TIKVAH-ETHIOPIA


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


" በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ዳግም የመሬት ናዳ እና ጎርፍ ተከስቶ በሰዉና ንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል " - የአከባቢው ነዋሪዎች

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ከሰሞኑ በአከባቢያቸዉ ነፋስ ቀላቅሎ እየጣለ ያለዉ ከባድ ዝናብ የመሬት ናዳ እና ጎርፍ በማስከተሉ በሰዉ ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል።

ከሚያዚያ 9/2017 ዓ/ም  ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በአከባቢዉ እየጣለ ያለዉ ዝናብ በተለይም ፦
- ጎሬ ኦዳ፣
- ጃዉላ ዉጋ ማሽታሌ፣
- ኤላ፣
- አማሮ ሻጌ፣
- ቡልቂ በተባሉ አከባቢዎች ባስከተለዉ ከባድ ነፋስ፣ ከፍተኛ የዉሃ ሙላት እና የመሬት መንሸራተት  የ3 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ4 በላይ ቤቶች በመሬት ናዳዉ መስመጣቸዉንና፤ የእርሻ ማሳዎች እንዲሁም የቤት እንስሳት ጭምር በመሬት መንሸራተቱ መወሰዳቸዉን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።

በወረዳዉ ሰሞኑን በተከሰተዉ ዳግመኛ  የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በጎዶ አንደኛ ትምህርት ቤት እና በአንድ የሃይማኖት ተቋም ግቢ ተጠልለው እንደሚገኙ የሚናገሩት ነዋሪዎቹ የዝናብ ሁኔታዉ ቀጣይነት ያለዉ ስለሚመስል አሁንም ከፍተኛ ስጋት ዉስጥ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

" በወረዳዉ የዛሬ ዓመት በተከሰተዉ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን መሉ በሙሉ መልሶ የማደራጀቱ ስራ ባልተጠናቀቀበት ይህ መከሰቱ ስጋታችንን ከፍ ያደርገዋልም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ የገዜ ጎፋ ወረዳ አደጋ ስጋት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማስረሻ ማናዬ በበኩላቸው በአካባቢው እየጣለ ባለዉ ከባድ ዝናብ በወረዳዉ አራት ቀበሌያት በሰዉ፣ በንብረትና በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ማድረሱን አስታዉቀዋል።

ተጨማሪ አደጋዎች እንዳይከሰቱ የወረዳዉ መንግስት በልዩ ተኩረት እየሰራ ነዉ ያሉት አቶ ማስረሻ ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች የማቋቋም ስራም እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ባሳለፍነዉ ዓመት በአከባቢዉ የተከሰተዉ መሰል የመሬት መንሸራተትና ናዳ ምክንያት በርካታ ሰዎች መሞታቸዉ የሚታወስ ሲሆን አሁንም ድረስ በአከባቢው በስጋት የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ መልሶ የማቋቋም ስራዉ አለመጠናቀቁን በቅርቡ የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia


#AddisAbaba

" በ3 ወራት ውስጥ 943 ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዲፈቻዎች ምዝገባ ተከናውኗል !! "

የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት ጋር  የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን መዝግቦ በአንድ መስኮት አገልግሎት ለመስጠት የጋራ ስምምነት ፈጽመው እየሰሩ ሲሆን ላለፉት 3 ወራት ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን አፈፃፀም በጋራ ገምግመዋል።

በዚህም ወቅት በቀረበ ሰነድ 996 ተገልጋዮች በ3 ወራት የኩነት ምዝገባ አገልግሎቱን በፍርድ ቤቶች በአንድ መስኮት ማግኘታቸው ተመላክቷል።

ከዚህም ውስጥ ውሳኔ ያገኙ 943
#ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው #ጉዲፈቻዎች በወቅቱ ምዝገባ በማድረግ በአንድ ማዕከል በፍ/ቤቶች አገልግሎት መሰጠቱ ተመላክቷል።

Via
https://t.me/addisvaitalpress/9155

@tikvahethiopia


#DStvEthiopia

🏆 ኤምሬትስ ስታዲየም ከባድ ትንቅንቅ ይጠብቀዋል🔥

⚽️ ከ15 ዓመታት በኃላ አርሰናል ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ ተመልሷል!

