው የቻይና ሺጂያን-19 መንኩራኩር ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል
(መሠረት ሚድያ)- ትናንት ከምሽቱ 1:30 ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ባሉ በርካታ ዞኖች አንድ ግዙፍ 'ክስተት' ሰማይ ላይ መታየቱን በአካባቢ ያሉ ሰዎች መመልከታቸውን ሲናገሩ እና ምስሎችን ማህበራዊ ሚድያ ላይ ሲያጋሩ ቆይተዋል።
በዚህ ዙርያ መሠረት ሚድያ ለአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ (European Space Agency) ማብራርያ የጠየቀ ሲሆን በኢትዮጵያ የታየው ክስተት ሰው ሰራሽ የጠፈር ቁስ ስብርባሪ ወደ ምድር ንፍቀ ክበብ ሲመለስ (re-entry ሲያደርግ) መሆኑን አብራርቷል።
ኤጀንሲው አክሎም ስብርባሪው የቻይናው ሺጂያን-19 (ShiJian-19) ሊሆን እንደሚችል ጨምሮ ገልጿል።
"በየአመቱ ከመቶ ቶን በላይ የሰው ሰራሽ የጠፈር ቁሶች ከቁጥጥር ውጭ ሆነው ወደ መሬት ይመለሳሉ" ብሎ መረጃውን ለመሠረት ሚድያ ያጋራው የአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ ይህም በየአመቱ በመቶዎች ለሚቆጠሩ ክስተቶች መታየት ምክንያት ነው ብሏል።
አክሎም "አንዳንዱ [የጠፈር ቁስ ስብርባሪ] መሬት ላይ ሊወድቅ ይችላል፣ ነገር ግን እንደ ጠፈር ሮኬት ያሉ ሁሉንም ቁሶች ተቆጣጥሮ ሰው በማይኖርበት አካባቢ እንዲወድቁ ማድረግ አይቻልም። አነስተኛ ቁሶች ራሳቸው ተቃጥለው ያልቃሉ፣ ትልልቅ አካላትን ግን ተቆጣጥሮ ወደ ምድር መመለስ ገና እያደገ ያለ ቴክኖሎጂ ነው፣ እድገቱም ዘገምተኛ ነው" በማለት የኤጀንሲው ቃል አቀባይ ለሚድያችን ተናግሯል።
የትናንት ምሽቱ ክስተት እንደ ምዕራብ ጉጂ፣ ወላይታ፣ አርባ ምንጭ እና ሞያሌ አካባቢ መታየቱ የተገለፀ ሲሆን በኬንያ ማርሳቢት ግዛትም መታየቱ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በበኩሉ የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ሁኔታውን በቅርበት እያጣራን እንደሚገኝ አስታውቋል።
የጠፈር ስብርባሪ ማለት አገልግሎታቸው ያበቃ ሳተላይቶች፣ ግልጋሎት የማይሰጡ መንኩራኩሮች፣ የሮኬት ማቀጣጠያ ተተኳሾች፣ ከጠፈር ላይ ግጭት የተረፉ ስብርባሪዎች እንዲሁም በጠፈር በረራ ወቅት ተገንጥለው ያመለጡ ቁሳቁሶች ሊሆኑ እንደሚችሉ መረጃዎች ይጠቀማሉ።
እነዚህ በከፍተኛ ፍጥነት የሚጓዙ ስብርባሪዎች ለሌሎች ሳተላይቶች ስጋት ቢሆኑም መሬት ላይ ላሉ ሰዎች የሚፈጥሩት የሞት ወይም የአካል ጉዳት ስጋት ከአንድ ትሪሊየን ውስጥ አንድ ብቻ መሆኑን የ 'ዘ ኦሮስፔስ ኮርፖሬሽን' መረጃ ይጠቁማል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia
- ስብርባሪው የቻይና ሺጂያን-19 መንኩራኩር ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል
(መሠረት ሚድያ)- ትናንት ከምሽቱ 1:30 ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ባሉ በርካታ ዞኖች አንድ ግዙፍ 'ክስተት' ሰማይ ላይ መታየቱን በአካባቢ ያሉ ሰዎች መመልከታቸውን ሲናገሩ እና ምስሎችን ማህበራዊ ሚድያ ላይ ሲያጋሩ ቆይተዋል።
በዚህ ዙርያ መሠረት ሚድያ ለአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ (European Space Agency) ማብራርያ የጠየቀ ሲሆን በኢትዮጵያ የታየው ክስተት ሰው ሰራሽ የጠፈር ቁስ ስብርባሪ ወደ ምድር ንፍቀ ክበብ ሲመለስ (re-entry ሲያደርግ) መሆኑን አብራርቷል።
ኤጀንሲው አክሎም ስብርባሪው የቻይናው ሺጂያን-19 (ShiJian-19) ሊሆን እንደሚችል ጨምሮ ገልጿል።
"በየአመቱ ከመቶ ቶን በላይ የሰው ሰራሽ የጠፈር ቁሶች ከቁጥጥር ውጭ ሆነው ወደ መሬት ይመለሳሉ" ብሎ መረጃውን ለመሠረት ሚድያ ያጋራው የአውሮፓ ስፔስ ኤጀንሲ ይህም በየአመቱ በመቶዎች ለሚቆጠሩ ክስተቶች መታየት ምክንያት ነው ብሏል።
አክሎም "አንዳንዱ [የጠፈር ቁስ ስብርባሪ] መሬት ላይ ሊወድቅ ይችላል፣ ነገር ግን እንደ ጠፈር ሮኬት ያሉ ሁሉንም ቁሶች ተቆጣጥሮ ሰው በማይኖርበት አካባቢ እንዲወድቁ ማድረግ አይቻልም። አነስተኛ ቁሶች ራሳቸው ተቃጥለው ያልቃሉ፣ ትልልቅ አካላትን ግን ተቆጣጥሮ ወደ ምድር መመለስ ገና እያደገ ያለ ቴክኖሎጂ ነው፣ እድገቱም ዘገምተኛ ነው" በማለት የኤጀንሲው ቃል አቀባይ ለሚድያችን ተናግሯል።
የትናንት ምሽቱ ክስተት እንደ ምዕራብ ጉጂ፣ ወላይታ፣ አርባ ምንጭ እና ሞያሌ አካባቢ መታየቱ የተገለፀ ሲሆን በኬንያ ማርሳቢት ግዛትም መታየቱ ታውቋል።
የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በበኩሉ የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ሁኔታውን በቅርበት እያጣራን እንደሚገኝ አስታውቋል።
የጠፈር ስብርባሪ ማለት አገልግሎታቸው ያበቃ ሳተላይቶች፣ ግልጋሎት የማይሰጡ መንኩራኩሮች፣ የሮኬት ማቀጣጠያ ተተኳሾች፣ ከጠፈር ላይ ግጭት የተረፉ ስብርባሪዎች እንዲሁም በጠፈር በረራ ወቅት ተገንጥለው ያመለጡ ቁሳቁሶች ሊሆኑ እንደሚችሉ መረጃዎች ይጠቀማሉ።
እነዚህ በከፍተኛ ፍጥነት የሚጓዙ ስብርባሪዎች ለሌሎች ሳተላይቶች ስጋት ቢሆኑም መሬት ላይ ላሉ ሰዎች የሚፈጥሩት የሞት ወይም የአካል ጉዳት ስጋት ከአንድ ትሪሊየን ውስጥ አንድ ብቻ መሆኑን የ 'ዘ ኦሮስፔስ ኮርፖሬሽን' መረጃ ይጠቁማል።
መረጃን ከመሠረት!
@MeseretMedia