Posts filter


አሳዛኝ ክስተት ‼️

ታዳጊዋ ተደፍራ ከተገድለች በሆላ ተሰቅላ ተገኝታለች ፡፡

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች የ8 አመት ታዳጊ ስትሆን ነዋሪነቷ በምዕራብ ሸዋ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ ሲሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከተፈፀመባት በኋላ ህይወቷ ሲያልፍ አስክሬ* ን ሰቅ* ው ሄዷል።

ለታዳጊዋ ሲምቦ ብርሃኑ ፍትህ
እየተጠየቀ ይገኛል።

@sheger_press
@sheger_press


ዛሬ በተጀመረው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤው ምን ተነሳ ?

በጉባኤው መክፈቻ የብልጽግና ፓርቲ ፕረዝደንት ዶ/ር አብይ አህመድ ከተናገሩት፥

፧- ይህ ጉባኤ በኢትዮጲያ የፓለቲካ ታሪክ መላው ብሄር ብሄረሰብን  ያካተተ እና አሳታፊ ያደረገ የመጀመሪያው የፓለቲካ ፓርቲ ነው።

፣-በኢትዮጲያ የፓለቲካ ፓርቲዎች ታሪክ ብልፅግና የራሱን ሀገር በቀል ሀሳብ ይዞ መምጣት የቻለ የመጀመሪያው የፓለቲካ ፓርቲ ነው(መደመር)።

፣-ብልፅግና ብዙ ፈተናዎች ገጥመውት  አልፉል፣ዛሬ ፈተናዎችን ጨፍልቆ የማለፍ አቅም አለው።

፧-በሀገሪቱ እዚህም እዛም ግጭቶች አሉ የእነዚህ ግጭት ጠንሳሾች የትናንት አባቶች ናቸው፣ የዛሬው ትውልድ የሚፈልገው ሰላም ነው።

፣- ግጭት በቅቶናል፣ ጠመንጃ ያነገባችሁ አውርዱ፣ በሰላም እንታገል በሰላም ለመታገል በራችን ክፍት ነው፣ብልፅግና የጀመረውን የሰላም አማራጭ ይቀጥላል።

፧-በብልፅግና ባለፍት ስድስት አመታት አንድም ታራሚ ቶርች (torch) አልተፈፀመበትም።

፣- የፓለቲካ ፓርቲዎች የተሻለ ሀሳብ አምጡ፣ የተሻለ ሀሳብ ማምጣት ከቻለ ፓርቲ ብልፅግና ይማራል፣ሀሳብ ይወስዳል።

፣-ብልፅግና ይህ ጉባኤው ወደ ቀጣዩ አዲስ ምእራፍ የሚያንሰራራበት ነው።

፣-ከዚህ ጉባኤ በኃላ ቃል የተገቡ የሚፈፀሙበት፣የተመጀሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶች የሚፈፀሙበት እና የሚቀጥለው ዓመት የማይሸጋገሩበት፣
የተገብ ቃሎችን በተግባር የሚፈፅሙ አመራሮች በፓርቲው የሚሰየሙበት ጉባኤ ይሆናል ብለዋል።

ፓርቲው በቀጣይ ሁለት ቀናት የሚያካሂደው ጉባኤ ይቀጥላል።(ethio fm )

@sheger_press
@sheger_press

6.9k 0 7 26 102

😭😭😭

አፋር ዛሬ ሀዘን ላይ ነች

@sheger_press
@sheger_press


Update‼️

"የጅቡቲው መንግስት ነው " በተባለ ድሮን አፋር ክልል ዛሬ ጥቃት የተፈፀመባቸው አብዝሃኞቹ አርብቶ አደሮች ናቸው ተብሏል።

@sheger_press
@sheger_press


አፋር ሲያሩ ቀበሌ︎‼

አፋር ክልል በኤሊዳዓር ወረዳ ሲያሩ ቀበሌ ዛሬ ረፋድ ላይ ለጊዜው ምንነቱ ባልታወቀ ጦር መሳሪያ ጥቃት የ8 ሰዎች ማለፋን እና በርካቶች እንደቆሰሉ የመረጃ ምንጮቼ ያደረሱኝ ጥቆማ ያመለክታል። ከጅቡቲ የተላከ"የድሮ ጥቃት ነው" የሚሉ መረጃዎች ሲዘዋወሩ ተመልክቻለሁ።ግን የተረጋገ ጉዳይ የለም።


@sheger_press
@sheger_press


#ሰማይን የለጎመውና እሳት ያዘነመው ቅዱስ

ንጉሱ አክአብና ሚስቱ ንግስቲቱ ኤልዛቤል አብያተ ክርስቲያናትን ዘግተው አብያተ ጣኦታትን በመክፈት ነቢያትና ካሕናትን ያስገድሉ ጀመር፡፡ በዘመናቸው የነበረው ነቢዩ ቅዱስ ኤሊያስ “ተው” ቢላቸው አልሰማ አሉት፡፡ በዚህ ጊዜ "ሕያው እግዚአብሔር አምላከ ኃይል: ዘቆምኩ ቅድሜሁ: ከመ ኢይረድ ጠል በእላ መዋዕል ዘእንበለ በቃለ አፉየ" “በፊትህ የቆምኩ ሕያው እግዚአብሔር አምላክ ሆይ እኔ ካልተናገርኩ በስተቀር በዚህች ምድር ዝናም አይዝነም” ብሎ 3 ዓመት ከ6 ወር ዝናም ከሰማይ እንዳይወርድ ዘግቷል፡፡ ቤል የተሰኘውን ጣኦት አምላካቸውን እሙን ይዩት ብሎ፣ አንድም እግዚአብሔር የሰጣቸውን እየበሉ እንዴት ጣኦት ያመልካሉ የሚል የሃይማኖት ቅንአት ይዞት ነው፡፡

በተለይ የደሀውን ናቡቴ ርስት በመውሰዷ የገሰጻት ንግስቲቱ ኤልዛቤል ናቡቴን ስታስገድለው "የናቡቴ ደም በእናንተ ላይ አይቀርም፡፡ የአንቺንም ደም ውሻ ይልሰዋል" ብሏት ነበርና በእልህና በጥላቻ 900 ነቢያትና ካሕናት አስፈጅታለች፡፡ አንድ መቶ የሚሆኑትን ግን የአካአብ የጦር ቢትወደድ አቢድዩ በአንድ ዋሻ ደብቆ አድኗቸዋል፡፡ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ900 ዓ.ዓ የተወለደው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኤልያስ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ርዕሰ ነቢያትም ተብሎ ይጠራል፡፡ ሲወለድ አራት ብርሃን የለበሱ ሰዎች መጥተው ወደ ቤታቸው መጥተው በእሳት መጎናጸፊያ ሲጠቀልሉት ቤቱ ብርሃን ተሞልቶ ነበር፡፡ ወላጆቹ ይህን ነገር በጊዜው ለነበሩ ነቢያትና ካሕናት ነግረዋቸዋል፡፡

በመጨረሻም ነቢዩ ቅዱስ ኤልያስ አክአብንና ቢትወደዱን አብድዩን አገኛቸው፡፡ “እስከመቼ በሁለት ልባችሁ ታነክሳላችሁ እግዚአብሔር አምላክ ከሆነ እርሱን አምልኩ እርሱንም ተከተሉ፣ ቤል አምላክ ከሆነ ደግሞ እርሱን አምልኩ እርሱንም ተከተሉ፤ ይህ እንዲሆንም መስዋዕት ሰውተን መስዋዕት ከሰማይ ወርዶ የበላለት አምላክ ነው” አላቸው፡፡ በዚህ ተስማምተውም በመጀመሪያ የጣኦቱ ካሕናት መስዋዕት ቢሰዉ ከሰማይ እሳት ወርዶ የማይበላላቸው ሆነ፡፡ ነቢዩ ቅዱስ ኤልያስም ያሾፍባቸው ጀመር፡፡ አምላካችሁ እንቅልፋም ነውና ተኝቶ ይሆናል ጮኻችሁ ጥሩት፣ አምላካችሁ እንጂ ዋዘኛ ነውና ከእረኞች ጋር ይጫወት ይሆናል” እያለ፡፡

