Posts filter


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ቴምር ሪልስቴት
‼️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው ሱቅ

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate


🔥12ተኛ ዙር የፎሬክስ ትሬዲንግ ውድድር!!! 🔥
(ከሚያዚያ 20 እስክ ግንቦት 1)

1️⃣ 1ኛ ሽልማት🥇 ፡ 60,000 ብር
2️⃣ 2ኛ ሽልማት🥈 ፡ 45,000 ብር
3️⃣ 3ኛ ሽልማት🥉 ፡ 30,000 ብር
4️⃣ 4ኛ ሽልማት🥉 ፡  8,000 ብር
5️⃣ 5ኛ ሽልማት🥉 ፡  8,000 ብር

📌ስለውድድሩ ሙሉ መረጃ ከታች የተቀመጠው የብርፎሬክስ ቴሌግራም አካውንት ላይ ታገኛላችሁ
👉👉👉@birrforex  👈👈👈

⭐️ውድድሩ የፊታችን ሚያዚያ 20 ይጀምራል፣ አሁኑኑ ወደ ብርፎሬክስ ቴሌግራም አካውንት በመሄድ ቦታችሁን ያዙ⭐️


• ፋስት ትራክ አስመጪ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የአይቲ ሶሉሽንስ ኩባንያ አንዱ ነው። እውነተኛ ምርቶችን እና እንደ Canon,Lenovo, DELL,HP,EPSON,APC,Cisco ወዘተ የመሳሰሉ እውነተኛ ምርቶችን የሚሸጡ እንዲሁም ከ30+ የአይቲ አለም አቀፍ ኩባንያዎች ጋር የእዉነተኛ ኦቶራይዝድ ወኪሎች ናቸዉ።

በአሁኑ ጊዜ የኮምፒዉተር አክሰሰሪ ለመግዛት ከፈለጉ ልክ እንደ:
✅Canon 2224 ኮፒየር ፣
✅HP 4003dn ፒሪንተር ፣
✅HP 2600 F1 ስካናር ፣
✅Epson EB-X49 LCD ፕሮጄክተር ፣
✅DELL OPTIPLEX 3000 ኮምፒዉተር
✅TP LINK 8 port ስዊች ፣
✅TP Link 16 port ስዊች ፣
✅TP Link 24 port ስዊች ፣
✅TP Link C20 ራዉተር ፣
⭐️ እያከፋፈሉ ስለሆነ ወይም በጅምላ እየሸጡ ስለሆነ መግዛት ለምተፈልጉ በተመጣጣኝ ዋጋ ይገኛል።

⭐️አድራሻ: ሰላም ሲቲ ሞል ቁ .2 ከጎላጉል ታወር ጀርባ (ሁለተኛ ፎቅ #201)

📞 የበለጠ መረጃ ለማግኘት በስልክ ቁጥር:
⁃ 0942191313
⁃ 0949810000
⭐️ ቴሌግራም ቻናላቸዉን ይቀላቀሉ:
https://t.me/fasttrackimports


የአዲስ አበባ ፖሊስ የሠርግ አጃቢ አሽከርካሪዎችን አስጠነቀቀ

በአዲስ አበባ ከተማ በዓላትና ሰርግን ምክንያት በማድረግ የትራፊክ መጨናነቅ የሚፈጽሙ መንገድ የሚዘጉ አሽከርካሪዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳሰበ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ እንዳሉት፣ ሕብረተሰቡ የጸጥታ አካላት የሚያስተላልፉትን የቅድመ ጥንቃቄ መልዕክቶች በአግባቡ እየተገበረ መሆኑን ተከትሎ በከተማዋ የወንጀል ድርጊቶች እየቀነሱ መምጣታቸውንም ገልጸዋል።

መጪውን የሰርግ ወራት ተከትሎ በከተማዋ የትራፊክ ፍሰት ላይ ያልተገባ የመንገድ መጨናነቅ የሚፈጽሙ አሽከርካሪዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

