ሰሌዳ | Seleda


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Other


የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ @Contact_officework ያናግሩን

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Other
Statistics
Posts filter


ኢትዮቴሌኮም እንደ አማዞን፣ አሊባባ እና ኢ-ቤይ አይነት የዲጂታል ገበያን ወደ ኢኮኖሚው አስገባ።

ይህ የዲጂታል ገበያ ወይም ማርኬት ፕሌስ  “ዘመን ገበያ“ ይሰኛል።

በብሔራዊ ደረጃ  የዚህ የዲጂታል ገበያ ባለቤት ኢትዮ ቴሌኮም ነው።

ኩባንያው  ዘመን ገበያ የተሰኘ ፤
ሀገር አቀፍ የዲጂታል የገበያ ሜዳ ዛሬ በይፋ አስጀምሯል።

ኢትዮ ቴሌኮም ለኢኮኖሚ እድገት ያግዛሉ ያላቸውን ምዕራፎች በመለየት በቴክኖሎጂ እንዲታገዙ በማድረግ፤ ውጤታማና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በቴክኖሎጂ በማስታጠቅ ገበያውን በብርቱ እያገዝኩ ነው ብሏል።

ኢትዮ ቴሌኮም የዘረጋው የዲጂታል መሰረተ ልማቶች እና ፈጣን ኢንተርኔት ግንኙነት፣ የክላውድ፣ ሞጁላር ዳታ ሴንተር እና የቴሌብር ዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መስፋፋት ይህን ዲጂታል ገበያ ወደ ፊት ይገፈትረዋል ተብሏል።

ኢትዮ ቴሌኮም በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ የኤሌክትሮኒክ ንግድን ማእዘን፣ ብሔራዊ የዲጂታል ግብይት  ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ምቹ ሜዳ  ፈጥሬያለሁ ብሏል።

ኩባንያው ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ የዲጂታል ግብይት ሥርዓት እውን እንዲሆን እና  የሰፊውን ገበያ ጉልበት እጠቀማለሁ ብሏል።

ይህን በማድረግም የዲጂታል ኢኮኖሚ ውጤቶችን በመዘርዘር ፤ በመቁጠር አስተማማኝ በተባለ ደህንነቱ በተጠበቀ እና ማእከላዊ ዲጂታል በተባለለት ገበያ ''ዘመን የዲጅታል ገበያን “ ወደ ኢኮኖሚው ወርውሮ ተግባራዊ ለማድረግ በብርቱ ሲደክም እንደነበር የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ተናግረዋል።

በመሆኑም ኩባንያው የዲጅታል ግብይትን አንድ ወደፊት የሚያዘምነውን  ሥርዓት ወደ ኢኮኖሚው ዛሬ በይፋ አስገብቷል ተብሏል።

ይህ ዘመን የተሰኘው የዲጂታል ገበያ ሜዳ፣ምርት እና አገልግሎት አቅራቢዎች  ከሸማቾች ይገናኙበታል መባሉን ሰምተናል።

በተለይም በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ድርጅቶች ከሸማቾች ጋር በቀላሉ ለማገናኘት እድል ይሆናል ተብሏል።

አዳዲስ የገበያ እድል በመፍጠርም የዲጂታል ኢኮኖሚን ለማፍታታት እንደሚያግዝ ሰምተናል።

ዘመን ገበያ ንግድን በማቀላጠፍና ከአነስተኛ ጀምሮ እስከ ትላልቅ የንግድ ድርጅቶች በማገናኘት፣ የገበያ ተደራሽነትን በማስፋት፣ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንዲጨምር፣ የሥራ ዕድል እንዲፈጠርና አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) እንዲያድግ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል።

በሎጅስቲክስ፣ በዲጂታል አገልግሎቶች፣ በዲጂታል ገበያ፣ በችርቻሮና በቴክኖሎጂ ዘርፎች የሀገር ውስጥ የሥራ ዕድሎችን በማነቃቃት ዘላቂ የኑሮ መተዳደሪያንና የማኅበረሰብ እድገትን ይደግፋል ተብሎለታል። 

ዘመን የዲጅታል ገበያ የከተማና የገጠር ማህበረሰቦችን በማገናኘት በመላው ኢትዮዽያ በዲጂታል ንግድ ውስጥ እኩል ተሳትፎ እንዲኖር ያስችላል መባሉን ከዛሬው ጉባኤ ሰምተናል።

ይህ ጅምር፤  የድንበር ተሻጋሪ የንግድ ዕድሎችን በማመቻቸት ፤ ወደፊት የአገር ውስጥ አምራቾችና ነጋዴዎች ዓለም አቀፍ ገበያዎችን እንዲያገኙ በማገዝ  ፤ ለውጪ ንግድ ዝግጁነትን ከፍ በማድረግ ለኢኮኖሚው በብርቱ ያግዛል ተብሏል።

@seledadotio
@seledadotio


900,000 ብር ምን መግዛት ይችላል?


📍በጣም ውስን ሱቆች ግን ብዙ ፈላጊ ስላለ ይፍጠኑ !!

💥ሱቅ ሽያጭ በመሀል ፒያሳ አድዋ ዜሮ ዜሮ !!

🌆ዋና መንገድ አፄ ሚኒሊክ አደባባይ አጠገብ !!

- G+5  የንግድ ሞል
-20 ካሬዎች
-ከጠቅላላ ዋጋ=3.9 ሚሊየን ጀምሮ
 
በ900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ

እንዲሁም

ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
        
👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
          ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
    
  👉2 መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
       
👉3 መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር

        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል!!

🌟በተጨማሪም  በሳር ቤት ፣ ሱማሌ ተራ ፣ በ አያት ፈረስ ቤት ፣ በጋርመንት በተለያዩ የካሬ አማራጮች ከ40% ቅናሽ ጋር አቅርበንሎታል።

ፈጥነው ይደውሉልን።

ስልክ -0943-15-55-42
          09-73-28-74-75


የእዉቁ ካርዲዮሎጂስት ፍቅሩ ማሩ ስርአተ ቀብር በዛሬዉ ዕለት በስዊድን ሀገር ተፈፅመ፡፡

በኢትዮጵያ በልብ ህክምና  ዘርፍ የመጀመሪያ የሆነዉን የልብ ህክምና ሆስፒታል ያቋቋሙት ካርዲዮሎጂስት ፍቅሩ ማሩ ባለፈዉ ዕሁድ  ከዚህ አለም ድካም ማረፈቸዉንና በዛሬዉ ዕለት ቀብራቸዉ በስዊድን ሀገር መፈጸሙን በአዲስ የልብ ህክምና ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ ፍቅረማሪያም ነግረውናል፡፡

በሰለጠነዉ አለም ተምረዉ ወደ ትዉልድ ሀገራቸዉ በመምጣት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነዉን የልብ ሆስፒታል በማቋቋም በልብ ህክምናዉ ከሩብ ክፍለ ዘመን በላይ ህዝባቸዉንና ሃገራቸዉ ያገለገለ ነበሩ።

የጥቁር አንበሳው የልብ ህሙማን ህክምና ማዕከል ፣ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል፣ ጎንደር ዩኒቨርስቲና ሌሎቹም የልብ ህክምናን እንዲጀምሩ ካገዙት ውስጥ መሆናቸውን ዶ/ር ቴዎድሮስ ነግረውናል፡፡

በትውልድ ኢትዮጵያዊ በዜግነት ሲዊድናዊ የሆኑት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ካለፈው አንድ አመት ወዲህ የጤናቸው ነገር ታውኮ በህክምና ላይ እንደነበሩ የነገሩን ዶ/ር ቴዎድሮስ ፍቅረማሪያም ከህልፊታቸው ከሳምንት በፊትም በአዲስ አበባ ተገኝተው  የአዲስ የልብ ህክምና የማስፋፊያ ስራን መርቀው መመለሳቸውን ተናግረዋል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


