TIKVAH-ETHIOPIA


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


#Update

" የሟች ቤተሰብ ተገኝቷል " - ፖሊስ

በሟች ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ በማጣቱ  ምክንያት የሟችን ፎቶ በመለጠፍ  ቤተሰቦቹን አፋልጉኝ ያለው የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ የሟች ቤተሰብ መገኘቱ አስታውቋል።

የማህበራዊ የትስስር ገፆችና ሚድያዎች በሟች ቤተሰብ ፍለጋ ያደረጉት የነቃ ወገናዊ ተሳትፎና ጥረት አመስግኗል።

ለሟቹ ቤተሰብ ክብር ሲባል ፎቶውን ከገፃቸው በማጥፋት እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።

በዚህም መሰረት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሟች ቤተሰብ ክብር የሟችን ፎቶ #ማጥፋቱን ለመላ አባላቱ መግለጽ ይወዳል።

ምናልባት በውስጥ የተቀባበላችሁም የሟችን ፎቶ ከስልካችሁ እንድታጠፉ እንጠይቃለን።

ሚያዝያ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት በዓዲግራት ከተማ አንድ ወጣት ተገድሎ ተጥሎ መገኘቱንና በግድያው የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች ሟቹ ከወደቀበት አቅራቢያ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር መዋላቸው መረጃ እንደላክልንላችሁ ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia


#Update

በኢራን " ኢስፋሃን ከተማ " ዛሬ ማለዳ ፍንዳታዎች የተሰምተው ነበር።

ይህች ከተማ የአገሪቱ አየር ኃይል መቀመጫ ፣ በርካታ ወታደራዊ ተቋማት ያሉባት ናት።

የኢራን መገናኛ ብዙኃን በደፈናው 3 ድሮኖች በኢራን የአየር መከላከያ ሥርዓት ወድመዋል ሲሉ ገልጸዋል።

#የአሜሪካ ባለልስጣናት እስራኤል ቅዳሜ ለተፈጸመባት ጥቃት ኢራን ላይ የሚሳኤል የአጸፋ ጥቃት ፈጽማለች ብለዋል።

የኢራን በይፍ የሰጠችው ማብራሪያ ባይኖርም የተሰማው ፍንዳታ ጥቃትን የማክሸፍ እንደነበር አሁን ላይ ከተማዋ በመደበኛ እንቅስቃሴ እንደምትገኝ ገልጸዋል።

የደረሰ አንዳች ጉዳት እንደሌለ ጠቁመዋል።

በኑክሌር ተቋማት ላይ ምንም ጉዳት አለመድረሱን ተነግሯል።

ምንም እንኳን በመገናኛ ብዙሃን እና በአሜሪካ ባለስልጣናት እስራኤል የጸፋ እርምጃ መውሰዷ ቢነገርም ሀገሪቱ እስካሁን በይፋ " ኃላፊነት እወስዳለሁ " አላለችም።

ኢራንም ፥ " እስራኤል ናት ይህንን ያደረገችው ቀጣይ እርምጃዬ ይሄ ነው " የሚል ይፋዊ ቃል አልሰጠችም።

ነገር ግን ጉዳዩ አሁንም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ስጋትን እንደደቀነ ይገኛል።

ሀገራት ከወዲሁ በእስራኤል ላሉ ዜጎቻቸው ማስጠንቀቂያ እየሰጡ ናቸው።

ኢራን እስራኤልን ከቀናት በፊት መደብደቧን ተከትሎ እስራኤል የአፀፋ እርምጃ እንደማይቀርላት ተናግራለች።

ኢራንም እስራኤል የአጸፋ እርምጃ እወስዳለሁ ካለች እስከ ዛሬ ጥቅም ላይ ያልዋለ መሳሪያ እንደምትጠቀምና እርምጃዋ ከመጀመሪያው እየከፋ እንደሚሆን አስጠንቅቃለች።

ኢራን ፥ ጦርነቱ እንዲስፋፋ እንደማትፈልግ ነገር ግን ደፍሮ የሚያጠቃት የትኛውም አካል ካለ " እጁን እንቆርጥለታለን " ስትል ነው ከሰሞኑን የዛተችው።

@tikvahethiopia


#ሴጅ_ማሠልጠኛ

10ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy and Auditing) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።

👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Facebook: https://www.facebook.com/sagetraininginstitute
Instagram: https://www.instagram.com/sage_training_institute/
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