ከተማዋን በማይመጥን መልኩ መንገድ በሚዘጉና የትራፊክ ፍሰቱን በሚያስተጓጉሉ አሽከርካሪዎች ላይ ተገቢው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድም ተናግረዋል።

Via @mussesolomon


እልፍ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ፋብሪካ

በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ከፍተኛ የትምህርት ዝግጅት እና በቂ ልምድ ባካበቱ ባለሙያዎች እንዲሁም ዘመኑ በደረሰበትን ምርጥ መሳሪያዎች በመጠቀም በተለያየ ዕድሜ ላይ ለሚገኙ ለተለያዩ የእንሰሳት አይነቶች፤ በንጥረ ነገር ደረጃቸውን ጠብቀው የተዘጋጁ መኖዎችን በማቅረብ ለእንሰሳት አርቢዎች በሙሉ የእረጅም ጊዜ ችግራቸውን በአስትተማማኝ ሁኔታ ለመፍታት የተቋቋመ እልፍ የእንሰሳት መኖ ማቀነባበሪያ።

በእልፍ የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ የምንሰጣቸው አገልግሎቶች፦
✅የእንቁላል ጣይ ዶሮ መኖ
✅ለቄብ ዶሮዎች
✅ለእንቁላል ጣይ ዶሮ ጫጩት
✅በተለያዩ ዕድሜ ለሚገኙ የስጋ ዶሮዎች
✅የስጋ ዶሮ ጫጩት(Broiler starter)
✅የስጋ ዶሮ ማሳደጊያ(Broiler
Grower)F1
✅የስጋ ዶሮ ማወፈሪያ (Broiler Finisher)F2
✅ለሚታለቡ የወተት ላሞች(special elif meno)
✅ለጊደሮች
✅ለጥጆች
✅ለስጋ አገልግሎት ለሚደልቡ በሬዎች፣ ፍየሎች፣ በጎች

የበለጠ መረጃ ለማግኘት በስልክ ቁጥር 0113811181/0953535370/
0985858522 ወይም በአካል ቢሮችን ለማግኘት አዲስ አበባ ብስራተ ገብርኤል ባይኔ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 300

ፋብሪካችን: ሰሜን ሸዋ ዞን በልጋ ከተማ አስተዳደር ቱሉፋ ከተማ እንገኛለን ይጉብኙን።


" የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው " - ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመው " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ አስታውቀው ትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ያሉ ሲሆን ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

Via @mussesolomon


ባለሁለትና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ተወሰነ

በነዳጅ የሚሠሩ ባለሁለትና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መወሰኑን፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በተለምዶ ባጃጅ የሚባሉት ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችና ባለሁለት እግር ሞተር ብስክሌቶች ወደ አገር ውስጥ ማስገባት እንደማይቻል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ደኤታ አቶ በሪሁ ሐሰን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትር ደኤታው ይህንን ያሉት ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም. አሃድ ቢዝነስ ግሩፕ፣ በአገር ውስጥ የተመረቱ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ባለሁለትና ባለሦስት እግር ተሽከርካሪዎችን ለገበያ ማቅረቡን በወዳጅነት ፓርክ በተዘጋጀ ሥነ ሥርዓት ሲያስታውቅ ነው፡፡

ኢትዮጵያ በየዓመቱ ለነዳጅ እስከ ስድስት ቢሊዮን ብር እንደምታወጣ የተናገሩት አቶ በሪሁ፣ ‹‹በታዳሽ ኃይል ላይ ያለንን ዕምቅ አቅም ተጠቅመን ከውጭ ከሚገባውን ደረጃውን ያልጠበቀ፣ ነዳጅ ላይ ጥገኛ ከመሆንና አዙሪት ውስጥ ከመግባት ይልቅ፣ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን እንደአማራጭ መውሰድ አለበት "ብለዋል።

Via @mussesolomon


ቻይና የክብደት መጠናቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳሰበች

በቻይና ሰሜናዊ ክፍል ዝናብ የቀላቀለ ከባድ ነፋስ መከሰቱን ተከትሎ የሰውነት ክብደት መጠናቸው ከ50ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳስባለች።

ከሀገሪቱ ደቡባዊ አዋሳኝ ሞንጎሊያ መነሻውን ያደረገው ነፋስ በሰዓት 150 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ቤጂንግ፣ ቲያንጂንን እና ሄበይን ጨምሮ የቻይናን ሰሜናዊ ክፍሎች እየመታ የሚገኝ አሁን ላይ የተከሰተው ከባድ ንፋስ ባለፉት 10 ዓመታት ከተመዘገቡት የመጀመሪያው መሆኑ ተገልጿል።

የተከሰተው ከባድ ንፋስ ደረጃ 13 ሲሆን ዝናብ ፣ በረዶ እና ነጎድጓድ የቀላቀለ  መሆኑን የቻይና  የአየር ትንበያ ኤጀንሲ የገለፀ ሲሆን ይህን ተከትሎ  የሰውነት ክብደታቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሚመዝኑ ዜጎች በንፋሱ እንዳይወሰዱ በማሰብ ነው ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያው የተሰጠው።

እንዲሁም ንፋሱ የባሰ አደጋ እንዳያስከትል አስቸኳይ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንደ ሚገኙ እና ፓርኮች እንዲዘጉ እንዲሁም ወሳኝ እና አስፈላጊ ያልሆኑ በረራዎች እንዲሰረዙም መደረጋቸው ተገልጿል።

Via @mussesolomon

51k 0 202 173

ኢትዮጵያ በአህዮች ብዛት በዓለም የመጀመሪያ ደረጃን ይዛለች ።

በዓለም ላይ 50 ሚሊዮን አህዮች እንዳሉ የ2025 ሪፖርት ያመለክታል። በኢትዮጵያ 10 ሚሊዮን አህዮች እንደሚገኙ ተገልጿል።

ካለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር ብዛቱ የጨመረ ሲሆን በዓለማችን ትንሽ አህዮች ያሉባት ሀገር ሱሪናሜ ስትሆን ሰባት አህዮች ብቻ ይገኛሉ። በአሜሪካ 52ሺህ አህዮች ይገኛሉ።

ኢትዮጵያ በ10.6 ሚሊዮን አህዮች ቀዳሚ ስትሆን ጐረቤት ሀገር ሰሜን ሱዳን በ7.6 ሚሊዮን አህዮች ሁለተኛ ሆናለች።
በ 3ኛ ደረጃ ፓኪስታን 5.8 ሚሊዮን
በ 4ኛ ደረጃ ቻድ 4.6 ሚሊዮን
በ 5ኛ ደረጃ ሜክሲኮ 3.3 ሚሊዮን በመከተል ቦታውን ይዘዋል።

Via @mussesolomon


በመዲናዋ እስከ ምሽት 4:00 ድረስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በማይሰጡ አሽከርካሪዎች ላይ የ5 ሺሕ ብር ቅጣት እንደሚጣል ተገለጸ

በአዲስ አበባ ከተማ እስከ ምሽት 4:00 ድረስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት በማይሰጡ አገልግሎት ሰጪዎች ላይ የ5 ሺሕ ብር ቅጣት እንደሚጣል የከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በደንብ ቁጥር 185/2017 በተደነገገው ደንብ መሠረት ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት የትራንስፖርት አገልግሎትን መስጠት እንደሚጠበቅበት አሳውቆ ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት በፊት የትራንስፖርት አገልግሎትን ማቋረጥ፣ ከስምሪት መስመር ውጪ አገልግሎት መስጠት፣ አቆራርጦ መጫንና የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ካወጣው ሕጋዊ ታሪፍ ውጪ ሕብረተሰቡን ማስከፈል እንደማይቻል ቢሮው በጥብቅ አሳስቧል፡፡