በአዲስ አበባ ከተማ ካሉ የደረጃ "ሀ" እና  ደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ውስጥ  55ሺህ የሚሆኑት  ነገዴዎች በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ እንደነበር  ተገለፀ ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ካሉ የሂሳብ መዝገብ እንዲዙ ከሚገደዱ  ከ1 መቶ 1 3 ሺህ በለይ  የደረጃ "ሀ" እና  ደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ውስጥ  55ሺህ የሚሆኑት  ነጋዴዎች በቁርጥ ግብር ሲስተናገዱ እንደነበር  የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ገልጷል ፡፡

ግብር ከፋዩ በህጉ መሰረት የሂሳብ መዝገብ ከመያዝ ይልቅ  በተለያዩ ምክንያቶች በቁርጥ ግብር ለመስተናገድ ካለው ፍላጎት እንደሆነ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የህዝብ ግንኙነነት ዋና ዳይሪክተር አቶ ሰውነት አየለ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

የሂሳብ መዝገብ እንዲይዙ በህግ የሚገደዱ ግብር ከፋዮች ከመጪው ሀምሌ 1 ቀን  የግብር ማሳወቂያ ወር ጀምሮ ግን የተሟላ የሂሳብ መዝገብ በመያዝ ካልመጡ በስተቀር አይስተናገዱም  ሲል  አቶ ሰውነት   አስታውቀዋል፡፡

የሚዘጋጀው የሂሳብ መዝገብ ደግሞ ሙያዊ አውቀት ባለው ባለሙያ መዘጋጀት አለበት ያሉት ዋና ዳይሪክተሩ ግብር ከፋዮች የሂሳብ መዝገብ ለማዘጋጀት  የሚያስችል ዝግጂት ከወዲሁ ማድረግ እንደሚገባቸው ጠቁመዋል::

@seledadotio
@seledadotio


ሩሲያ ሙሉ የተኩስ አቁም ለማድረግ ከተስማማች ዩክሬን በማንኛውም መልኩ ለውይይት ዝግጁ ነች ሲሉ ዘለንስኪ ለትራምፕ ተናገሩ፡፡

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ሩሲያ ጦርነቱን ለማቆም ያላትን ቁርጠኝነት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም ስምምነት በማድረግ ማሳየት አለባት ብለዋል፡፡

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ፤ሩሲያ ሙሉ እና ቅድመ ሁኔታ የሌለው የተኩስ አቁም ተግባራዊ በማድረግ ፈቃደኛነቷን ካሳየች ኪቭ “በምንም ዓይነት መልኩ” የሰላም ንግግሮችን ለመጀመር መዘጋጀቷን አስታዉቀዋል፡፡

ዘሌንስኪ ከትራምፕ ጋር አደረግኩት ባሉት ውይይት የጦር ሜዳው ሁኔታ መገምገሙን እና የ 30 ቀናት የተኩስ አቁም በአስቸኳይ እንዲጀመር ሀሳብ መቅረቡን አንስተዉ፤ ሩሲያ ይህንን ሀሳብ እንድትደግፍ እየጠበቅን ነው ብለዋል፡፡

ዩክሬን ለዲፕሎማሲያዊ ንግግር ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል፡፡

ዩክሬን በማንኛውም መልኩ ለመነጋገር ዝግጁ መሆኗን አረጋግጣለሁ፤ይህ የሚሆነዉ ግን ሩሲያ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የተኩስ አቁም በመጀመር ጦርነቱን ለማስቆም ያላትን ቁርጠኝነት ካሳየች ብቻ ነዉ ብለዋል ፡፡

የዩክሬኑ መሪ አክለውም ትራምፕ የተኩስ ማቆም ሃሳብን እንደሚደግፉ እና ጦርነቱን እንዲያበቃ ለመርዳት ያላቸውን ፍላጎት አረጋግጠዉልኛል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


