TIKVAH-ETHIOPIA


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
መልዕክት መቀበያ @tikvah_eth_BOT
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
#ኢትዮጵያ


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


" ... በከተማው የንጥቂያ እና ዝርፊያ ወንጀሎች #መባባስ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ እያስነሳ ነው " - የጋምቤላ ፖሊስ

በጋምቤላ ከተማ በሞተር ሳይክሎች ላይ የሰዓት ገደብ ተጣለ።

በጋምቤላ ከተማ በተሽከርካሪ የሚፈፀም ስርቆትና ዝርፊያን ለመከላከል ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ድረስ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎች ላይ እገዳ መጣሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰናይ አኩዎር ፤ በከተማው የንጥቂያና ዝርፊያ ወንጀሎች #መባባስ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ እያስነሳ ነው ብለዋል።

በከተማዋ እየተስፋፋ በመጣው የዝርፊያና መሰል ወንጀሎች በዋናነት ተጠቂዎቹ ሴቶችና አቅመ ደካሞች እንደሆኑ ገልፀው ወንጀሎቹን ለማስቀረት የፀጥታ ሀይሉ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ ተናግረዋል።

በተለይም በከተማው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎችን በመጠቀም የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልክ፣ ቦርሳና መሰል ንብረቶችን በመንጠቅና በመዝረፍ የተሰማሩ እንዳሉ በተደረገው ክትትል ለማወቅ መቻሉን አስረድተዋል።

በመሆኑም እነዚህንና መሰል ወንጀሎችን ለመከላከል ሲባል የፀጥታ ቴክኒክ ኮሚቴ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ከግንቦት 20 /2015 ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎች እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ መጣሉን ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።

መረጃው የክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው።

@tikvahethiopia


#UNMAS

ፈንጂዎችን እና ሌሎች የጦር መሣሪያ ቅሪቶችን የማስወገድ ተልዕኮ የተሰጠው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት (UNMAS) በዋናነት በትግራይ ክልል እንዲሁም ጦርነት በተካሄደባቸው አዋሳኝ የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዲሰማራ የኢትዮጵያ መንግሥት ፈቅዷል።

ፈንጂዎችና ሌሎች ያልፈነዱ የጦር መሣሪያ ቅሪቶች ጦርነት በተካሄደባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ አካባቢዎችን ከፈንጂዎች ለማጽዳት እንዲቻል፣ የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት እንዲሰማራ መፈቀዱን የአፍሪካ ኅብረት መረጃ ያመለክታል።

የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት በቅርቡ በመቐለ ከተማ ቢሮውን እንደሚከፍትና ዋና መቀመጫውን በመቐለ አድርጎ በሁሉም ጦርነቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች ኃላፊነቱን ለመወጣት እንደሚሰማራ ተነግሯል።

በዚህ ወር በአፋር ክልል በፈነዳ የወደቀ የሞርታር ጥይት የአራት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን በትግራይ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 300 በሚሆኑት ውስጥ በርካታ የጦር መሳሪያ ቅሪቶች ተገኝተዋል።

Via Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia


" ምዕራባውያን ሚዲያዎች ተሸንፈዋል " - ኤርዶጋን

የቱርክ ጠቅላይ ምርጫ ካውንስል የመጀመሪያ ደረጃ የምርጫ ውጤት የአሁኑ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምርጫውን #ማሸነፋቸውን አመልክቷል።

ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ምርጫውን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በአንካራ ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገዋል።

ምን አሉ ?

ፕሬዜዳንቱ በንግግራቸው " ዛሬ ማንም የተሸነፈ የለም ሁሉም 85 ሚሊዮን ህዝብ አሸንፏል። " ያሉ ሲሆን " አሁን ጊዜው የአንድነት፣ በአገራዊ ግቦቻችን እና ሀገራዊ ህልሞቻችን ዙሪያ መዋሃድ ነው " ብለዋል።

በንግግራቸው የምዕራባውያን ሚዲያዎች እሳቸውን " ለማጥፋት " ሲሰሩ እንደነበር በመጠቆም ፤ " የምዕራባውያን ሚዲያዎች ተሸንፈዋል " ሲሉ ተደምጠዋል።

