" ምዕራባውያን ሚዲያዎች ተሸንፈዋል " - ኤርዶጋን
የቱርክ ጠቅላይ ምርጫ ካውንስል የመጀመሪያ ደረጃ የምርጫ ውጤት የአሁኑ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምርጫውን #ማሸነፋቸውን አመልክቷል።
ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ምርጫውን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በአንካራ ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገዋል።
ምን አሉ ?
ፕሬዜዳንቱ በንግግራቸው " ዛሬ ማንም የተሸነፈ የለም ሁሉም 85 ሚሊዮን ህዝብ አሸንፏል። " ያሉ ሲሆን " አሁን ጊዜው የአንድነት፣ በአገራዊ ግቦቻችን እና ሀገራዊ ህልሞቻችን ዙሪያ መዋሃድ ነው " ብለዋል።
በንግግራቸው የምዕራባውያን ሚዲያዎች እሳቸውን " ለማጥፋት " ሲሰሩ እንደነበር በመጠቆም ፤ " የምዕራባውያን ሚዲያዎች ተሸንፈዋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
ኤርዶጋን በቱርክ በዋጋ ንረት ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን መፍታት፣ ከምንም ነገር በላይ " በጣም አስቸኳይ " እና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን በንግግራቸው አንስተዋል።
@tikvahethiopia
የቱርክ ጠቅላይ ምርጫ ካውንስል የመጀመሪያ ደረጃ የምርጫ ውጤት የአሁኑ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምርጫውን #ማሸነፋቸውን አመልክቷል።
ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ምርጫውን ማሸነፋቸውን ተከትሎ በአንካራ ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገዋል።
ምን አሉ ?
ፕሬዜዳንቱ በንግግራቸው " ዛሬ ማንም የተሸነፈ የለም ሁሉም 85 ሚሊዮን ህዝብ አሸንፏል። " ያሉ ሲሆን " አሁን ጊዜው የአንድነት፣ በአገራዊ ግቦቻችን እና ሀገራዊ ህልሞቻችን ዙሪያ መዋሃድ ነው " ብለዋል።
በንግግራቸው የምዕራባውያን ሚዲያዎች እሳቸውን " ለማጥፋት " ሲሰሩ እንደነበር በመጠቆም ፤ " የምዕራባውያን ሚዲያዎች ተሸንፈዋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
ኤርዶጋን በቱርክ በዋጋ ንረት ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን መፍታት፣ ከምንም ነገር በላይ " በጣም አስቸኳይ " እና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን በንግግራቸው አንስተዋል።
@tikvahethiopia