ሱፊይ አሕለሱና ወልጀመዐህ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Transport


╔════◈◉◈════╗
                     أهل السنة والجماعة
            ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⚪️አህለሱና ወልጀመዓህ ስንል የሰለፎችንና የኸለፎችን የግንዛቤ ዘይቤ የሚከተሉ ማለት ነው።
🔴ይህ መንገድ ሌሎች የኢስላም አስተሳሰብ ተከታዮችን አያከፍርም
🔎አመላካች የሰሪን ምንዳ ያገኛልና ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩልን
╚════◈◉◈════╝

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Transport
Statistics
Posts filter


እነሆ አንድ ሶስተኛውን የታላቁ እንግዳችንን ቀናቶች አሰናብተን ወደ 11 ቀናት ተሸጋግረናል ፤ ኢላሂ እየሞከርን ነው እና አግዘን 🤲

🌹 ያ ረመዷን 🌹


ብዙ ክርስቲያኖች ሙስሊሙች ጀነት ገበተው 70ሺህ ሚስት ይሰጣቸዋል ምናምን እያሉ ያለግጣሉ 70ሺህ ሴት ቢሰጣቸው የሚጠሉ ይመስል😄😄😄😄

ቀልዱ ቀልድ ነው ግን ሲጀመር በዚህ ጉዳይ ለመጨቃጨቅ ቅድሚያ በአላህ በመልክተኞች በቁርአንን ማመን አለብህ በዚህ ሳታምን አሁን ያነሰህው ነጥብ ላይ ብንጨቃጨቅ ጥቅም የለውም። ምክንያቱም እኔም አንተም ገነተ (ጀነት)ደርሰን አልመጣንም ከህዋስ ውጪ ስለሆነ ነገር ነው የምንወያየው። እኔ በቁርአን በመልክተኛው ስለማምን እሳቸው በነገሩኝ ሁሉ አምኜ ተቀብያለሁ። እናንተ ደግሞ በመልክተኛው ስለማታምኑ ይህን ነገር አትቀበልም አለቀ።


ግን እስኪ በሚገባህ ቋንቋ እናውራ የሆነ ግለሰብ የሆነ ስራ እንድትሰራ አዘዘህ በሚገባ ስራህን ሰርተህ ስጨርስ ዱባይ ወስዶ በሚገርም ሆቴል ውስጥ ዞሪያህ በሴቶች ተከበህ የፈለከውን እየበላህ እየጠጣህ እንድታሳልፍ ቢያደርግልህ ክፋቱ ምንድነው ⁉️

✍ዘ.ሐ




የአላህ ስራ ይገርመኛል

ኢኽዋን በሙፍቲ ሀጂ ዑመር ላይ ህፃናቸውን፣ እብዳቸውን፣ የአረብ ሀገር ገርዳሜዎችን አንስተው እንዳላሰደቡ ፤ ዛሬ ላይ መድኸሊን ሾመባቸው ፤ ከእነሱ የባሱ ከእኔ ውጪ የሚሉ ቀስ እያሉ ኢኽዋንን ከጫወታ እያወጡት ነው ፤ ነገ ታዘቡኝ ኢኽዋን የሚባል ለታሪክ አይቀርም ፤ አልጀዛኡ ቢጂንሲ አመል(ምንዳ የስራ ቢጤ ነው)💀💀💀💀 ለማንኛውም በረመዳን በደንብ ዉሃ መጠጣት አትርሱ

✍ዘ.ሐ




ሀሰተኛ ነብያት ሀሰተኛ ክርስቶሶች ድንቅን ተዐምር ማሳየት ይችላሉ ይላል መፅሐፍ ቅዱስ የኛ ሀገር ነብይ ተብየውች እንዃን እውነተኛ ነብይ ሊሆኑ ይቅርና እንደ ሀሰተኛ ነብያት እራሱ ተዓምር ማሳየት ሳይሆን ሚችሉት ድራማ መስራት ነው። እስኪ እውነተኛው ቀርቶ ውሸተኛ ነብይ ሁኑ😂😂😂

✍ዘ.ሐ


🌹ሱሁር ለፈጅር ሶላት መነሳት እንደምንችል ያሳየናል።
🌹ተራዊህ የለሊት ሶላትን መስገድ እንደምንችል ያሳየናል።
🌹ፆም ከስሜታችን በተቃራኒ ራሳችንን መቃወም እንደምንችል ያሳየናል።
🌹የረመዷን ወር በኢማናችን ላይ ግዜያዊ ጭማሪ ሳይሆን..ይህንን በየቀኑ ማድረግ እንደምንችል ያሳየናል።

