ፍልስፍና™


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Blogs


Wave & promo contact us @Fredobasn

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Blogs
Statistics
Posts filter


ስራ እየፈለጋችሁ ነው?
እስካሁን የአፍሪወርክ ቻናልን አልተቀላቀላችሁም? በአፍሪወርክ በየወሩ ከ1000 በላይ የተለያዩ ስራዎች ይለቀቃሉ።


የለም ያሉት የሉም‼️

ጀርመናዊው ፈላስፋ ፍሬድሪክ ዊሃልም ኒቼ የፓስተር ልጅ ነው። አዳሪ ትምህርት ቤት ሲገባ በፍልስፍና ፍቅር ወደቀ። በጊዜ ሂደት የራሱን ፍልስፍና ይዞ ተገለጠ። እግዚአብሔር የለም እግዚአብሔርን ሰዎች ራሳቸውን ለማፅናናት የፈጠሩት ፈጠራ ነው በሚል ፍልስፍና ብዙዎችን አሳመነ። በተለይ Joyful Wisdom በተባለ ስራው እግዚአብሔርን በብዙ ኮነነ ተሳለቀበት። የኒቼን ያህል እግዚአብሔርን የተቃወመ ፈላስፋ የለም ነው የሚባለው።

ይህ ፈላስፋ በተለይ የአውሮፓ ምሁራንን በማሳመን ከካርል ማርክስ ቀጥሎ የሚደርሰው አልነበረም። ዛሬም ይህ ፈላስፋ ብዙ ተከታዮች አሉት።

ታዲያ እግዚአብሔር የለም ያለው ይህ የዓለማችን ስመጥር የኒሂሊዝም ፈላስፋ ፣ አሟሟቱ የከፋ ነበር። በ1889 በአዕምሮ መታወክ ሲታመም ቆይቶ ፍፁም እብድ ሆነ። በእህቱ ቤት ሲሰቃይ ኖሮ እንዳበደ ህይወቱ አለፈ።

የለም ያሉት የሉም ፤ የለም የተባለው አለ!

ከጥላሁን ሁሴን


By: ፍልስፍና™
ለሌሎች መፅሐፎች @bookshelfeth1 ተቀላቀሉ።




ለመጀመሪያ ጊዜ ሽምግልና ሄድኩኝ። ያው ዳሩለት ለማለት ነው እንግዲህ። እና የልጅቷ አጎቶች ተቆጡ።

"ገና የመጀመሪያ ዲግሪዋን ማግኘቷ ነው፤ ሁለተኛ፣ ሶስተኛ ዲግሪዋን ከያዘች በኋላ ጋብቻው ይደርሳል፤ ምን ያስቸኩላል አሉ።"

"ትዳርም ተይዞ ትምህርቱ ይቀጥላል" አልን።

በዚህ ተስማምተን ላጫት ልጅ ደወልኩለት።

"መማር አለባት ብለው ቤተሰቦቿ ተቆጥተዋል፤ ታስተምራታለህ ወይ?" አልኩት።

"ትማራለች፣ አስተምራለሁ፣ ትማራለች" አለ።

"ጥሩ ያው ትማራለች" ብሏል አልን። እናም በሁለተኛው ወር አረገዘች።

"እንዴ... ምነው ትማራለች አላልክም ወይ?" ብንለው

"ከሕይወት ነው ያልኩት"

✍️ አለማየሁ ገላጋይ (🎈HBD 🎂)

Via ኖኅ book delivery




ይህ ፓስታ ሳይሆን ሐዋሳ ከተማ ከ8 ዓት ህፃን ጉሮሮ በቀዶ ህክምና የወጣ ትል/ፓራሳይት/ ነው።

ትሉ የልጁን ጉሮሮ በመዝጋት ከተበከለ በኋላ በቀዶ ጥገና ተወግዷል።

እነዚህ ትሎች/ፓራሳይቶች/ ወደ አንጀታችን የሚገቡት የእጃችንን ንፅህና ባለመጠበቅ ነው። በተጨማሪም ንፁህ ያልሆኑ/የተበከሉ ፍራፍሬዎችን እና አትክልቶችን በመመገብ ወደ እኛ ይተላለፋል።

ስለዚህ የምግብ ንፅህናን በመጠበቅ እራሳችንን እና ሌሎችን ከበሽታው እንጠብቅ!
(ዶክተር ናፊያ),Photo credit hakim


አንድ የቤተክርስቲያን ሰባኪ ለረዥም ሰዓት በመንበርከክ ወደ ፈጣሪ ሲፀልይ ከቆየ በኋላ ፈጣሪውን በድንገት እንዲህ ሲል ጠየቀው፡- "አምላክ ሆይ! በእንተ ዘንድ አንድ ሚሊዮን ዓመት ስንት ይሆን?"
ፈጣሪም መለሰ "አንድ ሴኮንድ፡፡"
በቀጣዩ ቀን ይህ ሰባኪ በተመሳሳይ እየፀለየ አሁንም ፈጣሪውን ሌላ ጥያቄ ጠየቀው፡·
"አምላክ ሆይ! በአንተ ዘንድ አስር ሚሊዮን ዶላር ስንት ይሆን?"
ፈጣሪም መለሰ "አንድ ሳንቲም።"
በዚህ ጊዜ ሰባኪው "እንግዲያውስ አምላክ ሆይ አንዲት ሳንቲም ብቻ ልትስጠኝ ትችላለህ?"
ፈጣሪም መለሰ፡- "አንዲት ሴኮንድ ብቻ ታገሰኝ!"

ምንጭ ፦ ጥበብ ፱(የፍርሀት ካቦች)
ፀሀፊ ፦ ሀይለጊዮርጊስ ማሞ (ጲላጦስ)
VIA የጥበብ መንገድ


ካታርሲስ(Catharsis)

፨፨፨

የአሪስቶትል የፍልስፍና ሃሳብ ካታርሲስ /ስሜትን ማጥለል / ይባላል ። የካታሪስ ቲዎሪ ባጭሩ ሲቀመጥ ይህንን ይመስላል...

" አንድ ሰው የቅርብ የሆነ ዘመዱ ወይም ወዳጁ ሲሞት የሚያለቅሰው ለሟቹ ሰው በማዘን ሳይሆን በማዘኑና በማልቀሱ ግን ራሱ የሚያገኘው እፎይታ(relief) ስላለ ነው። በለቅሶውም የራሱ ሃጢያትና ክፋት ካሳ እንደሚያገኝለት ያምናል። "

በሌላ አገላለጽ አሪስቶትል ይህንኑ ሲያስረዳን...

"አንድ ንፁህ ሰው በሞት ሲቀጣ ብትመለከትና ብታለቅስ፤ ንፁህ ሰው ያለጥፋቱ በመሞቱ ሳይሆን ያለቀስከው ራስህን በሰውዬው ቦታ በማስቀመጥ 'እኔ በዚህ ሰው ቦታ ብሆንስ?' በሚል ስሜት ስለምትንገላታ ነው። እንግዲህ በሰው ሞት ውስጥ የራስህን ሞት ማየት ካታርሲስ ይባላል" ይለናል ።

join us @philosophyeth
Join our book store channel @bookshelfeth1

Contact us @Fredobasn or @hisandphilobot


የኢትዮጵያ ፖለቲካ 👎
ሁሌም አሳቢ ሰዎችን እንደበላና እንደቀጠፈ ነው።


ለእስልምና እምነት ተከታይ የፍልስፍና ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ረመዳን ከሪም!


