NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as social media & multimedia production.
Voice of voices
ንሥር ኢንተርናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የማያዳላ እና ገለልተኛ የመገናኛ ተቋም ነዉ። ማህበራዊ ሚዲያ እና መልታይሚዲያ እምራች ሁኖ ይሰራል።
አማራ ድምፅ!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


መረጃ ችሎት
፨፨፨፨፨፨፨፨

ዛሬ ችሎት የቀረቡት እነዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማሪያም ፣ በዳኞች ‹‹የሁለቱ ተከሳሾች የስልክ ቅጂ ስላልተሰማን ...! ‹‹በሚል ምክንያት ለሳምንት ሀሙስ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል። ጠበቆቻቸው ‹‹ለእኛ የሰጣችሁን የድምፅ ቅጂኮ በደንብ ይሰማል። ይሄ ቀጠሮ ለማራዘም በቂ ምክንያት አይሆንም !›› ሲሉ ተከራክረዋል። ምናልባትም የዛሬ ሳምንት ሲቀርቡ ‹‹ ድምፃቸውን የምናደምጥበት ሄድ ፎን ተበላሽቷል!›› የሚል ምክንያት ሊያቀርቡም ይችላሉ።

በነዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ የክስ መዝገብ የቀረቡት የህሊና እስረኞችም በተመሳሳይ ‹‹መስከረም አበራ ስላልቀረበች ....!›› በሚል ምክንያት ለቀጣይ ሰኞ ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷቸዋል።

በችሎቱ ‹‹ አቃቢ ህጎች ማረሚያ ቤት መጥተው 'በአማራ ጉዳይ የገባችሁትን በሙሉ የክስ ሂደቱን ገና አምስትና አስር አመት እናቆየዋለን!' የሚል ንግግር ተናግረውናል። ይህ ችሎት ፍትህ ይሰጠናል ብለን አናምንም! ›› የሚል ሀሳብ ቀርቧል።

ጠበቆች በበኩላቸው ‹‹...ከዚህ ችሎት ያተረፍነው ስኳርና ደም ግፊት ብቻ ነው!›› እስከማለት የደረሠ ምሬታቸውን አሰምተዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከማይካድራ ተይዘው ለአመታት የታሰሩት የህሊና እስረኞች ተለዋጭ የሁለት ወር ጊዜ ቀጠሮ መሰጠቱን ተከትሎ ፣ በተንዛዛው የፍትህ ስርአት ላይ ቅሬታቸውን በማቅረባቸው በአንደኛው ተጠርጣሪ ላይ ችሎት በመድፈር የ3 ወር እስር ተላልፎበታል!

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
አርብ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2


በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ትናንት ሐሙስ የካቲት 13/2017 ዓ.ም. ተያይዘው በተሠሩ አራት ቤቶች ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 16 ሰዎች ሲገደሉ 10 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ቤተሰቦች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጥቃቱ በዞኑ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ እነገሽ ቀበሌ (ሐሙስ ገበያ) በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሐሙስ ረፋድ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በሦስት ሱቆች እና ሻይ ቤት ላይ መድረሱን ቢቢሲ ያናገራቸው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

"[ድሮን] ስትዞረን ነበር" ያሉ አንድ የዓይን እማኝ ጥቃቱ ከደረሰበት ስፍራ በግምት 100 ሜትር ርቀት ላይ እንደነበሩ ጠቅሰው፤ የጥቃቱ ሰለባዎች መንገድ ላይ ሲጫወቱ የነበሩ ህፃናት፣ ገበያተኞች እና ሻይ እየጠጡ የነበሩ ሰዎች ናቸው ብለዋል።

"ከፍተኛ ፍንዳታ" መፈጠሩን የሚናገሩት እማኙ፤ ወዲያው "አካባቢውን አቧራው፤ የቤቱ ፍርስራሽ በጭስ" እንዳፈነው እና ድንጋጤ እና ግርግር እንደተፈጠረ ገልፀዋል።