ፓኪስታን ሦስት የጦር ሰፈሮቼ ላይ ጥቃት አድርሳለች ስትል ሕንድ ብትከስም ኢዝላማባድ ግን ውንጀላውን ውድቅ አድርጋለች።

ፓኪስታን ሦስት የጦር ሰፈሮቼ ላይ በሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሚሳኤሎች ጥቃት አድርሳለች ስትል ሕንድ ብትከስም ኢዝላማባድ ግን ውንጀላውን ውድቅ አድርጋለች።

የሕንድ ጦር አገሪቱ በምታስተዳደረው የካሽሚር ግዛት በሚገኘው በጃሙ እና በፑንጃብ ግዛት በሚገኘው ፓታንኮት የጦር ሰፈሮቿ ፓኪስታን የሞከረችውን ጥቃት ማክሸፉን ገልጿል።

በሕንድ ቁጥጥር ስር በምትገኘው የካሽሚሯ በጃምሙ ከተማ ሐሙስ አመሻሹ ላይ ፍንዳታዎች መሰማታቸውን እና መብራት መቋረጡ ተዘግቧል።

የፓኪስታን የመከላከያ ሚኒስትር ከጥቃቱ ጀርባ እጃቸው እንደሌለበት ለቢቢሲ ተናግረዋል።

"እስካሁን ጥቃት አልፈጸምንም። ምንም አላደረግንም። ጥቃት አድርሰን ደግሞ አንክድም" ሲሉ ካዋጃ አሲፍ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ቀደም ሲል ሐሙስ ዕለት ሕንድ የፓኪስታንን የአየር መከላከያ መምታቷን እና ኢዝላማባድ ረቡዕ ምሽት ሕንድ ውስጥ የሚገኙ ወታደራዊ ዒላማዎችን ለመምታት ያደረገችውን ሙከራ "ማክሸፏን" አሳውቃለች።

ሕንድ ረቡዕ ዕለት በፓኪስታን እና በፓኪስታን ቁጥጥር ስር በሚገኘው ካሽሚር ውስጥ የሚገኙ ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ ፓኪስታን ድርጊቱን ሌላ "የጥቃት አባባሽ ድርጊት" ስትል ጠርታዋለች።

ሕንድ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የዓለም መሪዎች መረጋጋት እንዲሰፍን ጥሪ አቅርበዋል።

በድንበር አካባቢ የሚፈጸመው ጥቃት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤቶቹን ወደ ከፍተኛ ግጭት ሊያመራቸው ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።

ይህም ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ በሁለቱ አገራት መካከል የከፋው ግጭት ተደርጎ ተወስዷል።

@seledadotio
@seledadotio


❗️ነዳጅ ጭመረ
ከሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ ተለውጧል! ቤንዚን ከ112.67 ወደ 122.53 ብር አድጓል!

@seledadotio
@seledadotio


የኢትዮጵያ ተመራማሪዎች ከአለም በበለጠ የሳይንሳዊ ጽሑፎቻቸው ይሰረዛሉ - አዲስ ጥናት

በቅርቡ ይፋ የሆነ አንድ አዲስ ጥናት በኢትዮጵያ ተመራማሪዎች የተጻፉት ሳይንሳዊ ጽሑፎች ከአለም ውስጥ ካሉ ከማንኛውም ሀገር ተመራማሪዎች በበለጠ መጠን ተሰርዘዋል ወይም ተመልሰው ተወስደዋል ሲል አመልክቷል ።

ይህም በኢትዮጵያዊያን ተመራማሪዎች የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ፅሁፎች ከእውነት የራቁ ወይም ከፍተኛ የጥራት ችግር ያለባቸው በመሆናቸው ከአሳታሚዎች እንዲሰረዙ መደረጉን አመልክቷል።

በህንድ የሚገኝ የውሂብ ሳይንቲስት የሆኑት አቻል አግራዋል ባካሄዱት ይህ ጥናት፣ ኢትዮጵያ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ቀዳሚ ስትሆን ሳውዲ አረቢያ፣ ፓኪስታን፣ ቻይና እና ግብፅ በመቀጠል ከፍተኛውን የፅሁፍ መሰረዝ መጠን ያሳዩ ሀገራት ናቸው።

