ሰበር ዜና ጥብቅ ምስጥር!!!💥
የአብይ ከሚድያ መጥፋት -ምንስ ተፈጥሮ ነው??
ካሜራ ቀደዳ የሚወደው የጨቋኙ አገዛዝ መሪ ከካሜራ እይታ ከራቀ ድፋን ሶስት ሳምንታት ተቆጠሩ። በበዓለ ሲመታቸው ወጥተው “እኛ በከፍታ ላይ ነን!” “ማንም አይገለብጠንም!” የሚለውን መፈክር ሳያሰማ ቀርቶዋል!
እዚህ ላይ አንዳንዶች የኢሳያስን ምሳሌ እየጠቀሱ ከሚድያ መጥፋት ከኢሱ የለመደው አዲስ ጨዋታ ነው ሊሉ ይችላሉ። ነገር ግን የአብይን ባህሪ ላወቀና ሚድያ ላይ ላለመጥፋት የሚያደርጋቸው አነጋጋሪ ነገሮች ላስተዋለ፦
ለአብነት ያህል “ድሮን ሰራሁ!” “መሳሪያ መሸጥ ጀመርን”፣ “በስንዴ ምርት ከአፍሪካ አንደኛ ነን!” “የኳስ ጨዋታው”፣ “ሽንኩርት እንጂ ዶሮ እየበላችሁ አይደለም”፣ ጉብኝቶቹ የሚያሳዩት ከሰዉ አዕምሮ ላለመውጣት የሚያደርገው መፍጨርጨር ኹኖ ሳለ ዛሬ ላይ ይህንን ትልቅ የበዓለ ሲመት ዕድል አግኝቶ እንዴት ሳይታይ ቀረ?
ግን ምን ኾኖ ይሆን? እንደ መለስ ዜናዊ ሞቱን በኢቲቪ በሰበር ዜና ልንሰማው ይሆን እንዴ?? አንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ መረጃዎችን ከውስጥ የደህንነት አካላት በትንሹም ቢሆን ፈልፋላ ሰብስባለች አብራቹህን ቆዩ!!
የብልፅግና አሸባሪ ቡድን መሪ አብይ አህመድ ባለፉት ጥቂት ወራት ከፍተኛ የጤና እክል ገጥሞት እንደነበረ አሁን ላይም እንዳገረሸበት አንድ አምሐራ ዕዝ ሚድያ ከተለያዩ አካላት ለማወቅ ችላለች። ለአገዛዙ ቅርብ ከሚባሉ ሰዎች ለማወቅ እንደተቻለው አብይ ክብደቱ በከፍተኛ ሁኔታ እንደቀነሰ፣ ከጀርባው ያለው የጭንቅላቱ ጠባሳ በከፋተኛ ሁኔታ እየሰፋ እንደሄደ፣ ጸጉሩ እጅግ ሲበዛ እየሳሳ እንደሄደ፣ ከፋተኛ የሳይኮሎጂ ሀኪሞች እንዳደረሱን መረጃ ከሆነ መረጋጋት እንደማይታይበት መቅበዝበዝ እንደሚያበዛ ለአንድ አምሐራ ዕዝ ሚዲያ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ከፋተኛ የሳይኮሎጂ ሳይካትሪስት ሹክ ብሎናል። እንቅልፍ የለውም ወይም ወዳጆቹ እንደሚሉት ስልጣኔን በሌሊት ይነጥቁኛልብሎ ስለሚፈራ ሌሊት አይተኛም። ከተማውን ይዞራል። ስለዚህ ቀን ለመንቃት ሲል ከደቡብ አፍርካ ያስመጣው ሬድ ቡል (red bull) አብዝቶ ይጠጣል (የአገር ውስጡ ሬድ ቡል ይመርዙታል ብሎ ይፈራል)።ቀንም ላይ ስልጣኔን አጣለሁ ፍራቻው ሰንቆ ስለሚይዘው ሜክሲኮ አካባቢ በሚገኘው የድሮን መቆጣጠሪያ ክፍል በመግባት አዲስ አበባን በድሮን ይቃኛል። 67 የሚደርሱ ጠባቂዎቹንም ቀይሯል።አሁን ላይ ማንንም አያምንም።
