TIKVAH-ETHIOPIA


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


" የብቃት ምዘና ፈተናውን በመጋቢት 2017 ዓ.ም ለመስጠት ዝግጅት እያደረግን ነው " - ጤና ሚኒስቴር

ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ፦
- Medicine
- Nursing
- Public Health
- Anesthesia
- Pharmacy
- Medical Laboratory Science
- Midwifery
- Dental Medicine
- Medical Radiology Technology
- Environmental Health
- Psychiatric Nursing
- Pediatric & Child Health Nursing
- Emergency & Critical Care Nursing
- Surgical Nursing
- Physiotherapy
- Optometry
- Human Nutrition ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የመውጫ ፈተን ያለፉ እንዲሁም በጤና ሚኒስቴር በኩል ተመዝግበው የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች በመጋቢት 2017 ዓ.ም ፈተናውን ለመስጠት በዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውዋል።

የዚሁ ፈተና ምዝገባ ከየካቲት 24 - መጋቢት 7/2017 ዓ.ም የሚከናወን ይሆናል።

ፈተናውን የሚወስዱ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን
http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት እንዲመዘገቡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ከተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውጪ ምንም ዓይነት የምዝገባ ጥያቄ እንደማያስተናግድት ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።

ተመዛኞች በተጠቀሱት ቀናት ተመዝግበው ሲስተሙ የሚሰጣቸውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ስሊፕ print አድርገው በመያዝ ሲመዘገቡ በመረጡት የፈተና ጣቢያ በፈተናው ወቅት እንዲገኙ ተብሏል።

ማሳሰቢያ ፦

1. እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድመው በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ። ከፍተኛው የተመዛኝ ቁጥር በደረሰበት የፈተና ጣቢያ ላይ ተጨማሪ ምዝገባ ማከናወን የማይቻል መሆኑ ተነግሯል።

2. ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጣ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጎ ካልያዘ ፈተናውን መውሰድ የማይችል መሆኑን ማሳሰቢያ ተላልፏል።

3. በጥር 30/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ተፈትነው ያለፉና በዚህ የብቃት ምዘና ፈተና ለመቀመጥ የተዘጋጁ ነገር ግን ቴምፖረሪ ዲግሪ ከተቋማቸው ያልደረሰላቸው ተመዛኞች ከትምርት ሚኒስቴር ይህ ጉዳይ ቀጥታ ከሚመለከተው የስራ ክፍል የትብብር ደብዳቤ ማያያዝ የሚጠበቅባችሁ መሆኑ ተመላክቷል።

#MoH

@tikvahethiopia


" ትርፍ ተሳፋሪዎች ከሌሉ አገልግሎት መስጠት ይከብደኛል " - የአዲስ አበባ የአውቶብስ አገልግሎት ድርጅት

ከወንበሮች በተጨማሪ ቆመው የሚሄዱ ተሳፋሪዎች ከሌሉ መደበኛ አገልግሎት ለመስጠት እንደሚቸገር የአዲስ አበባ የአውቶብስ አገልግሎት ድርጅት አስታውቋል፡፡ 

በከተማዋ አገልግሎት የሚሰጡ አውቶቡሶች አብዛኛውን ጊዜ ሰዎችን በብዛት አሳፍረው የሚንቀሳቀሱ መሆናቸው ይታወቃል፡፡

" ተገልጋዮችን ከአቅም በላይ እንዲጨናነቁ ማድረግ ለምን አስፈለገ ? ተጠቃሚ ደንበኞችን የሚመጥን የአውቶብስ ቁጥር ማሟላት ያልተቻለውስ ለምንድን ነው ? " በሚል ከአሐዱ የተጠየቀው የአዲስ አበባ የአውቶብስ አገልግሎት ድርጅት ምላሽ ያለው ሰጥቷል።

የድርጅቱ የቴክኒክ አገልግሎትና ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታምሩ ፉፋ ፤ " ይህ የተደረገው የአውቶብሶችን መለዋወጫ እና የነዳጅ ወጭን ጨምሮ ሁሉንም አስፈላጊ ወጪዎች በራሱ እንዲሸፍን የተሰጠውን መመሪያ ለመተግበር በወንበር ልክ ብቻ አሳፍሮ መንቀሳቀስ የሚያዋጣ ሆኖ ባለመገኘቱ ነው " ብለዋል፡፡

በተለይ የከተማዋን ረጅም ርቀት የሚጓዙ አውቶብሶች ብዙ ተገልጋዮችን አሳፍረው የመጓዝ ግዴታ እንዳለባቸው የገለጹት አቶ ታምሩ፤ " አውቶብሶቹ በሚያሳፍሩበት አካባቢ ረጃጅም ሰልፎች ቢኖሩም ቆመው የሚሄዱ ሰዎች ቁጥር ግን አነስተኛ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ደንበኞች 'ቀጣይ ተረኛ አውቶቡስ ይመጣል' ብለው እንዲያምኑ የተገነባው ሀሳብ ጥሩ ቢሆንም፤ ድርጅቱን ኪሳራ ላይ የሚጥል እና አውቶብሶቹ ሲመላለሱ መያዝ ያለባቸውን ሰው ልክ ይዘው እንዳይመላለሱ አድርጓል ሲሉም አክለዋል፡፡

" በብልሽት ምክንያት የቆሙ አውቶቡሶችን መለዋወጫ አሟልቶ ወደ አገልግሎት እንዲመለሱ ለማድረግ እና ሌሎችም ወጪዎችን ለመሸፈን ቆመው የሚሄዱ ደንበኞችን መጫን ግዴታ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪ በመታወቂያ የሚገለገሉ ደንበኞችን አስመልክቶ አዲስ እየተሻሻለ ያለ አሰራር መኖሩ የተገለጸ ሲሆን ፤ ይህ አሰራርም መደበኛ ተጠቃሚዎች ላይ የተፈጠረውን ቅሬታ የሚፈታ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

እየተሸሻለ ያለው አስራር ተግባራዊ ሲደረግ፤ ሃሰተኛ መታወቂያዎችን የሚጠቀሙ አካላትን ለመለየት ያስችላልም ተብሏል፡፡

Credit - Ahadu / አሐዱ

@tikvahethiopia


“ ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል ” - የፐርፐዝ ብላክ ባለአክሲዮኖች

ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ሕብረት ባንክ ካለው ገንዘብ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለውን ገንዘብ እንዲያንቀሳቅስ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም በዐቃቢ ህግ ይጎባኝ ውሳኔው መታገዱን የፍርድ ቤት ሰነድና ባለአክሲዮኖች አመለከቱ።

ሁነቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዱት ባለአክሲዮኖች የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንት ለሰባት ወራት ተዘግቶ መቆየቱን፣ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ክርክር ሲካሄድ ቆይቶ እንደነበር ገልጸዋል።

በክርክር ሂደቱም፣ ፍርድ ቤት ሕብረት ባንክ ከተቀመጠው ገንዘቡ ውጪ በሌሎች ባንኮች ያለው የፐርፐዝ ብላክ ገንዘብ እንዲንቀሳቀስ፣ ለማንቀሳቀስ አስተዳዳሪ እንዲሾም ወስኖ እንደነበር አስረድተዋል።

“ነገር ግን ዐቃቤ ሕግ ውሳኔውን በመቃወም ይግባኝ ጠይቆ የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ አሳግዶታል” ብለዋል።

“ድርጅቱ ለኪራይ፣ ደመወዝና ለሌሎች ወጪዎች ክፍያ ባለመፈጸሙ ሠራተኛው ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቋል” ያሉት ባለክሲዮኖቹ፣ “ድርጅቱ የሚፈርስ እንኳን ከሆነ አግባብ ባለው መንገድ መፍረስ ነበረበት እጅግ ከባድ ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉ አማረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ሰነድ፣ “መዝገቡ ከቀጠሮ በፊት የቀረበው ይግባኝ ባይ በቀን 10/6/2017 ዓ/ም በተፃፈ አቤቱታ ያቀረዝነው ይግባኝ ታይቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ የፌ/ከፍ/ፍርድ ቤት በወ/መ/ቁ 326384 የሰጠው ውሳኔ ታግዶ እንዲቆይ እንዲታዘዝልን በሚል ባቀረበው አቤቱታ ነው” ይላል።

አክሎም፣ ይግባኝ ቅሬታ ለመስማት ለ20/06/2017 ዓ/ም የተያዘው ቀጠሮ ተሰብሮ የእግድ አቤቱታውን በመመርመር ዝርዝር ትዕዛዝ መስጠቱን ያስረዳል።