ሌላ የዓይን እማኝም በፍንዳታው አካባቢው በአቧራ ጭስ መሸፈኑን ጠቅሰው፤ በስፍራው ለመተያትም አስቸጋሪ እንደነበር ተናግረዋል።
በደቂቃዎች ውስጥ ጥቃቱ ወደ ተፈፀመባቸው ቤቶች ደርሰው የቆሰሉ ሰዎችን እንዳወጡ እና አስከሬን እንዳነሱ የተናገሩት ሌላ የዓይን እማኝ "የሚጫወቱ ህፃናት እና ቆርቆሮ ሊገዙ የመጡ ሰዎች ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል" ብለዋል።

ከሟቾቹ ውስጥ ሙሉጌታ በለጠ የተባለ የስምንት ዓመት ልጃቸው እንደሚገኝበት የተናገሩ አንድ እናት፤ ልጃቸው ሱቆቹ ደጃፍ ላይ ኳስ እየተጫወተ እያለ ስለመገደሉ ለቢቢሲ በሐዘን ውስጥ ሆነው ተናግረዋል።
ጥቃቱ ሲደርስ ተጠራጥረው የአንደኛ ክፍል ተማሪ የነበረው ልጃቸውን ሙሉጌታ ፍለጋ፣ ፍንዳታው ወደ ደረሰበት ስፍራ መሄዳቸውን የተናገሩት እናት "ልጄን ንፁሃኖች [አስከሬን] መሃል እንኩት ብሎ [ሞቶ] አገኘሁት" ብለዋል።

ሙሉጌታ ሦስተኛ ልጃቸው እንደሆነ የተናገሩት እናት፣ አብሯቸው የሚኖር ብቸኛ ልጃቸው እንደሆነ ጠቅሰው "ቢያመኝ መድኃኒት ገዝቶ፤ ቡና አፍልቶ፤ ሻይ አፍልቶ የሚታዘዘዝ ልጄ ነው" በማለት በሐዘን በተዘጋ ድምጽ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ጥቃቱ ከደረሰባቸው ቤቶች አንዱ የሆነው ሻይ ቤት በአካባቢው ማኅበረሰብ ድጋፍ የተሠራ መሆኑን የተናገሩ አንድ ነዋሪ፤ በጥቃቱ የሻይ ቤቱ ባለቤት ልጅ የሆነው ታደሰ ጌታቸው የተባለ የ15 ዓመት ታዳጊ ሲገደል የስድስት ዓመት ሕጻን ደግሞ ከባድ ጉዳት እንደደረሰበት ገልጸዋል።

የጥቃቱ ሰለባዎች "ንፁሃን ላይ አይጥልም" በሚል ድሮኗ በአካባቢው ስታንዣብብ መዘናጋታቸውን የገለፁት እማኙ "ሰብሰብ ብሎ እየተጫወተ፤ እያወራ የነበረ" ሰው ላይ ጥቃቱ መድረሱን ገልፀዋል።

ቢቢሲ የደረሰውን ተንቀሳቃሽ ምስል እና ፎቶዎች ከገለልተኛ ወገን ማረጋገጥ ባይችልም ጣራቸው የተነሳ፣ ግድግዳቸው የፈራረሱ ቤቶች፣ የወዳደቁ የጣራ ቆርቆሮዎች፣ አልባሳት እና ጫማዎችን በምስሎቹ ላይ ይታያሉ።

ጥቃቱ ከደረሰበት አካባቢ በቅርብ ርቀት ሱቃቸው ውስጥ እንደነበሩ የተናገሩ ሌላ የዓይን እማኝ ጥቃት የደረሰባቸው ሱቆች የነዳጅ ችርቻሮ መሸጫ እና የቆርቆሮ ማከፋፈያ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የጥቃቱ ሰለባዎች በአብዛኛው "ቆርቆሮ ሊገዙ የመጡ" ሰዎች መሆናቸውን ገልፀዋል።

