#ጥቆማ ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት፣ ለንግድ ባንክ እና ለፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት!
ከ180,000 በላይ ተከታይ ያለው አንድ ቬሪፋይድ የሆነ የቴሌግራም ቻናል ፈጣን የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እየሰበሰበ ይገኛል።
በ15 ቀን ፖስፖርት ለማግኘት 4,500 ብር፣ በ10 ቀን 6,800፣ በ5 ቀን 8,000 ብር እና በ2 ቀን 12,000 ብር በማለት በግለሰብ ስሞች በተከፈቱ የንግድ ባንክ አካውንቶች እየሰበሰቡ ይገኛሉ።
እስካሁን ብቻ በደረሱን ጥቆማዎች ገንዘብ እየተሰበሰቡባቸው ያሉት አካውንቶች "አስረስ" በተባለ ግለሰብ የአካውንት ቁጥር 1000533898908 እንዲሁም 'ህይወት' በተባለች ግለሰብ የአካውንት ቁጥር 1000522976303 ነው።
እነዚህ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ሰራተኛ በመምሰል ግለሰቦችን የሚቀርቡ አጭበርባሪዎች የቴሌግራም አካውንታቸው እውነት እንዲመስል ለቴሌግራም ክፍያ በመፈፀም ቬሪፋይድ አስደርገዋል። ፖስፖርት ለማግኘት በጣም እየተንገላታ ያለውን ህዝብ ታርጌት በማድርግ እየመዘበሩ ይገኛሉ።
የእኔ ጥያቄ...
- እነዚህ ግለሰቦች መቸም የባንክ አካውንት ካለ መታወቂያ አይከፍቱም፣ ህዝብ ዘርፈው ካለተጠያቂነት መጥፋት ወይም መሰወር ይችላሉ?
- ግለሰቦቹስ የኢሚግሬሽን ሰራተኞች ናቸው? (ተቋሙን ለማግኘት ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም)
- የኢትዮጵያ የፋይናንስ አገልግሎት ደህንነት እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲህ ህጋዊ የባንክ አካውንቶችን ተጠቅመው ህዝብ በሚዘርፉ ዙርያ ምን እየሰራ ነው?
- የኢሚግሬሽን ቢሮውስ ትክክለኛ የማህበራዊ ገፆቹን ደጋግሞ በማስተዋወቅ ለምን ይህን ወንጀል አይከላከልም?
(ለማንኛውም ትክክለኛው እና በድረ-ገፁ ላይ የተቀመጠው የኢሚግሬሽን ቴሌግራም አካውንት ይህ ነው:
https://t.me/ICS_Ethiopia)
Via Ethiopia Check
@sotubee #sotubee #ሶቲዩብ