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች መዘጋታቸው፣ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍስሃ እሸቱ (ዶ/ር) አገር መውጣታቸው አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" እገዳው ተነስቷል " - ኢሰመኮ

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም. ፦
- የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል፣
- የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶች
- ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች በኢትዮጵያ የተባሉ 3 በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ የሚሠሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ በታኅሣሥ ወር 2017 ዓ.ም. የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል እና የሕግ ባለሙያዎች ለሰብአዊ መብቶችን በድጋሚ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ እና የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማእከልን ማገዱ ይታወሳል።

ኢሰመኮ ታኅሣሥ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ የሚተላለፉ እገዳዎች በሲቪል ምኅዳሩ እና በማኅበር የመደራጀት መብቶች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንዳይፈጥሩ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስቧል።

በተጨማሪም ኢሰመኮ በድርጅቶቹ እገዳ ላይ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ምርመራ ያከናወነ ሲሆን የደረሰባቸውን ግኝቶች እና ምክረ ሐሳቦች ለሚመለከታቸው አካላት ማጋራቱን አመልክቷል።

ኢሰመኮ በተለይ አዲስ በተሾሙት ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ በኩል ጉዳዩን በልዩ ትኩረት በመከታተል ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን እና እገዳ ከተጣለባቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን በማድረግ ለጉዳዩ መፍትሔ ለማስገኘት ሢሠራ እንደቆየ ጠቁሟል።

ይህ የኢሰመኮ ጥረት ውጤት በማስገኘቱ በ4ቱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ላይ ተጥሎ የነበረው እገዳ ከዛሬ የካቲት 24 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የተነሳ በመሆኑን ኢሰመኮ አሳውቋል።


@tikvahethiopia


#SafaricomEthiopia

⛺🗺 ሃይኪንግ ላይ ሆናችሁ ዳታ መጠቀም ፈልጋችሁ ታውቃላችሁ? እነሆ አዲስ ቅመም!
💨⚡ የትም ይዛችሁት መሄድ የሚያስችላችሁ እስከ 6 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom #1Wedefit #Furtheraheadtogether


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#ብርሃን_ባንክ
የብርሃን ጉዞጎ ተጠቃሚዎች ብቻ የሚያገኙትን ልዩ ቅናሾች እና ጥቅሞች ያግኙ፣ ይህም ጉዞዎን የበለጠ ተመጣጣኝ እና አስደሳች ያደርገዋል።
👉ደንበኞች በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው ከ10 በላይ አለም አቀፍ የአየር መንገዶች የበረራ ትኬቶችን ዋጋ ማወዳደር ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት አየር መንገድ የበረራ ትኬቶች ላይ ቅናሽ ዋጋዎች እንዲያገኙ ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት ሰዓት እና ዋጋ አስተማማኝ የበረራ ቡኪንግ ለመያዝ ያስችላል።
👉በሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች፣ በሞባይል ወይንም በኢንተርኔት ባንኪንግ ክፍያዎችን መፈጸም ያስችላል፡፡
👉ያለ ተጨማሪ ክፍያ ሳምንቱን ሙሉ ለ 24 ሰዓታት የባለሙያ ምክር እና እርዳታ እንዲያገኙ ያስችላል።
ስለ ብርሃን ጉዞጎ (GuzoGo) አገልግሎት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በ0116506355 /0116507425 ወይም በነፃ የጥሪ ማዕከል ቁጥር 8292 ላይ ይደውሉ፤
እንደስማችን ብርሃን ነው ስራችን
#eticket #guzogo #internetbanking #mobilebankingbanking #berhanbank #bank #finance #Stressfreebanking #bankinethiopia


#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የመጋቢት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

#ነዳጅ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia


#MoE

" በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የካቲት 21/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከ ሰርኩላር፤ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ እና የሠራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ጠቀሜታ እንዳለው ይገልጻል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑንም ያትታል።

በዚህም በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ እንደሚገባ / እንደ ቅደመ ሁኔታ መቀመጡን አሳስቧል።