ንጹሕ_ምንጭ _ኢትዮጵያ ሊፈፀም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀረው

በግዮን ሆቴል እስከ ሚያዚያ 13 ብቻ፡፡
ለልጆችዎ ቦታ አለን


📌ማስታወሻ :- በተለይ ሚያዚያ 12 እና 13 ምሽት 11ሰአት ጀምሮ በዓይነቱ ልዩ የሆነ የኪነጥበብ ምሽት ከ ዐውደ ርእዩ ጋር በጥምረት ይቀርባል።
📌ማስታወሻ :- በተለየ መንገድ ቅዳሜ ሚያዚያ 12/2016ዓ.ም. የልጆች ልዩ የመዝናኛ ኪነ ጥበባዊ ዝግጅቶች ይካሄዳል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች ላይ እንዲገኙ ለሌሎችም እንዲያጋሩ በታላቅ አክብሮት እንጋብዛችኋለን። ለበለጠ መረጃ ፦0966767676 ወይም 0944240000 ይደውሉ። INSTAGRAM | TELEGRAM | @hamereberhan' rel='nofollow'>YOUTUBE | TWITTER | TIKTOK |WEBSITE


#ኢትዮጵያ

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች አንድ አባት  በጎረምሶች ተከበው ሲመቱ ፣ ሲሰደቡ ፣ ሲዘለፉ ፣ ሲዋከቡ በቪድዮ ታይቷል።

ይህን እጅግ አሳፋሪና በምን አይነት ሁኔታ ላይ እንዳለን ሚያሳይ ቪዲዮ ያጋሩት ደግሞ እራሳቸው የድርጊቱ ፈጻሚዎች ናቸው።

ድርጊቱ ብዙዎችን ክፉኛ አስቆጥቷል። በርካቶች ስለ ነገ በማሳብ ፍርሃት ውስጥ ከቷቸዋል።

በእርግጥ በሀገራችን ያላየነው ግፍ ፣ ያልሰማነው ክፉ ተግባርና ጭካኔ ምን አለ ? እንዘርዝር ብንልስ ቦታው፣ ጊዜው  ይበቃናል ? በፍጹም !

ከዚህ በፊትም እንደምንለው በቪዲዮዎች ተቀርጾ የምናየው ምናልባትእድለኞች ሆነን ከብዙ አንዱ እንጂ ስንት ያላየነው ይኖራል።

ወደ ቪድዮው ስንመለስ ተከበው ሲመቱ፣ ሲዋከቡ ፣ ሲዘለፉ የነበሩት አባት ' እንጀራ ፍለጋ እግር ጥሏቸው እንደመጡ ' ይገልጻሉ የሚጠይቀን የለም ባዮች ጎረምሶች ' እዚህ አካባቢ ምን ትሰራለህ ? ለምን እዚህ መጣህ ? ከመጣህበት ቦታስ እንጀራ የለም ? ' ሲሉ እጅግ በንቀት ያዋክቧቸዋል።

ይህን ተግባራቸውን እንደ በጎ ስራ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አጋርተውታል።

የትኛውም ዜጋ በገዛ ሀገሩ የመንቀሳቀስ መብት አለው ? ካልሆነ ስለምን #ኢትዮጵያዊ ይባላል ? ጥፋት ካለበት ፣ ከተጠረጠረ የሚጠይቀው ህግ እንጂ የሰፈር ጎረምሳ አይደለም። ግለሰቦቹ ጥርጣሬ አለን ካሉ ህግን ማሳወቅ እንጂ ማነው ፤ የትኛው ህግ ነው ይህንን መብት የሰጣቸው ? 

ይህ ተግባር በተለይ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተነዛ ያለው የጥላቻ ስብከት ምን ያህል ስር እንደሰደደ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ሲሆን ነገን እጅግ አስፈሪ ያደርገዋል።

ግልጽ የሆነ የብሄርና የግለሰቦች ጥላቻ ፣ ልብም አእምሮም በጥላቻ መሞላት፣ አይንም በጥላቻ መታወር ፦
- ሌላው ይቅር ታላላቆቻችን እንዳናከብር
- ለእምነታችን ፣ ለሃይማኖታችን ቦታ እንዳይኖረን
- ለሰው ልጅ ትንሽ እንኳን ቦታ እንዳንሰጥ
- ለህግ እና ስርዓት ቅንጣት ታክል ደንታ እንዳይኖረን
- ባህል፣ ወግ ፣ አብሮነት ለሚባለው ጉዳይ ቦታ እንደሌለን
- ነገ እኔስ ምን ይገጥመኛል ? ምን እሆን ይሆን ? በህይወት አጋጣሚ የት እሄዳለሁ ፣ ምን አካባቢ እገኛለሁ የሚለውን ለማገናዘብ እንኳን እንዳንችል ያደርገናል።

ሰዎች ወደው ሳይሆን በስርዓት፣ በግለሰቦች፣ በአንቂዎች ፣ በሚዲያዎች... አማካኝነት ነው ጥላቻ እንዲውጣቸው እና ማገናዘብ ፣ ቆም ብሎ ማሰብ የሚባለውን መሰረታዊ ነገር እንዲያጡት የሚሆነው።

ሰዎች ከመሰል ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አብሮነት ፣ ፍቅር ፣ መግባባት፣ መከባበር ፣ ህግ ፣ ስርዓት፣ ወንድማማችንነትን ከማስተማር ባለፈ በህግ ማረም ፣ ነገ መዘዙ የከፋ እየሆነ ስለሚሄድ ከወዲሁ እንዲገታ በአንድ ላይ ማውገዝ ፣ ተበዳይን መካስ ፣ እውነት ህግ የበላይ ነው የምንል ከሆነም ለራሳችን ስንል ህግን ሁሌም ማስከበር ነው።

ዛሬ ላይ እንዲህ ያሉና ከዚህ ቀደምም በየሀገሪቱ ክፍሎች የሰማናቸው ፍጹም አደገኛ የሚባሉ ጉዳዮች የሳምንት አጀንዳ እየሆኑ እያለፉ ይመስለን ይሆናል ግን በእርግጠኝነት መዘዛቸው የከፋ ሊሆን ይችላል።

ውጤታቸው ዛሬ ሳይሆን ውሎ አድሮ ምናልባትም አመታትን አልፎ ይታይ ይሆናል ስለሆነም እናስብበት ! ትውልዱን ከስህተቱ እናርመው ፤ ወገኑን እንዲጠላ ሳይሆን እንዲወድ ፣ እንዲያከብር እናስተምረው።

በሁሉም ዘንድ አውቀናል ታውቀናል ፣ ዛሬ ስልጣን አለን፣ ሚዲያውም የኛው ነው የምንል ሰዎችም ' አይ የኔ ወገን ስለሆነ ፍጹም ጻዲቅ ነው ፣ አይሳሳትም ፣ ጀግና ነው ፣ ቢሳሳትም ምንም ችግር የለውም እኔ እከላከልለታለሁ ' ከሚል አደገኛ እና ብዙ መዘዘ ካለው አመለካከት መራቅ ይገባናል።

#TikvahFamily
#Ethiopia

@tikvahethiopia


#ATTENTION🚨

“ የካንሰር ሕመም እየጨመረ ነው ” - ዶክተር አስቻለው ወርቁ

በኢትዮጵያ የካንሰር ተጠቂዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን፣ በተለይም ማኀበረሰቡ ትንቦሆ፣  አልኮል ነክ ነገሮችን ከመጠቀም እንዲታቀብ ጥሪ ቀረበ።

ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት እየተሰጠ ቢሆንም በተለይ በኢትዮጵያ በኩል የፋይናንስ እጥረት ችግር እንደፈተነው ማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ተቋሙ የ20ኛ ዓመት ምስረታውን በማስመልከት መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ካንሰር #በኢትዮጵያ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? በበሽታው የተጠቂ ሰዎች ቁጥር ቀነሰ ወይስ ጨመረ ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል።

የተቋሙ የቦርድ አባልና የውስጥ ደዌ ባለሙያው ዶክተር አስቻለው ወርቁ ምን አሉ ?

“ በጣም እየጨመረ ነው ያለው። ለመጨመሩ የተለያዩ ምክንያቶች ይኖራሉ። በአጠቃላይ ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎች እየጨመሩ ነው። የካንሰር ህመምም እየጨመረ ነው።

ለምሳሌ፦ የሳንባ ካንሰርን ብናዬው ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ነው ያለው። የምንመረምረው ጥቂት ሰዎችን ስለሆነ በዚያችው ዳታ ተመርኩዘን ነው የምንገልጸው። ማኀበረሰቡን ያማከለ የዳሰሳ ጥናት ካልሰራን ቁጥሩን በትክክል መግለጽ ከባድ ነው።

