Posts filter


አሳዛኝ መረጃ‼️

ንግስ አክብረው በመመለስ ላይ የነበሩ ምዕመናንን ላይ የመኪና አደጋ ደርሶ 18 ሰው ማረፉ ተሰማ።

መነሻቸውን ሐዋሳ እና ሻሸመኔ ከተማ አድርገው የመጋቢት አቦ ክብረ በዓልን በአርባምንጭ ዝጊቲ አቦ በማክበር ወደ መጡበት በመመለስ ላይ የነበሩ ምዕመን

ወላይታ ዞን በዴሳ ከተማ መሻገሪያ ድልድይ ስር የተሳፈሩበት መኪና ፍሬን ተበጥሶ በመግባቱ ከ18 በላይ ምዕመናንን ከእዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰማ።

አደጋው ዛሬ ምሽት 12:30 አከባቢ የደረሰ ሲሆን የተሳፈሩበት መኪና ወንዝ ውስጥ የገባ ከመሆኑ የተነሳ የሟቾች ቁጥር ከእዚህ በላይ ያሻቅባል ተብሎ ይጠበቃል።

እግዚአብሔር ነፍሳቸውን ከደጋጎች ጎን ያሳርፍልን

@sheger_press
@sheger_press


በቀርሳ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሀረርጌ ዞን ቀርሳ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለጸ።

አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ ከዋታር ከተማ ወደ ቀርሳ ከተማ ሲጓዝ ከሞተር ሳይክል ጋር በመጋጨቱ የአራት ሰዎች ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር መሆኑን የመምሪያው የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ካስዬ አበበ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል። (FBC)

@sheger_press
@sheger_press


PAVEL‼️

የቴሌግራም መስራች Pavel Durov ተመስርቶበት ከነበረዉ ክስ ነፃ በመባል ፈረንሳይ ለቃዋለች።

በጣም ጨንቆን ነበር😂😂

@sheger_press
@sheger_press


የ51 ተሳፋሪዎቹን ሕይዎት የታደገው ጀግና ሹፌር

እጁን በጥይት ተመትቶ ንፁህ ደሙን እያዘራ የ51 ተሳፋሪዎቹን ህይዎት የታደገው ጀግና

ጀግናው ሹፌር አየለ እውነቱ በሙያው የተመሰገነና የተከበረ የህዝብ ማመላለሻ ሀገር አቋራጭ አውቶብስ አሽከርካሪ ነው ።

መጋቢት 03 ቀን 2017 ዓ/ም ምድቡ ወደሆነው ወልድያ ከተማ ፣ እንደወትሮው ሁሉ 51 ተጏዦቹን አሳፍሮ ከሌሊቱ 10:30 ሰዓት ከአዲስ አበባ ላምበረት ተነስቶ በጭፍራ በኩል ወደ ወልዲያ ጉዞ ጀመረ ።

ይሁን እንጅ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት አካባቢ አፋር ገዋኔ አካባቢ እንደደረሱ አምነውት የተሳፈሩ ወገኖችን እንደያዘ ሀገር አማን ብሎ ወደፊት እየከነፈ ባለበት ወቅት ማንነታቸው ያልታወቁ የታጠቁ ሀይሎች ጀግናው (ሽፍቶች) ሹፌር አየለ እውነቱ ላይ አነጣጥረው የጥይት እሩምታ ያወርዱበት ጀመር።

በዚህ የጥይት እሩምታ ቀኝ እጁ ላይ ከባድና ግራ እጁ ላይ ቀላል ጉዳት ቢደርስበትም ህመሙን ዋጥ አድርጎ ንፁህ ደሙን እያዘራ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ የሁለት ልጆቹና መላው ቤተሰቡ አምላክ ጥበቃ ፣ የሚያሽከረክረውን አውቶብስ በብስለት ተቆጣጥሮ እንዳይወድቅ አድርጓል ፣ በዚህም አውቶብስ ውስጥ የሚጏዙ 51 ተሳፋሪዎችን ህይዎት ታድጏል።

ረዳቱ ተስፋዬም የሚፈሰውን ደም በጨርቅ አስሮ በአካባቢው ወደሚገኝ ህክምና ቦታ እንዲደርስ አድርጓል። ሹፌር አየለ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ህክምና በመከታተል ላይ ይገኛል።

ክብር በሞትና በህይዎት መካከል በስንት ፈተና እያለፉ ህዝብንና ሀገርን ለሚያገለግሉ ፣ ክብር ጥቃታቸው ጉዳታቸው ሞታቸው ውለታቸው ቢዘነጋም እነሱ በየመንገዱ እየወደቁ ፣ እየሞቱ አካላቸውን እያጡ ነፍሳቸውን አደጋ ላይ ጥለው ለሙያቸው ለታመኑ ጀግና የሀገራችን አሽከርካሪዎች ። ...

ክብር ለሹፌሮች።

@sheger_press
@sheger_press

7.8k 0 6 14 171

የእስራኤል ወታደሮች ሁለት ኢትዮጵያዊያንና አንድ ኡጋንዳዊ ተኩሰው መግደላቸው ተገለፀ

የእስራኤል ወታደሮች፣ ትናንት ከዮርዳኖስ አቋርጠው ወደ እስራኤል የገቡ ሁለት ኢትዮጵያዊያንና አንድ ኡጋንዳዊ ተኩሰው መግደላቸውን የአገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ወታደሮቹ የተሠጣቸው ትዕዛዝ የማስጠንቀቂያ ተኩስ እንዲተኩሱ እንደነበር ዘገባዎቹ አመልክተዋል።

በርካታ ጥገኝነት ጠያቂዎችና የሕገወጥ ሰዎች ዝውውር ሰለባዎች ከዮርዳኖስ ወደ እስራኤል እንደሚገቡና ድንበር ጠባቂ ወታደሮች እንዲመልሷቸው ሥልጣን እንደተሠጣቸው ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

ወታደሮቹ ግድያውን የፈጸሙት፤ ማቾቹ "ስጋት የሚደቅን" እንቅስቃሴ በማድረጋቸው እንደሆነ የአገሪቱ መከላከያ ባለሥልጣናት ተናግረዋል ተብሏል።

አንድ ኢትዮጵያዊን ጨምሮ አምስት የውጭ ዜጎች ደሞ ታስረው ወደ ዮርዳኖስ እንዲመለሱ እንደተደረጉ ተገልጿል።

@sheger_press
@sheger_press


#ለእሳትነት የቅድስና ማዕረግ የደረሰው አባት

ታላቁ ሊቅ አርእስተ ሊቃውንት ከሚባሉ አባቶች አንዱ ነው። አባቱ ኤስድሮስ እናቱ ኤሚሊያ ይባላሉ። ባልና ሚስት ከተቀደሰ ትዳራቸው አምስት ወንድና አንድ ሴት ልጅ አፍርተዋል። የሚገርመው እህቱ ቅድስት ማቅሪና ገዳማዊት ስትሆን አምስቱም ወንዶች ጳጳሳት መሆናቸው ነው። የሁሉ የበላይ የሆነው ግን ቅዱስ ባስልዮስ ነው። ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ ከሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ሊቃውንት አንዱ ነው። የቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊም መምህር ነው። ቅዱስ ባስልዮስ ገዳማዊ ጻድቅ፣ ብዙ ምሥጢር የተገለጸለት ሊቅ፣ የብዙ ምዕመናን አባት፣ የቂሣርያ ሊቀ ጳጳሳት፣ ብዙ ተአምራት ያደረገና ከከዊነ እሳት ከፍጹምነት የደረሰ ነው። በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳያንን ሆስፒታል ያስገነባ እርሱ ነው።

በርካታ ድርሰቶችም ደርሷል። መጽሐፈ ቅዳሴን ዛሬ በምናውቀው መንገድ ያሰናሰለው እርሱ ሲሆን በርካታ ሥርዓቶች ሰርቷል የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍትንም ተርጉሟል። ቅዱስ ባስልዮስ በቂሣርያ ማዛካ ቀጰዶቅያ ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡ በዛም የረጅም ጊዜ ጓደኛው ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን ተዋውቋል፡፡ ሁለቱም በአቴንስ በ342 ዓ.ም አካባቢ ጀምሮ ለስድስት ዓመት ተቀምጠዋል፡፡ ባስልዮስ አቴንስን በ348 ለቆ ወደ ግብጽና ሶርያ ከተጓዘ በኋላ በሀገሩ በቂሣርያ የሕግ ሥራ በመለማመድና የንግግር ችሎታ ሲያስተምር እንደቆየ ታሪኩ ያስረዳል፡፡ ቅዱስ ባስሊዮስ ጥሩ ተናግሮ የማሳማን ጸጋ የታደለ ነበር፡፡ እርሱ ግን ሕጋዊ የማስተማር ሥራውን ትቶ ሕይወቱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡                                                                                       

