Sheger Press️️


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


Official channel of sheger press
If you want to give a suggestion or comment, contact us 👉 @birukepromo

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


የ17 አመቷን የግል ተበዳይ የግብረ-ስጋ ግንኙነት በመፈጸም አንገቷን አንቆ የገደለው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ

ከእኔ ጋር በፍቅር ጓደኝነት ለመቀጠል ፈቃደኛ አልሆነችም በሚል የ17 አመቷን የግል ተበዳይ አስገድዶ የግብረ-ስጋ ግንኙነት በመፈጸም ሕይወቷ እንዲያልፍ ያደረገ ግለሰብ በጽኑ እስራት ተቀጣ።

አብዱ ኪያር ዩሱፍ የተባለው ተከሳሽ በጳጉሜን 01 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 6፡30 ሰዓት በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ሰፈራ ቀርሳ ቢላ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የግት ተነዳይን አንገቷን አንቆ በመያዝ በአካባቢው ወደሚገኝ ካባ በሚወስዳት ጊዜ ላለመሄድ ስትታገለው ነበር።

ግለሰቡ የግል ተበዳይ ጩኸት ስታሰማ በድጋሚ በልብስ ማሰሪያው ጨርቅ አንገቷን አጥብቆ በመያዝና እራስዋን እንዳትከላከል በማድረግ የግብረ-ስጋ ግንኙነት የፈጸመባት እና አንገቷን በእጅ እና በልብስ የወገብ ማሰሪያ ጨርቅ በማነቅ ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርጓል።

በዚህም ግለሱቡ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶበት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 11ኛ ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቶ በክርክሩ ሂደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ የመከላከያ ማስረጃ እንደሌለው በመግለጹ ፍርድ ቤቱ ለሰራው ወንጀል በ25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡

@sheger_press
@sheger_press


ብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ አቋቁሞ በሚቃወሙት እና በሚተቹት ላይ ስም ማጥፋት ዘመቻ እንደሚያካሂድ ተገለጸ‼️

በገዢው ብልፅግና ፓርቲ ‘የሚዲያ ሠራዊት’ የሚል መጠሪያ ያላቸው የፓርቲው አባላት፤ መንግሥትን በሚተቹ እና በሚቃወሙ ግለሰቦች ላይ በፌስቡክ በተደረጉ የሐሰተኛ መረጃ እንዲሁም ‘የጥላቻ ንግግር’ ተብለው ሊቆጠሩ የሚችሉ ጽሑፎች እና ምስሎች ሥርጭት ላይ እንደተሳተፉ ቢቢሲ ባደረገው ምርመራ ማረጋገጡን አስታወቀ።

#የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ አቡነ ጴጥሮስ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ መጓዛቸውን ተከትሎ በወቅቱ የተሰራጩ መረጃዎችን ቢቢሲ በማሳያነት አቅርቧል።

በቤተክርስቲያኗ እና በገዢው ፓርቲ መካከል የተፈጠረውን ቅራኔ ተከትሎ “ሰበር መረጃ፤ አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮበለሉ”፣ “አሜሪካዊው አቡነ ጴጥሮስ ከሀገር ኮብልለዋል!” እና “ከአሜሪካዊ አቡነ ጴጥሮስ ኩብለላ ጀርባ ያሉ እውነታዎች!” የሚል መግቢያ ያላቸው መረጃዎች በወቅቱ ተሰራጭተው እንደነበር አውስቷል።

“ለምንድነው ላይክ፣ ሼር የማታደርጉት?” የሚል ጥያቄ ለተሳታፊዎቹ እንደሚያቀርብ፤ የሚዲያ ሠራዊት አባላት ላክይ፣ ኮሜንት እና ሼር ማድረጋቸውን የሚያሳይ “ስክሪን ሻት” እንዲልኩ እንደሚጠየቁ ቢቢሲ በግሩፑ የተደረጉ የመልዕክት ልውውጦችን ዋቢ በማድረግ አስታውቋል።

መንግስትን የሚቃወሙ ጽሁፎችን ባጋሩ የፌስቡክ ገጾች ላይ ‘የሚዲያ ሠራዊቱ’ አባላት ተዘጋጅቶ የተሰጣቸውን ጽሁፎች ኮሜንት እንደሚያደርጉ አረጋግጫለሁ ብሏል።

@sheger_press
@sheger_press


በጃኔቫ ፤ በመንግስት ላይ የተቃዉሞ ድምጽ ያሰሙ ሰዎችን የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤት አወገዘ

በጃኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤት፣ ማክሰኞ'ለት ለኢትዮጵያዊያን ተረጂዎች ገንዘብ ለማሰባሰብ ጄኔቫ ውስጥ በተካሄደው ዓለማቀፍ መርሃ ግብር ላይ የተወሰኑ ኢትዮጵያዊያን ተቃውሞና ጩኸት ማሰማታቸውን አውግዟል።

አራቱ ትዉልደ ኢትዮጵያዊያን ሰዎች በጉባኤው ተገኝተዉ በኢትዮጵያ እየደረሱ ናቸዉ ያሏቸዉን ጉዳዮች በመጥቀስ በጭኸት ስብሰባውን አዉከዉ እንደነበር ሸገር መዘገቡ አይዘነጋም።

ፖሊስ ጩኸት ያሰሙትን ኢትዮጵያዊያን ይዞ ከአካባቢው እንዳራቃቸው ጽሕፈት ቤቱ ገልጧል። ጽሕፈት ቤቱ፣ ለድርቅ ተጎጂዎች ዓለማቀፉ ኅብረተሰብ እርዳታ በሚያሰባስብበት መድረክ ላይ ጩኸት ማሰማት፣ የአገር ጠላትነት ፖለቲካ እንጂ የተቃውሞ ፖለቲካ አይደለም በማለት ተችቷል።

የኢትዮጵያዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ፣ ባልተገባ ቦታ ጩኸት በማሰማት "አገር አዋራጅ" የኾነ ድርጊት የሚፈጽሙ ግለሰቦችን ሊቃወማቸው እንደሚገባም ጽሕፈት ቤቱ አሳስቧል።

ቋሚ መልዕክተኛ ጽሕፈት ቤቱ፣ በአገር ክብር ላይ እጃቸውን የሚዘረጉ ግለሰቦችን በሕግ አግባባብ የምጠይቅበትን አሠራር እከተላለሁ በማለትም አስጠንቅቋል።

Via ዋዜማ

@sheger_press
@sheger_press

6.8k 0 1 11 103

በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ በደረሰው የመኪና አደጋ የ6 ወጣቶች ህይወት አለፈ ።

አደጋ የደረሰው በእዣ ወረዳ ወርት ቀበሌ እንጨት ጭኖ ወደ ከተማ በመጓዝ ላይ የነበረው ሲኖ የጭነት ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ ከራሱ ጋር በሲኖው ላይ በስራ ላይ የነበሩ የ6ወጣቶች ህይወት ሲያልፍ በ10 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት መድረሱን ከወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ መረዳት ችለናል ።

ጉዳት የደረሰባቸውም ሰዎች በሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸውም ይገኛል።

የእዣ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤ

@sheger_press
@sheger_press


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
Who's here? 
We've asked for a free link to a paid channel, for our subs.
x2-x3 Signals here

👉 CLICK HERE TO JOIN 👈
👉 CLICK HERE TO JOIN 👈
👉 CLICK HERE TO JOIN 👈

❗️JOIN FAST! FIRST 1000 SUBS WILL BE ACCEPTED


ሊቅ አዕላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን መጠኑ ከፍተኛ የኾነ ገንዘብ ወደ ግል ሒሳባቸው ሊያስገቡ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ ተባለ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ የኾኑት ሊቅ አዕላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን በጸጥታ አካላት ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዋዜማ ከታማኝ ምንጮች ሰምታለች።

ምክትል ሥራ አስኪያጁ ትላንት ማክሰኞ ሚያዚያ 9 ቀን በጸጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ አፍሪካ ኅብረት ዋና መስሪያ ቤት አካባቢ በሚገኝ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ መጠኑ ከፍተኛ የኾነ ገንዘብ ወደ ግል ሒሳባቸው ሊያስገቡ ሲሉ መሆኑን ምንጮች ለዋዜማ መናገራቸውን ሸገር ፕረስ ከዋዜማ ከዘገባ ተመልክቷል።

ሊቀ አዕላፍ በላይ በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ልደታ ወደሚገኘው አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዳቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ተረድታለች።

ሊቀ አዕላፍ በላይ ከዓመታት በፊት ከቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ልዩነት ከፈጠሩ በኋላ፣ በእርቅ ወደ ቤተክህነት ተመልሰው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ኾነው እንደተሾሙ ይታወሳል።

Via ዋዜማ

@sheger_press
@sheger_press

9.3k 0 11 18 83

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል-የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት

ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል፡፡

ጀንበር ጠልቃ በወጣች ቁጥር ከጦርነት ውጭ ማሰብ የማይችለው የህወሓት ቡድን ከዉጭ እና ከዉስጥ ጠላቶቻችን ጋር ተናብቦና ተቀናጅቶ በርካሽ ፖለቲካዊ ብያኔና ፍረጃ በጊዜያዊ አሥተዳደሩ ካቢኔ አማካኝነት መጋቢት 16/2016 ዓ.ም የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት ማወጁና መቀስቀሱ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ ይህን የመላ ኢትዮጵያ ጠላትና የደኅንነት ስጋት የሆነውን የህወሓት ቡድን ባለፉት ሦስት ዙሮች ከተደረገው ደም አፋሳሽ ጦርነት ትምህርት ሊወስድ ይችል ይሆናል በሚል ጭላንጭል ተስፋ  የፌዴራል መንግሥት እጅግ እልህ አስጨራሽ ትዕግስት ተላብሶ ውይይቶች እንዲካሄዱ ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደረግ ቆይቷል፡፡

የአማራ ክልል መንግሥትም በተደጋጋሚ ከትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር ጋር በፌዴራል መንግሥት አማካኝነት ውይይት ለማድረግ በርካታ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም ህወሓት ይህን የሰላም አማራጭ ወደ ጎን በመተው የማንነት ጥያቄ ያለባቸውን የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ አካባቢዎች ላይ ወረራ ፈፅሟል፡፡

ህወሓት ወረራ የፈፀመባቸው የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት አካባቢዎች የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመፅደቁ በፊት በነበሩ አሥተዳደራዊ መዋቅርና አደረጃጀት በኀይል ጠቅልሎ ከመውሰድ ጀምሮ የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከመፈጸም ድረስ አሰቃቂ ጥፋት የፈጸመባቸው አካባቢዎች  ናቸው፡፡ እነዚህ አካባቢዎች ስቃይ በተሞላበት ችግር ውስጥም ኾነው በወቅቱ ለነበረው መንግሥት የማንነትና ራስን በራስ የማሥተዳደር ጥያቄዎችን በማንሳት፣ መብቶቻቸው እንዲከበሩላቸው ሲጠይቁ የነበሩ መኾኑ በበርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች የተረጋገጥ ጉዳይ ነው፡፡

ተቸንካሪነት ዋና መለያ የኾነው የህወሓት የጥፋት ቡድን ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የፈጸመውን አሰቃቂና ታሪክ ምንጊዜም የማይዘነጋው የባንዳነት ተግባር ተከትሎ በተቀሰቀሰው ጦርነት በመላ ኢትዮጵያዊያን እና በጀግኖች የፀጥታ ኀይሎች አማካኝነት የሽንፈት ፅዋን ከመጎንጨቱ ባሻገር የማንነትና የራስ አሥተዳደር ጥያቄ ያለባቸውን አካባቢዎች በጉልበት ተገፎባቸው የነበረውን ራሳቸውን የማሥተዳደር ነጻነት መቀዳጀት ችለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ይህ ኹኔታ ያልተመቸው ተቸንካሪው የህወሓት ቡድን በሦስት ዙሮች ከተደረገው ጦርነት ማግሥት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በማክበር በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የድርሻውን ከመወጣት ይልቅ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የተለያዩ ጥፋቶችን ሲፈጽም ቆይቷል፡፡አሁንም እየፈጸመ ይገኛል፡፡

ስለሆነም የአማራ ክልል መንግሥት ይህን መሰሉን የህወሓትና የግብረ አበሮቹን ፖለቲካዊ ግልሙትና እና ደም አፋሳሽ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀብና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በማክበር በአጭር ጊዜ በወረራ የያዛቸውን አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ እየጠየቅን ይህ የማይኾን ከኾነ የአማራ ክልል መንግሥትና ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ በመኾን ሀገርን ከማፍረስ መታደግና ሕዝባችንንም ከጥቃት ለመከላከል የምንገደድ መኾኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

የተከበራችሁ በክልላችን በየደረጃው ያላችሁ የፖለቲካና የጸጥታ መዋቅር አባላት፡- ከሰሜን ዕዝ ጥቃት በኋላ ትህነግ በቀሰቀሰው ጦርነት ሕዝባችን ቀጥተኛ ተጠቂ በመኾኑ ምክንያት ለበርካታ ችግሮች ተዳርጎ የነበረ መኾኑ ይታወቃል፡፡ ኾኖም ግን በየደረጃው የሚገኙ የመዋቅር አባላት ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ ጥምር የጸጥታ ኃይሎችና ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በመኾን ሀገር አፍራሽ የጥፋት ኀይሉ ላይ የተቀዳጀው ድል ታሪክ አይዘነጋውም፡፡ ዛሬም እንደ ትናንቱ በፅናትና በቁርጠኝነት ሕዝቡን በማደራጀት አካባቢያችሁን በመጠበቅ ታሪካዊ ኀላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

የተከበርከው የክልላችን ሕዝብ፡- በተደጋጋሚ ጥቃት የፈጸመብህ የጥፋት ኀይል ዛሬም እንደ ትናንቱ ወረራ ፈጽሟል፡፡ በመኾኑም መላ የክልላችን ሕዝብ ከሐሰት ፕሮፓጋንዳ እና ሠርጎ ገቦች ራስህን በመጠበቅ ከክልል መንግሥትና በየአካባቢው ከሚገኙ አሥተዳደሮች ጋር የጠበቀ ቁርኝት በመፍጠር ጠላቶቻችን የከፈቱብንን ጥቃት ለመመከት  በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከመንግሥት ጎን በመሰለፍ የድርሻህን እንድትወጣ የከበረ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ለኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት፡- የፌደራል መንግሥት ህወሓት የቀሰቀሰው ደም አፋሳሽ ጦርነት በሰላም እንዲቋጭ ማድረጉን ሳናደንቅ አናልፍም፡፡ ከፕሪቶሪያው ስምምነት በኋላም ጥያቄዎች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ የተደረገውን ጥረት በሙሉ ልብ በመደገፍ ለውጤታማነቱ የድርሻችንን ስንወጣ ቆይተናል፡፡ ኾኖም ግን ህወሓት በተደጋጋሚ የተሰጠውን ዕድል ባለመጠቀም የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሲያፈርስ ቆይቷል፡፡ አሁንም በሙሉ አቅሙ ወደ ጦርነት ገብቷል፡፡ ይህን እኩይ ድርጊቱን የአፍሪካ ኅብረትና የዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በቦታው ተገኝተው አረጋግጠዋል፡፡በመኾኑም ይህን እብሪተኛ ቡድን በአጭር ጊዜ ከወረራቸው አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ በማድረግ ሕዝባችንን ከጥፋት መታደግና የሀገራችንን ሉዓላዊነት ማስከበር ይገባል፡፡

ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ
ህወሓት ከምስረታዉ ጀምሮ ለአማራ ሕዝብ ባለው ሥር የሰደደ ጥላቻ  ምክንያት በአማራ ሕዝብና በመላ ሀገሪቱ ሕዝብ ላይ የማያባራ ደም አፋሳሽ ጦርነትን ሲቀሰቅስ ኖሯል፡፡ ለዚህም ነው ህወሓት የኢትዮጵያም ኾነ የአፍሪካ ቀንድ አለመረጋጋት ምንጭ ነው የምንለው፡፡

ኾኖም በአሳሳች የፕሮፖጋንዳ ሥራዎቹ ምክንያት የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በተደጋጋሚ በህወሓት ጉዳይ ላይ የተሳሳተ አቋም ሲይዝ ተስተውሏል፡፡ ዛሬ ግን ለዚህ አሳሳች ፕሮፖጋንዳው ያልተመቼ ኹኔታ ተፈጥሯል፡፡ በጠራራ ጸሐይ የአፍሪካ ሕብረትና ዓለም አቀፍ ታዛቢዎች በተገኙበት ወቅት ወረራ መፈጸሙ በገሃድ ታይቷል፡፡

በመሆኑም ከዚህ ቀደም እንዳደረገው በአሁኑ ወቅት የዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ማወናበድ አይችልም፡፡ የአማራ ክልል መንግሥትና ሕዝብ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ህወሓት የፈጸመብንን ወረራ በጥብቅ እንዲያወግዝና ከጎናችን እንዲቆም የከበረ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
ሚያዚያ 08 /2016 ዓም
ባሕር ዳር

@sheger_press


ጌታቸው ረዳ‼️

የሕወሃት ኃይሎች በራያ አላማጣ አንዳንድ ቦታዎችን መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ፤ የፕሪቶሪያዉ ስምምነት ጠላቶች ያደረጉት እንጂ በሕወሃት አልያም ጊዜያዊ መስተዳድሩ የተፈጸመ አለመሆኑን አቶ ጌታቸዉ ረዳ ተናገሩ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ፣ በደቡብ ትግራይና በሌሎች በኃይል የተያዙ የትግራይ ግዛቶች ባኹኑ ወቅት የተፈጠረው ክስተት በፌደራል መንግሥቱ እና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወይም በሕወሃት ወይንም በትግራይ እና በአማራ ክልሎች መካከል የተፈጠረ ግጭት አይደለም ሲሉ ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ በኤክስ ትስስር ገጻቸው ላይ መለጠፋቸውን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።

ጌታቸው፣ ክስተቱ ኹለቱ ወገኖች የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እያደረጉት ያለውን አወንታዊ ግንኙነት ለማደናቀፍ የፈለጉ የስምምነቱ ጠላት የኾኑ ኃይሎች የፈጠሩት ነው በማለት ከሰዋል።

ከሩቅም ከቅርብም የግጭት ማቆም ስምምነቱ ጸር የኾኑ ኃይሎች ጦር እየሰበቁ መኾኑን የጠቀሱት ጌታቸው፣ ብቸኛው አዋጭ መንገድ ግን ሰላም ነው ብለዋል።

ኹለቱ ወገኖች ችግሮችን ለመፍታትና የሚስማሙባቸውን ጉዳዮች ለማጎልበት አዲስ አበባ ውስጥ ስብሰባ ላይ እንደኾኑም ጌታቸው ጠቁመዋል።

ሕወሃት ጥቃት ከፍቶ ተቆጣጥሯቸዋል የተባሉት አካባቢዎችን በተመለከተም አብን ማምሻውን ጠንከር ያለ መግለጫ አሰራጭቷል።

አብን የሕወሃት ኃይሎች በድጋሚ በአማራ ሕዝብ ላይ "አራተኛ ዙር" ጥቃት ከፍተዋል ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። የፌዴራሉ መንግሥትና የአማራ ክልላዊ መንግሥት ሕወሃት በአማራ ሕዝብ ላይ የከፈተውን ሌላ ዙር ጥቃት ባስቸኳይ እንዲያስቆሙ የጠየቀው አብን፣ የአማራ ሕዝብ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የሕወሃትን ጥቃት እንዲመክትም ጥሪ አድርጓል።

አብን፣ መንግሥት የሕወሃትን ጥቃት በዝምታ ከተመለከተ፣ ድርጊቱ "የኹሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ" እንዲኾን ፈቅዷል ማለት ነው ብሏል።

አብን ይህን መግለጫ ያወጣው፣ የሕወሃት ኃይሎች በራያ አላማጣ አካባቢ አንዳንድ ቦታዎችን እየተቆጣጠሩ ስለመኾኑ በተሰማ ማግስት ነው።

@sheger_press
@sheger_press


ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን የተሰጠ መግለጫ
***
ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ የማይማረው ህወሐት ለአራተኛ ዙር በህዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል። የፌዴራልና የአማራ ክልል ክልሉ መንግስታትም በህዝብ ላይ የተቃጣውን የጥፋት ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

የኢትዮጵያ ህዝብ ዘላለማዊ ጠላት የሆነው ወያኔ ህወሐት በህዝብ ትግል ተገፍትሮ ወደ ትግራይ ከተሰበሰበ በኋላ በተደጋጋሚ ወረራ በመፈፀም በህዝባችን ላይ ለጆሮ የሚከብድ ዘግናኝ ግፍ ፈፅሟል። ምንም እንኳን ህወሐት በተደጋጋሚ ጊዜ በቆሰቆሰው ጦርነት የአማራ እና የአፋር ህዝብ በቀጥታ የገፈቱ ቀማሽ ይሁኑ እንጅ ዋና ዓላማው ኢትዮጵያ ሐገራችንን መበታተን እና የፈራረሰች ሐገር መፍጠር መሆኑን በአፈ ቀላጤው በኩል በተደጋጋሚ ተናግሯል።

ይህ የእናት ጡት ነካሽ ቡድን የሐገራችን ደጀን የሆነውን የሰሜን እዝ የመከለከያ ሰራዊት በማጥቃቱ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያጋጠመውን ቁጣ መቋቋም ተስኖት ለሶስተኛ ጊዜ እየተመላለሰ ያደረገው የሐገር ማፍረስ ሙከራ ባይሳካለትም እንኳን አድፍጦ ለጦርነት ከመዘጋጀት ግን ቦዝኖ አያውቅም።

ህወሐት ከጦርነት ውጭ መኖር የማይችል፣ በጦርነት አድጎ በጦርነት ያረጀ ቡድን በመሆኑ በመላው የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ አማፂያንን ከማስታጠቅ አልፎ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በመወገን ሐገራችንን የጦር ቀጠና ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ነበር የከረመው። በቀጥታ ከሚደግፋቸው የጥፋት ኃይሎች በተጨማሪ የራሱን ኃይል በማደራጀት የሰርጎ ገብ ኃይል እየላከ ህዝባችንን ሲረብሽ መክረሙ ሳያንሰው በአሁኑ ሰዓት በራያ በኩል ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ከፍቶ ይገኛል።

ኋላ ቀርነት እና ግትርናት ዋና መገለጫው የሆነው የጥፋት ቡድን የሚሊዮኖችን ህይዎት በቀጠፈውና ከተደጋጋሚ ስህተቱ ባለመማር ዛሬም ለሌላ ዙር እልቂት ተዘጋጅቶ በህዝባችን ላይ ጦርነት ከፍቷል።

በህዝቦች እኩልነት እና በብሔረሰቦች መብት ፈፅሞ የማያምነው ህወሐት እኔ የማልገዛት ኢትዮጵያ ተረጋግታ መኖር የለባትም የሚል ያልተገራ ክፉ አመሉን በተደጋጋሚ አሳይቷል። በዚህም እንደ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እኩልነትን ፈፅሞ እንደማይሻ አረጋግጧል።

ለህዝባችን የሚከተሉትን መልዕክቶች እናስተላልፋለን

1. ምንም እንኳን አሸባሪው እና ተስፋፊው ወያኔ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጠላት ቢሆንም ፣ በተለይ የአማራ ህዝብ የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ ጦርነቱን የመመከት ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኘው ሕዝባችን ካለፈው የጥፋት ግዜ በመማር ከታሪካዊ ጠላቱ የሚሰነዘርበትን ወረራ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት እንዲመክት፣

2. ህዝባችን ከወያኔ ትጥቅ አስፈች ፕሮፖጋንዳ ራሱን እንዲጠብቅ እና ከዚህ ታሪካዊ ጠላት የሚመጣን ማንኛውንም ውዥንብር ጆሮ እንዳይሰጥ፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የወገን ኃይሎች ለወያኔ የሚያሳዩትን የተለሳለሰ የባንዳነት መንገድ ህዝባችን ፈፅሞ እንዳያዳምጥ እና እንዲህ ያሉትን ቡድኖች አጥብቆ እንዲታገል፣

3. የአማራ እና የአፋር ህዝብ የጦርነቱ ዋና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኃይሎች የሚፈልጉትን ሁሉ በማቅረብ ከሐገሩ ጎን እንዲቆም

4. ህዝባችን ይህን ታሪካዊ ጠላት በመቅጣት የተለመደ ጀግንነቱን እንዲወጣ ስንል ጥሪ እያቀረብን፤ በተለይ መንግስት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በዝምታ የሚመለከት ከሆነ፤ ህዝባችን ስርአትን አምኖ ችግሮች ሁሉ በህግ አግባብ ይፈታሉ የሚል ቀናኢነቱ ማታለያ ሆኖ ከዋለ፤ ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ እንዲሆን መንግስት የፈቀደ መሆኑን ታሪክ የሚመዘግበው ሀቅ ይሆናል።