Via
@tikvahuniversity

292.8k 3 1.1k 1.6k

#Earthquake

ዛሬ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም በዓዲግራት ፣ በዓድዋ፣ ፣ ወቕሮ ፣ መቐለ ጨምሮ በበርካታ የትግራይ አከባቢዎች ከቀኑ 5:30 ጀምሮ ለሰከንዶች የቆየ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘርት ተከሰተዋል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ከዓዲግራት 46 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሬክተር ስኬል 5.2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደነበር አመልክቷል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንባር ላይ መከሰቱ ተነግሯል።

@tikvahethiopia


#SafaricomEthiopia

ዝግጁ ነሽሽሽሽሽ?? የሳፋሪኮም ቅድሜያ ለሴቶች 5ኬሜ ሩጫ ምዝገባ ጀምሯል M-PESAን ተጠቅመሽ 540 ብር የነበረውን ቲሸርት
በ 389 ብር ብቻ አግኚ!!!
ከM-Pesa ጋር አብረን እንፍጠን። #Andegna #WomensRun #MPESASafaricom


#ዓድዋ129

ዛሬ የካቲት 23 መላ የኢትዮጵያ ህዝብና ጀግኖች አርበኞች በአንድነት የኢጣሊያንን ቅኝ ገዢ ጦር ዓድዋ ላይ ድል ያደረጉበት በዓል እየተከበረ ይገኛል።

ንጉሰ ነገስት አፄ ሚኒልክ የመሯቸዉ ኢትዮጵያዉን ጀግኖች ኢትዮጵያን የወረረ ጠላታቸዉን ዓድዋ ላይ መትተዉ አሳፍረዉ፣ አዋርደው ፣ አንገት አስደፍተው የመለሱት ልክ በዛሬው ዕለት ከ129 ዓመታት በፊት ነበር።

#ዓድዋ
#የመላአፍሪካውያንድል
#Ethiopia

@tikvahethiopia


#ዓድዋ

እንኳን ለ129ኛው የዓድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ !

" ዓድዋ ዛሬ ናት አድዋ ትናንት
መቼ ተነሱና የወዳደቁት
ምስጋና ለእነርሱ ለዓድዋ ጀግኖች
ለዛሬ ነፃነት ላበቁኝ ወገኖች
የጥቁር ድል አምባ ዓድዋ
አፍሪካ እምዬ #ኢትዮጵያ❤
ተናገሪ
የድል ታሪክሽን አውሪ !!  " - ጂጂ

መልካም የድል በዓል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ !!

@tikvahethiopia


#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ የተሰማው ከፍተኛ ድምጽ የ129ኛው ዓድዋ ድል በዓልን ምክንያት በማድረግ የተተከሰ የመድፍ ድምፅ ነው።

@tikvahethiopia


#እንድታውቁት #AddisAbaba

ከዛሬ ለሊት 6:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ ነገ 7:00 ሠዓት ድረስ መንገዶች ይዘጋሉ።

129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ነገ ፒያሳ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይከበራል።

ይህን ተከትሎ ፦

- በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት
- ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ
- ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር
- ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ
- ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት
- ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ
- ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ዮሐንስ መብራት የሚወስዱት መንገዶች ከዛሬ የካቲት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ከለሊቱ 6፡00 ሠዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

ህብረተሰቡም ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በ 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia


“ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር ነው የሚሸጠው ” - የጋሞ ልማት ማኀበር

በተለይ የውጪ አገር የገበያ ትስስር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ ከአዞ ሽያጭ እስከ 60 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገቢ እያጣች መሆኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባምንጭ የጋሞ ልማት ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

ከሦስት ዓመታት በፊት ትንሽ የአዞ ስጋና ቆዳ ለውጪ አገራት ይሸጥ እንደነበር፣ ከዚያ በኋላ በገበያ ትስስር ክፍተት ገቢው በመቀዛቀዙ እንደ አዲስ ለማንሰራራት እየተሰራ መሆኑን ማኀበሩ አስረድቷል።

ስለአዞ ሽያጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው የማህበሩ አርባምንጭ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኘ፣ “ ከ3 አመታት በፊት 10፣ 15 ነበር የሚሸጠው። ከ3000 እስከ 5000 አዞዎች ሲሸጡ የነበረው ከ10 ዓመት በፊት ነው። እየቀሰ መጥቷል ” ብለዋል።

የማኀበሩ ሥራ የአርባምንጭ አስኪያጅ አቶ ዲዊት ዳኘ ምን አሉ ?