አንዳንዴ እድለወርቅ ጣሰው እንደተባለችው ተዋናይት ለረዢም ሰዓት ሳልንቀሳቀስ እጀን አነባብሬ ይችን ዓለም በዝምታ መታዘብ ያምረኛል! ግን ምን ማረፊያ አለ?! አሁን ዩ ቲዮብ ላይ የድሮ መዝናኛ ፕሮግራም እያየሁ ነበር ፤ አንዱ የሃያ ሰባት እንስሳትን ድምፅ አስመስየ ማውጣት እችላለሁ ብሎ  እንደበግ፣ እንደአንበሳ ፣እንደድመት  ሲጮህ ቆየና  ...በመሃል እህ አህ አለ...

ጋዜጠኛው "ይሄ የአህያ ነው?" አለ
ልጁ " አይ የኔ ነው ፣ ጉሮሮየን እያጠራሁ ነው"
Alex
Via ህብረ ቀለማት

Join us @philosophyeth
Join our book store channel @bookshelfeth1
🖍 for advertisements @hisandphilobot


የፈጣሪ ህልውና በሳይንስ መነፅር .pdf
6.5Mb
ሌሎች መፅሃፎችን ለማግኘት የመፅሃፍት ቻናላችንን ይቀላቀሉ
Join us @philosophyshelf1
Join us @philosophyshelf1




#ሰሞንኛ
(በእውቀቱ ስዩም)

በኔና በናንተ መሀል ይቅርና፥   ፒያሳ አካባቢ ቤት ሲፈርስ የሆነ ግርግር ጠብቄ ነበር፤ ወፍ የለም! ወፍ ብቻ ሳይሆን  ወንጭፍም የለም!  እኔ ቤት የለኝም እንጂ ቤት ቢኖረኝ እና እናፍርስ ብለው ቢመጡብኝ ጉድ ይፈላ ነበር፤  ከዶዘሩ  ፊትለፊት፥  እንደ አብርሽ ዘጌት ፥እግሮቼን አንፈራጥጨ ቆሜ መንገድ እዘጋ ነበር ፤ ከዛ ትቦየን ይዘጉትና መንገዱን ይከፍቱታል  ፤
  
ስሙኝማ ! በቀደም ዋናው የትራንስፖርቱ ሰውየ  በሚድያ ላይ ቀርበው፥ በነዳጅ እሚሰራ መኪና እዚህ አገር ድርሽ እንደማይል ከተናገሩ በሁዋላ የሚከተለውን አስከተሉ፤

“ የሞተር አልባ የትራንስፐርት አማራጮች ላይ እንሰራለን፤አንደኛው ሞተር አልባ ዜጎች በእግር እንዲሄዱ፤ (እንፈልጋለን) አንደኛ ለጤናቸው ጥሩ ነው ፤ ሁለተኛ ተሽከርካሪ መጠቀምን ይቀነሳል፤ አካባቢ ላይ ብክለት ይቀንሳል ፤ ሌላው ሳይክል ነው፤ እሱን መጠቀም ነው፤ በእንስሳ የሚሰራ ጋሪ ፤ ማበረታት ነው ያለብን፤ ማዘመን እንችላለን፤ ያህያና የፈረስ ጋሪ እሱን እያዘመን እንደ ትራንስፖርት አማራጭ ስራ ላይ እንዲውሉ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጥሩ ውጤት ተገኝትዋል፡ “

በውነት ልማትን  መንቆር ሱስ  ካልሆነብን በቀር  አሁን  ይሄ ሀሳብ  ምን ይወጣለታል? በበኩሌ ሀሳቡን ግጥም አድርጌ ደግፌ ጥቂት ማሰተካከያ ብቻ አበረክታለሁ፤

ዜጎች በእግር እንዲሄዱ ማበረታታቱ  ጥሩ ነው፤ ግን ከኮተቤ ወይራ ሰፈር እየተመላለሰ የሚሰራውን ሰውየ በእግርህ ሂድ ማለቱ  ትንሽ ሊከብድ ይችላል፤ ስለዚህ  መስርያቤቱን ወደ ቤቱ ገፋ አድርጎ ማቅረብ  ቢቻል ! ወይም ዜጎች በእግራቸው እየሄዱ የሚሰሩትን ስራ መፍጠር ቢቻል ሸጋ ነው!   አለበለዝያ  ብዙ ዜጎች ጤናቸውን ለመጠበቅ ሲሞክሩ ስራቸውን ሊያጡ ይችላሉ፤