5. በህወሐት ችግር የአማራና የትግራይ ህዝቦች እንዲሁም መላ ሀገሪቱና ቀጠናው ችግር ውስጥ እየወደቀ በመሆኑ ይህ በአስቸኳይ እንዲቆም እያሳሰብን በተለይ የፌዴራሉ መንግስትና የአማራ ክልል መንግስት በህዝባችን ላይ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

ሚያዝያ 07/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ

@sheger_press
@sheger_press


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ጳጳሱ በጩቤ ተወጉ🥹

ታዋቂው  የኤሲሪያን  (አሶራውያን) ኦርቶዶክስ ቄስ ብጹዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል (ቢሾፕ ማር ማሪ) ሲድኒ ውስጥ በዘውትራዊውና የተመለደው ቀጥታ የሚሰራጭ  የስብከት መርሃ ግብራቸው ላይ ሳሉ ማንም ባልገመተው ሁኔታ አንድ ሰው በፍጥነት ተጠግቶ በጩቤ ፊትና አንገታቸው ላይ ወግቷቸዋል።

የጉባኤው አባላት ጳጳሱን ለመርዳት ሲጮሁ እና ሲጣደፉ ይሰማሉ። አንድ ሰው በቁጥጥር ስር መዋሉን የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስ አስታወቀ።

በጥቃቱ አራት ሰዎች ቆስለዋል ሲል ኒው ሳውዝ ዌልስ አምቡላንስ ተናግሯል።

ዜናውን በርካታ አለምአቀፍ የመገናኛ አውታሮች ዘግበውታል።

@sheger_press
@sheger_press


በኢትዮጵያ 56 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ምንም አይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ አንድ ጥናት አመላከተ፡፡

የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ አደረጉት ባለዉ ዓመታዊ ጥናቱ ላይ እንደገለፀው በኢትዮጵያ 56 በመቶ የሚሆኑ የ 2ኛ እና የ 3ኛ ክፍል ተማሪዎች ምንም አይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ አረጋግጫለሁ ብሏል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሲያከናዉን የቆየዉን ጥናት ይፋ አድርጓል ። በዚህም ከትግራይ ክልል በስተቀር በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ 401 ትምህርት ቤቶች እና በ 16 ሺህ ተማሪዎች ላይ በተደረገ ጥናት ዉጤቱ መገኘቱን አስታዉቀዋል።

ይህ ቁጥር ከባለፉት አመታት ጋር ሲነፃፀር በመጠኑ መሻሻል አሳይታል የተባለ ሲሆን ከሁለት አመት በፊት የተደረገው ጥናት ምንም ማንበብ የማይችሉት 63 በመቶዎች እንደነበሩ ጥናቱ አመላክቷል።

@sheger_press
@sheger_press


ከደቡብ ሱዳን ተሻግረዉ ወደ ጋምቤላ ክልል የመጡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ የሙርሌ ታጣቂዎችን ወደመጡበት መመለስ ቢቻልም አሁንም በአንዳንድ አካባቢዎች ይገኛሉ ተባለ

ከደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰዉ በመግባት በተከታታይ ጥቃት ሲፈጽሙ የነበሩት የሙርሌ ታጣቂዎች ከሰሞኑ በጋምቤላ ክልል ዲማ ወረዳ ጥቃት ፈጽመዉ እንደነበር ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

ታጣቂዎቹ መጋቢት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ጥቃቱን ፈጽመዋል የተባለ ሲሆን አሁንም በወረዳዉ ሁለት ቀበሌያት ላይ እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ ስማቸዉን የማንጠቅሳቸዉ የወረዳዉ አንድ ባለስልጣን ለጣቢያችን ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹ በአኩላ እና አቻኛ ቀበሌዎች እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ የተባለ ሲሆን በተለይም አኩላ በተሰኘዉ ቀበሌ በጸጥታ ሀይሎች ቅኝት እና ክትትል እየተረገ ነዉ ብለዉናል። አንዳንዶቹም በዚህ ክትትል ከመሸጉበት በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ተነግሯል። ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ታጣቂዎች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰዉ መግባታቸው ከተሰማ በኋላ እንዲመለሱ ቢደረግም አሁንም በሁለቱ ቀበሌያት እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።

ከደቡብ ሱዳን የሚሻገሩ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጵያ ድንበር ዘልቀዉ በመግባት በተለይም የዲማ ወረዳን ከደቡብ ሱዳን ጋር በሚያዋስኑ አካባቢዎች ጥቃቶችን ፣ እገታ እና የእንስሳት ዘረፋ ሲፈጽሙ እንደነበር ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን መዘገቡ ይታወሳል።

@sheger_press
@sheger_press


ማስተር አብነት ከበደ ፋዉንዴሽን ተመሰረተ

ከእናንተ ደጋግ ወገኖቼ ጋር የጀመርነው በጎ ስራ አንድ ደረጃ ከፍ ብሎ ወደ ህጋዊ ተቋም/ፋውንዴሽን ያደገ ስለሆነ እንኳን ደስ አለን እያልኩ
ይህንኑ ስራ በተደራጀ እና በተጠናከረ መልኩ ለመስራት በህጋዊ ተቋም ደረጃ የተመሠረተው ማስተር አብነት ከበደ ፋዉንዴሽን በሁሉም የሀገራችን አከባቢዎች ላይ በመገኘት አቅመ ደካማና ጧሪ የሌላቸውን እናቶችና አባቶች ከጎዳና ህይወት በማንሳት በቋሚነት ድጋፍ እንዲያገኙ በጽናት ይሰራል።

ይህ ድል የሁላችንም ነዉና በሁሉም ነገር ራሳችሁን ሰጥታችሁ ከጎኔ ለቆማችሁ ዉድ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ወገኖቼ ፈጣሪ ይስጥልን።

አመሠግናለሁ 🙏
ማስተር አብነት ከበደ

@sheger_press
@sheger_press


"ብሔራዊ ባንክ ሐሙስ ሚያዝያ 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው የፋይናንስ ስታቢሊቲ ሪፖርት (Financial Stability Report) የባንክ ብድሮች በጥቂት ተበዳሪዎች እጅ ተከማችተው እንደሚገኙ ጠቅሷል‼️

👉ባንኮች ከሰጡት አጠቃላይ ብድር 23.5 በመቶውን ያበደሩት ለአስር ግለሰቦች ነው ተብሏል።😳

በአገሪቱ ያሉት ሁሉም ባንኮች እስካለፈው ዓመት ሰኔ መጨረሻ ድረስ በሥራ ላይ ካዋሉት አጠቃላይ 1.9 ትሪሊዮን ብር ብድር ውስጥ 23.5 በመቶውን ያበደሩት ለአሥር ተበዳሪዎች እንደሆነ በሪፖርቱ ተካቷል።

ከፍተኞቹ አሥር ተበዳሪዎች ከአጠቃላይ የባንክ ብድር መጠን ውስጥ በ2014 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ ከነበረው 18.7 በመቶ ነው በ2015 ዓ.ም. መገባደጃ ላይ ወደ 23.5 ያደገ ነው ተብሏል።"(ሪፖርተር)

@sheger_press
@sheger_press


ባቲ‼️

ዛሬ የባቲ ከተማ ትልቁ የሠኞ ገበያ በአተት በሽታ ምክንያት በገዥና ሻጭ ሳትደምቅ ትውላለች‼️

በአማራ ክልል በባቲ ከተማ እና ባቲ ወረዳ ላይ በተለያዩ የገጠር ቀበሌዎች አካባቢ በተከሰተው #የአተት አጣዳፊ በሽታ ምክንያት ባቲ ከተማ አስ/ር ላይ  በየሣምንቱ የሚውለው ትልቁ ዛሬ ሰኞ ገበያ ሚያዚያ 7/2016ዓ/ም በገዥና ሻጭ ለህዝቦቿ ደህንነት ስትል ሳትደምቅ ጭርታ በዝቶባት የምትውል መሆኗ ተረጋግጦአል ።

በመሆኑም ዛሬ ሚያዚያ 7ቀን 2016 ዓ/ም ባቲ ከተማ ላይ ምንም አይነት ገበያ የማይውል መሆኑን ማህበረሰቡ ተረድቶ የሚገጥሙንን ችግሮች በጋራ በመከላከል ሀላፊነታችን እንወጣ ሲል የባቲ ከተማ አስተዳዲ የጤና ግብረ ሀይል  ያሣስባል።

የከተማ አስተዳደሩ የጤና ግብረ-ሀይል ከባቲ ሰኞ ገበያ ተጨማሪም የተለያዩ ክልከላዎችን የከለከለ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ፦

👉1ኛ.በየመንገዱ ላይ ተጠባብሰው የሚሸጡ ምግቦች

👉2ኛ.ሀብሀብና የተለያዩ ፍራፍሬዎችን በመንገድ ላይ ዘርግቶ መሸጥ

👉3ኛ.ቀርሣ ውሃ እና ከአውሳ በር በታች የሚገኙ ውሃዎችን ከመጠቀም መቆጠብ።

👉4ኛ.የህፃናት ኬጂ ትምህርት ቤቶች ዛሬ ዝግ ሆኖ የሚውል በመሆኑ ወላጆች የኬጂ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ባለመላክ ንፅህናቸውን ጠብቆ በቤታቸው እንድቀመጡና በንፅህና እድመገቡ ማድረግ

👉5ኛ.ማህበረሰቡ የራስንና የአካባቢውን ንፅህና ጠብቆ ያልቀዘቀዙና ያልተበላሹ ምግቦችን በመመገብ የአተት በሽታን መከላከል የሚገባ መሆኑን ገልፆ አጣዳፊ ተቅማጥና ትውኪያ ከገጠመዎት ፈጥነው ወደ ጤና ተቋማት መምጣት እንዳይዘነጉ ሲል አሳስቧል።

@sheger_press
@sheger_press


መረጃ ‼️

ኦነግ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ስለ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ተጨማሪ መረጃዎችን አውጥቷል::

