🫴አንዳንዶቹ ለምን በአምስት ተከላካይ ይጫወታል ይላሉ አንዳንዶቹ ለቡድኑ ድክመት ተጠያቂ ሲያደርጉት አያለሁ
በመጀመሪያ አንድ ምናገረው ነገር በ wingback መጫወት በአምስት ተከላካይ ተጫወተ አያስብልም ኳስ ሲያጡ አምስት አደለም አስራ አንዱም በራሳቸው ሜዳ ሲደረደሩ እንመለከታለን ይህ የዘመኑ እግርኳስ የመከላከል ጥበብነው ኳሱን ሲይዙ በዛውልክ በብዛት ወደተጋጣሚው ሜዳይሄዳሉ ይህ ሲስተም ለዩናይትድ አስቸጋሪ አደለም አልሆነም ሲስተሙ እንዴውም ሚወደድና ስኬታማ ሚያደርግነው ...
ትናንት ቡድኑ 2-0 እየመራ ወደመልበሻ ክፍል ሲያመሩ ጌሙን አልጨረሱም ሁለተኛው አጋማሽ ጥንቃቄ ይፈልጋል ብየነበር ከስልሳኛው ደቂቃ ጀምሮ እነሱ ወደጌሙ ሲገቡ ዩናይትዶች ከጌሙ መውጣት ጀመሩ ይህ የሲስተሙ ሳይሆን የራሳቸው የተጨዋቾች ችግርነው ጌሙን እንዴት መቆጣጠር እንዳለባቸው ያውቃሉግን ያንአላደረጉም ...አሁንም የዩናይትድ ድክመት ጌሙ ሳያልቅ የሆነሰአትለይ ሁሉንም ነገር ይተዋሉ ይህነገር ከፊትነስ ድክመቶች ጋር ሚያያዝ ቢሆንም የኳሊቲውም ችግር አብሮ መነሳት አለበት
ትናንት የመጨረሻውን 15 ደቂቃ ለመጫወት እረፍት ሲወስዱ ሩበን የመጨረሻውን ሪስክ ወሰደ ያም ሌኒ ዮሮን መሃልላይ በመተው ዳሎናሻው አስፍተው በሁለቱ ኮሪደሮች ተጠግተው እንዲገኙ ካደረገ በኋላ ማግዌርን ወደ አጥቂነት ወሰደው እዚችላይ በታክቲክ ስሌዳው ለተጨዋቾቹ የመጨረሻውን ነገርእንዲሞክሩ እየነገራቸው ነበር አብዛኛው የጌሙ እንቅስቃሴ በግራበኩልሆነ ሉክሾና ሃሪ አማስ ያሉበትን ክፍል በመጠቀም በፍጥነት ወደተጋጣሚው ሜዳይገቡና ለሃሪ ክሮሶችን ይጫወታሉ ደጋግመው አደረጉት ጫናው በረታ ሁለቱጎሎች ተገኙ ... ይሄ የአሞሪም ውሳኔና የታክቲክ ትግበራ ትልቅ ክሬዲት ሊሰጠውሚገባነው ...
ሲስተሙን እንኳን ተጨዋቾች እኛም መላመድ አዲስ ቢሆንብንም በሂደትግን ሁሉም እየተረዳው እንደመጣ መናገር ይቻላል በዚህ ሲስተምኮ ወደምርጥ ብቃት የመጡ ተጨዋቾች በዝተዋል ዮሮ ዲላት ማዝ ማግዌር ካስሜሮ ብሩኖ በዚህ ሲስተም ምርጥብቃት እያሳዩነው ከዚህ በፊት የነበረው ዩናይትድኮ በቡድን ብቻአደለም በግልም ብዙዎች ጥሩ አልነበሩም አሁንግን በተናጠል መሻሻሎች እያየንነው ያንማስቀጠልና ወደቡድን ጥንካሬ መቀየር ሚቻልበት ጊዜም ይመጣል ዋናው አስፈላጊ ነገር ስኳዱን update ማድረግ እንጂ ሲስተሙ መቀየሩ አደለም ።
#
@the_red_forever_mv