ኤርዶጋን በቱርክ በዋጋ ንረት ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን መፍታት፣ ከምንም ነገር በላይ " በጣም አስቸኳይ " እና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን በንግግራቸው አንስተዋል።

@tikvahethiopia


#EthiomartShopping

ሴኩሪቲ ካሜራ ሽያጭና ነፃ ገጠማ : 0911582926

security camera CCTV (ባለ 4 አና ባ 8 ካሜራ) ለቤትዎ፤ ለድርጅት፤ ለሱቅ፤ ለፋርማሲ፤ ለዳቦ ቤት፤ ለቡቲክ፤ ለህንጻዎ ፤ ለመጋዘንዎ አና ለንብረትዎ የአመታት ልምድ ባለው ድርጅታችን ሴኩሪቲ ካሜራ ያስገጠሙ።

- 4 ካሜራዎች :- 4 ባለ 20 ሜትር ኦሪጂናል የካሜራ ኬብሎች  35,000 ብር
-8 ካሜራዎች :- 8 ባለ 20 ሜትር ኦሪጂናል የካሜራ ኬብሎች 50,000 ብር

ቦሌ መድሀንያለም ቤዛ ህንጻ 208


#ExodusPhysiotherapy

በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ለትክሻ፣ለወገብ ህመም;ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች ፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !

የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ     #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን።

ስልክ ፦ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.me/ExodPhysioClinic


#UPDATE

በቱርክ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ #አሁናዊ የድምፅ ቆጠራው 99.20 በመቶ ደርሷል።

በዚህም የአሁኑ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን 52.08 % በመቶ ድምፅ ምርጫውን እየመሩ ሲሆን የኤርዶጋን ዋነኛ ተቀናቃኝ ክሊክዳርጎሉ 47.92 % ድምፅ በማግኘት እየተከተሏቸው ነው።

አሁናዊው ውጤት የኤርዶጋንን ማሸነፍ እና ለ5 ዓመታት የሀገሪቱ መሪ ሊያደርጋቸው የሚችል መሆኑን የሚያመላክት መሆኑን ተከትሎ ደጋፊዎቻቸው ደስታቸውን ለመግለፅ አደባባይ ወጥተዋል።

የሀገራት መሪዎች ለኤርዶጋን የ " እንኳን ደስ አልዎት " መልዕክት እያስተላለፉ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia


#UPDATE

በቱርክ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ አሁናዊ የድምፅ ቆጠራው 97.94 በመቶ ደርሷል / የድምፅ ሳጥን ተከፍቶ ቆጠራ ተካሂዷል።

በዚህም የአሁኑ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን 52.14 % በመቶ ድምፅ ምርጫውን እየመሩ ሲሆን የኤርዶጋን ዋነኛ ተቀናቃኝ ክሊክዳርጎሉ 47.86 % ድምፅ በማግኘት እየተከተሏቸው ነው።

ከወዲሁ የሀገራት መሪዎች ለአሁኑ ፕሬዜዳንት የ " #እንኳን_ደስ_አልዎት " መልዕክት እያስተላለፉ ይገኛሉ።

@tikvahethiopia


#Update

ዛሬ በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በድጋሜ ህዝቡ ድምፁን ሲሰጥ ውሏል።

በአሁን ሰዓት የድምፅ ቆጠራው እየተካሄደ ይገኛል።

እስካሁን ባለው 96.01 በመቶ የድምፅ ሳጥን ተከፍቶ በተካሄደ ቆጠራ ፦

- ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን 52.28 % 
- የኤርዶጋን ዋነኛ ተቀናቃኝ ክሊክዳርጎሉ 47.72 % ድምፅ አግኝተዋል።

በቱርክ ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው ምርጫ ተወዳዳሪዎች የሚፈለገውን ያህል  ድምጽ (ከ50 በመቶ በላይ) ማግኘት ባለመቻላቸው ምርጫው በድጋሚ እንደሚደረግ መገለፁ የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia


" ከፍትሕ ማምለጥ እንደማይችሉ ማሳያ ነው "