♦️✨«በዚህ ዐለም ላይ እንደረመዷን ኑር..በአኺራ እንደ ዒድ ትኖራለህ..!!»✨♦️


የአሏህ መልእክተኛ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ ይላሉ :-

“ ድሀዎችን ፈልጉልኝ ፤ ሲሳይን የምትለገሱትና ጠላትም ላይ ድልን የምትቀዳጁት በድሀዎቻችሁ አማካኝነት ነው “ ።

አቡ ዳውድ


አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏሂ ወበረካቱህ ፤ ኡስታዝ ስላልተመቻቸው የዛሬ አውዶሁል በያን ደርስ አይኖርም


♦️✨ሀቂቃ የሠይዳችንﷺ ሙሀባ ያለው እና በእርሳቸው ያመነ ክብራቸው መነካቱ ያሳምመዋል እንጂ ከእርሳቸው ፖለቲካን አስበልጦ ዝም አይልም!!

«ሠውየው ለሠይዳችንﷺ ያለው መሀባ ምልክቱ ከቻለ በየቀኑ ካልቻለ በ3ቀኑ እርሳቸውን አስታውሶ/ናፍቆ ስቅስቅ ብሎ ማለቀሱ ነው» ይላሉ ሸይኽ ሀቢብ ዑመር(ሀፊዘሁሏህ)

የሚገርመኝ ሠይዳችንንﷺ ተሷድቧል በተባለው ሠው ዙርያ ለገደብ አላፊነቱ እርምጃ ይወሰድበት ሲባል አይ ልክ ነው የሠራው እያሉ ካፊሮቹ እንኳ ለዛ ለቆሸሸው አንደበቱ ሽፋን እየሠጡት ነው።

«መጅሊሡ ምን እየሠራ ነው?» ብለው ወንድሞች ሲጠይቁ..ምን እየሠራ እንደሆነ ምን አገባችሁ ሚል ኮመንትም አየሁ ..ወሀብያ ለነብዩﷺ ሳይሆን ለመጅሊሱ ነው ሽፋን ሚሠጠው

⛔️አሁንስ የመደራጀት /ራስን ችሎ ተቋም የመሆን አስፈላጊነት ገባህ?


ሙጀሲማን በማክፈር ዙሪያ በኡስታዝ ፈኽሩዲን እና በጀምዒያው ኡስታዝ አብዱሏህ ጎበዜ መካከል የተደረገ ውይይት

በውይይቱ
————

👉 ከኛ በኩል ቀጣይ ነጥቦች ተነስተዋል :-

# የአሽዐሪያ ሚዛን የሚደፋው ቀውል ሙጀሲሞችን በሁለት ከፍሎ መመልከት ሲሆን እነርሱም ሙጀሲም ሙሶሪህና ገይሩ ሙሶሪህ ይሰኛሉ

# ሙጀሲም ሙሶሪህ ( ተጅሲምን ከነ መልለያዎቹና መግገለጫዎቹ ) ለአሏህ የሚያፀና ሰው በመክፈሩ ላይ ልዩነት እንደሌለ

# ሙጀሲም ገይሩ ሙሶሪህ
አሏህ ጂስም ነው ግን እንደጂስም ያልሆነ የሚል እንዲሁም ጂስም የሚለውን ቃል ለአሏህ ከተጠቀመ በኃላ የተጅሲምን መግገለጫዎች ውድቅ ያደረገ ሰው በመክፈሩ ላይ በዑለሞች መካከል ልዩነት እንዳለና ከትላልቅ የዐቂዳ ዑለሞቻችን የመጣው እንዲህ አይነት ሰዎችን አለማክፈር ነው ።

# ሙጀሲማን በደፈናው ስለማክፈር የመጡ የዑለሞቻችን አቋሞች ሙጥለቅ እንደሆኑና “ ሙጀሲም ሙሶሪህን “ እንደፈለጉበት እኚህን አቋሞች ያስተላለፋልን ዑለሞች ግንዛቤ እንደሚያስይዝ

# ውይይቱ መመርኮዝ ያለበት በኛ የግል ግንዛቤ ሳይሆን በዑለሞቻችን ግንዛቤ እንደሆነ

👉 ከጀምዒያ በኩል

# የጂስምን ትርጉም እያወቀ ለአሏህ ጂስም የሚለውን ቃል የተጠቀመ ሰው ይከፍራል ፤ ከዚህ ቃል ሌላ ትርጓሜ ፈልጌበት ነው ቢል ቦታ አንሰጠውም ( አረቦች ሆነው ለአሏህ ጂስም የሚለውን ስያሜ የተጠቀሙት ከራሚያዎችን ያላከፈሩትን ታላቁን የኢማም ራዚንና የሌሎች ዑለሞችን አቋም ረድ ማድረግ አልቻሉም)