10 ሰዎችን መርምሮ 5 ሕሙማን ቢገኝ 50 በመቶ ማለት አይቻልም። ምክንያቱም ያልተመረመሩ ብዙ ስለሚኖሩ። እንደ አጠቃላይ ካየነው ግን ፦
- የሳንባ፣
- የአንጀት፣
- የጉበት፣
- የማህፀን፣
- የደም ሴል ካንሰር ታማሚሞች ቁጥራቸው እጅግ ባጣም እየጨመረ ነው ያለው። ” ብለዋል።

ካንሰር ዋነኛ የሞት እና የስቃይ ምክንያት እየሆነ መምጣቱን ቁጥሮች እንደሚያመላክቱ ተገልጿል።

ለአብነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከሞቱ ሰዎች ካንሰር የመገኘት እድሉ ከፍ ብሏል። ምክንያቱም የሳንባ ካንሰር ካሉት የካንሰር ዝርዝሮች ወደ 6ኛ ደረጃ ላይ ነው ያለው ተብሏል።

የማቲዎስ ወንዱ ካንሰር ሶሳይቲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንዱ በቀለ ምን አሉ ?

“ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትንባሆ መሸጥም መግዛትም እንዳይችል የሚነገርበት ጊዜ መቼ ነው ?

ትንባሆ ነክ ነገሮች፣ አልኮል በሽታውን እያስፋፉት ነው።
 
ከ3,000 በላይ የካንሰር ሕሙማንና ቤተሰባቸውን እረድተናል። በአሁኑ ወቅት 175 ለካንሰር ሕሙማንና ለቤተሰባቦቸው፦

° ከአገራቸው የሚመጡበት ሙሉ የትራንስፖርት፣
° ከውጪ የሚገዙ መድኃኒቶች፣ 
° በሆስፒታል ውጪ በግል ተቋማት ለሚሰሩ የላብራቶሪ ምርመራ፣ 
° ሆስፒታል ለተኙት ሕሙማን ለአንዳንድ ነገር መሸፈኛ በወር 1,000 ብር፣
° እየታከሙ ለሚማሩ ተማሪዎች በወር 1,000 ብር፣
° 24 አልጋ ባለው የካንሰር ሕክምና ማዕከል በየዕለቱ ለቁርስ፣ ምሳ፣ በክሰስና እራት ወጪዎችን እየሸፈንን ነው። ”

NB. ማቲዎስ ወንዱ የኢትዮጵያ ካንሰር ሶሳይቲ የአቶ ወንዱ በቀለ የ4 ዓመት ጨቅላ ልጃቸው በካንሰር በሽታ ሕይወቱ ማለፉን ተከትሎ ቤተሰቦቹ የደረሰባቸውን መሪር ሀዘን “ ማቲዎስ ቢሞትም ብዙ ማቲዎሶችን ማዳን እንችላለን ” በሚል መልካም አስተሳሰብ በመቀየር በ15 መስራች አባሎች ሚያዚያ 9 ቀን 1996 ዓ/ም የተመሠረተ ለካንሰር ሕሙማን የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" የሟች ኪስ ውስጥ #ማንነቱን የሚገልጽ መረጃ ስላላገኘን ፎቶውን ለማሰራጨት ተገደናል "  - የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ

በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዓዲግራት ከተማ  ቀበሌ 03 በተባለ መጠጥ ቤቶች በብዛት በሚገኙበት ቦታ ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ሌሊት አሰቃቂ ግድያ ተፈፅሟል።

አስቃቂ ግድያው በመፈፀም የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች በህዝብ ጥቆማ የሟቹ አስከሬን በወደቀበት አከባቢ በሚገኝ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር ውለው የሟች አስከሬን ወደ ዒድግራት ሆስፒታል ተወስደዋል።

የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ምርመራው ጨርሶ ለቀብር የሟቹ ቤተሰብ ቢያፈላልግም ዜናው እስከ ተጠናቀረበት ቀን ሰዓትና ደቂቃ የሟች ቤተሰብ አልተገኙም።

በሟቹ ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ እንዳላገኘ የገለፀው የዓዲግራት ፓሊስ ፤ የሟቹ ፎቶ በሚድያና በማህበራዊ የትስስር ገፅ ለማስራጨት መገደዱን ገልጿል።

ሟቹን የሚያውቅ ካለ ወደ ዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት ደውሎ እንዲያሳውቅ ፖሊስ ትብብር ጠይቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

