#UNMAS
ፈንጂዎችን እና ሌሎች የጦር መሣሪያ ቅሪቶችን የማስወገድ ተልዕኮ የተሰጠው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት (UNMAS) በዋናነት በትግራይ ክልል እንዲሁም ጦርነት በተካሄደባቸው አዋሳኝ የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዲሰማራ የኢትዮጵያ መንግሥት ፈቅዷል።
ፈንጂዎችና ሌሎች ያልፈነዱ የጦር መሣሪያ ቅሪቶች ጦርነት በተካሄደባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ አካባቢዎችን ከፈንጂዎች ለማጽዳት እንዲቻል፣ የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት እንዲሰማራ መፈቀዱን የአፍሪካ ኅብረት መረጃ ያመለክታል።
የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት በቅርቡ በመቐለ ከተማ ቢሮውን እንደሚከፍትና ዋና መቀመጫውን በመቐለ አድርጎ በሁሉም ጦርነቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች ኃላፊነቱን ለመወጣት እንደሚሰማራ ተነግሯል።
በዚህ ወር በአፋር ክልል በፈነዳ የወደቀ የሞርታር ጥይት የአራት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን በትግራይ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 300 በሚሆኑት ውስጥ በርካታ የጦር መሳሪያ ቅሪቶች ተገኝተዋል።
Via Ethiopian Reporter
@tikvahethiopia
ፈንጂዎችን እና ሌሎች የጦር መሣሪያ ቅሪቶችን የማስወገድ ተልዕኮ የተሰጠው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት (UNMAS) በዋናነት በትግራይ ክልል እንዲሁም ጦርነት በተካሄደባቸው አዋሳኝ የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዲሰማራ የኢትዮጵያ መንግሥት ፈቅዷል።
ፈንጂዎችና ሌሎች ያልፈነዱ የጦር መሣሪያ ቅሪቶች ጦርነት በተካሄደባቸው የሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች፣ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት እያደረሱ በመሆኑ አካባቢዎችን ከፈንጂዎች ለማጽዳት እንዲቻል፣ የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት እንዲሰማራ መፈቀዱን የአፍሪካ ኅብረት መረጃ ያመለክታል።
የተመድ ፈንጂ ማስወገድ አገልግሎት በቅርቡ በመቐለ ከተማ ቢሮውን እንደሚከፍትና ዋና መቀመጫውን በመቐለ አድርጎ በሁሉም ጦርነቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች ኃላፊነቱን ለመወጣት እንደሚሰማራ ተነግሯል።
በዚህ ወር በአፋር ክልል በፈነዳ የወደቀ የሞርታር ጥይት የአራት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን በትግራይ ከሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል 300 በሚሆኑት ውስጥ በርካታ የጦር መሳሪያ ቅሪቶች ተገኝተዋል።
Via Ethiopian Reporter
@tikvahethiopia