#ነእፓ
ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ፤ ዛሬ በላከልን መግለጫ መንግስት ከጁመዓ ሰላት በኃላ በምዕመናን ላይ እርምጃ መውሰዱንና ይህንንም በፅኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል።
ፓርቲው ፤ " ባለፉት ጥቂት ወራት በ ' ሸገር ከተማ ' እየተካሄደ ያለውን ' ህገወጥ ' መስጂዶችን የማፍረስ እርምጃ በሰላማዊ መንገድ በመቃወም በአዲስ አበባ በተለይ በአንዋር መስጂድ ከጁምአ ሰላት በኃላ ድምጻቸውን ባሰሙ ሙስሊሞች ላይ በተወሰደው እርምጃ የሰው ህይወት አልፏል ፣ በርካታ ምዕመናን ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል " ያለ ሲሆን " የተወሰደው የእብሪት እርምጃ ነው ፤ ይሄንንም በፅኑ እናወግዛለን " ሲል አሳውቋል።
መንግስት ከሀይማኖት ተቋማት ላይ እጁን እንዲያነሳ ፣ የሀይማኖት እና የመንግስትን ህገመንግስታዊ ልዩነት እንዲያከብር ፓርቲው በላከልን መግለጫው ጠይቋል።
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ፦
- መንግስት የጀመረው መስጊዶችን የማፍረስ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ተባባሶ ወደ ከፋ ሀገራዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ችግር ከመቀየሩ አስቀድሞ እርምጃውን በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ እስከ አሁን ለደረሱ የህይወት፣ የንብረት እና የስነ ልቦና ጉዳቶች ህዝብን በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤
- ዜጎች የመንግስትን የተሳሳቱና ብልሹ አሰራሮችን የመቃወም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን እንዲያከብር፣
- መንግስት በሀይማኖት ተቋማት ላይ በሚወስደው ኢ -ህገ መንግስታዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ ጣልቃ ገብነት ሀገራችን ወዳልተፈለገ የፖለቲካ ቀውስ መግባቷን ከቅርብ የሀገራችን ታሪክ ትምህርት በመውስድ ራሱን እና ሀገራችንን ከቀውስ እንዲታደግ፣
- መንግስት ራሱ ከፈጠረው ተምኔታዊ የብልጽግና እና ልዕልና ትርክት በተቃራኒ ሀገራችን በተጨባጭ ያላችበትን ጥልቅ እና አሳሳቢ የደህንነት፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ቀውሶችን ከግምት ያስገባ፣ ዜጎች ያሉበትን የከፋ ድህነት እና ስራ አጥነት፣ አድሏዊ እና ብልሹ አሰራር፣ ሙስና፣ በሰላም ወጥቶ የመግባት ስጋት፣ . . . ችግሮችን ያገናዘበ ፈጣን እና ስር ነቀል የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ሀገሪቱን ከከፋ የፖለቲካ ቀውስ እንዲታደግ አሳስቧል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia