ሰሌዳ | Seleda


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Other


የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Other
Statistics
Posts filter


በግንባታ ላይ ባለው የመቄዶኒያ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ የተከሰተ የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ

በግንባታ ላይ ባለው የመቄዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ ተከስቶ የነበረ እሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 3 መቄዶኒያ የአእምሮ ህሙማንና የአረጋዊያን መርጃ ማህበር እያስገነባ ባለዉ ህንጻ ስር ባለ መጋዘን ላይ እሳት አደጋ መከሰቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ንጋቱ ማሞ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ በደረሰዉ ጥሪ መሰረት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች በቦታዉ ፈጥነዉ በመድረስ እሳቱ ሳይስፋፋ በፍጥነት መቆጣጠር ችለዋል።

በእሳት አደጋዉ በመጋዘን ውስጥ የነበሩ ልዩ ቁሳቁሶች ላይ መጠነኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በሰዉ ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን ተናግረዋል።


#EarthQuake

" በኢትዮጵያ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ለ22 ቀናት ወደ መሬት ለመውጣት ተፈጥሯዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው ቅልጥ አለት የመወጠር ሁኔታ አሁን ረገብ ብሏል " ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂዮ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ኤልያስ ሊዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን/ኢቲቪ ተናግረዋል።

" አሁን ባለን መረጃ ቅልጥ አለቱ ወደታች እየወረደ ነው ፤ በዚህም ምክንያት ባለፉት 2 ቀናት የተመዘገበው የመሬት መንቀጥቀጥ ዝቅተኛ ነው " ብለዋል።

" ቀደም ሲል የነበረው ስጋት ባለፉት ቀናት ቀንሷል " ያሉት ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር) ፥ " ነገር ግን በስምጥ ሸለቆ ውስጥ የምንገኝ እንደመሆናችን ስጋቱ ተመልሶ ሊመጣ ይችላል " ሲሉ ተናግረዋል።

" ስምጥ ሸለቆ እና አካባቢው በተፈጥሮ ለመሬት መንቀጥቀጥ ተጋላጭ መሆኑ የማይቀየር ተፈጥሯዊ እውነታ ስለሆነ እንደ ሀገር፣ እንደ ህዝብ የራሳችንን ጥንቃቄና ዝግጀት ማድረግ ያስፈልጋል " ሲሉ ለቴሌቪዥን ጣቢያው በሰጡት ቃል አስገብዝበዋል።

ባለፉት ቀናት እና ሳምንታት በአፋር ፣ ፈንታሌ አካባቢ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ እንደነበር ይታወቃል። የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ እስከ አዲስ አበባ እና ሌሎችም ከተሞች ዘልቆ የተሰማ ነው።


በኦሮሚያ 'የሽማግሌዎችን ትዕዛዝ አላከበረችም' የተባለች እናት በተፈጸመባት ግርፋት ተጎድታ ሆስፒታል ገባች

ቅዳሜ ጥቅምት 9 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በምስራቅ ቦረና ዞን ዋጪሌ ወረዳ 'የሽማግሌዎችን ትዕዛዝ አላከበረችም' በሚል ከዛፍ ጋር ታስራ በባለቤቷ የተደበደበችው እናት በአስጊ ጤና ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ የቤተሰብ አባሏ ተናገሩ።

በአሁኑ ወቅት በሐዋሳ ሆስፒታል በህክምና ላይ የምትገኘው ኩሹ ቦናያ የተባለችው እናት በደረሰባት ግርፋት ክፉኛ ተጎድታ የአካሏ ግራ ክፍል አይሰራም። የራስ ቅሏ ተሰብሯል በማለት የቤተሰብ አባሏ ገልጸዋል።

የአካባቢው አቃቤ ሕግ በበኩላቸው ግርፋቱን መፈጸማቸው የተጠረጠሩ ባለቤቷን ጨምሮ ስምንት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ መካሄዱን ተናግረዋል።

የሦስት ልጆች እናት የሆነችው እናት በኦሮምያ ምስራቅ ቦረና ዞን ዋጪሌ ወረዳ የሽማግሌዎችን ትዕዛዝ አልተቀበለችም በሚል ከዛፍ ጋር ታስራ በባለቤቷ የተገረፈችው ግለሰብ በአሁን ሰዓት በሐዋሳ ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እያደረገች መሆኑ ተገልጿል።

በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች መካከል የቅጣት ውሳኔውን አስተላልፈዋል የተባሉት ሽማግሌዎች የዋስትና መብታቸው ተከብሮ ሲለቀቁ ባለቤቷ ግን አሁንም በቁጥጥር ስር እንደሚገኝ አቃቤ ሕግ ገልጿል።

የሦስት ልጆች እናት የሆነችውን ሴት ዋጪሌ ገበያ ላይ አስሮ የመግረፉ ድርጊት የተፈጸመው ባለፈው ወር መስከረም 9/ 2017 ዓ.ም. መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።


#Infinix_TV

ፍሬም አልባ ስማርት ቲቪ፣ ኩልል ያለ ድምፅ፣ የአንድሮይድ 11 ሲስተም የተገጠመለት፣ ዩቱዩብ ቢሉ ኔት ፍሊክስ አማዞን ቢሉ ኢንተርኔት ያለምንም እክል በፍጥነት ከሶፋዎት ምቾት ላይ ሆነው በስማርት ሪሞት መጠቀም የሚያስችል፤ ካፈለጉም በድምጾት የሚያዙት አዲሱን የኢኒፊኒክስ ስማርት ቲቪ X5 እናስተዋውቆት በ32 በ43 እና55 ኢንች ይጠብቁት፡፡

@Infinix_Et | @infinixet?_t=8qe2yVJoUeU&_r=1' rel='nofollow'>@Infinixet

#InfinixTVX5 #Infinix #ElevateYourSpace #PerfectFit #tvx5


ሂዝቦላህ የጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ መኖሪያ ላይ ያነጣጠረ የድሮን ጥቃት ሰነዘረ

የእስራዔል ጦር እንዳስታወቀው÷ ዛሬ ጠዋት ላይ ከሊባኖስ የተላኩ ድሮኖች በቄሳሪያ ከተማ ጥቃት መፈፀማቸውን ተከትሎ በከተማዋ ከፍተኛ የፍንዳታ ድምፅ ተሰምቷል፡፡

በጥቃቱ በከተማዋ የሚገኘው የጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁ መኖሪያ ዒላማ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን፤ በአካባቢው በሰዎች ላይ ጉዳት አለመድረሱ ተመላክቷል፡፡

የእስራዔል ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ጥቃቱ በተሰነዘረበት ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ባላቤታቸው በአካባቢው እንዳልነበሩ አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም ሁለት ድሮኖች ከሊባኖስ ተነስተው በከተማዋ ጥቃት ለመፈፀም እየበረሩ በነበረበት ወቅት በእስራዔል አየር ሀይል ተመትተው ወድቀዋል ተብሏል፡፡

ጥቃቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታኒያሁን ለመግደል በማለም በኢራን የተቀነባበረ ነው ሲል የሀገሪቱን ባለስልጣናትን ጠቅሶ ኢየሩሳሌም ፖስት ዘግቧል።


የዶ/ር ደብረጽዮን ቡድን ሰላማዊ ትግል እንደሚያደርግ አስታወቀ

በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. በመቐለ፣ ሰማዕታት ሐውልት አዳራሽ ከባለሃብቶች ጋር ባካሄደው ስብሰባ፣ እርሳቸው የሚመሩት ቡድን ሰላማዊ ትግል እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡

በዚሁ ስብሰባ ላይም፣ ከምርጫ ቦርድ ህጋዊ ዕውቅና ባልተሰጠው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ያልተሳተፉትንና በቡድናቸው የተባረሩትን የድርጅቱን አመራሮች ወቅሷል፡፡

“ጉባዔ እንዳናካሂድ ብዙ ሙከራ ተደርጎብናል፡፡ ጉባዔ አለማካሄድ ድርጅቱን ማፍረስ ነው። ይሁንና ወደ ጉባዔ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሰን እያለ፣ እነርሱ ግን ‘አንገባም’ ብለው አንገራገሩ። ‘ጉባዔው ከተካሄደ ጦርነት ይከተላል’ ተባለ። የጉባዔው ተሳታፊዎች ጉባዔው ወደሚካሄድበት ቦታ እንዳይመጡ ጥረት ተደርጓል።” ሲሉ ዶ/ር ደብረጽዮን ተናግረዋል፡፡