ፍቶ፦ የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት 
                                             
@tikvahethiopia            


#Ethiopia #Attention🚨

የትራፊክ አደጋ የበርካቶች ህይወት እየቀጠፈ ይገኛል።

በዚህ ወር ብቻ ፦

- በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምስራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 2 ሰዎች ሲሞቱ 5 ሰዎች ተጎድተዋል።

- በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ወረዳ ከኔጌሌ ወደ ዶዶላ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ መኪና 'አላንቱ' ላይ ከ " ሲኖትራክ " የጭነት መኪና ጋር ተጋጭቶ የ15 ሰዎች ህይወት አልፏል። ሌሎችም ተጎድተዋል።

- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በካፋ ዞን ጨና ወረዳ ፤ ከዋቻ ወደ ቦንጋ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሸከርካሪ እና ከሚዛን ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ ተሸከርካሪ በጨና ወረዳ ቦባ በላ ቀበሌ ተጋጭተው 5 ሰዎች ሲሞቱ 13 ሰዎች ተጎድተዋል።

-  በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን በእዣ ወረዳ ወርት በተባለች ቀበሌ እንጨት ጭኖ ሲጓዝ የነበረ #ሲኖ_ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ   የ6 ወጣቶች ህይወት ወዲያዉ ሲያልፍ በ10 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋዉን የከፋ ያደረገው ሲኖ ትራኩ  ወጣቶችን እንጨት ላይ አሳፍሮ እየተጓዘ ባለበት ወቅት አደጋው በመድረሱ ነው።

ከላይ በተጠቀሰው እና በይፋ በታወቀው ብቻ 28 ዜጎች በትራፊክ አደጋ ህይወታቸውን አጥተዋል። በርካቶች የአካል ጉዳተኛ ሆነው።

እባካችሁ ጥንቃቄ አይለያችሁ !

@tikvahethiopia


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
የረቂቅ መንገድ

እራሳችንን እንደመስታወት የምናይበት…ሌሎችን እንደ መፅሐፍ የምናነብበት! የጠፋብን ያልተገለጠልን ነገር ካለ ያለጥርጥር የረቂቅ መንገድ ላይ እናገኘዋለን።

በቅርብ ቀን በአቦል ቲቪ 465!

የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።
የዲኤስቲቪ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #YerekikMenged #የረቂቅመንገድ


"ጥበብ እንደ መፈወሻ መንገድ/  Art as a path to healing" ኦላይን የስዕል ኤግዚቢሽን

በትግራይ መቐለ ከተማ ከወርሃ የካቲት እስከ ሚያዝያ 2016 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየውና ከ387 ተመዝጋቢዎች የተመረጡ 61 ታዳጊና ወጣት ሰአልያን የተሳተፉበት የቡድን የስእል ውድድር አሸናፊዎችን በመለየት ተጠናቋል።

በውድድሩ ወጣቶቹ በ10 ቡድን በመከፋፈል 10 ስዕሎችን ያቀረቡ ሲሆን፤ ስዕሎቹም ጦርነትን፣ ዘረኝነትን፣ የእርስ በርስ ግጭትና ጠባብነት በማውገዝ ሰላም አንድነት ስር እንዲሰድ የሚሰብኩ ነበሩ።

እነዚህን ስዕሎች ኦላይን በተዘጋጀው ኤግዚቢሽን እንድትመለከቷለቸው እንጋብዛለን።

ወደ ኤግዚቢሽኑ ጎራ ለማለት ተከታዩን ሊንክ ይጠቀሙ https://redeem.tikvahethiopia.net/paintings

#USAID     #RTG   #TikvahEthiopia


" ጥናቱ ሙሉ በሙሉ ቆሟል " - የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሰዓት ከስምንት ወደ 16 ሰዓት ለማራዘም የተጀመረው ጥናት መቆሙን የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።

ጥናቱ የተጀመረው በከተማ አስተዳደሩ ሥር በሚገኙ የመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች የግል ገቢ እንዲኖራቸው፣ እንዲሁም የከተማዋን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማነቃቃት ታስቦ መሆኑን ቢሮው ማስታወቁ ይታወሳል።

አሁን ላይ ግን የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሥራ ሰዓት ለማራዘም የተጀመረው ጥናት ሙሉ ለሙሉ ቆሟል፡፡

የከተማው የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጣሰው ገብሬ (ዶ/ር) ፥ " የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችን የሥራ ሰዓት ለማራዘም መነሻ ጥናት ተደርጎ ነበር ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅት ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የለም " ሲሉ ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል።