አስከሬን ተደራርቦ እና ከባድ ጉዳት ደርሶበት ማግኘታቸውን የተናገሩ አስከሬን ያነሱ የዓይን እማኝ ደግሞ "ደኅና ነው፤ ይተርፋሉ ያልናቸው በጥቃቱ የተጎዱ ሰዎች ወዲያውኑ ነበር የሞቱት" ሲሉ ስለ ደረሰው ጉዳት ተናግረዋል።
12 ሰዎች ቆስለው በአቅራቢያ ወደ ሚገኝ የግል ክሊኒክ መምጣታቸውን ያረጋገጡ አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የጤና ባለሙያ፣ ሁለት ታዳጊዎች ወደ ክሊኒኩ እንደመጡ ወዲያ ሕይወታቸው እንዳለፈ ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

ከ10ሩ ቁስለኞች መካከል አራቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የተናገሩት ባለሙያው፤ ክሊኒኩ አነስተኛ በመሆኑ ቁስለኞቹ ተኝተው መታከም ባለመቻላቸው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ገልፀዋል።

በአካባቢው የደኅንነት ስጋት ምክንያትም ቁስለኞቹን ለተሻለ ሕክምና ሪፈር ማድረግም እንዳልተቻለ የሕክምና ባለሙያው አክለው ተናግረዋል።ሕጻን ሙሉጌታን ጨምሮ በጥቃቱ የተገደሉ ሰዎች የቀብር ሥነ ሥርዓት በዕለቱ ሐሙስ በአካባቢው ባለ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን መፈፀሙን የተጎጂ ቤተሰቦች እና ነዋሪዎች የገለፁ ሲሆን፤ ማንነታቸውን መለየት ያልተቻሉ የሰባት ሰዎች አስከሬን በአንድ ላይ መቀበራቸውንም ተናግረዋል።

ጥቃቱን ተከትሎ የአካባቢው ማኅበረሰብ ስጋት እና ድንጋጤ ውስጥ መሆኑን የተናገሩ አንድ ነዋሪ፣ ጥቃቱ ለምን እንደተፈፀመ ሕዝቡ ግራ እንደገባው በመጥቀስ "ምን አድርገን ነው?" በማለት እየጠየቀ እና "እየተጨነቀ" ነው ብለዋል።

"የአካባቢው ማኅበረሰብ በጣም ነው ያዘነው። መንግሥት እንደዚህ ያደርጋል ብለንም አልጠበቅንም። የደም ጎርፍ ነው የነበረው። ንፁሃን፤ ሕፃናት ወዳድቀው፤ ቤቱ ፈራርሶ ሲታይ ሰው መሆን በራሱ ያስጠላል" በማለት ያሉበትን ሁኔታ ገልፀዋል።

"ቤቶች ተዘግተዋል። ከፍተኛ ድንጋጤ ነው ያለው፤ ከፍተኛ ሐዘን ላይ ነው ያለው። ዛሬ እኔ ቤት ወደቀ፤ ነገ እኔ ቤት ይወድቃል በሚል ስጋት ላይ ነው ያለው። [ሐሙስ] ማታ ቤቱ ያደረ ሰው የለም" ሲሉም አክለዋል።
በእነገሽ ቀበሌ እና በአጎራባች የገጠር ቀበሌዎች የፋኖ ኃይሎች እንደሚንቀሳቀሱ ነዋሪዎች የተናገሩ ሲሆን፤ በየጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ዋና ከተማ ግንደ ወይን ከተማ ደግሞ የመንግሥት ኃይሎች እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በአማራ ክልል ሁለት ዓመት ሊሞላው በተቃረበው በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄደው ግጭት የቀጠለ ሲሆን፣ በግጭቱ መካከል የብልፅግና ኃይሎች በሚፈጸሙ ጥቃቶች ንጹሃን ሰዎች ሰለባ እንደሚሆኑ የመብት ድርጅቶች በተለየዩ ጊዜያት ያወጧቸው መግለጫዎች ያመለክታሉ።

✍️ቢቢሲ አማርኛ




ነገሩ ወደ ጦርነት እየተንደረደረ ይመስላል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ዲፕሎማቶቹ በኢትዮጵያ አየር መንገድ  በአገዛዙ ታገቱ ። ፋሽስቱ አብይ አህመድ አሊ የኢትዮጵያ  9 የኤርትራ ዲፕሎማቶቸን ከአገር ሊወጡ ሲሉ በቦሌ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
አርብ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት : nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084