በኋላም የሰር መስዋዕት ጊዜ ደረሰ ይበቃችኋል አላቸው፡፡ እርሱም መስዋዕቱን አዘጋጅቶ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ “አምላከ እስራኤል እግዚአብሔር ሆይ፣ እኔ እከብርበት፣ እበላበት፣ እጠጣበት ብዬ አይደለም ለአምልኮትህ ቀንቼ እንጂ ይህነ መስዋዕት ተቀበል” ብሎ ቢያመለክት ከሰማይ እሳት ወርዶ ከመስዋዕቱና ከተረበረበው እንጨት እልፎ መሬቱን እስኪልሰው ድረስ በልቶለታል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን ታላቅ ነቢይ እግዚአብሔር ስለሰጠው ሦስት ጸጋዎች ታከብረዋለች፡፡ ስለድንግልናው፣ ስለምንኩስናው (እጅግ ጥቂት ለቁመተ ስጋ ያህል ብቻ ይመገብ ነበርና)፣ ስለ ብሕትውናው (ከሰዎች ርቆ ይኖር ነበርና፡፡

ከሰማይ እሳት ያወረደ፣ ዝናም እንዳይወርድ ሰማይን የለጎመ ድንቅ ባህታዊ ነው፡፡ በመጽሐፈ 1ኛ ነገስት 17፣2 የሰፈረው ታሪኩ እንደሚሳየውም ወደብሔረ ሕያዋን በእሳት ሰረገላና በእት ፈረስ አርጓል፡፡ በመጨረሻም በዘመነ ሐሳዌ መሲህ መጥቶ በሰማዕትነት ያርፋል፡፡ መታሰቢያው ታሕሳስ 1 ነው፡፡ የዘመናችን ባሕታውያንም ስጋዊውን ዓለም ትተዋልና መንፈሳዊ በረከት የታደሉ ናቸው፡፡ ገዳማቸውን በማገዝ በዓታቸውን በማጽናት ከበረከታቸው እንሳተፍ፡፡                 


ድጋፍ ለማድረግ :-ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አድነት  ገዳም
                        ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
                        1000442598391
                        አቢሲኒያ ባንክ
                        141029444


ለተጨማሪ መረጃ:- 
   የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957     
                         ወይም 0938644444


Video is unavailable for watching
Show in Telegram


የሰላሌ የነዋሪው ሰቆቃ

በኦሮሚያ ክልል ግጭት ከከፋባቸው አከባቢዎች አንዱ የሆነው ሰላሌ በግጭቱ ምክንያት የነዋሪዎች ሕይወት ለአደጋ መጋለጡን እየተናገሩ ነዉ።

ነዋሪዎቹ እንደሚሉት እገታ፣ ማስፈራሪያና ቅሚያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባበሰ ነዉ። አንድ የሰሜን ሸዋ ዞን የደብረጽጌ ከተማ ነዋሪ እንደሚሉት የመንግሥት ፀጥታ አስከባሪዎችና አማፂያን ሠላም እንደሚያወርዱ የአካባቢዉ ህዝብ በተደጋጋሚ በአደባባይ ሠልፍ ጭምር ጠይቋል።

ተደጋጋሚዉ ጥያቄና ተማጽዕኖ መና ቀርቶ ታጣቂዎች የሚያደርሱት አስገድዶ ስወራ፣ እገታና ዘረፋዉ ቀጥሏል። የአከባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት ገበያ ለመሔድና እና ለቅሶ ለመድረስ እንኳን እየሠጉ ነዉ። 

ከአንድ ሳምንት በፊት ከደብረሊባኖስ አከባቢ ለገበያ በመኪና ሲጓዙ የነበሩ 50 ያክል ነጋዴዎች ሳዲኒ ብዮ በሚባል የያያ ጉሉለ ወረዳ ታፍነው እንደተወሰዱ ሌላዉ ነዋሪ አስታዉቀዋል።