በጉባዔው ላይ እርሳቸው የሚመሩት የህወሓት ቡድን ያለፉትን ስድስት ዓመታት ፖለቲካዊ ስራዎች መገምገሙን የጠቆሙት ዶ/ር ደብረጽዮን፤ “በዚህ ጉባዔ ተበትኖ የሚገኘውን ሕዝባችንን ወደ ቀድሞ ቀዬው እንዲመለስ፣ መሬታችን ተመልሶ በእኛ አስተዳደር ስር እንዲሆን፣ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥና በኢኮኖሚ ግንኙነቶችና በሌሎች ተጀምረው በነበሩ ጉዳዮች ላይ ጥናት በማካሄድ እንቅስቃሴው ዳግም እንዲጀመር ውሳኔዎችን አስተላልፈናል” ብለዋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን የህወሓት፣ የትግራይ ሃይሎች፣ የምሁራንና ተቃዋሚ ድርጅቶች በመቀናጀት እንደመሰረቱት በማስረዳት፣ “ለአስተዳደሩ የጊዜ ገደብ አስቀምጠንለት ነበር። ይሁንና በክልላችን ሰላም ልናሰፍን አልቻልንም። ሕዝባችን ወደ ቀዬው አልተመለሰም። ባለሃብቶችና ነጋዴዎች ትግራይን መልሶ ወደ መገንባቱ ሊገቡ አልቻሉም” ሲሉ ወቀሳቸውን ሰንዝረዋል፡፡


አራተኛው የብሪክስ አስተባባሪዎች ስብሰባ ተጀመረ

በስብሰባው ላይ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታና የኢትዮጵያ የብሪክስ ጉዳይ ምክትል አስተባባሪ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ የተመራ ልዑክ እየተሳተፈ ይገኛል።

ስብሰባው የካዛን ረቂቅ ስምምነትንና የብሪክስ አጋር አገራት አሠራርን ማዘጋጀት ላይ ትኩረቱን አድርጎ እንደሚካሄድ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

16ኛው የብሪክስ አባል አገራት የመሪዎች ጉባዔ ከጥቅምት 12 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም. በካዛን ከተማ ሩስያ ይካሄዳል።


በጫሞ ሐይቅ ጀልባ ሰምጦ 14ቱ ሰዎች አልተገኙም !

ሙዝ ጭኖ ሲመለስ የነበረ ጀልባ ጫሞ ሐይቅ ሰምጦ ከተሳፈሩ 16 ሰዎች ውስጥ ሁለቱ መገኘታቸውን የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገለጸ።

የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙት እና ገጽታ ግንባታ ድቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ረታ ተክሉ እንደገለጹት ትላንት ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ የጀልባውን አሽከሪካሪ እና 15 የቀን ሠራተኞችን ከሙዝ ጋር ጭኖ ከአማሮ ዞን አቡሎ አልፋጮ ወደ አርባምንጭ ሲጓዝ የነበረ ጀልባው መስጠሙን ተናግረዋል ።

በጀልባው ላይ ከነበሩ 16 ሰዎች ሁለቱ በጀሪካን ላይ ተንሳፈው የተረፉ ሲሆን 14ቱ ባለመገኘታቸው ፖሊስ በፍለጋ ላይ መሆኑን ኮማንደር ረታ ተናግርዋል ።

ከጀልባው ቀዛፊ ውጭ 15 ተሳፋሪዎች በሙሉ ሙዝ ለመጫን ከአርባምንጭ ዙሪያ አካባቢ የሄዱ መሆናቸውን የጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።


#ከፍተኛትኩረት በደቡባዊ የሀገራችን ክፍል በቅርብ አመታት ታይቶ የማይታወቅ የወባ ወረርሽኝ ተከስቶ ህዝብ እየረገፈ ነው

በአካባቢው ያሉ የጤና ባለሙያዎች እንደነገሩኝ በወላይታ፣ በከምባታ፣ በጉራጌ ዞኖች እንዲሁም በምስራቅ ወለጋ እና ዙርያው ወረርሽኙ ተባብሷል።

ፈጣን ትኩረት ያሻዋል፣ መሠረት ሚድያ በምሽት ዜናው ሁኔታውን በስፋት ይዳስሳል።


አልሻባብ በሞቃድሾ ባደረሰው የአጥፍቶ መጥፋት ጥቃት 7 ሰዎች ተገደሉ

የአጥፍቶ መጥፋቱ ጥቃት የደረሰው በፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም አካባቢ በሚገኝ አንድ ካፍቴሪያ ሲሆን የጥቃቱ ሰለባዎች የፖሊስ አባላት እና ንጹሃን መሆናቸው ነው የተዘገበው።