ካለፉት 22 ዓመታ ጀምሮ ሽሽት ላይ የነበረውና በሩዋንዳ የዘር ማጥፋት ወቅት ከዘር ማጥፋት እልቂት ለማምለጥ በቤተክርስቲያን የተሸሸጉ 2,000 (ሁለት ሺህ) ቱትሲዎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ በማስተላለፍ የተጠረጠረው ፉልጌንሴ ካይሼማ መያዝ ምንም ያህል ጊዜ ቢወስድ እንዲህ አይነት ድርጊት የፈፀሙ ሰዎች #ከተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይችሉ ማሳያ ነው ተብሏል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የግለሰቡን መታሰር መሰል ወንጀሎችን የፈፀሙ ከፍትህ ማምለጥ እንደማይችሉ ትልቅ መልዕክት የሚያስተላልፍ ነው ብለዋል።

ጉተሬዝ ፤ " እንዲህ አይነት ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ ሰዎች ከፍትህ ሊያመልጡ እንደማይችሉ እና ከሩብ ምዕተ አመት በኋላም ቢሆን #ተጠያቂ እንደሚሆኑ የሚያሳይ ኃይለኛ መልእክት ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

እ.አ.አ በ1994 በሀገረ ሩዋንዳ በአክራሪ ሁቱዎች በተፈጸመ የዘር ማጥፋት፣ 800 ሺሕ የሚሆኑ ቱትሲዎች መገደላቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia


#ነዳጅ

ለመጪው የ2016 ዓ/ም ወደ አገር ለማስገባት ለታቀደው 4.3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ 4.4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት አስታውቋል።

ኢትዮጵያ በ2016 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋትን ነዳጅ ለማስገባት የወጣውን ዓለም አቀፍ ጨረታ፣ " ቪቶል " የተባለው የባህሬን ኩባንያ በድጋሚ በማሸነፉ የኮንትራት ውል ስምምነት ተፈርሟል፡፡

ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት በ2016 ዓ.ም. ለማስገባት ያቀደውን ሙሉ ለሙሉ ቤንዚን፣ እንዲሁም ከጠቅላላው የነጭ ናፍጣ ግዥ 40 በመቶውን " ቪቶል " ኩባንያ እንደሚያስገባ ታውቋል፡፡

በስምምነቱ መሠረት ለ1 ዓመት የሚያስፈልገውን 760 ሺሕ ሜትሪክ ቶን ቤንዚንና 1.2 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ነጭ ናፍጣ ኩባንያው ያቀርባል፡፡

" ቪቶል " ጨረታውን ያሸነፈው ከሁለት ሌሎች ኩባንያዎች ጋር ተወዳድሮ እንደሆነ ተነግሯል።

" ቪቶል " እየተጠናቀቀ ላለፈው የበጀት ዓመት በተመሳሳይ የወጣውን ጨረታ አሸንፎ ሲያቀርብ ነበር።

ለ2016 በጀት ዓመት ያስፈልጋል ተብሎ የታቀደው ነዳጅ ከ2015 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በስምንት በመቶ ብልጫ አለው፡፡

በተናጠል ሲታይ ቤንዚን ስምንት በመቶና ነጭ ናፍጣ አምስት በመቶ ጭማሪ ይኖራቸዋል፡፡ 

Via Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia


#EthiomartShopping

ሴኩሪቲ ካሜራ ሽያጭና ነፃ ገጠማ : 0911582926

security camera CCTV (ባለ 4 አና ባ 8 ካሜራ) ለቤትዎ፤ ለድርጅት፤ ለሱቅ፤ ለፋርማሲ፤ ለዳቦ ቤት፤ ለቡቲክ፤ ለህንጻዎ ፤ ለመጋዘንዎ አና ለንብረትዎ የአመታት ልምድ ባለው ድርጅታችን ሴኩሪቲ ካሜራ ያስገጠሙ።

- 4 ካሜራዎች :- 4 ባለ 20 ሜትር ኦሪጂናል የካሜራ ኬብሎች  35,000 ብር
-8 ካሜራዎች :- 8 ባለ 20 ሜትር ኦሪጂናል የካሜራ ኬብሎች 50,000 ብር