“ የአዞ ቆዳ የሽያጭ ሂደቱ ተቀዛቅዞ ቆይቶ አሁን ሽያጭ አልተጀመረም። አሁን በማኀበሩ ተወስዶ እየተሰራ ነው። ቆዳቸው ለሽያጭ የደረሱ ከ2500  በላይ አዞዎች አሉን። እንዴት እንደሚቀጥል ከአገር ውስጥ ካምፓኒዎች ጋር እያወራን ነው።

አሁን ተነጋግረን የውል ሂደት ላይ ነው ያለነው እሱን ጨርሰን ሽያጩ ይካሄዳል ብለን እናስባለን። በፊት ሲሸጥ የነበረው ቆዳው ብቻ ነው። ግን የአዞ ስጋው፣ ጥርሱ፣ ይፈለጋል። ስጋው በሌሎች አገራት በጣም ይፈለጋል።

አሁን 4,000 የአዞ ጫጩቶችን ለመሰብሰብ እንቁላል ዝግጁ ሆኖ ነው ያለው። ከሦስት ወራት በኋላ ጫጩት ከተፈለፈለ በኋላ ከሀይቁ ወደ ማኀበር ይመጣሉ።

የአዞ ቆዳና ስጋ በጣም ዋጋው ውድ ነው። ስለዚህ ትክክለኛ ማርኬት ሊንኬጅ ተፈጥሮ ስርዓቱ ቢዘረጋ እንደ አገር ትልቅ ገቢ እናገኛለን። በተለይ በዘርፉ የሚሰሩ የውጪ አገር ካምፓኒዎችን እያነጋነርን ነው ” ብለዋል።

ከ2,500 በላይ አዞዎች ለሽያጭ ቢቀርቡ ምን ያክል ገቢ ማግኘት ይቻላል ? ስንል የጠየቅናቸው አቶ ዳዊት፣ የአንድ አዞ ቆዳ አንድ ሴንቲሜትር 5 ዶላር እንደሚሸጥ፣ የአንድ አዞ ቆዳ እስከ 45 ሴንቲሜትር እንደሚሆን፣ አንድ አዞ በትንሹ እስከ 22 ሺሕ ብር እንደሚሸጥ፣ በጠቅላላ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ሊገኝ እንደሚችል አስረድተዋል።

በማኀበሩ ስንት ሠራተኞች አሉ ? የአዞ ስጋ ምግብነት ላይ ይውላል ወይ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ስጋ ይበላል። በኛ አልተለመደም። ግን የኛ ሰዎች የ40 ዓመት ልምድ አላቸው። ብራንቹ ተቋቁሞ 41 ዓመቱ ነው። ረጅም ልምድ ያላቸው ሰዎች አዞ የመመገብ ልምድ አላቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አቶ ዳዊትና አንድ የማኀበሩ አስጎብኝ በኢትዮጵያ ብዙ እንዳልተለመደ፣ ኬኒያን ጨምር በሌሎች አካባቢዎች አዞ ለምግብነት እንደሚውል ተናግረዋል።

አቶ ዳዊት፣ “ የአዞ ሬስቶራንት ለመክፈት ” እንዳሰቡ ገልጸው፣ “ ፈረንጆች ይመጣሉ እዚህ ይመገባሉ፤ ቀስ በቀስ የኛ ሰዎችም እያዩ እየተመገቡ ይሄዳሉ ” ነው ያሉት።

አክለው፣ በማኀበሩ ወደ 35 ገደማ ሠራተኞች እንዳሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ሲሆን፣ የማኀበሩ አስጎብኝ በሰጡት ገለጻ ደግሞ፣ “60 በመቶ የሚሆኑት ሰራተኞች የአዞ ስጋ ይመገባሉ” ብለዋል።

አንድ አዞ ለሽያጭ ለመቅረብ ብቁ እስከሚሆን ድረስ 62 ኪሎ ግራም ስጋ እንደሚመገብ፣ አዞ የሚመገበው የአሳ፣ የአዞ ስጋ እንደሆነ፣ አሳማ ሌሎች የእንስሳት ዝርያዎች እንዳሉ፣ የህክምናና ሌሎችን ጨምሮ በአጠቃላይ ማኀበሩ በአመት እስከ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚደረግ ተመልክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

15 last posts shown.