ኃላፊው በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ መስጠት እንደማይፈልጉ ተናግረዋል።

ወደፊት የታሰበው አሠራር ተግባራዊ ይደረጋል አይደረግም የሚለውን እንደማያውቁ ገልጸዋል።

ጥናቱ የተጀመረው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር የሚገኙ መሥሪያ ቤቶችን የሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 አስቀድሞ ለማስጀመርና ከ11፡30 በኋላ እስከ ምሽት ለማስቀጠል ታቅዶ ነበር፡፡

ዕቅዱ ይፋ የተደረገው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የከተማዋ መ/ቤቶች አገልግሎት አሰጣጥን አስመልክቶ መሆኑን ቢሮው ግንቦት 3 ቀን 2015 ዓ.ም. ከባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው ውይይት መግለጹን ሪፖርተር ጋዜጣ በዘገባው አስታውሷል።

@tikvahethiopia


“ ለፍጻሜው ምክንያት እንሁን ”

የመጠናቀቂያ ጊዜ ላለፈው የቅድስት ሥላሴ ካቴደራል እድሳት 85 ሚሊዮን ብር ድጋፍ በማድረግ “ ለፍጻሜው ምክንያት እንሁን ” ስትል ቤተክርስቲያኗ ጥሪ አቀረበች።

የካቴደራሉ እድሳት በውሉ መሠረት ሥራው የሚጠናቀቅበት የጊዜ መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ/ም የነበረ ቢሆንም፣ የውጪ ምንዛሬ ተጠይቆ ባለመገኘቱ ለመጠናቀቅ ተጨማሪ የ3 ወራት የጊዜ ለኮንትራክተር እንደተጨመረ ቤተክርስቲያኗ ገልጻለች።

ሥራው የሚጠናቀቅበት የጊዜ ገደብ ያለፈው ከውጪ አገር የሚገቡ ፦
- የዶም ኮፐር ቀለም፣
- የውጫዊ ግድግዳ ቀለም፣ 
- ሞዛይኮች፣ 
- ጀነሬተር እንዲሁም መብራቶችን ለማስገባት በውጪ ምንዛሪ የሚገዙ በመሆናቸው ምንዛሪው ቢጠየቅም ባለመገኘቱ ነው ተብሏል።

የቅድስት ሥላሴ ካቴደራል ኃላፊዎች ይህን ያሉት ዛሬ (ሐሙስ ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ/ም) በካቴደራሉ ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

በዚህም የካቴደራሉ ህንጻ ጥገና ሥራ 75 በመቶ እንደደረሰ፣ ለማጠናቀቅ 85 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ፣ እስካሁን 90 ሚሊዮን ብር ማሰባሰብ እንደተቻለ፣ ለእድሳት በ172 ሚሊዮን ብር ውል እንደተገባ አስረድተዋል።
 
አብዛኛው ማህበረሰብ ካቴደራሉ ከፍተኛ የገንዘብ አቅም እንዳለውና እርዳታ የማይፈልግ እንደሆነ ያለተጨባጭ መረጃ የተሳሳተ ግንዛቤ በማሳደሩ ለእድሳቱ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እጥረት በማጋጠሙ ሁሉም ሰው በሁሉም ባንኮች በአጭር ቁጥር 7829 ማስገባት ርብርብ እንዲያደርግ ተጠይቋል።

ካቴደራሉን ለማደስ 18 ወራት ያህል ጥናት እንደተደረገ፣ በዚህም ህንጻውን ከሚያድሰው ቫርኔሮ ከተባለ ድርጅት ጋር በመዋዋለ የውስጥና የውጪ እድሳት እየተደረገ መሆኑ ይታወቃል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

Photo Credit - ንቁ

@tikvahethiopia


#NEVACOMPUTER

በጣም በተመጣጣኝ ዋጋ ዘመናዊ የሆኑ 2023 እና 2024 ቢዝነስ ላኘቶፓች፣ እጅግ ፈጣን የሆኑ የኤዲቲንግ ላፕቶፓች እንዲሁም ለተማሪዎች ቅናሽ የሆኑ ኢሮፕ ስታዳርድ እና ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች አሉን። ከበቂ መስተንግዶ መረጃ እና ከአንድ አመት ዋስትና ጋር እንጠብቆታለን።

ነቫ ኮምፒዉተር ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ👇
https://t.me/nevacomputer