✨ መድፈኞቹ በአርቴታ እየተመሩ የኤንሪኬን በብዙ ሽልማቶች ያጌጠውን ፒኤስጂን ማሸነፍ ይችሉ ይሆን?
⚡️ ዴምቤሌ ፣ ሳካ ፣ ሃኪሚ እና ቲምበር የእንግሊዝና የፈረንሳይን ኮከቦች በሰሜን ለንደን መብራቶች ስር ይጫወታሉ!

🌟 የዋንጫውን አንድ እጅ የሚይዘው ቡድን ማነው?

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #UCL #ARSPSG


#Update

ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶ የነበረው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው ታገደ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያን መሰረት እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብሮ በቤተክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ እንዲያከናውን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን ፍቃድ መሰጠቱ ይታወሳል።

ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት " ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም " በሚል ርእስ የተላለፈው ትምህርትን ውዝግብ በማሰነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያው ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው መታገዱን የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ዛሬ አሳውቋል።

@tikvahethiopia


የአዲስ አበባ ከተማ የተርሚናል አገልግሎት አሰራርና ቁጥጥር ደንብ ቁጥር 186/2017 ምን ይላል ?

የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 84/2016 አንቀጽ 95 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ደንብ አውጥቷል፡፡

ደንቡ ምን ይላል ?

በተርሚናል አገልግሎት ሥራ ላይ የሚደራጁ ተርሚናል ኢንተርፕራይዞች የሥራ እና ክህሎት ቢሮ በሚያወጣው መስፈርት መሠረት እንደሚደራጁ ይገልጻል።

ቀደም ሲል ተደራጅተው በህጋዊ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የተርሚናል ኢንተርፕራይዞች መስፈርቱን አሟልተው ሲቀርቡ ዳግም እንዲደራጁ እንደሚድረገም ያመለክታል።

የአደረጃጀት መስፈርቱን ያሟሉ ማህበራት ሲደራጁ በተርሚናል ኢንተርፕራይዙ ስም መደበኛና ዝግ የሂሳብ አካውንት መክፈት እንደሚኖርባቸውም ይገልጻል።

በተርሚናል አገልግሎት ሥራ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የሥራ ውል እንዲገቡ ይደረጋሉ።

የሚገቡት ውል ለ1 ዓመት ነው። የስራ አፈጻጸማቸው እየታየ ለአንድ አመት ለአንድ ጊዜ ብቻ ሊታደስ እንደሚችል ደንቡ ይገልጻል።

የተርሚ ማል ኢንተርፕራዞቹ የውል ዘመናቸው ከመጠናቀቁ በፊት የቁጠባ ካፒታላቸውን ታሳቢ በማድረግ ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ የሚሸጋገሩበር ሥራ በሥራና ክህሎት ቢሮ በኩል ይሰራል።

ኢንተርፕራይዞቹ ከሰበሰቡት ጠቅላላ ገቢ 30% (ሰላሳ በመቶ) የግዴታ ቁጠባ ይቆጠባሉ። 50% (ሃምሳ በመቶ) በመደበኛ ተንቀሳቃሽ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ገቢ ይደርጋሉ።

የተርሚናል ኢንተርፕራይዞች ከሚያገኙት ጠቅላላ ገቢ ላይ 20% (ሀያ በመቶ) ለመንግስት ገቢ ያደርጋሉ።

(ሙሉ ደንቡ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia


" ለፍትሃዊ ጥያቄያችን ፍትሃዊ ምላሽ እንሻለን !! "

የመቐለ 70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበራት አመራርና አባላት " ጥያቄያችን ላለፉት 6 ዓመታት ሰሚ ጀሮ አጥቷል " በማለት በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት በሰላማዊ ሰልፍ ምሬታቸውን ገልፀዋል።

ከ6 ዓመታት በፊት ለአንድ አባወራ 70 ካሬ ሜትር የመኖሪያ የቤት ግንባታ መሬት ለመሰጠት በሚፈቅድ መመሪያ መደራጀታቸው ገልጸው ከጦርነት በኋላ ነባሩ መመሪያ በመጣስ በአፓርታማ ነው የምትስተናገዱት መባላቸው ኢፍትሃዊ እንደሆነ ገልጸዋል።