Via @mussesolomon


ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ የፓስፖርት ጥንካሬ መመዘኛ 185ኛ ደረጃ ላይ ስትገኝ አየርላንድ ቀዳሚ ሆናለች።

ኢትዮጵያ  ትላንት በዓለም አቀፍ አማካሪ ድርጅት ኖማድ ካፒታሊስት ይፋ በሆነው የ2024 የኖማድ ፓስፖርት መመዘኛ ከ199 ሀገራት ተወዳድራ 185ኛ ደረጃን ይዛለች።

አየር ላንድ አንደኛ ደረጃ ላይ ስትገኝ በፓስፖርቷ 176 ሀገር ያለ ቪዛ ያስገባሉ፤ የኢትዮጵያ ፓስፖርት 57 ሀገራት ያለ ቪዛ ወይንም በደረሱበት ሀገር አየር ማረፊያ ላይ ቪዛ ይመታለታል፤ ጎረቤት ሀገር ደበቡ ሱዳን 184ኛ  ኬንያ 134ኛ ኤርትራ ደግሞ 197ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን አፍጋኒታስታን 199ኛ ደረጃ መጨረሻ ላይ ተቀምጣለች።

መመዘኛው ከቪዛ ነፃ የመጓዝ እድልን ብቻ ሳይሆን እንደ ግብር፣ ዓለም አቀፋዊ ገጽታ እና የግል ነፃነቶችን የመሳሰሉ ነገሮችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በዓለም ዙሪያ ያሉ 199 ፓስፖርቶችን ጥንካሬ ገምግሟል።

ከፍተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት የአውሮፓ ያልሆኑ ፓስፖርቶች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ኒውዚላንድ ሲሆኑ ሁለቱም በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

Via @mussesolomon


የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው።

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቁ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)።

Via @mussesolomon


ትራምፕ ለቲክቶክ መተግበሪያ ያስቀመጡት የጊዜ ገደብ አንድ ሳምንት ብቻ ቀርቶታል።

ከጥቂት ሳምንታት በፊት የመተግበሪያውን የአገልግሎት ጊዜውን ስለማራዘም ለቀረበላቸው ጥያቄ "ይመስለኛል" የሚል ምላሽ የሰጡት ፕሬዚዳንቱ ቀጣዩ ርምጃቸው ምን ሊሆን ይችላል የሚለው በርካቶችን እያነጋገረ ይገኛል።

ቲክቶክ በአሜሪካ ምድር ከቀናት በኋላ ዳግም ይዘጋል ወይስ ዳግም የአገልግሎት ጊዜው ይራዘም ይሆን ከ ቀናት በኋላ የምናይ ይሆናል።

Via @mussesolomon


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

ዒድ ሙባረክ


Via @mussesolomon


የALX ‘Pathway Program’ን በመውሰድ፣ የአለምአቀፍ ዲግሪ እና ሙሉ ስኮላርሺፕ እድል ለማግኘት ይመዝገቡ። የዚህ ስኮላርሺፕ እድል በጥቅሉ በአመት የ85,000 አሜርካን ዶላር፣ ወይም የ11 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር፣ ተመጣጣኝ ዋጋ አለው።

ALX ከ14 ታዋቂ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር የትብብር ስምምነት አለው። አብዛኛዎቹ ትምህርት ቤቶች የሚገኙት America ሲሆን፣ Europe እና South Africa የሚገኙም አሉ።

የዚህ የትብብር ስምምነት ዋና ይዘት፣ የALX Pathway ኘሮግራምን በስኬት የሚጨርሱ ልጆች፣ በእነዚህ ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ተቀባይነት እና የስኮላርሺፕ እድሎች የሚያገኙበትን መንገድ ማስፋት ነው።

የምዝገባውን ሂደት ደረጃ በደረጃ ማብራሪያ ለማየት፣ እንዲሁም ምዝገባውን በተሳካ ሁንያ ለማጠናቀቅ፣
ይህንን የቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ፡- https://t.me/ALXScholarship2ndBatch

ምዝገባው ከ5 ደቂቃ በላይ አይፈጅም!


