Posts filter


ኒውዝላንድ፣ ''ኢንቨስተርስ ፕላስ ቪዛ (IPV)'' የተሰኘ አዲስ የቪዛ አገልግሎት አስተዋወቀች፡፡

አዲሱ የቪዛ ሲስተም ለኢንቨስተሮች ብቻ የሚያገለግል ሲሆን፣ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን (FDI) ለመሳብ  ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡

''ኒውዝላንድ የኢንቨስትመንት መዳረሻ መሆኗን ለማሳየት ይጠቅማል'' ያሉት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ እና እድገት ሚኒስትር ኒኮላ ዊሊስ፣ አዲሱ ኢንቨስተርስ ፕላስ ቪዛ (IPV) ከመጪው ሚያዚያ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል፡፡

የኢሚግሬሽን ሚኒስትር ኢሪካ ስታንፎርድ፣ ''አዲሱ የቪዛ ፕሮግራም በዚህ በሰለጠነ ዓለም ኢኮኖሚ ካፒታልን ለመሳብ ይጠቅማል'' ብለዋል።
#nairametrics

@ThiqahEth


"ለገጠመን የኑሮ ውድነት ችግር ጥብቅ የሞነታሪ ፖሊሲ መከተል ግድ ይለናል'' - የህንድ ባንክ

ህንድ ሁሉም ባንኮች ወለድ እንዲያቆሙ አዘዘች፡፡

የህንድ ማዕከላዊ ባንክ የኢኮኖሚ ቀውስን ለመግታት በሚል ለመጀመሪያ ጊዜ የባንክ ወለድ እንዲቀር ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡ 

የባንኩ ገዥ ሳንጃይ ማልሆትራ፣ ''ለገጠመን የኑሮ ውድነት ችግር ጥብቅ የሞነታሪ ፖሊሲ መከተል ግድ ይለናል'' ሲሉ ተናግረዋል፡፡ 

ማልሆትራ፣ ''የዋጋ መረጋጋትን፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ እድገት እና የፋይናንስ መረጋጋትን ለመፍጠር የማክሮ ኢኮኖሚክ መሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል'' ብለዋል፡፡

በህዝብ ቁጥር ከዓለም አንደኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው እስያዊቷ ሀገረ ህንድ የምጣኔ ሃብት እድገቷ ላለፉት አምስት ተከታታይ አመታት እየቀነሰ መምጣቱን ሪፖርቶች አመላክተዋል፡፡
#aljazeera

@ThiqahEth


''የሆነ ቀን ዩክሬን የሩሲያ ሆና ልናያት እንችላለን'' - ትራምፕ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የዩክሬንን ባለስልጣናት፣ ''ስምምነት ሊያደርጉ ይችላሉ ላያደርጉም ይችላሉ፤ አንድ ቀን የሩሲያ ሊሆኑ ይችላሉ ላይሆኑም ይችላሉ'' ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ትራምፕ ዩክሬን በጦርነቱ ከአሜሪካ የተደረገላትን ወደ 500 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ድጋፍ፤ ያሏትን ማዕድናት በካሳ መልክ እንድታቀርብ አዘዋል፡፡

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አንድሪ የርማክ በበኩላቸው፣ ከሩሲያ ጋር ለሚደረገው ስምምነት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው፤ የደህንነት ዋስትና እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
#aljazeera    #associatedpress

@ThiqahEth


ግሪክ ባጋጠማት ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጠወቀጥ በሀገሪቱ ቱሪዝም እንቅስቃሴዋ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድሮባታል ተባለ፡፡

ከቀናት በፊት በውጭ ቱሪስቶች በስፋት የሚጎበኘው የሳንቶሪኒ ደሴት ለተከታታይ ሰባት ጊዜ  በሬክተር ስኬል ከ4 እስከ 5.2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል፡፡

ይህን ተከትሎ ባለስልጣናት የአስቸኳ ጊዜ አዋጅ አውጀዋል፡፡

የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋውን ተከትሎ ከ11,000 የሚበልጡ ነዋሪዎች ከሳንቶሪኒ ደሴት መውጣታቸው ተሰምቷል፡፡  
#france24

@ThiqahEth


''ፑቲን የሰዎች ሞት ሲያበቃ ማየት ይፈልጋል'' - ትራምፕ

ትራምፕ ወደ ነጩ ቤተመንግስት ከተመለሱ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከቭላድሚር ፑቲን ጋር የስልክ ውይይት አደውርገዋል፡፡

ሁለቱ መሪዎች የዩክሬንን ጦርነት ለማቆም በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል ተብሏል፡፡

ፑቲን፣ "የሰዎች ሞት ሲያበቃ ማየት ይፈለጋል" ብለዋል።

ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የሁለቱን ሀገራት ጦርነት ስልጣን በያዝኩ ማግስት አስቆመዋለሁ ቢሉም ጦርነቱ እስካሁን ድረስ እንደቀጠለ ነው፡፡ #thekoreatimes   #thenewyorkpost

@thiqahEth


''ቲክቶክን የመግዛት እቅድ የለኝም'' -ኤለን መስክ

የቴስላ እና ስፔስ ኤክስ ባለቤት መስክ በቻይናው የባይት ዳንስ ኩባንያ የሚተዳደረውን የቪዲዮ ማጋሪያ ቲክቶክ ለመግዛት እንደማያስብ አስታውቋል፡፡

መስክ፣ ''ቲክቶክ ቢኖረኝ ምን እንደምሰራበት እቅድ ስሌለለኝ ለጨረታ አልተዘጋጀሁም'' ብለዋል።

አሜሪካ የብሔራዊ ደህንነት ስጋት አለው ባለችው የቻይና ኩባንያ ላይ በመላ ሀገሪቱ እንዲዘጋ አልያ ከፊል ድርሻው ለአሜሪካውያን ባለሃብቶች እንዲሸጥ ጠይቃለች፡፡

ከሚሸጥ መዘጋቱን የሚመርጠው የባይትዳንስ ኩባንያ በባይደን ዘመን ተዘግቶ የነበረ ቢምንም፤ ትራምፕ እገዳው ለ75 ቀናት እንዲቆይ ወስነዋል፡፡ #cnn

@thiqahEth


የባንግላዴሽ ተቃዋሚዎች የቀድሞዋን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤተሰብ መኖሪያ ቤት  "ማቃጠላቸው" ተሰምቷል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በአንድ ሌሊት በፈጸሙት ጥቃት የሼክ ሀሲና ደጋፊዎች ቤት እና ንብረት ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈጽመዋል፡፡

የጥቃቱ መንስዔ የሼክ ሀሲና ደጋፊዎች የሽግግር መንግስቱን ለመቃወም አደባባይ ለመውጣት በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ማድረጋቸው ነው፡፡

የቀድሞዋ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼክ ሀሲና በስደት ከሚገኙባት ህንድ ሆነው ስለተቃውሞው ንግግር ያደርፋሉ ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ 

ተቃዋሚዎቹ ቤቱን ለማፍረስ ዶማና ሌሎች ቁሳቁሶችን ይዘው የገቡ ሲሆን፤ ኤክስከቫተር መኪና ይዘው የገቡ መኖራቸውም ተዘግቧል፡፡
#Algezira

@ThiqahEth


ትራምፕ "አናሳ ነጮችን ጨቁናለች" ባሏት ደቡብ አፍሪካ ላይ ማዕቀብ ጣሉ።

የደቡብ አፍሪካ መንግስት በነጮች የሚተዳደር መሬት ያለ ካሳ እንዲወረስ የሚፈቅድ ህግ አፅድቋል። 

ደቡብ አፍሪካ እስራኤልን በጋዛው ጦርነት በዘር ጭፍጨፋ ወንጀል በዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት መክሰሷ የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደርን ማስቀየሙ ተገልጿል።

ከዚህ ባለፈም ኢራን ጋር በንግድ፣ ፀጥታ እና የኑክሌር ማበልጸግ ፕሮግራም የጋራ መግባቢያ ስምምነት መፈጸሟ በአሜሪካ ዘንድ አልተወደደም። #thenationalpulse

@ThiqahEth


ከራዳር ተሰውሮ የነበረው አውሮፕላን ተከስክሶ ተገኘ።

የአሜሪካ ባህር ጠባቂ ኃይል የተሰባበረውን የአውሮፕላን ቅሪት ማግኘታቸውን አረጋግጠዋል።

አውሮፕላኗ በአላስካ ግዛት 10 ሰዎችን ጭና የነበረ ሲሆን፣ ወንዝ ዳር ተከስክሳ ተገኝታለች።

አውሮፕላኗ ከአናክላት ወደ አላስካ እየበረረች በነበረበት ወቅት ነበር ከራዳር የተሰወረችው። #bernama

@ThiqahEth


"ፍርድ ቤቱ በጋዛው ጦርነት በግልጽ ለፍልስጤም ያደላ አካሄድ ተከትሏል" - ትራምፕ

"የትራምፕን እርምጃ የፍርድ ስራየን በገለልተኛ እና ያለአድልዎ እንዳልሰራ ጫና ይፈጥርብኛል" - ICC

ትራምፕ በዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ ጥለዋል። ተቋሙ አመራሮች፣ ሰራተኞችና ቤተሰቦች ወደ አሜሪካ እንዳያቀኑ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡

ፕሬዜዳንቱ ማዕቀቡን የጣሉት ፍርድ ቤቱ የአሜሪካ፣ ''ወዳጅ ሀገር'' ሲሉ በጠሯት እስራዔል ላይ የሚያራምደው አቋም የተዛባ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡  

"ፍርድ ቤቱ በጋዛው ጦርነት በግልጽ ለፍልስጤም ያደላ አካሄድ ተከትሏል" በማለት ወቅሰዋል፡፡ 

የዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒም ኒታንያሁ በጋዛ የጦር ወንጀል ፈጽመዋል በማለት የእስር ትዕዛዝ አውጥቷል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ኒታንያሁ፣ ትራምፕ ፍርድ ቤቱ ላይ በጣሉት ማዕቀብ መደሰታቸውን ገልጸው ፕሬዝዳንቱን አመስግነዋል፡፡

ዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የትራምፕን እርምጃ የፍርድ ስራየን በገለልተኛ እና ያለአድልዎ እንዳልሰራ ጫና ይፈጥርብኛል ብሏል፡፡ 

የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ኦርሱላ ቫንደርሊን በበኩላቸው የትራምፕ ውሳኔ አለማቀፍ ፍትህ እንድጠፋ ያደርጋል ሲሉ ተችተዋል፡፡
#thedefensepost   #ashraqalawusat #irishnews

@ThiqahEth



#Update #Ethiopia

ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ የማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም ተወሰነ።

ከዚህ ቀደም የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረብ የሚቻለው እስከ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ መሆኑ ተገልጾ ነበር።

በዚህ መሰረት ቁጥራቸው 88,717 የሆኑ ግብር ከፋዮች የህትመት ጥያቄ ማቅረብ መቻላቸውን የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሤ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የገቢ ዘርፍ አመራሮች ጋር በበይነ መረብ ባደረጉት ውይይት ገልጸዋል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች የህትመት ጥያቄያቸውን ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች መኖራቸው ታሳቢ በማድረግ የህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም በውይይቱ ተወስኗል፡፡

እስከ አሁን ድርስ የህትምት ጥያቄ ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ የህትምት ጥያቄ እንዲያቀርቡ የተባለ ሲሆን የሲስተም መጨናነቅ እንዳይፈጠር የሲስተም ማሻሻያዎችን ማከናውን፣ የህትመት እና ስርጭት ተግባራት በሚፈለገው ደረጃ ለማከናወን ተጨማሪ የህትመት ማሽኖችን ወደ ስራ ማስገባት እና አትሞ በፍጥነት ማሰራጨት እንደሚገባ ስምምነት ላይ መደረሱ ተገልጿል።

@ThiqahEth     @tikvahethiopia


"2,000 አስክሬኖችን ሰብስቢለሁ። 900 የሚሆኑት ሆስፒታል ተልከዋል" - ድርጅቱ

በምሥራቅ ኮንጎ የሟቾች ቁጥር 3,000 እንደሚጠጋ ተ.መ.ድ አስታውቋል።

ተ.መ.ድ ከኤም 23 ጋር በመተባበር እስካሁን "2,000 አስክሬኖችን ሰብስቢለሁ" ያለ ሲሆን፣ "900 የሚሆኑት ወደ ሆስፒታል ተልከዋል" ብሏል፡፡

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በ"አማጺው ኤም 23 ቡድን" መካከል የተደረገው ጦርነት ከፍተኛ ወውድመት ማስከተሉን በሀገሪቱ የሚገኘው የተ.መ.ድ ተልዕኮ ምክትል ኃላፊ ቪቪያን ቫንድ ፒር ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት "አማጺ ቡድኑ" በተቆጣጠራት የጎማ ከተማ ወረርሽኝ ስጋት መኖሩን ጠቁሟል፡፡

