ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ፦
(ለሚመለከተው ሁሉ የቀረበ ሀሳብ)
➢ ነእፓ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ክልሎች አንዱ ትግራይ መሆኑና በጦርነቱ የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት እንደደረሰበት ገልጿል። በክልሉ እና በህዝቡ ላይ የደረሰው ከፍተኛ ጉዳት ዘላቂ ሰላም በመፍጠር በአፋጣኝ ሊቀየር ይገባል ብሏል። በመሆኑም ትግራይን በማስተዳደር ላይ ያሉ ኃይሎች በትግራይ ህዝብ ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ጉዳት ለመቀነስ እና በክልሉ ላይ ያንዣበበውን የጦርነት ስጋት ለመግታት ዳግም ወደ ጦርነት ከሚያመሩ ወታደራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና የሚዲያ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠቡ፣ በአንጻሩ ለሰላም መረጋገጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።
➢ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ከልል የተፈጠረውን ከፍተኛ የምግብ፣ የመድሀኒት እና ሌሎች ቁሳቁሶች ችግር ለመቅረፍ የፌዴራል መንግስት አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ወደ ክልሉ አንዲገባ መፍቀዱን አስታውሷል፤ በዚሁ መሰረት የፌዴራል መንግስቱ ምግብ፣ መድሀኒት እና ሌሎች ሰብአዊ ድጋፎች በበቂ ሁኔታ ወደ ክልሉ እንዲደርስ አስፈላጊውን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
➢ የፌዴራሉ መንግስት ፤ እንዲሁም የአማራ እና የአፋር ክልላዊ መስተዳድሮች እና የትግራይ ኃይሎች የተፈጠረውን ዳግም ወደ ጦርነት የመመለስ አደጋ ለማስወገድ እና ችግሩን በሰላማዊ መንድ ለመፍታት የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጠይቋል። የፌደራል መንግስት ጦርነቱ በሰላማዊ መንገድ እና በድርድር አንዲያልቅ የድርድር ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ በአስቸኳይ ወደ ተግባራዊ እርምጃ አንዲገባም ጠይቋል።
➢ የሀገር ሸማግሌዎች ፤ የፖለቲካ ፓቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፤ ባለሃብቶች፣ የተፈጠረውን የግጭት ስጋት ለማስወድ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ፤ የሚዲያ ተቋማት እና አክቲቪሰቶች ካለፈው ትምህት በመውሰድ ግጭት ቀስቃሸ የሆኑ መልእከቶችን ከማሰራጨት በመቆጠብ እና ሰላምን በማቀቀን ሀገራችን ዳግም ወደ ጦርነት እንዳትግባ ሙያዊ ግዴታቸውን ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንዲወጡ ጠይቋል።
➢ በማንኛውም ሁኔታ ለሚቀሰቀስ የእርስ በእርስ ጦርነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ትልቅ ዋጋ የሚከፍሉት ዜጎች ናቸው - ከአንድ አመት በላይ በሰሜኑ የሀገራችን ከፍል በተካሄደው ጦርነት ትልቅ ዋጋ የከፈሉትም መላው የሀገራችን ህዝቦች ናቸው። በመሆኑም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ያንዣበበው የጦርነት ስጋት ተወግዶ ሰላም እንዲረገጥ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጦርነትን በማውገዝ እና የሰላምን አርማ ከፍ አድርጎ በማውለብለብ ሰላም እንዲሰፍን የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
#ነእፓ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
(ለሚመለከተው ሁሉ የቀረበ ሀሳብ)
➢ ነእፓ በሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ክልሎች አንዱ ትግራይ መሆኑና በጦርነቱ የክልሉ ህዝብ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ጉዳት እንደደረሰበት ገልጿል። በክልሉ እና በህዝቡ ላይ የደረሰው ከፍተኛ ጉዳት ዘላቂ ሰላም በመፍጠር በአፋጣኝ ሊቀየር ይገባል ብሏል። በመሆኑም ትግራይን በማስተዳደር ላይ ያሉ ኃይሎች በትግራይ ህዝብ ላይ የደረሰውን ከፍተኛ ጉዳት ለመቀነስ እና በክልሉ ላይ ያንዣበበውን የጦርነት ስጋት ለመግታት ዳግም ወደ ጦርነት ከሚያመሩ ወታደራዊ ፣ ፖለቲካዊ እና የሚዲያ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠቡ፣ በአንጻሩ ለሰላም መረጋገጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።
➢ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ ከልል የተፈጠረውን ከፍተኛ የምግብ፣ የመድሀኒት እና ሌሎች ቁሳቁሶች ችግር ለመቅረፍ የፌዴራል መንግስት አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ወደ ክልሉ አንዲገባ መፍቀዱን አስታውሷል፤ በዚሁ መሰረት የፌዴራል መንግስቱ ምግብ፣ መድሀኒት እና ሌሎች ሰብአዊ ድጋፎች በበቂ ሁኔታ ወደ ክልሉ እንዲደርስ አስፈላጊውን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።
➢ የፌዴራሉ መንግስት ፤ እንዲሁም የአማራ እና የአፋር ክልላዊ መስተዳድሮች እና የትግራይ ኃይሎች የተፈጠረውን ዳግም ወደ ጦርነት የመመለስ አደጋ ለማስወገድ እና ችግሩን በሰላማዊ መንድ ለመፍታት የሚጠበቅባቸውን እንዲያደርጉ ጠይቋል። የፌደራል መንግስት ጦርነቱ በሰላማዊ መንገድ እና በድርድር አንዲያልቅ የድርድር ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ በአስቸኳይ ወደ ተግባራዊ እርምጃ አንዲገባም ጠይቋል።
➢ የሀገር ሸማግሌዎች ፤ የፖለቲካ ፓቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ በውጭ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፤ ባለሃብቶች፣ የተፈጠረውን የግጭት ስጋት ለማስወድ የድርሻቸውን እንዲያበረክቱ ፤ የሚዲያ ተቋማት እና አክቲቪሰቶች ካለፈው ትምህት በመውሰድ ግጭት ቀስቃሸ የሆኑ መልእከቶችን ከማሰራጨት በመቆጠብ እና ሰላምን በማቀቀን ሀገራችን ዳግም ወደ ጦርነት እንዳትግባ ሙያዊ ግዴታቸውን ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንዲወጡ ጠይቋል።
➢ በማንኛውም ሁኔታ ለሚቀሰቀስ የእርስ በእርስ ጦርነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ትልቅ ዋጋ የሚከፍሉት ዜጎች ናቸው - ከአንድ አመት በላይ በሰሜኑ የሀገራችን ከፍል በተካሄደው ጦርነት ትልቅ ዋጋ የከፈሉትም መላው የሀገራችን ህዝቦች ናቸው። በመሆኑም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ያንዣበበው የጦርነት ስጋት ተወግዶ ሰላም እንዲረገጥ መላው የሀገራችን ህዝቦች ጦርነትን በማውገዝ እና የሰላምን አርማ ከፍ አድርጎ በማውለብለብ ሰላም እንዲሰፍን የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
#ነእፓ #ኢትዮጵያ
@tikvahethiopia