የግል ኩባንያዎች ነዳጅ እንዲያስመጡ ተፈቀደ ።

የግሉ ዘርፍ ከሽያጭ በተጨማሪ ነዳጅ ማስመጣት እንዲችል የሚፈቅደው አዋጅ ስራ ላይ ዋለ፡፡

የነዳጅ ግብይት አዋጅ ቁጥር 1363/2017 ላለፈው 11 አመት በስራ ላይ የነበረውን አዋጅ የቀየረ ሆኖ ባለፈው ጥር ነበር በፓርላማ የፀደቀው፡፡ ይህ አዋጅ በሳለፍነው ሳምንት በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ መውጣቱን ተከትሎ ወደ ስራ መግባቱ ነው የታወቀው፡፡

በዚህም እስካሁን በመንግስታዊው የነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ብቻ ተይዞ የነበረውን የነዳጅ ከውጭ ገዝቶ የማስገባት ስራ ሌሎች ኩባንዎችም ማከናወን እንዲችሉ በር የሚከፍት ነው፡፡

የነዳጅ ንግድ የመንግስት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ አካል ሆኖ እየተሰራበት የሚገኝ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Via @mussesolomon


የነዳጅ ዋጋን መነሻ በማድረግ ከመጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በስራ ላይ የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በሚከተለዉ መሰረት ስራ ላይ እንዲዉል በመንግስት ተወስኗል።



Via @mussesolomon


በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ የወጣውን ደንብ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል

የአዲስ አበባ ከተማ ንግድ ቢሮ በምሽት የንግድ እና የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ የወጣውን ደንብ ቁጥር185/2017 ከዛሬ ጀምሮ  ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል።

ለዚህም ደንቡ በመውጣቱን  ይህ ደንብ ቀደም ብሎ የከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ ያስተላለፈውን ውሳኔ ለማስፈጸም በመሆኑ ከዛሬ መጋቢት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩን ቢሮው ገልጿል።

በመንገድ ዳር ያሉ ንግድ_ቤቶች ፣ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት እስከ ሶስት ሰዓት ተኩል የህዝብ ትራንስፖርት የሚሰጡ ደግሞ እስከ 4 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ደንቡ ያስገድዳል፡፡

Via @mussesolomon


የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.1 ተለክቷል

የአዋሽ አካባቢ ጠንካራ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ገልጸዋል።በአዲስ አበባ በርካታ አከባቢዎች እጅግ የጠነከረ ንዝረትም ለሰከንዶች ነበር።

ከአዲስ አበባ ውጭም በርካታ ከተሞች ላይ ንዝረቱ በደምብ ተሰምቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በ50 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ጠቁሟል።

በሬክተር ስኬልም 5.1 መለካቱን አመላክቷል።



Via @mussesolomon


በመስቀል አደባባይ ለሚከናወነው የኢፍጣር ፕሮግራም የተወሰኑ መንገዶች እንደሚዘጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ!
***
ይኸውም ነገ መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሠዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ የሚከናወነውን የኢፍጣር ፕሮግራም ምክንያት በማድረግ፦
👉 ከኦሎምፒያ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ )
👉 ከጥላሁን አደባባይ ወደ ሳንጆሴፍ መብራት (ጥላሁን አደባባይ ሲሆን ከባድ ተሽከርካሪ አጎና ላይ )
👉 ከለገሃር መብራት ወደ መሰቀል አደባባይ (ለገሃር መብራት)
👉 ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድየም (ቴሌ ማቋረጫ ላይ)
👉 ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ (ሀራምቤ መብራት ላይ )
👉 ከብሔራዊ ቤተ መንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ )
👉 ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መታጠፊያ ድረስ የሚዘጋ መሆኑን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች አማራጭ እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ያሳስባል።



Via @mussesolomon

20 last posts shown.