አንዳንድ በከፋተኛ ጥንቃቄ የጠየቅናቸው የቅርብ ሰዎች ደግሞ የአብይ ችግር ቀድሞ ያደረገው የአዕምሮ ቀዶ ጥገና ውጤት ነው ይላሉ። ከአመታት በፊት በዱባይ የተደረገለት ቀዶ ጥገናው በጊዜው የተሳካ ቢሆንም አሁን ላይ መልሶ ሳያገረሽበት አይቀርም የሚል መላ ምት ያስቀምጣሉ። አብይ ጠቅላይ ሚኒስቴር ከመሆኑ በፊት አዲስ አበባ በሚገኘው የኮርያ ሆስፒታል ከጭንቅላቱ ላይ ከፋተኛ የሆነ የረጋ ደም/ኢንፌክሽን ይመጠጥለት ነበር። ጠቅላይ ሚኒስቴር ከሆነ በኃላ ነው ወደ ዱባይ በመሄድ ዘላቂ መፍትሄ ለማግኘት ቀዶ ጥገና ያደረገው።
አብይ የሚተካው ምትክ ወይም ወራሽ አላዘጋጀም። ተተኪ የሌለው መሪ ደግሞ ከስራው ቦታው አይጠፋም። የጠፋ ጊዜም ትቶት በሄደው ላይ ሁሉም እንዲጣሉና እንዲጫረሱ ያደርጋል። ይህን የሚያደርግበት ዋንኛ ምክንያት ከሞተም በኃላ “አሁን መለስ ዜናዊ ይሻል ነበር እንደምንለው አብይ ከሱ የባሰ ሰው በመተካት አብይ ይሻል ነበር እንዲባል ይፈልጋል። “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው አህያ” መሆኑ ነው!
የአብይ መጥፋት ለሚቀጥሉት ሳምንታት ከቀጠለ በብልጽግና ቤት ውስጥ መናቆር የሚጀምር መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው። ለምን ቢባል ባንዳው ተመስገን ጥሩነህም ሆነ አደም ፋራህ ይህን የብልጽግና ስብስብ የሚመሩበት ስብዕናና እውቀት የላቸውም።
የኦህዴድ ስብስብ የራሱ ሰው ወደፊት እንዲመጣ ይፈልጋል። ይህም በኦህዴድ ውስጥ ሽኩቻ ይፈጥራል። በዚያ ላይ አሁን በስልጣን ላይ ያሉት የኦህዴድ ስብስቦች እርስበርሳቸው የሚጠላሉ ናቸው። ሽመልስና አዳነች አይዋደዱም። ፊልድ ማርሻል ብርሀኑና የአየር ኃይሉ ይልማ መርዳሳ እሳትና ጭድ ከሆኑ ሰነባብተዋል። ሁላቸውም የሚያጋምዳቸው ኃይል ቢኖር አብይ፣ የዘረፉት ሀብትና የበደሉት ህዝብ ተጠያቂ ላለመሆን ብቻ ነው።
በዚህ ሁኔታ ብልጽግና በስልጣን የመቆየቱ ነገር አጣብቂኝ ውስጥ ይገባል። ስለዚህ የመከላከያ ጄነራሎች ወደፊት የሚወጡበት አጋጣሚ ከፍ ይላል። ይህ የሚሆንበት ዋነኛ ምክንያት የአብይ መጥፋት መከላከያን ያፈርሰዋልና። ለምን ቢባል በአሁን ሰዓት መከላከያ እየተዋጋ ያለው የአብይን ጦርነት እንጂ ለኢትዮጵያ ልዑላዊነት ባለመሆኑ ነው። በዚህን ጊዜ እንደ TDF ፋኖና OLA ያሉ ኃይሎች ውጊያቸውን አጠናክረው ከተሞቹን የሚይዙበትና የሚያስተዳድሩበት እንዲሁም ወደ አዲስ አበባ የመምጣት ዕድል ይፈጠርላቸዋል።
የወገን ሃይል/የአማራ ፋኖ በጎጃም፣የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፣የአማራ ፋኖ በወሎ(ቤተ~አምሐራ)፣የአማራ ፋኖ በሸዋ በፋጥነት የአንድነት ምስረታውን ማፋጠን ይኖርባቸዋል፤ ካለዛ ነገሮች በፋጥነት አቅጣጫቸውን ይስታሉ።
ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!