በወታደራዊና በተለያዩ ተቋማት ላይ ያነጣጠረ ተደጋጋሚ የሽብር ጥቃት በመፈጸም የሚታወቀው አልሻባብ ለአሁኑ ጥቃትም ኃላፊነት ወስዷል።

ጥቃቱን አስመልክቶ አንድ የአይን እማኝ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደገለጸው ካፌው ሻይ በሚጠጡ ሰዎች ተሞልቶ እንደነበር ገልጾ ወዲያው በጩኸት ድብልቅልቁ መውጣቱን ተናግሯል።

የሶማሊያ መንግስት ህልውና በአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ጦር እና የአሜሪካ አየር ኃይል ድብደባ ድጋፍ ላይ የተንጠለጠለ መሆኑ ይታወቃል።

በአሁኑ ወቅት የሞቃድሾ መንግስት የአገሪቱን ፀጥታ በታህሳስ አገልግሎቱ ከሚያበቃው የአፍሪካ ህብረት ጦር ሙሉ ለሙሉ ለመረከብ እየሰራ መሆኑ አልጃዚራ ዘግቧል።


የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ማን ናቸው?

በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ማን ናቸው?

በሕገ-መንግስታዊነት፣ በሕግ የበላይነት፣ በዴሞክራሲ፣ ሃሳብን በነፃነት በመግለጽ፣ በሃይማኖት ነጻነት እንዲሁም በአንፃራዊ ሕገ-መንግስታዊ ሕጎች ላይ ትኩረት አድርገው ምርምር የሠሩ የሕግ ምሁር ናቸው።

በምርምሮቻቸው አፍሪካ ላይ ልዩ ትኩረት አድርገው ሠርተዋል፡፡

በአዲስ አበባ፣ በማዕከላዊ አውሮፓ እንዲሁም በሃዋሳ እና በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ድሕረ ምረቃ ባሉት ደረጃዎች አስተምረዋል።

የሕግ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡

ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከማዕከላዊ አውሮፓ ዩኒቨርሲቲ ያገኙ ሲሆን፣ የጁሪዲካል ሳይንስ ዶክትሬት ዲግሪያቸውንም ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ በሕገ መንግሥታዊ መርሆዎች እና በአንጻራዊ ሕግ ሠርተዋል፡፡

በበርካታ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የሕግና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ጽሑፎችን አሳትመዋል። በተጨማሪም በአማርኛ በሚታተሙ የሀገር ወስጥ ጋዜጦች ላይ የሕዝብ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ጽሑፎችን አሳትመዋል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት ረዳት ፕሮፌሰር እና የሕግ ትምህርት ቤቱ ኃላፊ ሆነው ያገለገሉ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ሕግ ጆርናል ዋና አዘጋጅ ሆነውም ሰርተዋል፡፡

በማዕከላዊ አውሮፓ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ሰመር ኮርስ የሕገ መንግሥት ትምሕርት ክፍል ተባባሪ ዳይሬክተር በመሆን አገልግለዋል።

በኢንዲያና ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምሕርት ቤት የሕገ መንግስታዊ ዴሞክራሲ ማዕከል ተባባሪ መምህር እንዲሁም ተመራማሪ ሆነው ሠርተዋል፡፡

ከነሐሴ 2012 እስከ ጥቅምት 2014 ዋና ዐቃቤ ሕግ፣ ከጥቅምት 2014 እስከ ዛሬ ድረስ የፍትሕ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል፡፡

እንደ የምስራቅ አፍሪካ ዓለም አቀፍ የዳኝነት ጉባኤ (EAIAC) ባሉት የሕግ ፎርሞችና ኮንፈረንሶች ላይ በመሳተፍ ገንቢ እና ለውጥ የሚያመጡ ሀሳቦችን በመስጠት ይታወቃሉ፡፡

ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) በአካዳሚክ ሕይወታቸው ያዳበሯቸው ልምዶቻቸው በመንግሥት ሥራዎቻቸውም ተግባራዊ ያደረጉ ትጉህ አገልጋይ ናቸው፡፡ በለውጡ መንግሥት ወደ ኃላፊነት ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያን ፍትሕ ዘርፍ በማሻሻል ይጠቀሳሉ።

ዶክተር ጌዲዮን የምዕራባውያን ሚዲያዎች የኢትዮጵያን ገጽታ ለማጠልሸት በዘመቱበት ወቅት በቢቢሲ ሃርድ ቶክ ላይ ቀርበው መሬት ላይ ያለውን እውነታ በማሳየት ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡

ጌዲዮን ጤሞቲዎስ(ዶ/ር) በዛሬው ዕለትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል፡፡


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ

በዚሁ መሠረት ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ሰላማዊት ካሳ የቱሪዝም ሚኒስትር እንዲሁም ሃና አርዓያሥላሴ የፍትሕ ሚኒስትር ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሹመዋል፡፡

በቅርቡ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው በተሰየሙት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ቦታ የተተኩት ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር) የፍትሕ ሚኒስትር በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡

በሌላ በኩል ሰላማዊት ካሳ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴዔታ እንዲሁም ሃና አርዓያሥላሴ ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡


የያህያ ሲንዋር መገደል የጦርነቱ ፍጻሜ አይደለም- ጠ/ሚ ኔታንያሁ


ይህን ተከትሎም የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በሰጡት መግለጫ÷ የያህያ ሲንዋር መገደል ከፍተኛ ድል ቢሆንም የጦርነቱ ፍጻሜ እንዳልሆነ አስታውቀዋል፡፡

በዚሁ መሠረት በሀማስ እገታ ሥር የሚገኙ እስራኤላውያን እስከሚለቀቁ ድረስ ጦርነቱ ይቀጥላል ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

በርካታ እስራኤላውያን እንዲገደሉ እና እንዲታገቱ በተደረገበት የጥቅምት 7 ጥቃት የያህያ ሲንዋር ሚና ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ የመሪው መገደል በአካባቢው ያለውን ሁኔታ ሊቀይረው እንደሚችል አመላክተዋል፡፡

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በበኩላቸው የያህያ ሲንዋር መገደል ለእስራኤል ብሎም ለአሜሪካ ትልቅ ድል መሆኑን ገልጸው÷ የመሪው መገደል ምን አልባትም ጦርነቱ በአጭር ጊዜ እንዲቋጭ ሊያደርገው ይችላል ብለዋል፡፡

በአንጻሩ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የኢራን ልዩ መልዕክተኛ በበኩላቸው÷ የያህያ ሲንዋር መገደል እስራኤልን ከምን ጊዜውም በላይ ለመፋለም የሚያነሳሳ የመንፈስ ጥንካሬ ይሰጠናል ብለዋል፡፡

ሁኔታው ጦርነቱን ከማብረድ ይልቅ ሊያባብሰው እንደሚችልም ነው ያስረዱት፡፡


ውቅሮ ትግራይ አዝናለች

በተዳረች በ4ኛ ቀኗ የተገደለችው ሙሽራ !

ባለፈው እሁድ በትግራይ ውቅሮ ከተማ የጋብቻ ስነስርዓቷን ፈፅማ የነበረችው ሊዲያ አለም ዛሬ ጥቅምት 7,2017 ዓም በትዳር አጋሯ ስለመገደሏ ተነግሯል ።

* በመነጋገር መፍታት

እየተቻለ እንዲህ ያሉ ነገሮችን መስማት በእጅጉ ያማል ።

የውቅሮ ነዋሪዎች
ፍትህ ለሊድያ በማለት በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ ።


የሐማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል እስራኤል ገለጸች

የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ጋዛ ውስጥ ባደረገው ኦፕሬሽን አዲሱ የሐማስ መሪ ያህያ ሲንዋር ተገድሎ ሊሆን እንደሚችል እያጣራ መሆኑን ገልጿል።

የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት እና የደህንነት ኤጀንሲ በጋራ ባወጡት መግለጫ የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ጋዛ ውስጥ ባደረገው ኦፕሬሽን ሦስት የሐማስ ቁልፍ አመራሮች ተገድለዋል።

ከተገደሉት መሪዎች ውስጥም አንዱ ያህያ ሲንዋር ሊሆን እንደሚችል በመግለጫው ተጠቁሟል።

ሐማስ በእስራኤል ላይ በፈጸመው የጥቅምት 7 ጥቃት ዋነኛ መሪ የነበረው ያህያ ሲንዋር እስራኤል ልትገድላቸው ከምትፈልጋቸው ሰዎች መካከል በግምባር ቀደምነት የሚጠቀስ ነው።


በሬክተር ስኬል 4.8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬ ሐሙስ እኩለ ቀን ላይ በአፋር አካባቢ ተከስቶ እንደነበር ቮልካኖ ዲስከቨሪ ዘግቧል።


