🦋Official Exit


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


Trust our info depend on it
Get the fastest news here 🔥

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


በመውጫ ፈተና ውጤት ምክንያት 90 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተዘግተዋል። - ትምህርት ሚኒስቴር

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተናን አስመልክቶ ባወጣው መመሪያ መሠረት፣ 90 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚያስፈትኗቸው ተማሪዎች 75 በመቶ ያህሉን ማሳለፍ ባለመቻላቸው መዘጋታቸው ተሰምቷል፡፡

የትምህርት ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ቱሹኔ ይህን ያሉት፥ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ በአዲስ አበባ ባዘጋጀው የአፍሪካ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዓለም አቀፍ ጉባዔ መድረክ ላይ ነው።

"መመሪያው ከተላለፈ በኋላ ራሳቸው ላይ ዕርምጃ የወሰዱ ተቋማት አሉ፡፡ በተለይ ከግሎቹ 90 ያህል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተዘግተዋል፡፡ አብዛኞቹ መመሪያውን ካዩ በኋላ ራሳቸውም እየዘጉ ናቸው" ብለዋል፡፡

ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እስካሁን የተዘጋ ባይኖርም ዝቅተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተቋማት እንዳሉም ሚኒስትር ደኤታው ተናግረዋል፡፡ ተዘግተዋል የተባሉት የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ሲያስተምሩ የነበሩ ቢሆኑም ስማቸው አልተጠቀሰም፡፡

"የእኛ ሥራ ሔዶዶ መዝጋት ሳይሆን፥ ተቋማቱ ያሉበትን ሁኔታ መግለፅና መማር ለሚፈልጉ ዜጎች ለውሳኔ እንዲረዳቸው ትክክለኛ መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ ነው" ያሉት ሚኒስትር ደኤታው፤ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የወጡ መመሪያዎችን በማየት ብቻ በራሳቸው ከገበያ የወጡ ተቋማት መኖራቸውንም ገልፀዋል፡፡ #ሪፖርተር
📄

@officialexit


📢NOTICE!

📌Please be informed that if Eid al-Adha falls on Friday, June 6, 2025, the exams scheduled for that day will be conducted on Saturday, June 7, 2025 @1:30pm.

⚠️P:S- Students are strongly advised not to bring smartphones or other electronic devices into the exam room.

©️AAU SCHOOL OF COMMERCE


YouTube 👁️ new thing their soon

https://youtube.com/@gbitube?si=A0tusd0ZB4XPmgUy

📄

@officialexit


May 30 revised-Sene2017-EXIT EXAM Schedule - 1 -(1).xls
235.5Kb
#ExitExam #Revised

ከአንድ ሳምንት በሗላ የሚሰጠው የ 2017 ሰኔ ወር ብሔራዊ የዩንቨርስቲ መውጫ ፈተና (university national exit exam) መርሐ ግብር(schedule)
➡️ሰኔ 2 management
➡️ሰኔ 3 Accounting
➡️ሰኔ 4 ህግ computer science, biology, sociology, social work.... እያለ ይቀጥላል
➡️ሰኔ 5 Midwifery, Pharmacy, Medical Radiology እያለ ይቀጥላል.........

📄

@officialexit


Forward from: Memi crypto🙄
ባለፉት 100 አመታት አለማችን ላይ የሚገኙ ባንኮች ቁጥር ከ28,000 ወደ 4500 ቀንሷል።
Join ➣ @memicrypto






Forward from: Memi crypto🙄
ከውጪ ዕርዳታ ቁርጥራጮች የምንጠብቅበት ጊዜ አይደለም ሲል የአፍሪካ ልማት ባንክ አስጠነቀቀ

የአፍሪካ መሪዎች በዚህ ሳምንት በአቢጃን እየተካሄደ በሚገኘው የአፍሪካ ልማት ባንክ ቡድን የ2025 ዓመታዊ ስብሰባዎች ላይ አህጉሪቱ የራሷን ካፒታል እንድታንቀሳቅስ እና የክልላዊ ውህደትን እንድታፋጥን ጠንካራ ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ ጥሪ የቀረበው፣ 47 የአፍሪካ አገራትን የሚነኩ አዳዲስ የአሜሪካ ታሪፎችን ጨምሮ በሚለዋወጠው ዓለም አቀፍ የንግድ ሁኔታዎች ምክንያት መሆኑ ተጠቁሟል።

በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ የአሥር ዓመቱን የሥራ ዘመናቸውን የሚያጠናቅቁት የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንዉሚ አዴሲና፣ ባደረጉት የስንብት ንግግር፣ “ይህ ከውጭ ዕርዳታ ቁርጥራጮች የምንጠብቅበት ጊዜ አይደለም” በማለት ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።

አዴሲና አክለውም፣ “አፍሪካ የራሷን ሀብት – ሰብዓዊ፣ ፋይናንስ፣ ተፈጥሮአዊ – መክፈትና ሁሉን አቀፍ ዕድገትን የሚያበረታቱ ውስጣዊ የእሴት ሰንሰለቶችን መገንባት አለባት” ሲሉ አሳስበዋል።

Read More

Source: capitalethiopia
Join ➣ @memicrypto


#MoE

በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞች ያሏቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስፈላጊውን ክፍያ ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ እንዲያደርጉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በርቀት፣ በማታ እንዲሁም በቅዳሜ እና እሑድ መርሐግብር የመውጫ ፈተና የሚወስዱ አመልካቾች ክፍያ የፈጸሙበትን የባንክ ደረሰኝ እስከ ማክሰኞ ግንቦት 12/2017 ዓ.ም ድረስ በኢሜይል eexmoe@gmail.com እንዲልኩ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

📄

@officialexit






Video is unavailable for watching
Show in Telegram
📄

@officialexit


#MoE

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠው የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ብቻ መራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

እስካሁን ያልተመዘገባችሁ የድጋሚ ተፈታኞች (Re-sitters) ከዚህ በፊት ለምዝገባ በተከፈተው የመመዝገቢያ ፕላትፎርም (https://exam.ethernet.edu.et) ገብታችሁ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ ተብሏል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ለመውጫ ፈተና የምትቀመጡ ተፈታኞች በተቋሞቻችሁ በኩል መመዝገባችሁን እንድታረጋግጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

የመውጫ ፈተናው ከሰኔ 2-10/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

ለፈተናው የምታመለክቱ አመልካቾች ለመመዝገብ የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ (ፋይዳ) ሊኖራችሁ ይገባል፡፡

📄

@officialexit


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሻሽሎ ባወጣው የአካዳሚክ ካላንደር የ2017 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 2-10/2017 ዓ.ም መሆኑን ያሳያል።

ዩኒቨርሲቲው የ2017 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ሰኔ 21/2017 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

(የተሻሻለው የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ካላንደር ከላይ ተያይዟል፡፡)
📄

@officialexit


የመውጫ ፈተና በድጋሚ መውሰድ ለምትፈልጉ በሙሉ


የዳግም ምዝገባ ቀነ ገደብ  እስከ ግንቦት 14 ተራዝሟል ፣ ምዝገባችሁን በቀነ ገደብ ውስጥ እንድታጠናቅቁ በድጋሚ እናሳስባለን ።

ለመመዝገብ👇
https://exam.ethernet.edu.et

Step 1 Provide Username

Step 2 Verify Fayda ID

Step 3 Review Fayda Profile

Step 4 Update Preference

Step 5 Complete Payment and Registration

📄

@officialexit


ዶርም ውስጥ በጩቤ...

ዛሬ ጠዋት በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ጫሞ ካምፓስ አንድ የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ዶርም ውስጥ እጅግ ሰቅጣጭ በሆነ መልኩ በጩቤ ተወግቶ ህይወቱ ማለፉን ከዩንቨርሲቲው ተማሪዎች ሰምተናል።

የግቢው ተማሪዎች ካምፓሱ ላይ ተማሪ ሲወጋ ይህ የመጀመሪያው አለመሆኑንና መወጋጋትም የተለመደ እየሆነ ነው ዩንቨርሲቲውም የተማሪዎቹን ደህንነት ለመጠበቅ ጠንካራ ስራ እየሰራ አይደለም ሲሉ ስጋታቸውን አጋርተውናል።


ከደቂቃዎች በፊት የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የሚከተለውን የሃዘን መግለጫ አውጥቷል👇

