Forward from: TIKVAH-ETHIOPIA
#እራሳችሁን_ጠብቁ !
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት አሁንም የጤና ስጋት ሆኖ ቀጥሏል አሉ።
ዶ/ር ሊያ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ ዓለም አቀፉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዛሬ ሲከበር ነው።
አጠቃላይ ህዝቡ፣ ሁሉም ተቋማትና የሚመለከታቸው አካላት ስርጭቱን ለመግታት በትብብር አንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አሁን ላይ ኮቪድ-19 ስርጭት የተስፋፋበት ወቅት በመሆኑ ድርብ ስራና ሃላፊነትን ይጠይቃል ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ፣ በጋምቤላ ክልል እና ከተሜነት በተስፋፋባቸው ሌሎች አካባቢዎች የኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭት እየጨመረ መምጣቱን ገልፀዋል።
በግንባታ ቦታዎች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተመሳሳይ የስርጭት መስፋፋት መኖሩን ጠቁመዋል።
ዶክተር ሊያ ፥ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች የህክምና ክትትል ማድረግ እና መድሃኒት በአግባቡ መውሰድ እንዳለባቸው መክረዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ቫይረሱ በደማቸው የተገኘባቸው ግለሰቦችን እና በቫይረሱ ምክንያት ወላጆቻውን ያጡ ህጻናት እና አረጋዊያንን በመንከባከበ የህብረተሰቡ ትብብር መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል - ENA
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በኢትዮጵያ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት አሁንም የጤና ስጋት ሆኖ ቀጥሏል አሉ።
ዶ/ር ሊያ ይህን ያሉት በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ ዓለም አቀፉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዛሬ ሲከበር ነው።
አጠቃላይ ህዝቡ፣ ሁሉም ተቋማትና የሚመለከታቸው አካላት ስርጭቱን ለመግታት በትብብር አንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
አሁን ላይ ኮቪድ-19 ስርጭት የተስፋፋበት ወቅት በመሆኑ ድርብ ስራና ሃላፊነትን ይጠይቃል ብለዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ፣ በጋምቤላ ክልል እና ከተሜነት በተስፋፋባቸው ሌሎች አካባቢዎች የኤች አይቪ ቫይረስ ስርጭት እየጨመረ መምጣቱን ገልፀዋል።
በግንባታ ቦታዎች እና ኢንዱስትሪ ፓርኮች ተመሳሳይ የስርጭት መስፋፋት መኖሩን ጠቁመዋል።
ዶክተር ሊያ ፥ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች የህክምና ክትትል ማድረግ እና መድሃኒት በአግባቡ መውሰድ እንዳለባቸው መክረዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ቫይረሱ በደማቸው የተገኘባቸው ግለሰቦችን እና በቫይረሱ ምክንያት ወላጆቻውን ያጡ ህጻናት እና አረጋዊያንን በመንከባከበ የህብረተሰቡ ትብብር መጠናከር እንዳለበትም አሳስበዋል - ENA
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia