የአማራ ፋኖ በጎጃም የ24 ስዓት አበይት ሁነቶች!!
===ሀ/ አውደ ውጊያዎች
1/ 1ኛ ክፍለጦር ኮ/ል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ በሜጫ ወረዳ ብራቃት ጋፊት ገብርኤል በተባለ ቦታ ሰፍሮበት የነበረውን ካንፕ መቆጣጠር ችሏል።
2/ ሀዲስ አለማየሁ 7ኛ ክፍለጦር አባይ ብርጌድ እና የክፋለጦሩ ተወርዋሪ ሃይል ደብረማርቆስ ቁይ መገንጠያ ላይ የነበረውን የአብይ አህመድ አሸባሪ ሃይል በደፈጣ ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።
3/በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለጦር የሶማ ብርጌድ የብልፅግና ተጠባባቂ ሃይል በመሆን ያገለግሉ የነበሩ የአረጋ ከበደ እና ሸገው ምናለ ቤተሰቦች ከፋኖ ጋር ሁኑ ተብለው ከአመት በላይ ቢጠየቁም እንቢ ብለው የነበር በመሆኑ ህግ ለማስከበር እቅስቃሴ በማድረግ 6ቱን በመማረክ ፣7ክላሽ ፣1ኢንፎርቲ እና የበርካታ ተተኳሽ ሲማረኩ ቀሪዎቹ ሩጠው መከላከያ ገብተዋል።
4/ በ5ኛ ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም ክፍለጦር ወደ ገጠሩ ክፍል እወጣለሁ ያለው ያሰበው አሸባሪው ሃይል በጀግኖቹ ሲቀጠቀጥ ውሏል። ከሽንዲ የተነሳው አሸባሪ ሃይል አስፍቶ ቢንቀሳቀስም ወላውሊት፣ ቆጥላን ፣ሎማን እና አንበር ላይ ከፍተኛ ምት ደርሶበታል።
=====ለ/ አቅምን የመገንባት ስራዎች ተሰርተዋል።
በ2ኛ ተፈራ ዳምጤ ክፍለጦር ደጋዳሞት ብርጌድ አመራርን የማብቃት ስልጠና እና የቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ተችሏል።
====ሐ/ ህዝብን የማንቃትና ማህበረሰባዊ ችግሮችን መፍታት
የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለ ጦር በአዋበል ወረዳ የየሰንበት ቀበሌ እና ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር የምክክር መድረክ አዘጋጅቶ ህዝብ እና ፋኖ ያለውን መስተጋብር:የጎበዝ አለቆች የስራ እንቅስቃሴ እና ህዝብ ለፋኖ እያደረገ ያለውን ድጋፍ በተመለከተ አመርቂ ውይይት አድርጓል።
የአማራ ፋኖ በጎጃም
አዲስትውልድ ፣አዲስ!! አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!
ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!