ተመራማሪው አግራዋል እንዳሉት፣ ይህ ሊሆን የቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ጥራት የሌላቸውን ፅሁፎች በንቃት የሚከታተሉና የሚያጋልጡ ጠንካራ የሳይንስ ባለሙያዎች ማህበረሰብ ባለመኖሩ ሊሆን ይችላል።

በአንጻሩ እንደ ፈረንሳይ ያሉ ሀገራት የምርምርን ታማኝነት በማረጋገጥ ረገድ ግንባር ቀደም ሲሆኑ፣ ጥራት የሌላቸውን ፅሁፎች በመለየትና በማስወገድ ረገድም ውጤታማ ናቸው ብለዋል።

@seledadotio
@seledadotio


900,000 ብር ምን መግዛት ይችላል?


📍በጣም ውስን ሱቆች ግን ብዙ ፈላጊ ስላለ ይፍጠኑ !!

💥ሱቅ ሽያጭ በመሀል ፒያሳ አድዋ ዜሮ ዜሮ !!

🌆ዋና መንገድ አፄ ሚኒሊክ አደባባይ አጠገብ !!

- G+5  የንግድ ሞል
-20 ካሬዎች
-ከጠቅላላ ዋጋ=3.9 ሚሊየን ጀምሮ
 
በ900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ

እንዲሁም

ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
        
👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
          ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
    
  👉2 መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
       
👉3 መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር

        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል!!

🌟በተጨማሪም  በሳር ቤት ፣ ሱማሌ ተራ ፣ በ አያት ፈረስ ቤት ፣ በጋርመንት በተለያዩ የካሬ አማራጮች ከ40% ቅናሽ ጋር አቅርበንሎታል።

ፈጥነው ይደውሉልን።

ስልክ -0943-15-55-42
          09-73-28-74-75


❗️የዲኤችኤል ኢትዮጵያ ሰራተኞች ዛሬ የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸው ተሰማ፡፡

የሰራተኛ ማህበር በማቋቋማችን ከአስተዳደሩ ጋር አለመግባባት ተፈጥሮ ቆይቷል ያሉት ሰራተኞቹ አሁን ያለውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም የሚያስችል የደሞዝ ጭማሪም ተከልክለናል ይላሉ፡፡

ጉዳዩን በመሀል ሲያሸማግል የቆየው የትራንስፖርትና መገናኛ ሰራተኛ ማህበር ፌዴሬሽን ጉዳዩን ለአለም አቀፍ የትራንስፖርት ፌዴሬሽን አሳውቂያለሁ ብሏል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


👀የአንድ ከተማ ነዋሪዎች ያለፍላጎታቸዉ የአደንዛዥ እጽ ወሰዱ

የቱርክ ፖሊስ ከ20 ቶን በላይ የተወረሰ ካናቢስ በማቃጠሉ የተነሳ የአንድ ከተማ ነዋሪዎች ያለፍላጎታቸዉ በአደንዛዥ እጽ መነቃቃታቸዉ ተሰማ

በቱርክ ዲያርባኪር ግዛት ውስጥ በምትገኘው የላይስ ከተማ 25,000 ነዋሪዎች ፖሊሶች 20 ቶን ካናቢስ በከተማው ውስጥ ካቃጠሉ በኋላ ያለፍላጎታቸው በአደንዛዥ እጽ ተነቃቅተዋል፡፡በኤፕሪል 18 የቱርክ ባለስልጣናት ከ 20 ቶን በላይ የተወረሱ ካናቢስ ለማቃጠል ኦፕሬሽን አድርገዋል፡፡ ይህም በሰፈሩ ውስጥ ያለው አየር በአደንዛዥ ጭስ እንዲወጠር አድርጓል ።