ስልክ፦ 0920153333
አድራሻ - መገናኛ ማራቶን ህንፃ ግራውንድ ፍሎር - NEVA COMPUTER
www.nevacomputer.com


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
ንጹሕ_ምንጭ _ኢትዮጵያ


ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ | ልዩ ታሪካዊ ዐውደ ርእይ
ሊፈፀም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀረው

በግዮን ሆቴል እስከ ሚያዚያ 13 ብቻ፡፡


ለልጆችዎ ቦታ አለን


በልዩነት ቅዳሜ ልዩ የህፃናት ዝግጅት


የመግቢያ ትኬትዎን ግዮን ሆቴል በር ላይ ያገኙታል። ለበለጠ መረጃ ፦09 66 76 76 76 ወይም 09 44 24 00 00 ይደውሉ። INSTAGRAM | TELEGRAM | @hamereberhan' rel='nofollow'>YOUTUBE | TWITTER | TIKTOK |WEBSITE


" ቲክቶክ ላይት " ጥያቄ ቀረበበት።

አዲሱ መተግበሪያው ' ቲክቶክ ላይት ' በፈረንሳይ እና ስፔይን አገልግሎት የጀመረው ቲክቶክ በህጻናት እና ተጠቃሚዎች የአዕምሮ ጤንነት ላይ ሊያስከትል ስለሚችለው አደጋ ያለውን ግምገማ በ24 ሰዓት ውስጥ እንዲያቀርብ ዛሬ የአውሮፓ ኮሚሽን ጠየቀ።

ከዋናው ቲክቶክ መተግበሪያ አነስ ብሎ የወጣው የቲክቶክ መተገበሪያ ተጠቃሚዎች #ተከፍሏቸው የቪዲዮ ምስሎችን እንዲመለከቱ በማድረግ በሚያስቆጥሯቸው ነጥቦች የመግዛት አቅምና ዋጋ ያላቸውን የስጦታ ካርዶችን የሚሽልም ነው፡፡

በመተግበሪያው ተሳታፊ ለመሆን ተጠቃሚዎች ቢያንስ እድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

ሽልማቱን ለማግኘት በቀን እስከ 1.06 ዶላር የሚደርስ ሽልማት ለማግኘት በየቀኑ አንድ ሰዐት ድረስ ቪዲዮውን መመልከት ይችላሉ፡፡

የአውሮፓ ኮሚሽን የቻይናው ቲክቶክ ባለቤት ባይትዳንስ (ByteDance) መተግበሪያውን ከመልቀቁ በፊት ሊያስከትል ስለሚችለው አደጋ ቁጥጥርና ጥንቃቄ ግምገማ ማድረግ ነበረበት ብሏል።

ጥያቄው የቀረበው ቲክቶክ ያወጣው አዲሱ " Task and Reward Lite " የተባለው መተግበሪያ፣ ለአካለ መጠን ያልደረሱ ሕፃናትን ደህንነት እንዲሁም በተጠቃሚዎች የአእምሮ ጤና ላይ ፣ በተለይ ሱስ አስያዥ ባህሪን ከማነሳሳት ጋር ተያይዞ ሊያመጣ የሚችለውን ተፅእኖ መሰረት በማድረግ ነው ” ሲል የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

መተግበሪያው ሊያስከትለው ስለሚችለው አደጋ ቁጥጥር እንዲሁም ጥንቃቄ ያለውን ግምገማ እንዲያቀርብ ከተሰጠው የ24-ሰዐት የጊዜ ገደብ ባሻገር፣ ቲክቶክ የተጠየቀውን ተጨማሪ መረጃ እ ኤ አ እስከ ሚያዝያ 26 ድረስ መስጠት አለበት ሲል ኮሚሽኑ አሳስቧል።

የቲክቶክ ቃል አቀባይ ፥ " አዲሱን መተግበሪያ በተመለከተ ከኮሚሽኑ ጋር በቀጥታ ተገናኝተናል፣ ለቀረበልን ጥያቄም ተገቢ ምላሽ እንሰጣለን " ማለታቸውን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል።

መረጃውን ቪኦኤ ፤ አዣንስ ፍራንስ ፕሬስን ዋቢ በማድረግ ነው ያስነበበው።

@tikvahethiopia


" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዜዳንት የሆኑት ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፥ " በወረራ " ተይዘዋል ያሏቸውን የትግራይ ክልል ግዛቶችን በሰላም ስምምነቱ መሰረት ነጻ እንዲወጡ እና የአካባቢዎቹ ሰላምና ደህንነት ተረጋግጦ ተፈናቃዮች ወደ ቀድሞ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ ኃላፊነት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ ወስደው እንዲሰሩ ከፌዴራል መንግሥት ጋር መግባባት ላይ መድረሱን ተናግረዋል።