በቴን ካረፈበት ሆቴል ሲወስዱት የነበሩት የፀጥታ ሀይሎች ክፉኛ እየደበደቡት እንደነበር - ይህንን የተመለከቱ እና የአይን ምስክር የሆኑ የሆቴሉ ጥበቃዎች ታፍነው እንደጠፉ - እንዲሁም በመጨረሻ ዩኒፎርም የለበሱ የፀጥታ ሀይሎች በቴ ላይ ግድያ ሲፈፅሙ የተመለከቱ እና ይህንኑ የመሰከሩ የአካባቢው ነዋሪዎች በመንግስት ሀይሎች ደብዛቸው እንዲጠፋ መደረጉን አስታውቋል::

@sheger_press
@sheger_press


ኢራን የእስራኤል ቅጣት ተጠናቋል አለች።

ቴህራን ጥቃቱን የመቀጠል ፍላጐት የለኝም ማለቷን ፕሬስ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኮማንደር በእስራኤል ላይ የተደረገው ዘመቻ "ከተጠበቀው በላይ ስኬታማ" ነበር ሲል አስታውቋል።

ኢራን በእስራኤል ላይ ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት ስታደርስ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል።

@sheger_press
@sheger_press


የአይን እማኞች ዛሬ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በነበረው የተኩስ ልዉዉጥ ሁለት መንገደኞች ጉዳት ደርሶባቸዋል አሉ

ዛሬ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በነበረው የተኩስ ልዉዉጥ በርካቶችን ያስደነገጠ ክስተት ነበር። በዚሁ የተኩስ ልዉዉጥ ወቅት ሁለት ሰዎች የተገደሉ ሲሆን በፖሊስ አባላት ላይም ጉዳት መድረሱን ዳጉ ጆርናል መዘገቡ አይዘነጋም።

በዚሁ ክስተት ህይወታቸዉን ካጡ አንድ መኪናቸዉን በማሽከርከር ላይ ከነበሩ ግለሰብ ዉጪ ሁለት መንገደኞች ላይም ጉዳት መድረሱን እማኞች ተናግረዋል።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው የተኩስ ልውውጥ በተፈጸመበት አካባቢ ነዋሪ ከሆኑ አንድ ግለሰብ ሁለት መንገደኞች ላይ ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የተኩስ ልውውጡ የተፈጸመው ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ወደሚያስወጣ መንገድ ላይ መሆኑን በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የአዲስአበባ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ “ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው። ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል” ብለዋል። ሌላ አንድ የግጭቱ ተሳታፊ የነበረ ግለሰብም መገደሉን አረጋግጠዋል።

@sheger_press
@sheger_press


ሌላ ጦርነት ፈነዳ‼️

በተፈራው መሰረት ኢራን በእስራኤል ላይ ከፍተኛ የሆነ የሚሳኤልና የአጥፍቶ ጠፊ ድሮኖች ጥቃት ከፍታለች ።

ቀይ ባህርና ሜድትራኒያን ቀጠና ውጥረት ውስጥ ገብቷል ።

በቀጥታ ስርጭቶች እየታየ እንዳለው እስራኤል እንዲሁም አጋሮቿ እንግሊዝና አሜሪካ የኢራንን ጥቃት ሙሉ በሙሉ ኢላማቸውን ከመምታት እንዲከሽፉ መከላከል ይችላሉ ወይ የሚለው ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ጆ ባይደን ኢራን ላይ ያለንን ጦር መሳሪያ በሙሉ እንጠቀማለን ሲሉ የዛቱ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ ዓለም ለኒውክሌር ጦርነት ከምንግዜውም በላይ ቀርባለች ሲሉ ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች እየዘገቡ ይገኛሉ።

@sheger_press
@sheger_press


ፈረንሳይ፣ በኦሮሚያ ክልል መቂ ከተማ ባለፈው ማክሰኞ ተገድለው በተገኙት የኦነግ አመራር በቴ ኡርጌሳ ግድያ ዙሪያ ምርመራ እንዲደረግ ጠይቃለች።

በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኢምባሲ ዛሬ ባወጣው አጭር መግለጫ፣ በበቴ ግድያ ላይ "አስቸኳይ"፣ "ገለልተኛ" እና "ሙሉ" ምርመራ እንዲደረግ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ አውሮፓ ኅብረት እና ሌሎች ዓለማቀፍ አጋሮች ያቀረቡትን ጥያቄ ፈረንሳይ እንደምትጋራው ገልጧል።

ፈረንሳይ፣ በተቃዋሚ ፖለቲከኛው ግድያ ዙሪያ "ፍትህ እና ተጠያቂነት" መስፈኑ አስፈላጊ መኾኑንም ገልጣለች።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት፣ በበቴ ኢርጌሳ ግድያ እጁ እንደሌለበት ገልጦ፣ በግድያው ላይ የወንጀል ምርመራ መጀመሩንና ምርመራው ሲጠናቀቅ ውጤቱን ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ ከቀናት በፊት መግለጡ አይዘነጋም።

@sheger_press

20 last posts shown.