በተከታታይ የመሬት መንቀጥቀጥ የሚከሰተው በመሬት ውስጥ የማግማ እንቅስቃሴ ኃይል ባለመቆሙ ነው ተባለ

የመሬት መንቀጥቀጥ በመሬት ውስጥ አለቶች ግጭት ሲፈጥሩ ወይም ሲላቀቁ በሚፈጠረው ክፍተት ከፍተኛ ድምፅ ሲገባ የሚከሰት ድንገተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ ወይም ንዝረት ነው።

በዚህም ከፍተኛ መንቀጥቀጥ ሲያጋጥም የመሬት መናድ፣ የህንፃዎች መፈራረስ እና ሌሎችም ተያያዥ አደጋዎች የሚያስከትል በመሆኑ የህይወት መጥፋትና ንብረት ውድመት ሊደርስ ይችላል።

በአፋር ክልል በተለይ ባለፉት ሳምንታት በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ በተለይም በአዲስ አበባና አካባቢው የተወሰኑ ሥፍራዎች በአጎራባች ከተሞች የመሬት ንዝረት ተሰምቷል።

ከዚህ ቀደም ጥቅምት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እሁድ ጠዋት በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበበት መሆኑ ይታወሳል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ለሦስተኛ ጊዜ ትናንትም በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ተከስቶ በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 6 አካባቢ የተመዘገበበት ሲሆን÷ንዝረቱ በአዲስ አበባና አካባቢው ተሰምቷል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ-ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር)÷ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተከታታይ የመሬት መንቀጥቀጥ የመከሰቱ ምክንያት በመሬት ውስጥ ያለው የማግማ እንቅስቃሴ ፈጣን (አክቲቭ) በመሆኑ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

የመሬት መንቀጥቀጥ በዚህ ወቅት ይከሰታል ወይም ይቆማል ብሎ መተንበይ አዳጋች መሆኑን አንስተው፤ በመሬት ውስጥ ያለው የማግም እንቅስቃሴ ሲያቆም አብሮ የሚቆም ይሆናል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡


አቢሲኒያ ባንክ ለኤቲኤም ተጠቃሚ ደንበኞቹ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

"የአቢሲንያ ባንክ ATM ሲጠቀሙ የሚስጥር ቁጥር አስቀድሞ እንደሚጠይቅ የሚታወቅ ሲሆን ፤ይህ አገልግሎት ተሻሽሎ የሚስጥር ቁጥር የሚጠይቀው ደንበኞች የብር መጠኑን ካስገቡ በኃላ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን" ሲል ነው ያሳሰበው።


ድምፃዊው ህይወቱ አለፈ

የቀድሞው የ one direction አባል ድምፃዊ ሊያም ፓይኒ በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል ።

የ 31ዓመት እድሜ ያለው ድምፃዊው ፤ በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ በመዝናናት ላይ የነበረ ሲሆን ፤ ከአንድ ሆቴል ወለል ላይ ወድቆ ህይወቱ እንዳለፈ ነው እየወጡ ያሉ መረጃዎች የሚናገሩት።

የአሟሟቱ መንስኤ ፖሊሶች እያጣሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።


ጠቅላይ ፍርድ ቤት እነ ጆን ዳንኤል ላይ የስር ፍርድ ቤት የሰጠውን የዋስትና ብይን አጸና

ነሐሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከአውሮፕላን አንወርድም በማለት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ተብለው የተከሰሱት ስድስት ግለሰቦች ላይ በስር ፍርድ ቤት ውድቅ የተደረገባቸውን የዋስትና ጥያቄን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አፀና።

ከ15 ቀናት በፊት በስር ፍርድ ቤት የዋስትና ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ብይን መስጠቱ ይታወሳል።

ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ የተባሉ ተከሳሾች ግን በጠበቆቻቸው አማካኝነት የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ መደረጉ አግባብ አለመሆኑን ጠቅሰው ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ብለው ነበር።

ይግባኝ ሰሚ ችሎቱ የይግባኝ ባዮችን አቤቱታን እና የከሳሽ ዐቃቤ ሕግ መልስ፣ የግራ ቀኝ ክርክርን መርምሮ የስር ፍርድ ቤት ዋስትና ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ከህግ አንጻር ተገቢ ነው በማለት ብይኑን በማጽናቱ ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን ይከታተላሉ።

20 last posts shown.