ይልቁንም በመንፈሳዊ ትምህርት ተስቦ በ350 ዓ.ም በአስተሳሰብ ከእሱ ጋር የሚመሳሰሉትን  በክርስትና ሕይወት እንዲጓዙ ወንድሙን ጴጥሮስን ጨምሮ ማሰባሰብ ጀመረ፡፡ አንድ ላይ ሆነው በቤተሰቡ ርስት ላይ አኔዚ አጠገብ ገዳም መሠረቱ፡፡ እኅቱ ማክሪናና ሌሎች ሴቶችም ራሳቸውን ለቅዱስ ተግባር በመነሣት ከባስልዮስ ጋር ይተባበሩ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስና ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ የአርያኒዝም የክህደት ትምህርት የቀጰዶቂያን ክርስቲያኖች እንዳይከፋፍል ሲታገሉ ቆዩ፡፡ በኋላም በትልቅ የጉባኤ ክርክር ከታዋቂ አርያናውያን ቴዎሎጂየንና ተናጋሪዎች ጋር ክርክር ለማድረግ ተስማሙ፡፡ በንጉሥ ቫሌነስ ተወካዮች መሪነት ከተደረገው ክርክር በኋላም ጎርጎርዮስና ባስልዮስ አሸናፊዎች ሆነው ወጡ፡፡

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ባስልዮስ የቂሣሪያን ከተማ አስተዳደር ተረከበ፡፡ አውሳቢየስ ግን በባስሊዮስ ፈጣን ችሎታና ዕድገት በማኅበረሰቡ ባገኘው ተቀባይነት በመቅናት ወደ ነበረበት የገዳም ብቸኝነት ኑሮ እንዲመለስ ፈቀደለት፡፡ ጎርጎርዮስ ግን በዚህም በዚያም ብሎ ባስልዮስን እንዲመለስ አሳመነው፡፡ በዚያች ከተማም ለበርካታ ዓመታት ውጤታማ አስተዳዳሪ ሆነ የተደነቀበትን ሥራ ሁሉ ለአውሳብዮስ ተወለት፡፡ በ362 ዓ.ም አውሳቢዮስ ሲሞት ቅዱስ ባስልዮስ እንዲተካው ተመረጠ፡፡ በዛውም ዓመት የቂሣሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነ፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ለሃይማኖቱ ቀናኢ የሆነ፣ በስብከቱ የሚታወቅ ደግና ለሰው አዛኝ ነበረ፡፡ በዚያም ወቅት ድርቅ ባስከተለው ረኀብ ምክንያት በግሉ ምግብና የሚጠጣ ነገር በማዘጋጀት ድሆችንና አቅመ ደካሞችን የሚያበላ፣ ሀብቱንም ድሆች እንዲጠቀሙ በነበረበት ቤተክርስቲያን አካባቢ የሚያድል አባት ነበር፡፡                                   

በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

                     




ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ለሆኑት ዲፕሎማቶች በተሰጠው ማብራሪያ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት አንደኛው የህወሓት ክንፍ ከውጭ ኃይል ጋር ግንኙነት ከመፍጠር በተጨማሪ "ግጭት ለመቀስቀስ ሙከራ እያደረገ ነው" ተብሎ ተወቅሷል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ መንግሥታቸው በትግራይ ክልል የተከሰተውን ወቅታቂ ሁኔታ በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን አመለክተው፤ አንደኛው የህወሓት ክንፍ "ጊዜያዊውን መንግሥት በግልፅ ኃይል ተጠቅሞ ለመናድ እየሞከረ ነው" ነው ብለዋል።

ከቅብር ወራት ወዲህ በትግራይ ክልል የተከሰተውን ውጥረት በተመለከተ ማዕከላዊው መንግሥት በይፋ መግለጫ ሲሰጥ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
BBC