የብልፅግና መሩ እና የኦሮሞዉ መንግስታዊ ገዳይ ቡድን ከቅርብ ወራት በፊት የአማራ የሚባልን ህዝብ ለማጥፋት በሚመስል መልኩ የጅምላ ግድያ ዘርን ተመርኩዘዉ ሲረሽኑ ሲገድሉ ሲያፈናቅሉ የኖሩ ከዚህ አልፎ ከሒትለር በከፋ መልኩ በአማራ ላይ በሰሩት ግፍ ለፍርድ መቅረብ ሲኖርባቸዉ ብልፅግና መሪ የኦሮሞዉ አስተዳድር ከፍተኛ የተባለ ስልጣንን ሰጥቷቸዋል።

አማራን ከነነፍሱ ሲያቃጥሉ ቤት ዉስጥ ዘግተዉ ህዝብ ሲያነዱ ሰዉ ከነነፍሱ ሰዉነት ሲተለትሉ ነፍሰጡር ሴቶችን ፅንስ በስለት ሲያዎጡ የነበሩ ነፍሰ በላዎች በዛሬዉ እለት ሹመት አግኝተዋል በዚህ መሰረትም፡-

1. አቶ ያደሳ ነጋሳ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሰላምና ደህንነት ጉዳዮች አማካሪ

2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ የኦሮሚያ ክልል ዓቃቤ ሕግ ምክትል ሃላፊ

3. አቶ ቶሌራ ረጋሳ   የኦሮሚያ ክልል ጸጥታና አስተዳደር ቢሮ ምክትል ሃላፊ ሆነው መሾማቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል ይላል መረጃዉ ።

እነዚህ በአማራ የንፁሀን ደም የጨቀዩ ነፍሰ ገዳዮች ለፍርድ የሚቀርቡበት ጊዜ ሩቅ ባይሆንም ከዚህ ድርጊት ግን አማራ መማር አለበት።

ብልፅግና መሩ የኦሮሙማ ቡድን አማራን ለማጥፋት ከየጫካዉ ተጠራርቶ  ህብረት ሲፈጥር  እኛም አማራዎች ለነፃነታችን ሳንዉል ሳናድር መደራጀት ልዩነትን ከመካከላችን ማጥፋት ይኖርብናል።

ምክንያቱም ትናንት ከገደሉን ነገ የከፋ ነዉ መሳሪያዉም በጀቱም ሁሉም ነገር በጃቸዉ ሲገባ አማራን ለማጥፋት ከትናንቱ በተሻለ እድል ያገኛሉና የኛ ምርጫ ተደራጅቶ እስከነፃነት ጫፍ መታገል ነዉ።

✍️H.M


የተማረከዉ መሳሪያ እና የጎንደር ፋኖዎች ድል

ወደለየለት ጦርነት ለመግባት ደወል የሚጠብቀዉ የሁለቱ ሀገር ፍጥጫ

የአማራ ተወላጆች ስላሉ የተሰረዘዉ ለስምሪት የተላከዉ የጋዜጠኞች ስብስብ ታገደ ።

በወሎ በጎጃም እና በጎንደር ትንቅንቁ እንደቀጠለ ነዉ የብልፅግነሠ ሰራዊትም ፋታ የለሽ ምት እየደረሰበት ነዉ ።ዝርዝር መረጃዉን በዩቱብ ቻናላችን ያድምጡ። 👇👇👇 https://youtu.be/dSKOwoRdK88


በቡራዩ በፖሊስ ጣቢያ ላይ የቦንብ ጥቃት ደረሰ
በሸገር ሲቲ ቡራዩ ከተማ አስተዳደር ከታ በሚባል አካባቢ በአንድ የፖሊስ ጣቢያ ላይ የቦንብ  ጥቃት መፈፀሙ ተነግሯል።

ምሽት ላይ በተፈፀመዉ ጥቃት የደረሰው ጉዳት ማወቅ ባይቻልም አምቡላንሶች ግን ይመላለሱ እንደነበር  የአካባቢዉ ነዋሪዎች ገልፀዋል ፡፡