የያያ ጉሌሌ ፊታል ከተማ አስተያየት ሰጪ አክለዉ እንዳሉት የፀጥታ ችግሩ ፋታ አይሰጥም። መኪና ሙሉ ሰዎች መወሰዳቸዉ የችግሩን ክፋት እንደሚያሳይ ነዋሪዉ ገልፀዋል። ይህ ቦታ ከአንድ ወር ግድም በፊት አምስት የዞን ባለስልጣናትን ጨምሮ የመንግስት ሰራተኞች የተገደሉበት አካባቢ ነው፡፡ ነዋሪዉ እንደሚሉት ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ የተወሰዱት ወደ 50 የሚሆኑ ገበያተኞች እስካሁን አልተመለሱም፤ «የመኪናዉ ሾፈርም አብሮ እንደተወሰደ ነው” ብለዋል፡፡

በቅርቡ ከዞን የመጣው የመንግስት ሠራዊትም ዘመቻ መክፈቱን ባስታወቀ በጥቂት ጊዜ ዉስጥ ከአካባቢዉ በመልቀቁ ምንም ለውጥ አልታየም፡፡ «ከዚህ ከተማ ውጪ ታጣቂዎች የማይገኙበት ሥፍራ የለም» ይላሉ ነዋሪዎቹ።

“ተቸግረናል፡፡ ከተማ ውስጥ እንኳ ቢሆን ተኝቶ የሚያድር ሰው አታገኝም፡፡ ሰው እየተደበቀ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሰ ነው ቀን የሚገፋው፡» ይላሉ። ነዋሪዉ እንደሚሉት ሁለቱ ተፋላሚዎች ብዙ ጊዜ ፊትለፊት ሲዋጉ አታይም፡፡ «የመንግስት ጦር ሲመጣ ጫካ ያለው በደፈጣ ነው የሚጠብቀው፡፡ ሁለቱ ተፋላሚዎች ተነጋግረው መግባባት ስላልቻሉ በመሃል የመጨረሻ ስቃይ እያየን ነዉ» አከሉ ነዋሪዉ።

የመንግስት የጸጥታ ሃይልም፣ አማጺዎችም የነዋሪዉን ሥልክ ሥለሚወስዱ መረጃ  መለዋወጥ እንኳን አዳጋች ሆኖ ህዝቡ ከዚህ በፊት ሲኖር ከነበረው ሃምሳ ኣመት ወደ ኋላ ተመልሶ እየኖረ ነው ብለዋል፡፡
(DW )

@sheger_press
@sheger_press


ትራምፕ 30,000 ሰነድ አልባ ስደተኞችን በጓንታናሞ ቤይ ለማሰር ማቀዳቸውን ገለፁ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞችን በጓንታናሞ ቤይ ለማሰር ማቀዳቸውን ገልፀዋል።

ትራምፕ ስለ ዕቅዳቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የተናገሩት በስርቆት ወንጀሎች የተከሰሱ እና ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸው ስደተኞች እንዲታሰሩ የሚደነግገውን የላርኪን ሪሌይ አክትን ሲፈርሙ ነው።

በጓንታናሞ ቤይ ውስጥ እስከ 30,000 የሚደርሱ ሕገ-ወጥ ስደተኞችን እንደሚያስሩ የገለፁት ፕሬዝዳንቱ፤ በሕገ-ወጥ ስደት ላይ የሚወስዱትን እርምጃ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተናግረዋል።

ይህ ዕቅድ ትራምፕ በሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸው በሕገ-ወጥ ስደት ላይ እርምጃ ለመውሰድ የገቡትን ቃል እውን ለማድረግ ያለመ መሆኑ ነው የተገለፀው።

ትራምፕ ስለ ዕቅዳቸው ሲናገሩ "ለአሜሪካ ህዝብ ስጋት የሆኑ ሕገ-ወጥ ስደተኞችን ለማቆየት በጓንታናሞ 30,000 አልጋዎች አሉን፤ ይህም ሕጋዊ ሰነድ የሌላቸው ስደተኞችን የመያዝ አቅማችንን በእጥፍ ያሳድጋል" ብለዋል።