በትግራይ ደረጃ የተደራጁት እነዚህ 60 ሺህ የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር ጥያቄ አቅራቢዎች የመኖሪያ ቤት የግንባታ መሬት አሰጣጥ አስመልክቶ በክልሉ ከተሞች የሚታየው ወጥ ያልሆነ አሰራር እንዲታረም ድምፃቸውን አስምተዋል።

በሌሎች ከተሞች ተፈቅዶ በመቐለ ከተማ ለ70 ካሬ የቤት መኖሪያ ግንባታ " መሬት አይሰጥም " መባሉ አጅግ እንዳስገረማቸውና እንዳሰዘናቸው ገልፀዋል።

ጥያቄያቸው የተደረጁበት መመሪያ በሚፈቅደው መሰረት የመኖሪያ የቤት ግንባታ መሬት ከማግኘት የዘለለ ፓለቲካዊ ተልእኮና ዓላማ እንደሌለው አስረድተዋል።

ከቤት ኪራይ ስቃይና ሰቆቃ እንዲገላገሉ የሚያስችል መንግስታዊ መፍትሄ እንደሚሹ ተናግረዋል።

ማህበራቱ ዛሬ ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት አከባቢ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችና መፈክሮች እያሰሙ አስከ እኩለ ቀን ቢጠብቁም ጥያቄዎቻቸው ሰምቶ ምላሽ የሚሰጥ የመንግስት ሃላፊ እንዳልተገኘ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከቦታው ሆኖ መረጃውን ልኳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

#TikvahEthiopiaFamilyMkelle

@tikvahethiopia            


" ሚስቱን ገድሎ ሊሰወር የሞከረዉ ግለሰብ በፖሊስና በሕብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ሊዉል ችሏል " - የጋሞ ዞን ፖሊስ

በአርባ ምንጭ ከተማ ባለቤቱ ገድሎ ሊሰወር የነበረ ግለሰብ መያዙን ፖሊስ ገልጿል።

የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ሬታ ተክሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ አርባ ምንጭ ከተማ ወዜ ቀበሌ ግድብ ሠፈር ነው።

ኮማንደር ሬታ ፤ የገዛ ባለቤቱን በመሳሪያ ተኩሶ በመግደል ሊሰወር የሞከረዉ ተጠርጣሪ በሕዝቡና በፖሊስ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪው አቶ ነብዩ ጌታቸው ኤፍሬም እንደሚባልና ከሟች ጋር በትዳር ዓለም አብረዉ እንደነበሩ በመካከላቸዉ በነበረው አለመግባባት ሟች ወላጆቿ  ጋር በመሄድ ላለፉት 5 ወራት ከቤተሰቦቿ  ጋር ትኖር እንደነበር ገልፀዋል።

በትናትናዉ ዕለት ተጠሪጣርዉ አስቦና አቅዶ ጧት 4 ሰዓት ገደማ " ላናግርሽ እፈልጋለሁ " በማለት ካስጠራት በኋላ ሰዉ የማያይበትን ሁኔታ በማመቻቸት በሽጉጥ አንገቷ ስር ደቅኖ ተኩሶ እንደ ገደላት አስረድተዋል።

በኃላም ለመሸሸግና ለመሰወር ሲሞክር  በፖሊስ ክትትልና በሕብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዉና ሟች በትዳር አብረዉ በነበሩበት ወቅት አንድ ልጅ አፍርተዉ እንደነበርም የፖሊስ መረጃ ያመለክታል።

ተጠርጣሪዉ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመበትን ሽጉጥ ወንዝ ዉስጥ እንደጣለ ቢገልፅም ፖሊስ ባደረገዉ ማጣራት ከደበቀበት በኤግዚቢትነት ይዞታል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia


#Tigray

የካቢኔ አባሉ ለእስር የዳረጋቸው ምንድን ነው ? 

በአሁኑ ወቅት በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ብቸኛ የተቃዋሚው የባይቶና ፓለቲካ ፓርቲ የካቢኔ አባል የሆኑት አቶ ታደለ መንግስቱ በፓሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ወደ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ መደረጋቸው አነጋጋሪ ሆኖ ውሏል።

የካቢኔ አባሉ አቶ ታደለ የመቐለ ማእከላይ ፍርድ ቤት የሚመሩት የመንግስት መስሪያ ቤት እንዲያስፈፅም የሰጠውን ውሳኔ ባለመተግበራቸው ምክንያት ዛሬ ረቡዕ ለ6 ወራት በእስር እንዲቆዩ ቢወሰነባቸውም ከ1 ቀን እስር በኋላ ተለቀዋል።

በምን ምክንያት ታሰሩ ? እንዴትስ ተለቀቁ ? 