በአካባቢዉ የኦሮሞ ነፃነት ጦር ብሎ እራሱን የሚጠራዉ ታጣቂ ቡድን ተደጋጋሚ ጥቃቶችን በአገዛዙ ባለ ስልጣኖች ላይ እየፈፀመ እንደነበር ሲነገር ቆይቷል።

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
አርብ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት : nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084




በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ እነገሽ ቀበሌ በሶስት ተከታታይ አነስተኛ ሱቆች ላይ በደረሰ የድሮን ጥቃት ህፃን ሙሉጌታ በለጠን ጨምሮ 16 ንፁሃን ወዲያውኑ ሲሞቱ 10 የሚሆኑት ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት አስተናግደው ህክምና ላይ እንደሚገኙ ታውቋል::

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
አርብ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት : nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084


ከዚህ በኃላ የልምምጥ ፣የልመና ብሎም የማሽሞንሞን ትግል አንታገልም።ትግስትም ልክ አለው።በየወረዳው የራሳችሁን የግል ፍላጎት ለማሟላት መመሪያ አናከብርም ስማችን ይበቃናል እኛው እንቁረጠው እኛው እንፍለጠው የምትሉ ቁንፅል አስተሳሰብ ያላችሁ ፋኖ መሳይ አጭበርባሪ ካላችሁ ከአሁኑ ሰዓት ጀምሮ ወደ ሰውነት ባህሪ በፍጥነት እንድትገቡ እንመክራለን።

የአማራ ፋኖን ትግል በሴራ ብሎም በጥቅም አሳልፎ ለመስጠት በግልም ይሁን በቡድን በትግላችን መሐል ገብቶ አጀንዳ የሚፈጠርን አካል ከአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት ቡድን ለይተን ስለማናየው ምላሻችን እርምጃ ብቻ ነው

በመሆኑም በክፍለ ጦራችን ውስጥ ባሉ ብርጌዶች ብሎም ማህበረሰባችን ውስጥ ያላችሁ እስስቶች በፍጥነት ከእንዲህ አይነት ተግባር ወጥታችሁ ሰው ሁኑ።በነፍጥ የጀመርነውን በነፍጥ እንጨርሰዋለን!!
አዲስ አብዮት
አዲስ ድል
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
በወንበዴዎች ወንበር የማይናውዝ አዲስ ትውልድ በክንዳችን እና በአንደበታችን እንፈጥራለን።
የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ!!

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
አርብ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት : nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ምስራቅ ጎጃም ጎንቻ እነሴ የንጹሃን የድሮን ጭፍጨፋ😭


ለድርድር የተቀመጡ የኦሮሞ ፓርቲዎችን ሙሉ የቀረፃ ሂደት ለመስራት የታዘዘው የመከላከያ ሚዲያ የጋዜጠኞች ቡድን ከስምሪት ታገደ።

የኦህዴድ ብልፅግና ፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) እየተሳተፉበት የሚገኘውን ድርድር ውይይትና የይስሙላ ተስማሞት በማካሄድ ላይ የሚገኙትን አመራሮችና መላው ተሳታፊዎች አጠቃላይ ሂደት ለመቅረፅ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈትቤትና በመከላከያ መረጃ ዋና መምሪያ ትዕዛዝ ቀረፃ ለማከናዎን ትዕዛዝ ተሰጥቶት የነበረው የመከላከያ ሚዲያ የጋዜጠኞች ቡድን ስምሪቱን እንዲያቆም ታዘዘ።

የቀረፃ ግዳጁ እንዲከናዎን መመሪያ ያወረዱት የመከላከያ ሰራዊት ስነልቦና ዳይሬክቶሬት ሀላፊ ሜጄር ጄኔራል እንዳልካቸው ወልደኪዳን አስቸኳይ ስብሰባ በማድረግ ስምሪቱን ያስቆሙ ሲሆን ስራው ቀድሞ በአንዳንድ የሚዲያ አካላት ዘንድ መድረሱን ተናግረው በበላይ አካል ትዕዛዝ መታገዱን ነግረዋቸዋል።