@sheger_press
@sheger_press


ኤርትራ የህወሓትን “የውስጥ የፖለቲካ ሽኩቻ የማባባስ ፍላጎት የላትም” ኤርትራ

ኤርትራ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረውን "የውስጥ ሽኩቻ የማባባስ ፍላጎት የላትም" ሲሉ የሀገሪቱ የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረ መስቀል ትናንት በኤክስ መገናኛ አውታር ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ግንኙነት መሻከር መጀመሩ በተለያዩ አካላት መነገር ከጀመረ ቆይቷል።

@sheger_press
@sheger_press


ማሳሰቢያ‼️

ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች
ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት የዲግሪ ህትመትና የትምህርት ማስረጃ አሰጣጥን በሚመለከት👇

በሀገራችን ባሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተለያዩ ፕሮግራሞች የሚሰጡ ዲግሪዎች ህትመት ወጥ በሆነ መልኩ ደህንነታቸው ተጠበቆ የዲግሪ ማስረጃ/ሰርተፍኬት ህትመት በማዕከል ለማሳተም ታስቧል ፡፡

ስለሆነም ከወዲሁ ለምናደርገው ቅደመ ዝግጅት ይረዳን ዘንድ በዲግሪ የምስክር ወረቀቱ ላይ ሊካተትላችሁ የምትፈልጉትን ሎጎና ሌሎች መካተት አለበት የምትሉትን እንድታካትቱ እና በዩኒቨርሲቲያችሁ በዚህ ዓመት የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉና ለምርቃት የተዘጋጁ የተማሪዎች ዝርዝር በመላክ ህትመቱ የሚፈጸም ሲሆን በቀጣይ ከዩኒቨርሲቲ አመራሮችና ሬጅስትራሮች ጋር በሚኖር ሰፊ የውይይት መድረክ ስለ አጠቃላይ አፈጻጸሙ ውይይት የሚደረግ ይሆናል፡፡

ስለሆነም በ2017 ዓ.ም ተመራቂዎች ጀምሮ ከላይ በተገለጸው አግባብ የሚፈጸም መሆኑን በመረዳት በተቀመጠው አቅጣጫ ተፈጻሚ እንዲሆን አሳስቧል።

@sheger_press
@sheger_press


ጥቆማ‼️

በሀገራችን ታማኝ የዜና ምንጮችን የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናል ነው!

ሊንክ👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


በትግራይ ሕግ እና ስርዓት ማስከበር እንጂ እየተደረገ ያለ መፈንቅለ መንግስት የለም:: ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተቀራርቦ ለመስራት የሚደረግ ግንኙነት ዛሬም ነገም ይቀጥላል።

ስለዚህ መቼ ነው [ወደ አዲስአበባ] የምትሄዱት የሚለው የቀጠሮ ጉዳይ ነው። ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመሆን ነው ግዚያዊ አስተዳደሩን ያቋቋምነው።

በተለይም የፕሬዝደንት ቦታ የሚመለከት ደግሞ ሁለታችን የተስማማንበት ነው የሚሆነው። ሁለታችን ያልተስማማንበት እንደማይሆን ከዚህ በፊትም ተረጋግጦ የቆየ ነው። ስለዚህ በግዚያዊ አስተዳደሩ የሚደረግ ማስተካከያዎች ይሁን የፕሪቶርያው የሰላም ስምምነት መፈፀም የሚያስችለን ግንኙነት ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ይቀጥላል"
- የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል አሰፋ

@sheger_press
@sheger_press


“የፌደራል መንግስት አሁን ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት ብሎ ትግራይ እንደማይገባ ተነግሮኛል ” - ጀ/ል ታደሰ ወረደ ዛሬ ከአዲስ አበባ መልስ የሰጠው መግለጫ

@sheger_press
@sheger_press


ለጥንቃቄ‼️

44 የተለያዩ የገበታ ጨው ምርት ዓይነቶች ሕብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳሰበ፡፡

