📒#ቅዱስ ራጉኤል ሊቀ መላዕክት †††🌹
†††••ወር በገባ በ1 የሊቀ መላዕክት ቅዱስ ራጉኤል ወርሐዊ መታሰቢያው ነው፡፡ጸሎቱ በረከቱ ለዘአለሙ ይደርብንና ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ራጉኤል ያደረገው ተአምር ይህ ነው፡፡
☞በጰንጤናዊው በጲላጦስ ዘመን አይሁድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ቀራንዮ በሚባል ቦታ በሰቀሉት ጊዜ
☞ለንጊኖስ የተባለ አንድ ጭፍራ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሣለ ቀኝ ጎኑን በጦር ወጋው፡፡
☞በዚያም ጊዜ መልአኩ ዑራኤል የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ክቡር ደሙን
ይቀዳ ዘንድ በእጁ የብርሃን ጽዋ ይዞ ቀረበ፡፡
☞እንደዚሁ መልአኩ ዑራኤል የክርስቶስን ደም በሚቀዳበት ጊዜ ለአይሁድ
አልተገለጸላቸውም ነበር ይህም የመላእክት አለቃ ዑራኤል የጌታችን የኢየሱስ
ክርስቶስን ደም በምድር ላይ ከጽንፍ ረጨው፡፡
☞በዚያን ጊዜም በመላአከ ብርሃናት ራጉኤል እጅ ፀሀይ ጨለመ ጨረቃም ደም
መሰለ ከዋክብትም ረገፋ እሱ ራጉኤል መልአክ በፀሐይና በጨረቃ በከዋክብትና
በሌሎችም ብርሃናት ሁሉ ላይ ሥልጣን ተሰጥቶታልና፡፡
☞ከብርሃናት አለቃ ከራጉኤል በቀር ፀሐይና ጨረቃን ከዋክብትንም
የሚያዠዛቸዉም የለም፡፡ ፀሐይን በጠፈረ ሰማይ ላይ በቀን ያበራ ዘንድ
አሠለጠነው፡፡ ጨረቃንም ብርሃኑን በሊት ይሰጥ ዘንድ አሠለጠነው፡፡ከዋክብትም
እንዲሁ ለሰማይ የፈረጥ ጌት ናቸው፡፡
☞ዳግመኛም መልአከ ብርሃናት ራጉኤል በከዋክብት ላይ ሰባት አለቆችን ሾመ፡፡
☞የኒህ የብርሃናት አለቆች የመላእክት ሰማቸው ነቢዮ፤ኢሳይያስ እንደስማቸው
ሸረህ መሽተሪህ አጣርድ ዝኁራ፤ዙኃል፤ቀመር ይባላል፡፡
☞እነዚህ የከዋክብት አለቆች ታዛዥነታቸው ለመላእክት አለቃ ለራጉኤል ነው፡፡
እሱ በብርሃናት ሁሉ ላይ የሠለጠኀ ነውና፡፡
☞ልመናው አማላጅነቱ ለሁላችን ይደረግልን፡፡
☞የጽሑፍ ምንጭ (ድርሳነ ራጉኤል)
☞ቅዱስ ራጉኤል ህይወት ለጨለማችሁ ሁሉ ብርሃን ይሆናችሁ፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
☞
https://t.me/Orthodoxtewahdoc