የሚዲያ ቡድኑ ሚሰሰጥራዊ ስራዎች እየተሰጡት የሚፈለግ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመጨመር ሲሰራ እንደቆየ የሚታወቅ ቢሆንም በሚዲያው ውስጥ የአማራ ብሄር ተወላጆች በመካተታቸው መሰረዙን ለማወቅ ተችሏል።

የመከላከያ ሚዲያ ቡድን የኪንግስ ሆቴሉን የኦሮሞ ፓርቲዎች ድርድር ከመቅረፅ ባለፈ በአማራ ክልል ካለው ወቅታዊ ግዳጅና በክልሉ እየተካሄደ ያለውን ጦርነትና ህዝባዊ ውይቶችን መሰረት በማድረግ ከሰሞኑ የጠቅላይሚኒስትሩ ስብሰባ እና በየዕዙ እየተካሄዱ ከሚገኙ ግምገማና ጉብኝት  ተኮር የአመራር ስብሰባዎች በኋላ በተመረጡ የአማራ ክልል አካባቢዎች የፀረ-ፋኖ ዘመቻዎች ላይ ያጠነጠኑ የሚዲያ ፕሮፖጋንዳ ስራዎችን ለመስራት አቅጣጫ እንደተሰጠውም ከውስጥ ምንጮች ታውቋል። 251

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
አርብ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት : nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084


፨ ብልፅግና በኮሪደር ልማት ስም የባህርዳርን ህዝብ ለመዝረፍ ተነስቷል።

፨የአማራ ፋኖ በሸዋ ጀግኖች የጥላትን ጦር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ድል ተቀዳጅተዋል።

፨ በጎጃም ምን ተፈጠረ አደረጃጀቶች ለምን የማስጠንቀቂያ መልዕክት አስተላለፉ።

፨ ዉጥረቱ እንደቀጠ ነዉ እርምጃዎችም ተጠናክረዉ ቀጥለዋል ። ሙሉ መረጃዉን በዩቱብ ቻናላችን ይከታተሉ

https://youtu.be/mZSXmg1Sfb8


ኤርትራ በአዲስ አበባ ያለውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታወቀ

ካለፉት ሁለት አመታት ወዲህ ግንኙነታቸው እየሻከረ የመጣው የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግስታት የቃላት ጦርነት መጀመራቸውን ተከትሎ ኤርትራ በአዲስ አበባ የሚገኘውን ኤምባሲዋን እየዘጋች መሆኑ ታውቋል።

የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ግንኙነታቸውን ያደሱት ሁለቱ ሀገራት በትግራይ የተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ላይ በጋራ ቆመው ቢዋጉም የፕሪቶሪያው ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ ግንኙነቱ መሻከር መጀመሩ ይታወሳል።

"ኤምባሲው ከዚህ በኋላ የአፍሪካ ህብረት ተወካዩን ይዞ ይቀጥላል፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኤምባሲ ስታፍ ግን እያሰናበተ ነው" ያሉን አንድ የኤምባሲው ምንጫችን ሂደቱ በፍጥነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ የኤርትራ መንግስት የአፍሪካ ቀንድን የማተራመስ አላማ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ነው፣ በአስቸኳይ እንዲቆም መደረግ አለበት በማለት አልጀዚራ ላይ በቀረበ ፅሁፋቸው አስነብበው ነበር።

የኤርትራው የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ለዚህ ምላሽ የሰጡ ሲሆን የፕሬዝደንቱን አስተያየት አጣጥለው የኢትዮጵያን መንግስት የቀጠናውን ሀገራት በመተንኮስ ከሰዋል።

የኤርትራ ኤምባሲ መዘጋት መጀመርን ተከትሎ በአስመራ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እጣ ፈንታ እስካሁን አልታወቀም። ላለፉት ጥቂት አመታት ኤምባሲው ክፍት ቢሆንም አምባሳደር ሳይመደብበት መቆየቱም ይታወሳል።