ቡድኑ ለአንድ ሳምንት የዘለቀውን ዘመቻ በመግታት ጊዚያዊ የተኩስ አቁም አውጇል፡፡
#voiceofamerica

@ThiqahEth


''በደቡብ አፍሪካ ጸረ-አሜሪካዊነት ተስፋፍቷል''  - ማርክ ሩቢዮ

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩቢዮ፣ ደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የቡድን 20 ስብሰባ እንደማይሳተፉ አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ባሳለፍነው ረቡዕ በደቡብ አፍሪካ ''አዲስ የመሬት አጠቃቀም ህግ'' ያስፈልጋል ማለታቸው በሁለቱ ሀገራት መካከል ውጥረት እንድሰፍን ምክንያት ሆኗል፡፡

ትራምፕ የራማፎዛ አስተዳደር በደቡብ አፍሪካ መሬት ያለ አግባብ እየወረሰ ነው ሲሉ ወንግለዋል። ፡፡

በጆ ባይደን አስተዳደር በነጩ ቤተመንግስት ምክትል ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አንድሪው ባቲ፣ ትራምፕ በደቡብ አፍሪካ ላይ ማራመድ የጀመሩት ፖሊሲ የአሜሪካን ብሄራዊ ደህንነነት የሚጎዳ ነው በማለት ተችተውታል፡፡ #newsbytes

@ThiqahEth


"ዓለማቀፍ ተቋማት በሉዓላዊነታችን ጣልቃ እንዲገቡ አንፈቅድም'' - አርጀንቲና

አርጀንቲና ከዓለም ጤና ድርጅት እንደምትወጣ ማስታወቋ ታውቋል።

ፕሬዝዳንት ዣቪየር ሚሌ አርጀንቲና በዓለም ጤና ድርጅት የሚኖራትን ተሳትፎ እንድታቆም ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ጀራርዶ ወርዚን ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ፣ ''ዓለማቀፍ ተቋማት በሉዓላዊነታችን ጣልቃ እንዲገቡ አንፈቅድም'' ብለዋል፡፡

የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ማኑዌል አዶርኒ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ የገለልተኝነት ችግር ይታይበታል ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

የአርጀንቲና ከዓለም ጤና ድርጅት የመውጣት ሃሳብ ይፋ የሆነው ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካ ከድርጅቱ እንደምትወጣ ከገለጹ ከሳምንት በኋላ ነው፡፡    #aninews

@ThiqahEth


ኤለን መስክ የአቬሽን ዘርፉ ገጠመውን ችግር ለመፍታት እንሰራለን አሉ፡፡

ቢሊየነሩ መስክ የሚመሩት የመንግስት አቅም ድፓርትመንት (DOGE) በአቬሽን ዘርፉ የሚስተዋሉ የደህንነት ችግሮችን ለመቅረፍ ማስተካከያ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡

መስክ በግል የኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ የአሜሪካ አውሮፕላኖች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተደጋጋሚ የመከስከስ አደጋ እየገጠማቸው መሆኑን ከፌደራል አቬሽን ባለስልታን ማወቅ ችያለሁ ብለዋል፡፡

ከቀናት በፊት የፌደራል አቬሽን ባለስልጣን የቅድመ አየር መንገድ ደህንነት መግለጫ ሲስተም ከአገልግሎት ውጭ ሆኖ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

ክስተቱ የደህንነት ስጋትን ፈጥሯል ያሉት መስክ፤ ከፕሬዝዳንት ትራምፕ ጋር በመሆን የአየር ትራፊክ ቁጥጥር ላይ ማሻሻያዎች እንደደረጉ እንሰራለን ሲሉ አብራርተዋል፡፡ #dailypost

@ThiqahEth


#Ethiopia

"አንድ ታዳጊ ወጣት ተገሏል ሁለት ደግሞ ቆስለዋል" - የሹፌሮች አንደበት

"ምን አጠፋን? ምን እናድርግ? ህግና መንግስት አለ ብለን ነው በትግስት እየጠበቅን ያለነው የ200 ብር ትራንስፖርት 1000 ብር ከፍለን በየ ቦታው ተሳቀን አሁን ገደሉን፣ አቆሰሉን እያልን፤ ያሳዝናል።

ዛሬ 28-05-2017 ጠዋት 2፡10 ከገንዳውሃ ጎንደር እየተጎዝነ ከ10 በላይ አባዱላ ተዘርፎል በጣም የሚያሳዝነው አንድ ታዳጊ ወጣት ተገሏል ሁለት ደግሞ ቆስለዋል።

እስከመቼ ይሄ ጉዳይ? እንደ ክልል የፀጥታ ችግር ስላለ በትግስት መመልከት ስለሚገባ ሁሉም በየቀኑ እየሞትንና ደም እያነባን ዝም አልን እስከመቼ?