@sheger_press
@sheger_press


መረጃ ‼️

ለፌዴራል መንግስት "በፕሪቶሪያዉ ስምምነት መሰረት ምእራብ ትግራይ ወደ ትግራይ ይመለስ ብዬ ስጠይቅ" 'ስለ ሁመራ ተዉ እና እስቲ አክሱምን በስርአቱ አስተዳድር' የሚል ምላሺ ከፌደራል መንግስቱ እየተሰጠኝ ነዉ ሲል ጌታቸዉ ረዳ አስታወቀ ፡፡

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ጌታቸዉ ረዳ ከክልሉ መገናኛ ብዙሃን ጋር የ
በትግርኛ ቋንቋ እረዘም ያለ ቆይታ አድርጎል ፡፡

በክልሉ ስላለዉ የፖለቲካ ክፍፍል ፣ ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነት አፈፃፀም ፕሬዚዳንቱ በዝርዝር ያነሳቸዉ ሃሳቦች ነበሩ

@sheger_press
@sheger_press


ህጻናት በአፍመፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ የሚያደርገውና የአማርኛ ቋንቋ የትምህርት አይነትን ከትምህርት ስርዓት የሚያስወጣ የአጠቃላይ የትምህርት አዋጅ ጸደቀ

የሀገሪቱ ህጎች ሁሉ የበላይ ነው የሚባለው ህገ መንግስቱን ይቃረናል የሚል የሰላ ትችት የቀረበበት የአጠቃላይ የትምህርት አዋጅን የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አፅድቆታል፡፡

ምክር ቤቱ ያጸደቀው አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ የምክር ቤት አባላት ህገ መንግስቱን ይቃረናል ሲሉ ተችተውታል፡፡

የምክር ቤቱ አባል ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) አዋጁ የአንድ መግባቢያ የሀገራዊን ቋንቋ አስፈላጊነት የዘነጋን ይመስለኛል ብለዋል፡፡

ህፃናትን በአፍ መፍቻቸው ቋንቋ ማስተማር መሰረታዊ የህፃናት መብት መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር ደሳለኝ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የማስተማር አስፈላጊነት ያክል ደግሞ አንድ አስተሳሳሪ የሆነ ሀገራዊ ቋንቋ አስፈላጊነት መርሳት የለብንም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የ 1986 የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ አማርኛ ቋንቋ በመላ ሀገሪቱ ትምህርት ቤቶች እንደ አንድ የትምህርት አይነት መስጠትን ይፈቅድ ነበር፡፡

ባለፈው ዓመት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው አዲሱ የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ ግን ይህንን ጉዳይ እንዲለወጥ ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡

እንደ እኔ አማርኛ ቋንቋ ኢትዮጵያ በረጅም ጊዜ በነበረችው የታሪክ መስተጋብር ውስጥ በጥሩ እና በመጥፎ የታሪክ ዘመናቸው ውስጥ አነሰም በዛም መስተጋብር ማስተሳሰሪያ ሆኖ ያገለገለ ቋንቋ ነው ብለዋል፡፡

የሰሜኑ ከደቡቡ የምስራቁ ከምዕራቡ ከራሱ ቋንቋ በተጨማሪ ሚግባባት ቋንቋ አማርኛ ነው፡፡ ይህን ቋንቋ በተለይ ከ1960ዎቹ እንቅስቃሴ ጀምሮ ቋንቋውን የአንድ ህዝብ ብቻ አድርጎ በኢትዮጵያዊያን መካከል ያለውን ድልድይ ፈጣሪ ቋንቋ የማሳነስ ሁኔታ እስከ ዛሬ ድረስ ይስተዋላል ብለዋል፡፡

‘’እኔ አማራ ስለሆንኩ አይደለም ይህን ጥያቄ የማነሳው’’ ያሉት ደሳለኝ ቢያንስ ልጆቻችን የሚነጋገሩበት ሚግባቡበት ቢጣሉ የሚታረቁበት አንድ የጋራ ቋንቋ ቢኖራቸው ለዚህም አማርኛ ቢያንስ ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ በመደበኛ አስከ 12 ክፍል ድረስ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ በአዋጁ ቢካተት ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት በምክር ቤቱ የሰው ሃብት ቴክኖሎጂ ስራ ስምሪት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ የሆኑት ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)አንድ ሀገራዊ ቋንቋ ቢሰጥ ለሚለው የትኛው ነው አገራዊ ቋንቋ? እስከዛሬ ድረስ በቋሚ ኮሚቴም ስንወያይበት ይሄ ነው ተብሎ አልተነገረንም ብለዋል፡፡