ነዳጅ የሚሰሩ መኪኖች አካባቢ መበከላቸው ሀቅ ነው፤  ይሁን እንጂ አንድ ዜጋ ከፒያሳ ቦሌ አራብሳ ድረስ በእግሩ ከሄደ የካልሲው ሽታ እንኩዋን አካባቢ  ጋላክሲውን ሊበክል ይችላል  ፤ ይሄ እንግዲህ ከሚሊዮን ጭቁን ብብቶች   የሚመነጨውን  የላብ ጠረን  ሳናነሳ ነው፤  ስለዚህ የትራንስፖርት ሚኒስተር   በእግር ለሚሄዱ ዜጎች ተለዋጭ ካልሲ እና ዶዶራንት ቢያሰናዳ አሪፍ ይሆናል  ! በተጨማሪም በየሁለት  ኪሎ ሜትሩም የህዝብ ገላመታጠቢያዎች ቢሰናዱ አይከፋም፤

ጋሪዎችን ማዘመን በሚለው ሀሳብም  ሙልጭ አድርጌ እስማማለሁ! ይሁን እንጂ  በዚህ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዘመን በፈረስ የሚጎተት ጋሪ አይነፋም! ስለዚህ የማይጎተት wireless ጋሪ መስራት ቢቻል ይጠቅማል ብየ አስባለሁ፤

በእንስሳ የሚሰሩ ጋሪዎች መኖር አለባቸው ከተባለም አይደብረኝም ፤  ይሁን እንጂ የአህያና ፈረስ ፋንድያና ሽንት የሚፈጥረው አህጉራዊ ብክለት ግን ይታሰብበት !  ለዚህም የሚከተለውን መፍትሄ በነጻ አበረክታለሁ፤   የፈረሶች መቀመጫ ላይ (ለካ አይቀመጡም) ፤በፈረሶች ጭስ ማስወጫ ዙርያ  ሸብ የሚደረግ  ምንጣፍ እሚያክል ዳይፐር ይዘጋጅ!

ፈረሶች ሲወጥራቸው ወደ ህዝብ መጸዳጃ ጎራ ብለው ፋንድያቸውን እንዲጥሉ ማሰልጠን ሌላው መፍትሄ ነው፤ በቂ በጀት ካለ ተጨማሪ ሀሳቦች ይኖሩኛል 🙌🏽

Join us 📢 @philosophyeth
For ads 🤖@hisandphilobot


አንድ ሰው ካህሊል ጂብራንን ጠየቀው፡-

"በሰዎች ውስጥ በጣም አስደናቂው ነገር ምንድነው?"

እርሱም፡

“ሰዎች በልጅነት ጊዜ ይሰለቻቸዋል ለማደግ ይቸኩላሉ፤ ከዚያም እንደገና ልጅ ለመሆን ይናፍቃሉ። ስለ ወደፊቱ ጊዜ በጭንቀት ያስባሉ እና የአሁኑን ይረሳሉ። ስለዚህ በአሁንም ሆነ በወደፊቱ ውስጥ አይኖሩም፤ የማይሞቱ መስለው ይኖራሉ ያልኖሩም ሆነው ይሞታሉ..። ”

Join us 📢 @philosophyeth
For ads 🤖@hisandphilobot


`` ህይወት ለማንም ነፃ ትምህርት አትሰጥም "ህይወት አስተማረኝ" ስትል ዋጋ እንደከፈልክ እርግጠኛ ሁን!። ``

                  -Nagib mahfouz

📢 telegram: t.me/philosophyeth
🤖 Bot: t.me/hisandphilobot


በሩን ዘግታችሁ መዘጋቱን ለማረጋገጥ ለምትመለሱ ሰዎች፤ ስልኩን ወደ ኪሳችሁ ካስገባችሁ በኋላ እየተደወለላችሁ ለሚመስላችሁ ለማጣራት ኪሳቹን ለምትዳስሱ፤ አንድ አረፍተ ነገር ተናግራችሁ ያልተደመጣችሁ መስሎአቹ ቃላት የምትደጋግሙ፤ በሳሎናችሁ መብራቱን አጥፍታቹ ነገር ግን እንደጠፋ ለማረጋገጥ ለምትመለሱ።

