" ... በከተማው የንጥቂያ እና ዝርፊያ ወንጀሎች #መባባስ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ እያስነሳ ነው " - የጋምቤላ ፖሊስ
በጋምቤላ ከተማ በሞተር ሳይክሎች ላይ የሰዓት ገደብ ተጣለ።
በጋምቤላ ከተማ በተሽከርካሪ የሚፈፀም ስርቆትና ዝርፊያን ለመከላከል ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ድረስ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎች ላይ እገዳ መጣሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰናይ አኩዎር ፤ በከተማው የንጥቂያና ዝርፊያ ወንጀሎች #መባባስ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ እያስነሳ ነው ብለዋል።
በከተማዋ እየተስፋፋ በመጣው የዝርፊያና መሰል ወንጀሎች በዋናነት ተጠቂዎቹ ሴቶችና አቅመ ደካሞች እንደሆኑ ገልፀው ወንጀሎቹን ለማስቀረት የፀጥታ ሀይሉ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ ተናግረዋል።
በተለይም በከተማው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎችን በመጠቀም የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልክ፣ ቦርሳና መሰል ንብረቶችን በመንጠቅና በመዝረፍ የተሰማሩ እንዳሉ በተደረገው ክትትል ለማወቅ መቻሉን አስረድተዋል።
በመሆኑም እነዚህንና መሰል ወንጀሎችን ለመከላከል ሲባል የፀጥታ ቴክኒክ ኮሚቴ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ከግንቦት 20 /2015 ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎች እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ መጣሉን ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።
መረጃው የክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው።
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ከተማ በሞተር ሳይክሎች ላይ የሰዓት ገደብ ተጣለ።
በጋምቤላ ከተማ በተሽከርካሪ የሚፈፀም ስርቆትና ዝርፊያን ለመከላከል ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ድረስ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎች ላይ እገዳ መጣሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰናይ አኩዎር ፤ በከተማው የንጥቂያና ዝርፊያ ወንጀሎች #መባባስ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ እያስነሳ ነው ብለዋል።
በከተማዋ እየተስፋፋ በመጣው የዝርፊያና መሰል ወንጀሎች በዋናነት ተጠቂዎቹ ሴቶችና አቅመ ደካሞች እንደሆኑ ገልፀው ወንጀሎቹን ለማስቀረት የፀጥታ ሀይሉ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ ተናግረዋል።
በተለይም በከተማው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎችን በመጠቀም የተንቀሳቃሽ የእጅ ስልክ፣ ቦርሳና መሰል ንብረቶችን በመንጠቅና በመዝረፍ የተሰማሩ እንዳሉ በተደረገው ክትትል ለማወቅ መቻሉን አስረድተዋል።
በመሆኑም እነዚህንና መሰል ወንጀሎችን ለመከላከል ሲባል የፀጥታ ቴክኒክ ኮሚቴ በወሰነው ውሳኔ መሰረት ከግንቦት 20 /2015 ከምሽቱ 3 ሰዓት እስከ ጠዋቱ 12 ሰዓት ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክሎች እንዳይንቀሳቀሱ እገዳ መጣሉን ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።
መረጃው የክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው።
@tikvahethiopia