እኔም የትኛው ነው? አገራዊ ቋንቋ የሚለውን ጥያቄ ሳነሳ ነበር ዛሬ ግን ያነሱት የምክር ቤት አባል አማረኛ ቋንቋ ነው ብለዋል በግልጽ የተቀመጠው ግን አማርኛ ቋንቋ የፌደራል የስራ ቋንቋ እንደሆነ ነው ብለዋል፡፡

ሌላው አቶ ጋሻነው ዳኛው የተባሉ የምክር ቤቱ አባል የትኛውም ህግ የሚመነጨው ከህገ - መንግስቱ መሆን አለበት ይላሉ፡፡ አሁን የወጣው አዋጅ ግን ህገመንግስቱ እስኪሻሻል ይላል፤ እስኪሻሻል ብሎ ህግ ማውጣት ይቻላል ወይ የሚል ጥያቄን ጠይቀዋል፡፡

ሌላው አዋጁ ከህገ መንግስቱ ጋር ይጣረሳል የሚለው ጥያቄ ያነሱት የምክር ቤቱ አባል  አበባው ደሳለው(ዶ/ር) ናቸው፡፡

ዶ/ር አበባው የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ አማርኛ ነው ይላል ህገመንግስቱ ደግሞ አንድ ህግ ሲወጣ ከህገ መንግስት ጋር ከተጣረሰ ተፈፃሚነት አይኖረውም ይላል ለምን የማይፈጸም ህግ እናወጣለን ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

አዋጆች ሲወጡ የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታት ነው ችግር የማይፈታ ነገር በአዋጁ ላይ ለምንድነው ለማስቀመጥ የተገደዳችሁት ሲሉ ዶክተር አበባ ጠይቀዋል፡፡ 

ነገሪ ሌንጮ(ዶ/ር) አዋጁ ከህገመንግስቱ ጋር የሚጣረስ ነገር የለውም ብለዋል፡፡

Via ሸገር ኤፍኤም

@sheger_press
@sheger_press

9.1k 0 11 16 94

አዲሱ አዋጅ‼️
በአዲሱ የንብረት ማስመለስ አዋጅ "አንድ ሰው ያለው ንብረት እና የነበረው ገቢ ካልተመጣጠነ ወደ ፍርድ ቤት ከማምራቱ በፊት በቅድመ ክስ ስርአት እንደሚጠየቅ" ፍትህ ሚኒስትር አስታወቀ‼️

የንብረት ማስመለስ አዋጅን በተመለከተ የአዋጁን ዓላማ፣ መሠረታዊ ይዘቶች፣ እንዲሁም ቀጣይ አተገባበር በተመለከተ የተፈጠሩ ብዥታዎችን ለማስተከከል በሚል ፍትህ ሚኒስትር መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫውም፤ በኢትዮጵያ ይህ ህግ ከመውጣቱ በፊት በወንጀል የተገኘ ሃብት ማስመለስን በተመለከተ ራሱን የቻለና ወጥ የሆነ የሕግ ማዕቀፍ ያልነበረ በመሆኑ በሕግ ማስከበር ሂደት ክፍተት ፈጥሮ ቆይቷል ብሏል።

የፍትህ ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሀና አርአያስላሴ ቀደም ሲል የንብረት ማስመለስ አዋጁን በተመለከተ ያለ ህግ ቢኖርም ብዙ ህጎችን ያካተተ እንዳልነበር ገልፀዋል።

ምንጩ ያልታወቀ ንብረትን በተመለከተ በቅድመ ክስ ሂደት ማንኛውም ሰው ጉዳዩን እንዲያስረዳ የሚቀርቡ ጥያቄዎች እና አቤቱታዎች የፍርድ ቤቶች የሥነ ሥርዓት ሕጎችንና መርሆዎችን ተከትለው ማጣራት እንደሚደረግባቸው አንስተዋል።