💢 ርእሱ “ ሙጀሲማን በማክፈር “ ዙሪያ ሆነ ሳለ ልክ እኛ ተጅሲምን ለአሏህ ማፅናት እንደሚቻልና ምንም ችግር እንደሌለው አድርገን እንደምናስተምር አድርጎ ረዥም ስብከት በማድረግ ከአውድ መውጣት

💢 የዑለሞችን ንግግሮች በዑለሞች ግንዛቤ ከመረዳት ይልቅ የራስን ግንዛቤ አስቀድሞ አንድ ሀሳብ ላይ ክችች ማለት ወዘተ ይገኙበታል

♦️ማጠቃለያ

እንደሚታወቀው በጀምዒያዎች አቋም መሰረት “ ሙጀሲማን ያላከፈረ እንደውም ለማክፈር የተጠራጠረ እንኳን እርሱ ይከፍራልና “ ፤ ኡስታዝ አብዱሏህ ሙጀሲሞቹን ከራሚዮችን ሙነዚህ ናቸው ብለው እነርሱን ከማክፈር ሲሸሹ በመርሀቸዉ መሰረት ራሳቸውን ያከፍሩ ይሆን ⁉️⁉️
https://t.me/sufiyahlesuna


ከረመዷን በፊት “ ሙጀሲማንበማክፈርና እነርሱን ያላከፈረን አሽዐሪ በማክፈር “ ዙሪያ ጀምዒዮችን ለውይይት ለመጋበዝ አሰበን ፤ አሁን ወቅቱ ረመዷን እንደመሆኑ መጠን የወሀቢያ ረብሻ እንደሚበዛ ፤ በዚህ ወቅት ደግሞ ከነ ልዩነታችን አንድ ሆነን እነርሱን መመከት ስለሚኖርብን ከረመዷን በኃላ እናድርገው ብለን ተስማምተን ነበር

ሆኖም ትላንትና ከወሀቢዮች ጋር ቢድዐን በተመለከተ ከተካሄደ የላይቭ የቲክቶክ ውይይት በኃላ ጀምዒዮች በራሳቸው ጊዜ ለውይይት መጥተው ቀጣዩ ውይይት ተደርጏል

ከጀምዒያ ጉልሀኖች መካከል ለውይይት ዝግጁ የሆነ ካለ በራችን ሁሌም ክፍት እንደሆነ ልናሳውቅ እንወዳለን


🤎 ኢላሂ
እንደ ንጋት ጀምበር ቀልባችንን በረመዷኑ የሚፀዳ አድርግልን 🩵




“ ከራሚያዎች ሙነዚህ ናቸው “ እስኪል ድረስ አንተፋተፈውኮ

ጀግናችን


ራስ ምታት
🛑🛑🛑

“ ምንኛ ያማረች ቢድዐ “
     ሰይዱና ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ

ዘኪ :- ሰይዱና ኡመር ረ.ዐ ኒእመቱል ቢዱአቱ ሀዚሂ (ምነኛ ያማረች ቢድዐ ነች) ብለዋል ምን ትላለህ ???

ወሀብያ: - በቋንቋ ደረጃ ነው ቢድዐ ያሉት

ዘኪ :- በቋንቋ ደረጃ ቢድዐ  ምንድ ነው?

ወሀብያ:- ከዚህ በፊት ምንም አይነት ምሳሌ የሌለው ወይም ተሰርቶ የማይታወቅ ነገር ነው

ዘኪ:- ስለዚህ ሰይዱና ኡመር  ረ.ዐ በዲን ላይ የማይታወቀ አዲስ ነገር ነው ያመጡት ማለት ነው ⁉️ እንዳንተ አባባል

ወሀብያ :- ነብዩ  ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም  ቂያም አልለይል  ሰግደዋል አዲስ ነገር  አይደለም

ዘኪ :- እሺ ታዲያ ለምንድ ነው ሰይዱና ዑመር “ ቢድዐ “ ብለው የሰየሙት ??? አንተ ደግሞ በቋንቋ ደረጃ ነው ያልከው : ነብዩ ዐለይሂስሰላት ወሰላም የሰሩትን  ስራ ከሆነ ያስቀጠሉት ለምን ቢድዐ  ብለው ይጠሩታል ???

ወሀብያ :- ወላሂ ግራ አጋባሀኝ

ዘኪ :- አብሽር እንቀጥልማ ፡ ነብዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም  በረመዳን የሰገዱት የትኛው ወቅት  ላይ ነው ??