ተከሳሹ የትግራይ የትራንስፓርት ቢሮ ሃላፊ አቶ ታደለ መንግስቱ ሲሆኑ ከሳሽ ደግሞ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ነው።

የክሱ ፍሬ ነገር በትግራዩ ጦርነት የተወሰደችበት ላንድ ክሩዘር V8 መኪና እንድትመለስለት የሚጠይቅ ነው።

ባለስልጣኑ ዓይነቷና የሰሌዳ ቁጥሯን ጠቅሶ በቢሮው አስፈፃሚነት እንድትመለስለት የጠየቀባት ላንድ ክሩዘር V8 መኪና የህወሓት ፅህፈት ሃላፊዋ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/ሄር ሲጠቀሙባት ነበር።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ የትራንስፓርት ቢሮ V8 መኪናዋ ለባለቤቱ እንድትመለስ እንዲያስፈፅም የቀረበበት ክስ በመቀበል የህወሓት ፓርቲ ሃላፊዋ (ወ/ሮ ፈትለወርቅ)  እንዲመለሱ ተጠይቀው አሻፈረኝ በማለታቸው ምክንያት ፍርድ ቤት ጉዳዩን ማስፈፀም ያልቻሉትን የቢሮውን ሃላፊ  (አቶ ታደለ) በእስር እንዲቀርቡ ያዛል።

ዛሬ ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም በፓሊስ ተይዘው ፍርድ ቤት የቀረቡት ሃላፊው ጉዳዩ እንዲያስፈፅሙ በተደጋጋሚ የቀረበላቸው ባለመተግበራቸው ምክንያት ለ6 ወር እንዲታሰሩ ይፈርዳል።

ሂደቱ እንዲህ እያለ ወደ ባለቤትዋ እንድትመለስ ጥያቄ የቀረበባት V8 መኪና ሚያዝያ 15/2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ በሸኚ ደብዳቤ በኤግዚብትነት ወደ ፓሊስ እጅ በመግባቷ ምክንያት ሃላፊው ከእስር ሊለቀቁ ችለዋል።

ከትግራይ የትራንስፓርት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በጦርነቱ ምክንያት ከመንግስታዊና ግለሰቦች ተወስደው በማይመለከታቸው አካላት የነበሩት ከ 2800 በላይ ተሽከርካሪዎች ወደ ባለቤቶቹ ተመልሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

ፎቶ፦ የLC V8 ምስል ከኢንተርኔት የተወሰደ

@tikvahethiopia


#ጥቆማ

ለዩኒቨርስቲ መምህራን የቀረበ የምርምር ስኮላር ጥቆማ።

የFulbright 2026-2027 የአፍሪካ ምርምር ስኮላር ፕሮግራም ይፋ ሆኗል።

ፕሮግራሙ ሁለት አይነት አሰጣጦች ሲኖሩት በመጀመሪያው ፕሮግራም ዶክትሬት የሚጠይቅ (Post-doctoral) ሲሆን ሁለተኛው ፕሮግራም የማስተርስ ድግሪን የሚጠይቅ ነው።

በሁለቱም ፕሮግራሞች ማመልከት የሚችሉት የዩኒቨርስቲ መምህራን (ሌክቸሮች) ናቸው።

የቆይታ ጊዜው እንደ ፕሮግራሙ አይነት ሲለያይ አመልካቾች ከነሐሴ 2026 በኋላ እና ከመጋቢት 2027 በፊት
#በአሜሪካ ተገኝተው ምርምራቸውን መጀመር መቻል አለባቸው።

የዕድሜ እና የፆታ ገደብ እንደሌለው የተገለጸ ሲሆን አመልካቾች ከJuly 31, 2025 በፊት ማመልከት ይጠበቅባቸዋል።

ይህ ዕድል ሚመለከታችሁ ዝርዝሩን ከኢንባሲው ድረ-ገጽ 👉
https://surl.li/qudtze ላይ ማግኘት ትችላላችሁ።

Via
@Tikvahethmagazine

9 last posts shown.