አቤቱታ የሚቀርብባቸውም ሰዎች በሕጉ መሰረት ያላቸውን ማስረጃዎች የማቅረብ በፍርድ ቤት ዘንድ ቀርበው የመደመጥ መብታቸው እንዲከበርላቸው ይደረጋል ብለዋል። (Ethiofm)

@sheger_press
@sheger_press


በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ ቡልቡላ ወረዳ 12 ሸገር ህንፃ ላይ ተከስቶ የነበረው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ ከቁጥጥር ስር ውሏል።

@sheger_press
@sheger_press


በቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ከፍተኛ የእሳት አደጋ ተከስቷል

በቦሌ ቡልቡላ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 አካባቢ የእሳት አደጋ መከሰቱን ነዋሪዎች ለጣቢያችን አስታውቀዋል።

የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ነግረውናል።

@sheger_press
@sheger_press


አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተሸሙ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ለአምስት ዓመታት ሲመሩ የነበሩት ዳንኤል በቀለ(ዶ/ር) ጊዜያቸውን ጨርሰው በፓርላማ ከተሰናበቱ ከአምስት ወራት በኋላ ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የስልጣን ዘመን ለስድስት ዓመታት የካቤኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው የሰሩትን አቶ ብርሃኑ አዴሎ ኮሚሽኑን እንዲመሩ በፓርላማ ተሾሙ።

ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነው ኢሰመኮ፤ ለሰብዓዊ መብቶች መስፋፋት፣ መከበር እና ጥበቃ የመስራት ስልጣን በአዋጅ የተሰጠው ሲሆን፣ ዳንኤል (ዶ/ር) ተቋሙን በመሩባቸው አምስት ዓመታት ኃላፊነታቸውን በብቃት የተወጡ ቢሆንም በሕግ እንዲጠየቁ ጭምር ከፓርላማ አንዳንድ አባሎች የቀረበባቸውን ጫና ተቋቁመው ተቋሙ ገለልተኛ በመሆን ለመስራት የሚያስችለውን አሠራር መዘርጋታቸው ይነገራል፡፡

በ2012 ዓ.ም. የተሻሻለው የኢሰመኮ ማቋቋሚያ አዋጅ፤ ተቋሙን በዋና ኮሚሽነርነት፣ በምክትል ዋና ኮሚሽነርነት እና በዘርፍ ኮሚሽነርነት የሚያገለግሉ ኃላፊዎች በተወካዮች ምክር ቤት እንደሚሾሙ ይደነግጋል።

አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ አእምሯዊ ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት ከተነሱ በኋላ ላለፉት አስር አመታት በግል የሕግ አማካሪነትና ጥብቅና ሥራ ላይ እንደነበሩ ታውቋል፡፡

@sheger_press
@sheger_press


ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

በዚህ መልኩ የቀረበውን ዝርዝር ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።

ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።

በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።

የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ ይዟል።

በዚህም1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን ያቀረቡትን አራት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 21 መሰረት በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ እያንዳንዳቸው አራት፣ አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የተወሰነውን የጽኑ እስራት ውሳኔን የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እጃቸው ከተያዘ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።

በጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@sheger_press
@sheger_press


#ቴምር ሪልስቴት
😱7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው 3 ሳይቶች
🎯1,አያት ሳይታችን
        👉 2መኝታ 87ካሬ
        ሙሉ ክፍያ 4,976,400ብር
         👉 3መኝታ 107ካሬ
        ሙሉ ክፍያ 6.1ሚሊዮንብር
         👉 3 መኝታ 121ካሬ
        ሙሉ ክፍያ 6.9ሚሊዮን ብር
🎯2,ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ፊት ለፊት
         👉3 መኝታ 113ካሬ
         10%ቅድመ ክፍያ 1ሚሊዮን ብር
          ሙሉ ክፍያ 10,961,000ብር
         👉3መኝታ 119ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 1.1ሚሊዮን ብር
        ሙሉ ክፍያ 11,543,000ብር
         👉ቀሪውን 90% በ15 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
🎯3,ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273


#በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ

መልአከ ብርሃናት፣ ለሚጠሩት ፈጥኖ የሚደርስ መሆኑን የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት በስፋት ይገልጹታል፡፡ ከሰባቱ ሊቃነ መላዕክት አንዱ ሲሆን በየዓመቱ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ይከበራል፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ዑራኤል፡፡ የስሙን ትርጓሜ ሊቃውተ ቤተክርስቲያን ሲያስቀምጡም “ዑራ” ማለት ብርሃን ማለት ሲሆን “ኤል” አምላክ ማለት ነው፡፡ በዚህም ዑራኤል ማለት የአምላክ ብርሃን፣ ወይም የብርሃን ጌታ ማለት ነው፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር በመባርቅትና በነጎድጓድ ላይ የተሾመው ታላቅ መልአክም ነው ቅዱስ ዑራኤል፡፡ በመጽሐፈ ሔኖክ 6÷2 መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ይሰማራል።

ምሥጢረ ሰማይና እውቀትንም ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለትም የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራ እርሱ መሆኑን ለነቢዩ ሄኖክ ነግሮታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ የመራ፣ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ እርሱ ነው፡፡ ሊቀ መልአኩ የጌታችንን ደም የረጨበት ጽዋ በሀገራችን በኢትዮጵያ እመጓ ቅዱስ ኡራኤል እንደሚገኝ ስፍረዋን የጎበኙ ጸሐፍትና የስፍራው አገልጋዮች ይገልጻሉ፡፡

ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን ያጠጣ፣ ኢትዮጵያዊውን ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በርካታ ቅዱሳት መጻሕፍትን አንዲደርሱ ያገዘ፣ የረዳና የዕውቀት ጽዋን ያጠጣ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ በርካታ ቅዱሳን አባቶች ምስጢር እንዲገለጥላቸው የረዳቸው ቅዱስ ዑራኤል መሆኑ በበርካታ የቤተ ክርስቲያናችን መጻሕፍት ሰፍሮ ይገኛል፡፡ አፋቸውን ከፍተው የምስጋና ቃል እንዲናገሩ፣ የሚጽፉበት ብዕር በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ለሕይወት ድህነት የሚሆን መልዕክት እንዲያስተላልፍ ቅዱስ ዑራኤል አግዟቸዋል፡፡ ይህም ምሥጢር ማናገር የመንፈስ ቅዱስ ሥራ ቢሆንም የተሠወረውን መግለጥ፣ በአዲስ ቋንቋ ማናገር ለመላእክት የተሰጠ ጸጋቸው መሆኑም ያሳየናል፡፡

ዛሬም በየገዳማቱ ያሉ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች ዓለምን ንቀው፣ ድንጋይ ተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው፤ ግርማ ሌሊቱን፣ ድምጸ አራዊቱን፣ ጸብአ አጋንንቱን ተቋቁመው በጾምና በጸሎት ሲተጉ ይህ ቅዱስ መልአክ ዑራኤል ፈጽሞ ይራዳቸዋል፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕይ 8÷4 “የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።” እንዲል በገዳማውያኑ መካከል ተገኝቶ ጸሎታቸውን ያሳርጋል፤ ልመናቸውን በአምላክ ፊት ያቀርባል፡፡ ቅዱሳን መካናትን ስናግዝ፣ ገዳማትን ስንረዳ፣ በዓታቸውን ስናጸና የገዳማውያኑ ጸሎትና በረከት ይደርሰናል፡፡    

ድጋፍ ለማድረግ:-ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




በአቶ መለስ ዜናዊ ዘመነ መንግስት የሚኒስትሮች ካቢኔ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ገብረማርያም ለኢትዮጵያ ሰብለአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ለመሰየም ዛሬ ጥር 22 ቀን 2017 ዓም ቀርበዋል። ሌሎች አራት ተወዳዳሪዎችም መቅረባቸው ታውቋል።

@sheger_press
@sheger_press

20 last posts shown.