ወሀብያ :- ለሊት ላይ ነው የሰገዱት

ዘኪ :- ትክክል ፡ ኡመር ረ.ዐ  የሰገዱትስ ??

ወሀብያ:- ከኢሻ በኃላ

ዘኪ:- እሺ ነብዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ስንት ረከአ ነው የሰገዱት ???

ወሀብያ:- 11ረከአ

ዘኪ:- ሰይዱና ኡመር  ረ.ዐ ስንት ረከአ ነው የሰገዱት?

ወሀብያ:- 23 ረከአ

    ( እዚህ ጋር ልብ ልንለው የሚገባ ጉዳይ አለ : እርሱም የወሀቢዮች ሙሀዲስ ተብዬው አልባኒና መሰሎቹ ተራዊህ ከ 11 ረከአ በላይ መጨመር ሱናን መቃረን ነው ብለው ያምናሉ ፡ በእጅ አዙር ሰይዱና ኡመር እነርሱ ዘንድ ሙብተዲእ ናቸው ፡ ሀገራችንም 11 ረከአ የሚሰገድባቸው መስጂዶች የዚህ አስተምህሮት ውጤቶች ናቸው )

ዘኪ :- ነቢያችን ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ተራዊህ የሚባል ስም ያውቁ ነበር ??

ወሀብያ:- አይ ፡  ሰይዱና ኡመር  ረ.ዐ ናቸው ተራዊህ ያሉት

ዘኪ :- ነብዩ ዐለይሂስሰላት ወስሰላም  በጀመዐ ሰግደውታልን ??

ወሀብያ :_ እርሳቸው ሳያውቁ ሰሀቦች ከኃላቸው ሰገዱ እንጂ ጀመአ ሰብስበው አልሰገዱም ፡  ኡመር ረ.ዐ ናቸው ጀመአ እንዲሰበሰብ አድርገው በጀመዐ ያስጀመሩት በመስጂድ ውስጥ ኢማም አድርገው።

ዘኪ :- ሰለዚህ የሰይዱና ኡመር ረዲየሏሁ ዐንሁ  ሰላት ከነብዩ ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ሰላት ጋር በብዙ ነገር ይለያል

✅ በረመዳን የተሰገደው ሰላት በሰይዳችን ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለምና በኡመር ረ.ዐ መካከል :-

💠 ነብዩ ሰ፡ዐ፡ወ የሰገዱት 11 ረከአ    
💠 ሰይዱና ዑመር 23 ረከአ
💠 የነብዩ ሰ፡ዐ፡ወ ሰላት አልለይል የሰገዱት የለሊቱ መጀመሪያ : መሀከልና መጨረሻ ላይ ነው
💠 ሰይዱና ዑመር ከዒሻእ በኃላ
💠 ነብዩ ሰ፡ዐ፡ወ የሰገዱት ብቻቸውን
💠 ሰይዱና ዑመር ጀመዐ ሰብስበው


🟢 ስለዚህ የተራዊህ ሰላት ከዒሻእ ሰላት  በኃላ፣በጀመዐ ፣መስጂድ ውስጥ ፣፣23 ረከዓ ወዘተ ሆኖ መሰገዱ  በሰይዱና ኡመር ረዲየሏሁ ዐንሁ የተጀመረ ስለሆነ ነው  ሰይዱና ኡመር “ ምነኛ ያማረች  ቢድአ  ናት “ ሲሉ የጠሩት።

ወሀቢያ :- አሁን ግልፅ እየሆነልኝ

ዘኪ :- “ እየሆነልኝ “ ??? ገና ሙሉ በሙሉ አልሆነልህም ማለት ነው ?? አብሽር ወንድሜ ሸይኾችህ አእምሮህ ላይ የደራረቡብህን ድሪቶ አውልቀህ ጣልና ሀቅን ፈልግ

https://t.me/sufiyahlesuna


አንድ ጨንገሬ ዲያቆን ስለ ነብዩ ሊያወራ ይፈልጋል። እኔም ነብይህ ማናቸው የሚለውን የታላቁ አሊም የአሊ ጁማዐ ኪታብን ልጋብዛቹ




የሀበሻ ሰው ዐሊሞች ፊት ፈትዋ ሲሰጥ :-

“ አፍው በሉኝና ከእርሶ በላይ ባላውቅም ይህ ነገር የሚቻል አይመስለኝም ወይም ይህ ነገር ሀላል ነው “

👉 እውነት ከእርሳቸው በላይ እንደማታውቅ ካመንክ ዝምምምምም በል ፤ ያልገባህን ጠይቅ እንጂ ዑለማእ አጠገብ ፈትዋ አትስጥ


Video is unavailable for watching
Show in Telegram

20 last posts shown.