ባለስልጣኑ በሰራው የገበያ ቅኝት ሥራዎች 44 ዓይነት የምርት መለያ ስም ያላቸው የተለያዩ በአዮዲን የበለፀጉ የምግብ ጨው በሚል ታሽገው ደህንነታቸውና ጥራታቸው ሳይረጋገጥ በተጨማሪም የሀገሪቱን አስገዳጅ ብሔራዊ ደረጃ እና የገላጭ ጽሑፍ ደረጃ ሳያሟሉና ሳይለጥፉ ሲቀርቡ የነበሩ ምርቶች መገኘታቸው ተመላክቷል፡፡

ምርቶቹም የሚከተሉት ናቸው፡-

1. አበሩሰ አዮዳይዝድ ጨው

2. ዛክ የገበታ ጨው

3. ሉሉ የገበታ ጨው

4. ሙሪዳ አዮዳይዝድ ጨው

5. እቱ የገበታ ጨው

6. እቴቴ የገበታ ጨው

7. እፍታ ጨው

8. ኤልሳ የገበታ ጨው

9. ሴፍ  የገበታ ጨው

10. NS አዮዳይዝድ ሳልት

11. ማሚ የገበታ ጨው

12. ሣሊህ  የገበታጨው

13. እማ የገበታ ጨው

14. አዮዲን የገበታ ጨው

15. ቃና የገበታ ጨው

16. ሀርመኒ የገበታ ጨው

17. ውዛት አዮዳይዝድ ሳልት

18. ሐበሻ ባለ አዮዲን ጨው

19. ሪል የገበታ ጨው

20. ሸጋ የገበታ ጨው

21. ጆይ አዮዳይዝድ ሳልት

22. ኮከብ የገበታ ጨው

23. ስኬት የገበታ ጨው

24. ፎር ኤም አዮዳይዝድ ሳልት

25. አዲስ የገበታ ጨው

26. ኤመሬት ጨው

27. አስቤዛ የገበታ ጨው

28. ቶም የገበታ ጨው

29. በረከት የገበታ ጨው

30. ሜናታ የገበታ ጨዉ

31. ቤስት አዮዳይዝድ  ጨዉ

32. አፊአ  የገበታ ጨው

33. ዋን በአዮዲን የበለፀገ የገበታ ጨዉ

34. አቢሲኒያ የገበታ ጨዉ

35. ማሩ የገበታ ጨዉ

36. ባና ኤዳይዝድ ጨው

37. ማራኪ ጨዉ

38. መክሊት የገበታ ጨዉ

39. ዳግም የገበታ ጨዉ

40. አዲስ የገበታ ጨዉ

41. አፍያ ጨዉ

42. ኦማር የገበታ ጨው

43. ገዳ የገበታ ጨው

44. NITSUH IODIZED SALT ናቸው።

@sheger_press
@sheger_press

8.2k 0 131 4 41

ፈረንሳይ ዜጎቿ ከትግራይ ክልል እንዲወጡ አሳሰበች‼️

የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ያለው አለመረጋጋት እየተባባሰ በመሆኑ ፈረንሳዊያን ወደ ትራይ ከመጓዝ እንዲቆጠቡ እንዲሁም አስቀድመው የገቡ ካሉ በአስቸኳይ እንዲወጡ አሳስቧል፡፡

በትግራይ ክልል በህወሃት የአርስበርስ ክፍፍል ምክንያት አለመረጋጋት የተከሰተ ሲሆን በነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የሕወሃት ክንፍ በጊዜያዊ አሰተዳድሩ ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራው ክንፍ ላይ መፈንቅለ መንግስት እየፈጸመ ይገኛል።

@sheger_press
@sheger_press


የሙዚቃ አቀናባሪው ካሙዙ ካሳ የጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ያለውን አድናቆት ገለፀ። በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰፈረው የአድናቆት መልዕክት "ክቡር ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ሆይ ፈጣሪ ካንተ ጋር ነውና ሀገር ወዳድ ልበቀና በሳል እና ጥበበኛ መሪ እንደሆንክ ገና አለም ይመሰክርልሀል እየመሰከርልህም ነው የሀገሬ የኢትዮጵያ መሪ በመሆንህ እኮራብሃለሁ" ብሏል።

በመጨረሻም እውነት ካንተ ጋር ነው ሲል ገልጿል።

@sheger_press
@sheger_press

8.3k 0 13 21 154

የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ 13 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈረደባቸው።

የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፤ ባሳለፍነው ሳምንት በሁለት ክሶች ጥፋተኛ የተባሉት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬ ላይ 13 ዓመት ፅኑ እስራትና 21 ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ፍርድ ማሳለፉን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ቤተሰብ አባል መረጃውን አድርሷል።

ፍርድ ቤቱ የቀድሞዉ ከንቲባ ካቀረቡት 8 የቅጣት ማቅለያዎች 4ቱን በመቀበል እና አራቱን ዉድቅ በማድረግ ነዉ የ13 ዓመት ፅኑ እስራት የፈረደባቸው።

በዚሁ በእሳቸው መዝገብ ተከሳሽ የነበሩት የቀድሞ የሀዋሳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ታርኩ ታመነ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት እነ 41 ሺህ ብር ፤ አቶ ታፈሰ ቱናሻ በ8 ዓመት ከ5 ወር ፅኑ እስራትና 51 ሺህ ብር እንዲሁም አቶ ሰይፉ ሌሊሴ የተባሉ ግለሰብ እንደዚሁ በ8 ዓመት ከ5 ወር እና 76 ሺግ ብር የገንዘብ ቅጣት ፍርድ ተላልፎባቸዋል።

@sheger_press
@sheger_press


#ክብሩና ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል አባት


ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ አባታችን በተወለዱ ጊዜ አንደበታቸው ከምስጋና የተገኘ፣ ስለሀገራችን መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው የጸለዩ፣ ገና በ3 ዓመታቸው በገዳም መኖር የጀመሩና ከማሕጸን ጀምሮ ለመንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የተለዩ፣ ከተወለዱ ጀምሮ እህል ያልቀመሱ፣ በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩ፣ ከጌታችን ጋር መሞት አይገባኝም ብለው የተከራከሩ ታላቅ ቋድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡

አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር የቆዩት ቅዱሳን በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ ይህም ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን እየለመኑ ነው፡፡

በተጋቡ በሰላሳ ዘመናቸው አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ክብሩና ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል ክህነቱ እንደ መልከጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ እንደወለደች መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምም ባረከችው ቅዱሳን መላዕክት ዘወትር ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡

ሕፃኑንም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማሩ አሳደጉት፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ሰጡት፡፡ ፍጹም የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮበታልና ሥራው ሁሉ በዕውቀት የተመላና የተቃና ሆነ፡፡ እንደ ቅዱስ እንጦንስም አስኬማ ሰጡት፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ ወደ ሰማያት አርገው በረከትና ጸጋ የተቀበሉ፣ አጋንንትን የሚያሳድዱበት፣ ድውያንን የሚፈውሱበት ታላቅ ጸጋ ተሰጣቸው፡፡ ከሰው ተለይተው ወደ ጫካ ገብተው ከስድሳ አንበሶችና ከስድሳ ነብሮች ጋር የሚኖሩት አባታችን፣ እንስሳቱ እርሳቸውን የረገጡትን መሬት ልሰው ጠግበው ይኖራሉ፡፡

ሰውነታቸው አንድ ክንድ ከስንዝር በሚረዝም ጠጉር የተሸፈነው አባታችን ወደ ሀገራችን መጥተው ተጋድሏቸውን ቀጠሉ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም ገዳማቶቻቸው ወዳሉባቸው ወደ ምድረ ከብድና ወደ ዝቋላ ተራራ ወሰዳቸው፡፡ በእነዚህ ገዳማት እየተመላለሱ ሲጸልዩና ሀገራችንን ሲባርኩም ኖረዋል፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ በሀገራች ያለውን የኃጢአት ስራ ባዩ ጊዜ በዝቋላ ሐይቅ አንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው መላው ኢትዮጵያን እንዲምርካቸው ጸልየው ቃል ኪዳን ተቀብለዋል፡፡ የመጨረሻ እረፍታቸውም በምድረ ከብድ ገዳም ነው፡፡ ይህ እረፍታቸውም በየዓመቱ መጋቢት 5 ታስቦ ይውላል፡፡ ገዳማትንና ገዳማውያንን እያሰብን ከበረከታቸው እካፈል፡፡
     

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444



19 last posts shown.