ከዚህ ውጭ የክልሉ ጸጥታ ኃይል ምንም አይነት የኃይል እርምጃ ለመውሰድ እንዳልተንቀሳቀሱ ከሰላም ስምምነቱ ጋር የሚጣረስ አንድም ነገር ላለመፈጸም በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

ጄነራሉ የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነቱን ለመገምገም በአፍሪካ ህብረት በተመራው የስትራቴጂክ ግምገማ  ወቅት እስካሁን ድረስ ስላልተሰሩ ጉዳዮች ተነስቶ እንደነበር እና እንዲሰራባቸው አቅጣጫ መቀመጡን አስታውሰዋል።

ከስትራቴጂክ ግምገማው በኃላም ለውጦች መታየታቸውን አመልክተዋል።

መሰረታዊ ከሚባሉት የስምምነቱ ክፍሎች እና ካልተፈጸሙት አንዱ ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው መመለስ ነው ያሉት ጄነራሉ " ተፈናቃዮች እንዲመለሱ የትግራይ ግዛት መከበር አለበት ብለዋል።

" በዚህ ላይ ' እንደ ራያና ጸለምቲ ቀላል ነው ፤ ምዕራብ ትግራይ ነው ከባዱ ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሁሉም ቀላል ነው ሁሉም ከባድ ነው ' እየተባለ ምክንያት ይቀርባል። አንዳንዴ ደግሞ ' አከራካሪ ቦታዎች ' እያሉ ይገልጹታል ሆኖም በህገ መንግሥቱ መሰረት ትግራይ ትግራይ ነው አከራካሪ የሚባል ነገር የለም ጥያቄ ካለ እንኳን በህግ አግባብ ነው መተግበር ያለበት " ሲሉ ተናግረዋል።

" ' በኃይል ይዣለሁ ፣ ይዣለሁ ማለቱ ፍጹም ሰላም አያመጣም " ሲሉ አክለዋል።

ጄነራሉ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ችግሮች ዘላቂ ሰላም በሚያመጣ መልኩ እንዲፈቱ እንደሚፈልግ ገልጸው " ለዚህም የመከላከያ ሰራዊት እና ፌዴራል ፖሊስ ኃላፊነት ወስደው እንዲሰሩ እየተደረገ ያለው " ብለዋል።

" በወረራ ተይዟል " ባሉት የትግራይ ክፍል ሁሉም ነገር ያለ አግባብ መቀየሩን አስታውሰው " ሁሉም ፈርሶ ወደነበረበት የትግራይ ቅርጽ እንዲመለስ ፌዴራል መንግሥት በትኩረት እየሰራ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

የትግራይ የጸጥታ ኃይል ስምምነቱን የሚያፈርሱ ተግባራት ላለመፈጸም ከፍተኛ ጥንቃቄ እያደረገ ነው ብለዋል።

" በማህበራዊ  ሚዲያ እና በሌሎችም ፦
- በራያ አላማጣ፣
- በኦፍላና ፣
- በኮረም ላይ ትኩረት አድርገው የሚናፈሱት ወሬዎች ከእውነት የራቁ ናቸው። እነሱ እንደሚሉት በኃይል መያዝ የምንፈልገው አካባቢ የለም። በስምምነቱ መሰረት በፌዴራል መንግሥት ጥረት ነጻ እንዲሆንልን ነው የምንፈልገው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ዘላቂ ሰላም የሚያረጋግጥና ዳግም ደም አፋሳሽ ጦርነትን የማይቀሰቅስ ተግባር እንዲፈጸም ነው የምንፈልገው በእርግጥ ችግሩን በሰላም ለመፍታት በነበረው ሂደት አለመግባባትና ፍጥጫ ነበር ይህ ለራሳቸው ሆነ ለሀገራችን ስለማይጠቅም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና የሰላም ተባባሪ እንዲሆኑ እንጥራለን " ብለዋል።

ዛሬ የአማራ ክልል መንግሥት በሰጠው ይፋዊ መግለጫ፤ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል።

እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ የፌዴራል መንግሥት የሰጠው አስተያየት የለም።

@tikvahethiopia

16 last posts shown.