ከገንዳውሃ እስከ ጎንደር ያለው መንገድ ከዚህ በፊት አብዛኛውን ጊዜ የማዕከላዊ ጎንደር የፀጥታ ችግር ይበዛ ነበር። አሁን ግን እነሱ አስተካክለው መንገዱን ሰላም ሲያደርጉ ምዕራብ ጎንደር በእጅጉ ብሷል ለምን?

ትኩረት ለምዕራብ ጎንደር ዞን። የፀጥታ መዋቅር ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን ችግሩን ባፋጣኝ እንዲስተካከል ሀሳቤን እያለቀስኩ አካፍላለው። ጎንደር አውሮፖ ሆነብን"
ሲል የሹፌሮች አንደበቶ አስታውቋል።

@ThiqahEth


#Ethopia

በትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰማ።

አደጋው ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የጭነት ተሽከርካሪ ከቆቦ ከተማ ወደ ድሬዳዋ ሲያመራ ከነበረ ዶልፊን ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡

በተፈጠረው አደጋም የ8 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ሃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በሦስት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን ነው የገለጹት፡፡

#ThiqahEth


''ቤታችንን ለቀን አንሄድም'' - ፍልስጤማውያን

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከእስራዔሉ አቻቸው ጋር በተገናኙበት ወቅት አሜሪካ በመልሶ ማልማት እቅድ ጋዛን ማስተዳደር እንደምትፈልግ ተናግረዋል፡፡

በጋዛ የሚገኙ ፍልስጤማውያን ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ ይደረጋል ማለታቸው፤ ነዋሪዎቹን አስቆጥቷል።

ቁጣቸውን ከገለጹ ፍልስጤማውያን መካከል ሳሚር አቡ ባዝል የተባለ የጋዛ ነዋሪ፣ ''ትራምፕ ከነሀሳቡ፤ ከነአመለካከቱ ሲዖል ይግባ፤ የትም አንሄድም፤ እኛ የእሱ የእጅ ገንዘብ አይደለንም'' ሲል ቁጣውን አሰምቷል፡፡

ለፍልስጤም እታገላለሁ የሚለው የሀማስ ቡድን፣ ''ፍልስጤማውያንን የሚጨቁን እና ለቀጠናው መረጋጋት አስተዋጽኦ የማያደርግ'' ሲል ነቅፎታል።

ሳውድአረቢያን ጨምሮ አንዳንድ የአረብ ሀገራት ደግሞ የትርምፕን አስተያየት አሳሳቢ እንደሆነ በመግለጽ ተቃውመውታል፡፡  

በተመሳሳይ መልኩ የአውሮፓ ሀገራት በበኩላቸው ፍልስጤማውያንን የማዘዋወር እቅድ አውግዘዋል፡፡

በርካታ ፍልስጤማዊያኑም፣ "ቤታችንን ለቀን አንሄድም" ሲሉ ከወዲሁ ሞግተዋል።
#anadoluagency #trtworld #easterneye

@ThiqahEth


የአፍሪካ ልማት ባንክ በማዕድን ግብይት እንዲፈጸም የሚያስችል እቅድ አቀረበ፡፡

ባንኩ፣ ''የወርቅ ደረጃ'' ሲል የገለጸው የመገበያያ ዘዴ የአህጉሪቱ ሀገራት ማዕድን ላይ የተመረኮዘ የግብይት ማስተካከያ ላይ እንዲያተኩሩ አሳስቧል፡፡

እንደባንኩ መረጃ ከሆነ በዓለም ላይ ካሉ የተፈጥሮ ማዕድናት 30 በመቶ የሚሆነው አፍሪካ ውስጥ ይገኛል፡፡

እቅዱ ስኬታማ እንዲሆን ሁሉም ሀገራት ቅድመ ስምምነት የተደረገበት የማዕድን ሀብት መጠን ሊያሟሉ እንደሚገባ ባቀረበው እቅድ ገልጿል፡፡

የአፍሪካ ልማት ባንክ አዲስ ያቀረበው እቅድ የአፍሪካ ሀገራት የሀገር ውስጥ መገበያያ ገንዘባቸውን በሌሎች ሀገር ማዕድናት በመለወጥ የንግድ ስርኣትን ማቀላጠፍ እንደሚቻል አስታውቋል፡፡
#iaafrica

@ThiqahEth

19 last posts shown.