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሥነ- ትምህርትና  ሥነ-ባህርይ ሳይንስ ትምህርት ቤት የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል የ2ኛ አመት ተማሪ የሆነው ናትናኤል ፀጉ አሰፋ  ከጓኛው ጋር በተፈጠረ የግል ፀብ በደረሰበት ጥቃት ዛሬ ጠዋት ሚያዚያ  28 ቀን 2017 ዓ/ም   ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል:: በመሆኑም ሕይወቱን ለማትረፍ በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከፍተኛ ርብርብ ቢደረግም ሳይሳካ በመቅረቱ ማምሻውን 12:30 ላይ ሕይወቱ አልፏል።

አደጋውን ያደረሰው ተማሪ በቁጥጥር ስር ውሎ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገ የሚገኝ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው የሕግ ሂደቱን በመከታተል  ውሳኔውን ተከታትሎ በአጭር ጊዜ ለሕዝብ ይፋ ያደርጋል::

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተማሪ ናትናኤል ከዚህ አለም በሞት መለየት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቡ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ሁሉ መፅናናትን ይመኛል።
📄

@officialexit


‼️ለመውጫ ፈተና ተፈታኞች (ለመጀመሪያ ጊዜ)

ስለክፍያ


መስፈርቱን እንደምታሟሉ ያሳወቅናችሁ እና የፋይዳ ቁጥር ቀርቶባችሁ የሰጣችሁ፣ ማክሰኞ ሚያዝያ 28 እና ረዕቡ ሚያዝያ 29፣ 2017 ዓ.ም ለትምህርት ሚኒስቴር የሚከፈል ብር 500 (አምስት መቶ) በዳሸን ሱፐር አፕ በመክፈል፣ ደረሰኙን ኮፒ በማድረግ፣ 08 ቁጥር በማወራረድ፣ የሚሰጣችሁን ሰማያዊ ደረሰኝ ቢሮ ቁ 02 እንድትሰጡ እያሳሰብን፣ ክፍያውን በወቅቱ ላላጠናቀቀ ተፈታኝ ሀላፊነት የማንወስድ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።

ማስታወሻ

የደረሰኙ ኮፒ ስትሰጡ ጀርባው ላይ፣

⚡️ ሙሉ ስም
⚡️ "ID"
⚡️ዲፓርትመንት እና
⚡️ባላ 16 ዲጂት የፋይዳ ቁጥር መፃፍ እንዳትረሱ።

✅ መክፈያ አካውንት: Dashen Bank 0008904786086
UNITY UNIVERSITY

📄

@officialexit


#MoH

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

ተመዛኞች ከዛሬ ሚያዝያ 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።

በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0115186275 / 0115186276 ላይ በመደወል  ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።

ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሚያዝያ 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልል ተቆጣጣሪ አካላት በመሔድ የሚጠበቅባችሁን ቅድመ ሁኔታዎች በሟሟላት የሙያ ፈቃድ መውሰድ የምትችላላችሁ ተብሏል።

የስም ፊደል ግድፈት ያለባችሁ ተመዛኞች ሙሉ በሙሉ የስም ትርጉም ለውጥ ከሌለው በስተቀር ከዲግሪያችሁ ጋር በማመሳከር የምትስተናገዱ መሆኑ ተገልጿል።
📄

@officialexit


Forward from: Memi crypto🙄
#DV2026
ውጤት ተለቋል ✌️

Diversity Visa 2026 selections are now available. Enter your confirmation number at dvprogram.state.gov/ESC/ to check if you have been selected. This is the ONLY way to check your Diversity Visa entry status.
Join ➣ @memicrypto


#MoE

በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ 50 ሺህ ትምህርት ቤቶች ውስጥ 80 በመቶ የሚሆኑት ከደረጃ በታች ናቸው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር

ከደረጃ በታች የሆኑ ትምህርት ቤቶችን ለማሻሻልና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን በትምህርት ሚኒስቴር ፕሮግራሞችና ጥራት ማሻሻያ ኃላፊ ዳዊት አዘነ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡

በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ እስካሁን ከ7,900 በላይ የቅድመ መደበኛ፣ 1ኛ ደረጃ እና 2ኛ ደረጃ አዳዲስ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን የገለፁት ኃላፊው፤ የ29,900 ትምህርት ቤቶች እድሳትና ጥገና ሥራ መከናወኑን ገልፀዋል፡፡

©️tikvahuniversity
📄

@officialexit



20 last posts shown.