✍️መሠረት ሚዲያ




ደጋዳሞት ብርጌድ እና መዝገቡ ዋለልኝ ብርጌድ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ክ/ጦር ደጋዳሞት ብርጌድ በዛሬው ዕለት ማለትም የካቲት13/2017 ዓ.ም ሁለት ዋና ዋና መርሀ ግብሮችን አከናውኗል።

አንዱና ዋነኛው የደጋዳሞት ብርጌድ ሁለተኛ ሻለቃ  በ2ኛ ክ/ጦር ስር ከሚገኘው ሌላኛው ብርጌድ ማለትም መዝገቡ ዋለልኝ ብርጌድ አራተኛ(ወይን ውሃ) ሻለቃ ጋር በጥምረት ለመስራት የሚያስችል ቀጠናዊ ትስስር ፈፅመዋል።

በዚህ መርሀ ግብር ላይ የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢ እና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው በስፍራው ተገኝተው የትግላችንን እና የድርጅታችንን ወቅታዊ ቁመና እና የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በተመለከተ ንግግር አድርገዋል።

ሌላኛው በዕለቱ ከተከናወኑ አበይት ተግባራት መካከል ጀግናው እና አይበገሬው የደጋዳሞት አርሶ አደር ለትግሉ ያለውን ሁለተናዊ ድጋፍ ለመግለፅ በራሱ ተነሳሽነት የጦር መሳሪያ ባለቤት የሆኑ አርሶ አደሮች ሙሉ በሙሉ የተገኙበትን የተሃድሶ ፕሮግራም ያካሄደ ሲሆን በፕሮግራሙም ከዝቋላ ወገም እስከ አረፋ መድሃኒያለም ድረስ የሚገኙ የጦር መሳሪያ ባለቤቶች ተገኝተዋል።

ይህንን ፕሮግራምም እንደተለመደው የደጋዳሞት ብርጌድ አባ ሻውል ሃይሌ ሁለገብ የኪነት ቡድን አድምቀውት ውለዋል።

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ክ/ጥር ደጋዳሞት ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል

https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2




የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ፓርቲ፣አምስት የፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ አባላት በአገዛዙ ታግተውብናል አለ።

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ፓርቲ፣ አምስት የፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ አባላት ባለፈው ዕሁድና ሰኞ በአገዛዙ የጸጥታ ኃይሎች ታግተውብኛል ብሏል።

ፓርቲው መጋቢት 14 መስራች ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግና 10 ሺሕ ፊርማ አሰባስቦ ለምርጫ ቦርድ ለማስገባት እየተዘጋጀ እንደነበር ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የፓርቲው አመራር ለዋዜማ አስረድተዋል።

ከታገቱት መካከል፣ የአደራጅ ኮሚቴው ምክትል ሰብሳቢ ሰብስቤ ዓለሙ ይገኙበታል ተብሏል። የእገታው ዓላማ፣ የተሰበሰበውን ፊርማ ለማጥፋትና ጠቅላላ ጉባኤውን ለማጨናገፍ ያለመ ነው ብሎ ፓርቲው እንደሚያምን ሃላፊዎቹ ጠቁመዋል።

ታጋቾቹ በእስር ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ስላልተገኙ፣ ፓርቲው ለምርጫ ቦርድና ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ሁኔታውን ማሳወቁም ተገልጧል።

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ሀሙስ የካቲት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር: x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣ https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም: https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:- tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት : nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084


ሰበር ዜና!
፨፨፨፨፨፨

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማሓራ) የምስራቅ አማራ ኮር 1 በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ ባለሽርጡ ክፍለጦር  እና በአርበኛ አባ ነጋ የሚመራው   ሀውጃኖ ክፍለጦር ቃኞች በሀብሩ ወረዳ 020 ልዩ ቦታው ሀብሩ  እየተባለ በሚጠራ ስፋራ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ፡፡