ቦሌ መድሀንያለም ቤዛ ህንጻ 208


በሲቢኢ ብር ነዳጅ ሲቀዱ ሁለት አማራጮች አሉ!
***************

 የመጀመሪያው

ራስዎ ወደ ሲቢኢ ብር መተግበሪያዎ ‘Quick Pay’ በመግባት ‘Fuel Payment’ የሚለውን የአገልግሎት አማራጭ መርጠው አስፈላጊውን መረጃ በማስገባት ክፍያ ፈጽመው ነዳጅ የሚቀዱበት ነው፡፡

 ሁለተኛው

ለነዳጅ ቀጂ ባለሙያው ሲቢኢ ብር የተመዘገቡበትን ስልክ ቁጥር ߹ የሰሌዳ ቁጥርዎን እና የሚቀዱትን ነዳጅ የገንዘብ መጠን አሳውቀው በሚደርስዎት አጭር መልእክት መሠረት የገንዘብ መጠኑን ትክክለኛነት አረጋግጠው ክፍያውን በመፈፀም ነዳጅ የሚቀዱበት አማራጭ ነው።

****************
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለመጫን ወይም ለማዘመን፡
ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787


#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ፤ ዛሬ በላከልን መግለጫ መንግስት ከጁመዓ ሰላት በኃላ በምዕመናን ላይ እርምጃ መውሰዱንና ይህንንም በፅኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል።

ፓርቲው ፤ " ባለፉት ጥቂት ወራት በ ' ሸገር ከተማ ' እየተካሄደ ያለውን ' ህገወጥ ' መስጂዶችን የማፍረስ እርምጃ በሰላማዊ መንገድ በመቃወም በአዲስ አበባ በተለይ በአንዋር መስጂድ ከጁምአ ሰላት በኃላ ድምጻቸውን ባሰሙ ሙስሊሞች ላይ በተወሰደው እርምጃ የሰው ህይወት አልፏል ፣ በርካታ ምዕመናን ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል " ያለ ሲሆን " የተወሰደው የእብሪት እርምጃ ነው ፤ ይሄንንም በፅኑ እናወግዛለን " ሲል አሳውቋል።

መንግስት ከሀይማኖት ተቋማት ላይ እጁን እንዲያነሳ ፣ የሀይማኖት እና የመንግስትን ህገመንግስታዊ ልዩነት እንዲያከብር ፓርቲው በላከልን መግለጫው ጠይቋል። 

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ፦

- መንግስት የጀመረው መስጊዶችን የማፍረስ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ተባባሶ ወደ ከፋ ሀገራዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ችግር ከመቀየሩ አስቀድሞ እርምጃውን በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ እስከ አሁን ለደረሱ የህይወት፣ የንብረት እና የስነ ልቦና ጉዳቶች ህዝብን በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤

- ዜጎች የመንግስትን የተሳሳቱና ብልሹ አሰራሮችን የመቃወም ህገ መንግስታዊ መብታቸውን እንዲያከብር፣

- መንግስት በሀይማኖት ተቋማት ላይ በሚወስደው ኢ -ህገ መንግስታዊና ኢ-ዴሞክራሲያዊ ጣልቃ ገብነት ሀገራችን ወዳልተፈለገ የፖለቲካ ቀውስ መግባቷን ከቅርብ የሀገራችን ታሪክ ትምህርት በመውስድ ራሱን እና ሀገራችንን ከቀውስ እንዲታደግ፣

- መንግስት ራሱ ከፈጠረው ተምኔታዊ የብልጽግና እና ልዕልና ትርክት በተቃራኒ ሀገራችን በተጨባጭ ያላችበትን ጥልቅ እና አሳሳቢ የደህንነት፣ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ቀውሶችን ከግምት ያስገባ፣ ዜጎች ያሉበትን የከፋ ድህነት እና ስራ አጥነት፣ አድሏዊ እና ብልሹ አሰራር፣ ሙስና፣ በሰላም ወጥቶ የመግባት ስጋት፣ . . . ችግሮችን ያገናዘበ ፈጣን እና ስር ነቀል የማስተካከያ እርምጃ በመውሰድ ሀገሪቱን ከከፋ የፖለቲካ ቀውስ እንዲታደግ አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia


#AmharaRegion

" 522 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ፤ የተገኘው ሀብት ግን ዝቅተኛ ነው " - የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ

በአማራ ክልል ፤ #በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች መልሶ ለመገንባት 522 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ሲል የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ አሳውቋል።

ይህን ያሳወቀው የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ የመንግሥትና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዓመታዊ የአጋርነት የምክክር መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።

ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ በተከሰተው ችግር 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዜጎች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅለው በክልሉ እንደሚገኙ የገለፀው ቢሮው ፤ 11 ነጥብ 4  ሚሊዮን ሕዝብ  ደግሞ በጦርነቱ ምክንያት በከፍተኛ  የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጫና ውስጥ እንደሚገኙ ጠቁሟል።

ሰባት ዞኖችና ሶስት ሜትሮፖሊታንት ከተሞች በጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸእ የተገለፀ ሲሆን እነዚህን ዞኖች መልሶ ለማቋቋም እና  መልሶ ለመገንባት ከ522 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ይጠይቃል ብሏል።

ጉዳት የደረሰባቸውን ዞኖች  መልሶ ለመገንባት ጥረት ቢደረግም  የተገኘው ሀብት ዝቅተኛ በመኾኑ የተፈለገውን ውጤት ማምጣት አለመቻሉን ቢሮው አመልክቷል።

ቢሮው ፤ መንግሥት ከሚያደርገው ሥራ ባለፈ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በተለያዩ የልማት ሥራዎች እና በመልሶ ግንታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህ ዓመትም በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 374 ፕሮጀክቶች በክልሉ እየተከናወኑ ነው ተባቧል።

ድርጅቶች በቀጣይም የጀመሩትን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።

#AMC

@tikvahethiopia


#Update

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ ባለ አስራ አንድ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ጉባዔዉን አጠናቋል።

ከአቋም መግለጫዎቹ መካከል ፦

- በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ በአንዋር እና በኑር መስጂዶች የተፈጠረው ክስተት #እንዴት_እንደተፈጠረና የደረሰውን ሞትና ጉዳት መንስኤዎች የሚያጣራ ከመንግስትና የእስልምና ጉዳይ ም/ቤት በጋራ ያሉበት ገለልተኛ አጣሪ ቡድን #በአስቸኳይ እንዲቋቋም ተጠይቋል።

- በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በ " ሸገር ከተማ " ኢስላምንና ሙስሊሞችን በናቀ መልኩ በመስጂዶች ላይ እየተደረገ ያለው የጅምላ ፈረሳ ሂደት በአስቸኳይ እንዲቆም፥ እንዲሁም ለፈረሱት መስጊዶች የክልሉ መንግስት #ምትክ_ቦታ በመስጠት በአስቸኳይ ተመልሰው እንዲገነቡ በማድረግ ሕዝበ ሙስሊሙን በይፋ ይቅርታ በመጠየቅ እንዲክስ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

- በኦሮሚያ ክልልም ሆነ በሌሎች የሀገራችን ክልሎች ለእምነት ቦታዎች ተገቢውን ክብርና ጥበቃ እንዲደረግ፥ እንዲሁም ለመስጂዶች ካርታ በመከልከልና ሆነ ብሎ ቢሮክራሲውን በማንዛዛት ሕዝቡን ላማረሩ ዘርፈ ብዙ ችግሮች መንግስት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት በአፋጣኝ እንዲፈታቸው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

- ሕዝበ ሙስሊሙ ከመሪ ተቋሙ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ጎን በመቆም ሃይማኖታዊ መብቶችን ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት በሕጋዊ እና ሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።

- መንግስት ኢስላም ጠል የሆኑ እና በመንግስት መዋቅር ዉስጥ በተለያዩ እርከኖች ያሉትን አካላት በመገምገም እና በማጥራት ሕዝብንና መንግስትን ሆነ ብለው ለማጋጨትና ሀገሪቷን ወደ ለየለት ቀውስ ለመውሰድ እየሰሩ ያሉ አካላትን ፈትሾ ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ መዋቅሩን እንዲያጠራ ጥሪ ቀርቧል።

(ዝርዝር የአቋም መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

15 last posts shown.