ውድ ወገኖቼ ወደ እብደት አፋፍ ላይ ናችሁና ደስ ይበላችሁ 😃

             
         -Dr አህመድ ካሊድ ተውፊቅ


📢 telegram: t.me/philosophyeth
🤖 Bot: t.me/hisandphilobot


አንዳንድ ግንኙነቶች አሉ. .  በዝምታ የሚያልቁ ንግግሮች፤ ያልተጨበጡ ደቂቃዊ ደቃቅ ቆይታዎች፤ ያልታቀፉ ገላዎች፤ ድፍረት ያልጎበኘው አሳብ ሽቶ ባነሳው ጠረን በዓይን በአንገት የሚናገሩት፤ መነካካት፣ መሳሳም፣ መተቃቀፍ፣ መላፋት የሚናፍቁ፤ አንዳንድ ግንኙነቶች አሉ ለመገናኘት ያልተፈጠሩ..

Via imagination

📢 telegram: t.me/philosophyeth
🤖 Bot: t.me/hisandphilobot


ሰውየው እስራኤላዊ ነው:: የታሪክ ተመራማሪ ነው:: ፕሮፌሰር ነው:: እዛው እስራኤል አገር University of Jerusalem ውስጥ የታሪክ መምህርም ነው:: One of the Brightest Mind on Planet Earth ይሉታል ምዕራባዊያኖች:: ሦስት ተፅዕኖ ፈጣሪ የሚባሉ ሳይንሳዊ  መፅሐፎችን ፅፏል::

ፕሮፌሰር Yuval Noah Harari

የዚህ ፕሮፌሰር የመጀመርያው Non-Fiction መፅሐፍ 'Sapiens: A Brief History of Humankind' ይባላል:: ፕሮፌሰሩ በዚህ መፅሐፉ የሰውን ልጅ [ዘረ-ሰብ] በታሪክ ውስጥ ያለፈበትን ረዥም ጉዞ ያስቃኘናል:: የሰው ልጅ ካልሰለጠነበት ዘመን የእንጨት ጦር ከመወርወር እስከ ተመዘግዛጊ ኒውክለር ሚሳኤሎች እስከማስወንጨፍ የሄደበትን ጉዞ ያትታል::  የሰው ልጅ ከጥንታዊ አደንና ቃርሚያ ህይወት እስከ ዘመናችን የካፒታል ስርዓት ያደረገውን ጉዞ ይዳስሳል::

ሁለተኛው Non-Fiction መፅሐፉ "Homo Deus: A Brief History of Tomorrow" ይባላል:: ፕሮፌሰሩ በዚህኛው መፅሐፉ ደግሞ የሚነግረን ስለ ሰው ልጅ የወደፊት ታሪክ ነው::  ዘመናዊው እና ዲጂታሉ ዓለም ሰብአዊነትን እንዴት እንደሚለውጥ ይተነብያል:: አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የሰውን ልጅ የበላይነት ቀምቶ አለምን በቁጥጥሩ ስር እንደሚያውል ፣ እንደ ባዮ-ቴክኖሎጂ እና ጄኔቲክ ኤንጂነሪንግ ያሉ የቴክኖሎጂ ዕድገቶች ሊያስከትሉ ስለሚችሉት ውጤቶችም ይጠነቁላል::  ከዚህ ጋር ተያይዞም በ2050ዓ.ም ሰዎች ሞትን ያሸንፋሉ:: ገንዘብ ያለው ማንኛውም ሰው ወደ ሆስፒታል እየሄደ ዕድሜውን ቻርጅ እያስደረገ እስኪሰለቸው ዘላለማዊ ሆኖ መኖር ይችላል:: ኢ-መዋዕቲ ነፍስ ይኖራቸዋል ይላል:: [ Humans are Essentially Algorithm, and the focus shifts from individual experiences and subjective values to objective data and accumulation of knowledge ]

