ወሀብያና &አሻኢራ
ወሀብያ: አላህ ሰማይ ላይ ለመኖሩ ብዙ ማስረጃ አለ።
አሻኢራ :ሁሉንም ተራ በተራ እንመልከታቸው ምን ትላለህ?
ወሀብያ:በደስታ :
አሻኢራ:የመጀመሪያ መረጃህን ጥቀስ
ወሀብያ :አላህ ሰለ ኢሳ ሲናገር እንዲህ ይላል
بَل رَّفَعَهُ اللَّهُ إِلَيْهِ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَزِيزًا حَكِيمًا (158"ይልቁኑ አላህ ወደሱ አነሳው"
ቁርአን አላህ ሱወ ኢሳን ወደሱ እንዳነሰው ይነግረናል ኢሳ ደግሞ የተወሰዱት ወደ ሰማይ ነው ስለዚህ አላህ ያለው ሰማይ ላይ ነው።
አሻኢራ:ሲጀምር አላህ አርሽ ላይ ነው ያለው ወይስ ሰማይ ላይ?
ወሀብያ:አርሽ ላይ
አሻኢራ:ስለዚህ አንተ የጠቀስከው ማሰረጃ የሚያገለግለው ሰማያ ላይ ቢኖር ነበር።
ወሀብያ:ማንኛውም ከፍ ያለ ነገር ሰማይ ይባላል ስለዚህ አርሽ ሰማይ ሊባል ይችላል።
አሻኢራ :ሲጀምር ሰማይ የሚል ቃል አሁን የጠቀስከው አንቀፅ ላይ የለም ኢሳ ዐስ ደግሞ በሀዲስ እንደተገለፀው ሁለተኛ ሰማይ ላይ ናቸው ታዲያ አላህ ሁለተኛ ሰማይ ላይ ነው?
ወሀብያ:በጭራሽ አላህ ያለው አርሹ ላይ ነው። ግን አንቀፁ ላይ ወደሱ اليه ብሏል
አሻኢራ :አሁን አንተ አላህ ኢለይሂ ወደሱ የሚል ቃል ስለተጠቀመ ነው የዚ አይነት አገላለፅ ግን ቁርአን ብዙ ቦታ ተጠቅሞል ትርጓሜው ግን አንት እንዳልከው አደለም
ለምሳሌ
ففرو إلى الله
"ወደ አላህ ሽሹ"
إني ذاهب إلى ربي سيهدين
እኔም ወደ ጌታይ ተጓዥ ነኝ ይመራኛልም
ሰው ሲሞት እንዲህ እንላለን
إنا لله وإنا إليه راجعون
"እኛም የአላህ ነን ወደሱ ተመላሿችነን"
እነዚህ ሁሉ አንቀፆች ወደ አላህ መሄድ የሚያመላክቱ ናቸው በጭራሽ ግን አንተ የምትለው ትርጉም የለውም።
ስለዚህ የጠቀስከው ማስረጃ መረጃ ሊሆን አይችልም።
ኢብራሂም ዐለይሂ ሰለም ወደ ጌታይ ተጓዥ ነኝ ሲሉ ወደ አዘዛቸው ቦታ ማለታቸው ነው እንጂ ወደላይ ማለት አደለም። አላህም ኢሳን ወደርሱ አነሳው ማለት ማንም የማይደርስበት ከአላህ ውጪ ማንም ሊደርስበት ወደ ማይችል ቦታ (ሰማይ)ወሰደው ማለት ነው።
በሌላ ማስረጃ እስክንገናኝ ደና እደር
https://t.me/sufiyahlesuna