በተደረገው ተጋድሎ ሁለቱ አርበኞች በፊት አውራሪነት እየመሩ ዙፋን ጠባቂው ሰራዊት የግል ትጥቅን ከማህበረሰባችን ለማስፈታት ከጊራና ወደ ሀብሩ ያመራውን ኃይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ መበታተን ተችሏል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ አርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የስናይፐሩ ንጉስ የጠላትን ኃይል ፊት ለፊት ገጥሞ 8 (ስምንት) የአብይ አህመድ የግል ወታደሮችን ወደ ማይመለሱበት አለም ሸኝቷቸዋል፡፡  በዚህ የተበሳጨው የስርዓቱ ወታደር ከፍተኛ የሆነ ኃይል ወደ መነዮ ቢያሰጠጋም አይበገሬዎቹ ፋኖዎች በሁለት አቅጣጫ የመጣውን ኃይል ድጋሜ እንዳያገግም ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ወደ መጣበት እየተበታተነ ቁስለኛውን እንኳን ማንሳት በማይችልበት ሁኔታ ተመልሷል፡፡

በዚህ አውደ ውጊያ ስርዓቱ ትጥቃቸውን ሊያስፈታ እንደመጣ የተረዱት የግል ታጣቂዎችና የባለሽርጡ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ  ይህን ኃይል ከደም መላሾቹ ጋር በመሆን በከፍተኛ ደረጃ የጠላትን ኃይል ተፋልመዋል፡፡

የጀግኖቹን በትር መቋቋም ያቃተው ይህ የባንዳ ስብስብና አማራን ትጥቅ አስፈታለሁ ብሎ የመጣ ኃይል ገሚሱ የንፁሀን ቤትን እንደ ምሽግ በመቁጠር በየቤቱ ስለገባ በአሁኑ ሰዓት አሰሳ እየተደረገ እየተለቃቀመ ይገኛል፡፡

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ-አማሓራ) የባለሽርጡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ መምህር መሀመድ ሞገስ

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማሓራ)
የካቲት 13 /2017 ዓ.ም


የፋሽስቱ አብይ ሰራዊት ግፍ እንዲህ አይነት ነው። የህጻናት እና ታዳጊዎችን ህይወት ጭምር በመቅጠፍ በርካቶችን ደግሞ ያለ ሙሉ አካል እንዲኖሩም አድርጓል።

ራሄል ጌቴ ትባላለች፤ ቢቡኝ ወረዳ ውስጥ ነው ትውልዷ።   የ11 አመት ታዳጊ ናት። የፋሽስቱ አብይ አህመድ ሰራዊት እግሯን ነጠቃት። እየሆነብን ያለው ይህ ነው። ከጦርነቱ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላቸው ህጻናት፣ ታዳጊዎች፣ ሴቶች እና አቅመ ደካሞች ታርጌት ተደርገው በየእለቱ ወገኖቻችንን እየቀበርን ነው።

ፋኖ አንድ ሆኖ መታገልና ማሸነፍ ያለበት እንደ ራሄል ያሉ እንቦቀቅላዎችን በማሰብ ነው። ከመጥፋታችን በፊት እንደ ህዝብ አንድ ልንሆንና ልንታገልም ይገባል። ትግል በጠብመንጃ ብቻ አይደለም። ሁሉም አማራ በሀሳብ፣ በሎጅስቲክስ፣ በገንዘብ፣ በሚዲያ፣ በዲፕሎማሲ፣ በአድቮኬሲ፣ በሙያው፣ በመረጃ እና በጉልበቱ ጭምር ትግሉን ማገዝ አለበት።

ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለአማራ ፋኖ

ንሥር ብሮድካስት መረጃ 
ሀሙስ የካቲት 13 ቀን 2017 ዓ.ም

=====================
ቤተሰብ ይሁኑ! ትግላችን በጋራ!

ትዊተር:
x.com/nisirinternati1     
ዮቱብ፣
https://youtube.com/@nibcnewsethiopia?si=_LD-OmtO1nJ0RVr2
ቴሌግራም:
https://t.me/nisirbroadcasting
ቲክታክ:-
tiktok.com/@nisirbroadcas
ዌብሳይት :
nisirbroadcasting.com
WhatsApp:  +1 (252) 574‑6084
Telegram:  +1 (252) 574‑6084

20 last posts shown.