ሦስተኛው መፅለፉ ደግሞ "21 Lessons For the 21st Century" የሚል ነው:: በዚህ መፅሐፉ ደግሞ ፕሮፌሰሩ የሚነግረን የአሁኑ ዘመን ሰው  ስለተደቀነበት ተግዳሮቶች እና መከራ ነው:: በዲጂታል ቴክኖሎጂ ፕላትፎርሞች Facebook, Twitter, Instagram, Tik Tok, Youtube ወዘተ የውሸት ዜናዎችና የተሳሳቱ መረጃዎች ይስፋፋሉ ሃገሮች እርስ በእርስ የሳይበር ጥቃት ይከፋፈታሉ::  [ በነገራችን ላይ ከዚህ በኋላ በጦር መሳርያ የሚካሄድ ጦርነት እንዳትጠብቁ ሁሉም ጦርነቶች ሁሉ የሚደረጉት በዲጂታል ነው):: ሌላው የተራቀቁ ማሽኖችና ሶፍትዌሮች እና የኮምፒውተር አልጎሪዝሞቾ በቅርቡ የሰዎን ልጅ አብዛኛውን ዘርፍ ይቆጣጠራሉ:: የቨርችዋል አለም ግዙፋን ካምፓኒዎች - የአንተን ማንነት ለሚፈልጉ ካምፓኒዎች መረጃህን ይሸጡታል:: በአጭሩ እኛ የሰው ልጆች በቀደመው 20ኛው ክፍለ ዘመን የፈጠርነውን የአኗኗር ፣ የአሰራር እና የመንግስት አስተዳደር ስርዓት ይዘን የገባንበትን 21ኛው ክፍለ ዘመንን መሻገር እንደማንችል አስረግጦ ይነግረናል::

ታዲያ ይሄ የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር እና የአለማችን ባለብሩህ አዕምሮ የተባለው ሰው ከሰሞኑን The Late Show with Stephen Colbert እና Jimmy Kimmel Live ሾዎችን ጨምሮ በተለያዩ የሚዲያ መድረኮች ላይ እየቀረበ እንደ መጥመቁ ዮሐንስ ብቻውን ከፊታችን ስለሚመጣው ክስተት እየጮኸ እየለፈፈ ነው::

ለምን? ምንስ ብሎ?

We are very near the end of our species because AI is a weapon of mass destruction to Humanity...የሰው ልጅ በታሪክ ሂደት ውስጥ ብዙ አጋዥ ቁሶችን ፣ መገልገያ ማሽኖችን በእጁ ሰርቷል ነገር ግን እነዚህ በሰው ልጅ የተሰሩ ነገሮችን ከድንጋይ ቢላ እስከ አቶሚክ ቦንብ ድረስ ብንመለከት በእኛ ቁጥጥር ስር ያሉ ናቸው እንዴት እና በምን አይነት ሁኔታ መጠቀም እንዳለብን የምንወስነው እኛ ሰዎች ብቻ ነን:: እንጂ እነዚህ ነገሮች በፍፁም በራሳቸው ውሳኔ ማሳለፍ አይችሉም ፣ አዲስ ሐሳብም መፍጠር አይችሉም::

ለምሳሌ የሰው ልጅ አቶሚክ ቦምብን ሰራ ነገር ግን ቦምቡ በራሱ ልፈንዳ ብሎ አይወስንም እኛ የት? እና መቼ? የሚለውን ነገር ካልወሰንን በስተቀር:: በተጨማሪም የሰው ልጅ ፕሪንተር ሜሽን ሰርቷል ነገር ግን ይሄ ፕሪንተር ሜሽን ፕሪንት የሚያደርገው እኛ የሰጠነውን ፅሁፍ ነው:: የእኛን ሃሳብ ነው እንጂ በራሱ አንድ ነጠላ ፊደል እንኳ ፅፎ ማተም አይችልም እኛ ካላዘዝነው::