ቢያንስ ለአምስት ቀናት ሰዎች እንደ መስከር እና እንደ መፍዘዝ፣ ማቅለሽለሽ እና ቅዠቶች ያሉ ምልክቶችን በመፍራት መስኮቶቻቸውን ክፍት መተው እና ከቤት ለመውጣት አልቻሉም። በ10 ቢሊዮን የቱርክ ሊራ ወይም 261 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገመተው ካናቢስ 20 ቶን 766 ኪሎ 679 ግራም የሚመዝን ሲሆን በ2023 እና 2024 ከመላው የዲያርባኪር ግዛት የተያዘ ነዉ፡፡

የአካባቢው ነዋሪ እንደተናገረዉ የእጹ ሽታ ለቀናት ከተማዋን ተቆጣጥሮ ቆይቷል ብሏል። መስኮቶቻችንን መክፈት አልቻልንም። ልጆቻችን ታመሙ፣ ያለማቋረጥ ወደ ሆስፒታል ሲንሄድ ነበር በማለት አክሏል፡፡የየሲል ኢልዲዝ ማህበር ሊቀመንበር ያህያ ኦገር እንዳሉት ምንም እንኳን በአደገኛ ዕጾች ላይ በተደረገው ውጊያ በባለሥልጣናቱ የተገኘው ስኬት አስፈላጊ ቢሆንም ካናቢሱ የተወገደበት መንገድ ግን ትክክል አይደለም ብለዋል።

@seledadotio
@seledadotio


የማሊ ወታደራዊ መንግስት የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ ገደበ፡፡

ከቀናት በፊት በከተማዋ ከተደረገዉ ሰልፍ በኋላ፤ ወታደራዊው መንግስት ‹‹ወደ ፊት እስከምናሳዉቅ ድረስ›› የፖለቲካ ፓርቲዎች ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ አይችሉም ሲል አግዷል፡፡

በሽግግር መንግስቱ ፕሬዝዳንት አሲሚ ጎይታ የተፈረመዉ የትዕዛዝ ወረቀት ፤ ገደቡ በፖለቲካ ላይ የሚሰሩ የትኛዉንም ተቋማት ይመለከታል ይላል፡፡

ይህ ዉሳኔ ባለስልጣናት የፖለቲካ ፓርቲዎችን አሠራር የሚመራውን ህግ መሰረዙን ካወጁ ከአንድ ሳምንት በኋላ የተወሰደ እርምጃ ነዉ፡፡

የፖለቲካ-ወታደራዊ ሽግግሩ ከታህሳስ 31 በፊት በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ለመጠየቅ እና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱ እንዲመለስ በደርዘን የሚቆጠሩ ፓርቲዎች ጥምረት መቋቋሙ ተገልጿል፡፡

ቅዳሜ እለት አዲሱ ጥምረት በዋና ከተማዋ ባማኮ የወታደራዊውን መንግስት እርምጃ በመቃወም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን አሰባስቧል።

በዚህ ሳምንት መጨረሻም ሌላ ተቃውሞ ተጠብቆ ነበር።

ከተቃውሞ ሰልፍ መሪዎች አንዱ የሆነው ቼክ ኡመር ዱምቢያ በአዋጁ አልተገረምኩም ማለታወቸውን አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


ፕሬዝዳንት ፑቲን ከቻይና ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተነግሯል

የሩሲያ እና የቻይና መንግስታት ሰፊ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በመተግበር ላይ ይገኛሉ - ብለዋል ቭላድሚር ፑቲን፡፡

ፑቲን ሺ ጂንፒንግ በ80ኛው የድል በዓል ከሩሲያ ጋር ለመሆን በመወሰናቸው አመስግነው፤ በድጋሚ በቻይና ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

ሩሲያ ለሺ ጂንፒንግ የሞስኮ ጉብኝት ትልቅ ቦታ አለው ብለዋል፡፡ሩሲያ እና ቻይና ግንኙነታቸውን የሚያጠናክሩት ለሕዝቦቻቸው ጥቅም እንጂ ከሌሎች ሀገራት በተቃራኒ ለመቆም አይደለም ሲሉም ተድምጠዋል። ሺ ሞስኮ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጉላቸዋል፡፡

የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ በበኩላቸው 80ኛውን የድል በዓል ምክንያት በማድረግ በበዓሉ ላይ በመገኘታቸው በጣም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ቻይና እና ሩሲያ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ታሪክ እውነታን ለማስጠበቅ ዝግጁ ናቸው ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አፅንዖት ሰጥተዋል።

የሩሲያ እና የቻይና ሐሰዝቦች ከ80 ዓመታት በፊት ታላቁን ድል ለመቀዳጀት ከባድ ዋጋ በመክፈል በዓለም ሰላም እንዲሰፍን እና ለሰው ልጅ እድገት ትልቅ ታሪካዊ አስተዋፅኦ አድርገዋል ሲል ስፑትኒክ ዘግቧል ።

@seledadotio
@seledadotio


❗️ትራምፕ በፍቃደኝነት አሜሪካን ለቀው ለሚወጡ ህገ-ወጥ ስደተኞች የ1ሺ ዶላር ማበረታቻ አቀረቡ

የአሜሪካ መንግስት በህገ ወጥ መንገድ በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙ ስደተኞች አሜሪካን ለቀው ለመውጣት ከወሰኑ 1,000 የአሜሪካ ዶላር እንደሚሰጥ እና የጉዞ ክፍያቸውን እንደሚሸፍን አስታውቋል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስለ ጉዳዩ ለጋዜጠኞች ሲያብራሩ ህገወጥ ስደተኞች የቀረበላቸውን አማራጭ የሚቀበሉ ከሆነ አንድ ቀን ወደ አሜሪካ የሚመለሱበት ህጋዊ መንገድ ሊሰጣቸው እንደሚችል ተናግረዋል።

@seledadotio
@seledadotio

እንዲሁም የአሜሪካ የሀገር ውስጥ ደህንነት ዲፓርትመንት (ዲ.ኤች.ኤስ) ፀሃፊ ክሪስቲ ኖም፤ ከአሜሪካ በራስ ፈቃድ መውጣት ከእስር ለመዳን፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ወጪ ቆጣቢው መንገድ ነው ብለዋል።

የሀገር ውስጥ ደህንነት ዲፓርትመንት አክሎም፤ እቅዱ የገንዘብ ወጪን እንደሚቀንስ እና እስካሁን ስደተኞችን ለመያዝ፣ ለማሰር እና ከሀገር ለማስወጣት በአማካይ ከ17,000 ዶላር በላይ ወጪ እንደተደረገ አስታውቋል።

ዲፓርትመንቱ አክሎም የመጀመሪያው ሕገወጥ ስደተኛ ከቺካጎ ወደ ሆንዱራስ ለመብረር አማራጩን እንደተቀበለ መግለፁን ቢቢሲ ዘግቧል።


ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካኝ በ132 ብር ተሸጠ

በጨረታው ለተሳኩ ሁሉም የዋጋ ጥያቄዎች የተመዘነ አማካይ ዋጋ በአንድ የአሜሪካ ዶላር 132.9643 ብር ደርሷል። በአጠቃላይ 16 ባንኮች በጨረታው የጠየቁትን የውጭ ምንዛሬ ድልድል ማግኘት ችለዋል።

ባንኩ ከ15 ቀናት በፊት ባካሄደው ተመሳሳይ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካኝ በ131.70 ብር መሸጡ ይታወሳል።

ብሔራዊ ባንክ በየ15 ቀናት የውጭ ምንዛሬ በጨረታ መሸጡን እንደሚቀጥል የገለጸ ሲሆን፣ ለዛሬው ጨረታ 50 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለባንኮች እንዲገዙ ቀርቦ ነበር። ቀጣዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከሁለት ሳምንታት በኋላ የሚካሄድ ሲሆን ዝርዝር መረጃዎች ከጨረታው ቀን በፊት ይፋ ይደረጋሉ።


@seledadotio
@seledadotio


የአሜሪካ እና ቻይና ባለስልጣናት የንግድ ጦርነት ለማርገብ በዚህ ሳምንት ንግግር ይጀምራሉ ተባለ

የአሜሪካ እና ቻይና ባለስልጣናት በሁለቱ የዓለም ግዙፍ ምጣኔ ሀብት ባለቤቶች መካከል የተከሰተውን የንግድ ጦርነት ለማርገብ በዚህ ሳምንት ንግግር እንደሚጀምሩ ተገለፀ።

የቻይና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሂ ሊፊንግ የፊታችን አርብ በሲውዘርላንድ ይጀመራል ተብሎ በሚጠበቀው ንግግር እንደሚሳተፉ የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የአሜሪካ ግምጃ ቤት ፀሐፊ ስካት ቤሰንት እና የዩናይትድ ስቴት የንግድ ወኪል ጀሜሰን ጊሪር ዋሽንግተንን ወክለው በንግግሩ እንደሚሳተፉ በቢሮዎቻቸው በኩል ገልፀዋል።

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ ዋይት ሐውስ ዳግም ከተመለሱ በኋላ ከቻይና በሚገቡ ምርቶች ላይ እስከ 145 በመቶ ታሪፍ ጥለዋል።

ቤጂንግ ለዚህ እርምጃ አጸፋ የሰጠች ሲሆን በአንዳንድ የአሜሪካ ምርቶች ላይ እስከ 125 በመቶ ቀረጥ መጣሏን አስታውቃለች።

የዓለም አቀፍ የንግድ ባለሙያዎች የአገራቱ ንግግር በርካታ ወራት እንደሚፈጅ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ንግግሩ የቻይና ምክትል ፕሬዝዳንት ሃን ዜንግ የዶናልድ ትራምፕን በዓለ ሲመት ከታደሙ በኋላ በከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ የሚደረግ የመጀመሪያው ግንኙነት ነው።

@seledadotio
@seledadotio


የፓኪስታን የመከላከያ ሚኒስትር ካዋጃ አሲፍ፡ "ህንድ ወደ ኋላ ከተመለሰች በእርግጠኝነት ይህንን ውጥረት መቀነስ እንችላለን ብለዋል"

@seledadotio
@seledadotio


☄️ ሰበር
ፓኪስታን አምስት የህንድ ተዋጊ ጄቶች እና አንድ ሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) መምታቷን ገለጸች።

የፓኪስታን ወታደራዊ ቃል አቀባይ ሌተናል ጄኔራል አህመድ ሸሪፍ ቻውድሃሪ ለሮይተርስ እንደገለጹት፣ እስካሁን ድረስ አምስት የህንድ ጄቶች ማለትም፡
👉🏻ሶስት ራፋሌ (Rafale)፣
👉🏻 አንድ SU-30 እና
👉🏻 አንድ ሚግ-29 - እና አንድ ሄሮን ሰው አልባ አውሮፕላኖች መመታታቸውን አረጋግጠዋል።

ህንድ፣ ፓኪስታን መታኋቸው ስላለቻቸው የጦር አውሮፕላኖች ጉዳይ እስካሁን ምላሽ አልሰጠችም።

@seledadotio
@seledadotio


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ህንድ 🇮🇳 በፓኪስታን የተለያዩ ከተሞች ላይ በርካታ የሚሳኤል ድብደባ አደረሰች

@seledadotio
@seledadotio


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ዓመታዊ የ'ጥቁር ፊት' ፌስቲቫል በቻይና

ከ 1,000 ለሚበልጡ ዓመታት በቻይና የሚከበረው የጥቁር ፊት ቀን ተሳታፊዎች እራሳቸውን እና በአቅራቢያ ያለ ማንኛውንም ሰው ጥቁር ቀለም በመቀባት ያሳልፋሉ - ሃብት እና መንፈሳዊ ጥበቃን ያመጣል በሚል እስከ አሁን መከበሩን ቀጥሏል ።

@seledadotio
@seledadotio

20 last posts shown.