በአጠቃላይ የሰው ልጅ ከዚህ በፊት የሰራቸው ቁሶች እና ሜሽኖች በእኛ ውሳኔ የሚመሩ እና የእኛን ሃሳብ የሚያስተጋቡ ነበሩ:: አሁን ግን ይሄ ሁሉ ነገር በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ በአደገኛ ሁኔታ ተለውጧል:: ምክንያቱም በራሳቸው ውሳኔ ማሳለፍ የሚችሉ ፣ አዲስ ሃሳብ የሚፈጥሩ እና ከሁኔታዎች ጋር ራሳቸውን በፍጥነት የሚያላምዱ እንደ ሰው ማሰብ የሚችሉ ንቃተ-ህሊና ያላቸው Artificial General Intelligence (AGI) ስለተፈጠረ:: ብሏል:: ይሄም ከፍተኛ እንደሰው የማሰብ ፣ የመረዳት አቅም ያለው ሰው ሰራሽ አስተውሎት በጣም እጅግ በጣም በቅርብ ጊዜ ውስጥ Exist ማድረጉ አይቀርም:: በጣም አስጊ ነው:: ብሎም አክሏል::

Of Course

ዋና መቀመጫውን San Francisco, California, USA ያደረገውና December 2015 የተቋቋመው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ምርምር ተቋም ወይም 'OpenAI'  በበኩሉ የመጨረሻ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ምርምር ግብ የሆነውን ከፍተኛ ሰው ሰራሽ የማሰብ አቅም ያለውን ሮቦት ወይም AGI Achieved አድርጊያለው ብሏል:: የዚህ ተቋም ዋና ስራ አስፈፃሚ Sam Altman ስዊዘርላንድ በተካሄደው የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ባዘጋጀው ወይይት ላይ ተገኝቶ

"ሰው ሰራሽ የማሰብ ችሎታ ያለው ሮቦት ወይም AGI በጣም ኃይለኛ ከመሆኑ የተነሳ በአስደናቂ ሁኔታ አለምን ይቀይረዋል" ብሏል:: እነዚህ AGI በተቆጡ ጊዜ የሰው ልጅ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳያደርሱና የሰው ልጅም በቀላሉ ታግሎ እንዲጥላቸው ከቀላል ማቴሪያል የተሰሩ ናቸውም:: ብለዋል የግብር አጋራቸው እነ ኤለን መስክ በበኩላቸው::

እውነት ግን እንደ ፕሮፌሰር ዮቫል ኖህ ሃራሪ ስጋት የሰው ልጅ በተፈጥሮ እና በሌሎች ፍጥረት ላይ የተሰጠውን የመሰልጠን እና የበላይነት ስልጣን በእነዚህ ሰው ሰራሽ አስተውህሎቶች ይነጠቅ ይሆን??

እኔ እንጃ እስኪ አብረን የምናየው ይሆናል በመጨረሻም በ1999 ለዕይታ በበቃው ሳይንሳዊ ልቦለድ ዘውግ ባለው 'The Matrix' ከተሰኘው ፊልም ላይ በተዘገነ ቃለ-ተውኔት (Dialogue) ልሰናበት::

"We marveled at our own magnificence as we gave birth to AI.....Singular consciousness that spawned an entire machine"

ከእንግዲህ 'I'm Not A Robot' ብለን የምንሞላው የCaptcha ቦክስም አይኖርም ማለት ነው:: Let's Strive For Peace on Earth 🙏


© YOAKIN BEKELE
From ከፍልስፍና ዓለም

🌐 Blogger:philosophyeth.blogspot.com
📢 telegram: t.me/philosophyeth
🤖 Bot: t.me/hisandphilobot

20 last posts shown.