TIKVAH-MAGAZINE


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን +251913134524

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


በ10 ከተሞች በሊዝ ጨረታ መሬት ለመውሰድ ካሸነፉት መካከል 71 በመቶ የሚሆኑት ስራ አለመጀመራቸውን ጥናት አመለከተ

በኢትዮጵያ 10 ከተሞች በሊዝ ጨረታ መሬት ለመውሰድ አሸናፊ ከሆኑት 636 ተጫራቾች መካከል 71 በመቶ የሚሆኑት ስራ አለጀመራቸውን ጥናት አመለከተ።

በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ከከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋ፣ አሶሳ፣ ጋምቤላ፣ ባህርዳር፣ ሐረር፣ ሀዋሳ፣ ጂግጅጋ እና ሰመራ ከተሞች በሊዝ ጨረታ መሬት በወሰዱ ግለሰቦችና በመሬት ተቋማት ላይ ጥናቱ መካሄዱ ተነግሯል።

በ2014 ዓ.ም ጥናቱ በተካሄደበት ወቅት መሬት ለመውሰድ ተጫርተው በሊዝ አሸናፊ የሆኑ ሁለተኛ ወይም ሶስተኛ ደረጃ የያዙ 636 ተጫራጮች ሲካተቱ የግንባታ ግብዓት እጥረት፣ የፋይናንስ አቅርቦት ችግር፣ የመሰረተ ልማት አለመሟላት ምክንያት ወደ ስራ አለመግባታችውን መሬት የወሰዱ ግለሰቦችና ተቋማት አስረድተዋል።

በሊዝ መሬት ወስደው ወደ ልማት ባልገቡ አካላት ላይ የሚመለከተው ተቋም በሚያከናውነው የክትትልና ቁጥጥር መላላት በ95 በመቶ በሚጠጉት ላይ እርምጃ #አለመወሰዱንም ጥናቱ አሳይቷል ሲል ኢዜእ ዘግቧል።

@TikvahethMagazine


በወር 15,000 ብር 💸💵💰💰 ማግኘት ይፈልጋሉ?

እንግዲያውስ
🚴‍♀️ ብስክሌት
🏍 ሞተር
🛵 E-bike ካልዎት ምን ይጠብቃሉ ከ ቢዩ ዴሊቨሪይ ጋር መስራት ይችላሉ።

💰ቢዩ ዴሊቨሪይ የምግብ አድራሽ ድርጅት ሲሆን ብስክሌት ፥ ሞተረ እና E-bike ካለው ግለሰብ ጋር አብሮ መስራት ይፈልጋል።

የስራ አድራሻ ፥ አዲስ አበባ

ለመመዝገብ:-


ከታች ባለ
ው ( Telegram Bot ) በመጠቀም የቀረባልችሁን ጥያቄ በመሙላት

✴️https://t.me/DriversRegistration_bot

ወይም

☎️ 9533 ላይ በመደወል መመዝገብ ይችላሉ።


ዩናይትድ ኪንግደም የህጻናት ደፋሪዎችን የወላጅነት መብት የሚነጥቅ ህግ ልታወጣ ነው

ዩናይትድ ኪንግደም በከባድ ወሲባዊ ጥቃቶች የተከሰሱ ህጻናት ደፋሪዎች በልጆቻቸው ላይ ያላቸውን መብት የሚነጥቅ ህግ ልታወጣ መሆኑ ተሰምቷል።

አዲስ ለሆነው ለዚህ ህግ መነሻ የሆነው አንዲት እናት ህጻናትን ደፋሪ ነው የተባለው የቀድሞ ባለቤቷ ከልጃቸው ጋር እንዳይገናኝ ለማድረግ 30 ሺህ ፓውንድ ለህጋዊ ክፍያ ማውጣታቸውን ተከትሎ መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል።

በዚህም በወሲባዊ ጥቃቶች ጥፋተኛ የሆኑ በህጻናት ላይ ወሲባዊ ዝንባሌ ያላቸው ግለሰቦች (ፒዶፋይልስ) የወላጅነት መብታቸውን ወዲያውኑ የሚገፈፍ ይሆናል ተብሏል። የፍ/ቤቶች፣ የማረሚያ ቤቶች፣ የአመክሮና የህገመንግሥታዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ኃላፊነት ያለው ሎርድ ቻንስለር በህጉ ላይ መስማማታቸውም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine


የመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እድሳት 75 በመቶ መድረሱ ተገለፀ

የመንበረ ጸባኦት ቅድስት ስላሴ ካቴድራል እድሳት በ172 ሚሊየን ብር እየተከናወነ ሲሆን የጥገና ሥራው 75 በመቶ መድረሱ ተገለፀ።

እድሳቱ በውሉ መሰረት መጋቢት 30 ቀን 2016 ዓ.ም መጠናቀቅ ቢጋባውም በገቢ ማነስ እና ህንፃውን ለማጠናቀቅ የሚረዱ ግብአቶች ከውጭ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ እጥረት ችግር መሆኑ ተገልጿል።

የካቴድራሉ እድሳት ለማጠናቀቅ 85 ሚሊየን ብር መሰብሰብ እንደሚጠይቅ የተገለፀ ሲሆን የካቴድራሉን እድሳት ከፍጻሜ ለማድረስ  አስተዋጽኦ እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።

@TikvahethMagazine


ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ አሳሳቢነቱ በጎላው የጋዜጠኞች እሥር እና ሌሎች ጉዳዮች ከጋዜጠኞች ጋር እንዲወያዩ ጥያቄ ቀረበ

ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ አሳሳቢነቱ በጎላው የጋዜጠኞች እሥር እና እንግልት፣ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ያሉባቸው ችግሮች ላይ ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እና ጋዜጠኞች ጋር ውይይት እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ጠየቀ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ይህንን የጠየቀው ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር ያደረጉትን ተከታታይ ውይይት አስመልክቶ ሲሆን የውይይት ጥያቄውን ከሦስት ሳምንት በፊት ለጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ማስገባቱን እና ምላሽም እየተጠባበቀ መሆኑን ዶይቸ ቬለ ዘግቧል።

በቅርቡ ጠቅላላ ጉባኤውን ያደረገውና  ከ80 በላይ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማትን ፣ የሙያ ማሕበራትን እና የበይነ መረብ እንዲሁም የማኅበረሰብ መገናኛ ብዙኃንን ያቀፈው ምክር ቤቱ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ጋር በተከታታይ ውይይት ሲያደርጉ ነገር ግን ላለፉት 6 ዓመታት ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እና ከጋዜጠኞች ጋር በዘርፉ ላይ ስላሉ ችግሮችን ውይይት #አለመደረጉን አስታውሷል።

@TikvahethMagazine


የውጭ ባለሀብቶች በጅምላ እና ችርቻሮ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቀደ

ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ መደረጉን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቀዋል።

በዚህም መሰረት የውጭ ባለሀብቶች በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላክ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎችን የሚያሟሉ የውጭ ባለሃብቶች ከማዳበሪያ እና ነዳጅ በስተቀር በሁሉም የገቢ ንግድ ኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ይችላሉ ተብሏል።

የጅምላ ንግድን በተመለከተ ከማዳበሪያ ጅምላ ንግድ በስተቀር በሁሉም አይነት የጅምላ ንግድ መስኮች መሰማራት ይቻላል ሲባል በተጨማሪም የውጭ ባለሀብቶች ቅድመ ሁኔታዎችን ሲያሟሉ ለአገር ውስጥ ባለሃብት በተከለሉ ሁሉም የችርቻሮ ንግድ ስራዎች መሳተፍ እንዲችሉ መፈቀዱንም ብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

@TikvahethMagazine


ከዘመኑ ጋር ይዘምኑ!

      ራሰዎን በአንድ ቋንቋ አይገድቡ! የተለያዩ ቋንቋዎችን ይማሩ! የስራ ፣ የትምህርት እና የህይወት አማራጭዎን ያስፉ !
    ስልክዎን ተጠቅመው የፈለጉትን ቋንቋ በታላላቅ ዩንቨርቲዎች እና ኮሌጆች በሚያስተምሩ  ብቁ መምህራኖቻችን ተምረው በራስ መተማመንዎን ያዳብሩ!
   
👉እንግሊዘኛ
👉አረብኛ
👉አፋን ኦሮሞ
👉አማርኛ  ቋንቋዎችን የትም ሀገር ቢሆን አያሳስበዎት  በኦንላይን እናስተምረዎታለን!

ብራይት የስልጠና ማዕከል
    ለብርሀናማ ሕይወት ትክክለኛ ቦታ
0970828287
0932878889
https://t.me/brighttraining90


👉👉MESTURAH STORE 👈👈

ማንኛውንም አይነት እቃ ከ SHEIN እና ከ ALI EXPRESS ትእዛዝ መቀበል ጀምረናል ከታች ባሉት Website የፈለጋቹትን መርጣቹ በቴሌግራም ሊንካችን ይላኩልን

የቴሌግራም ሊንካችን https://t.me/mesturahstore

የቲክቶክ ገፃችን @mesturahstore?_t=8lYRHxeLhfp&_r=1' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@mesturahstore?_t=8lYRHxeLhfp&_r=1

በተጨማሪም 0911267699

የ SHEIN website: https://www.shein.com/

የ ALI EXPRESS website: https://www.aliexpress.com/


የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ለ658 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እንዳሻው ጣሰው እንደገለጹት የኢድ አል ፈጥር እና መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ658 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ እንደተደረገላቸው ተናግረዋል።

በዚህም፦

🟢 በሙሉ ይቅርታ ወንድ 637 ፤ሴት 11 ፤

🟢 በልዩ ሁኔታ ወንድ 3 ሴት 3

በጠቅላላው 654 ታራሚዎች ሲሆኑ ለ 4 ወንዶች ደግሞ የእስራት ቅናሽ ተደርጎላቸዋል።

በክልሉ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን ስር ባሉ #ሰባት ማረሚያ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች በ2016 በጀት ዓመት ይቅርታ ሲደረግ ይህ ለ2ኛ ዙር ነው።

@TikvahethMagazine


በአለም ተወዳጁ የአረቢካ ቡና ዝርያ ከ600ሺ ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ መገኘቱ በጥናት ተረጋገጠ

በአለም ተወዳጅነትን ያተረፈው የአረቢካ ቡና ዝርያ ከ600,000 ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ደኖች ውስጥ በሁለት ሌሎች የቡና ዝርያዎች ተፈጥሯዊ ውህደት ስለመፈጠሩ ዓለማቀፍ የሳይንስ ተመራማሪዎች ቡድን በጥናት ማረጋገጣቸውን በኔቸር ጄኔቲክስ ላይ የወጣው የምርምር ውጤት ያመላክታል።

ይህ የአረቢካ ቡና ተክል መነሻው ኢትዮጵያ ሲሆን ተመራማሪዎች የዚህን የቡና ተክል የጂኖሚክ መረጃን በመጠቀም የቡናውን የረዥም ጊዜ ታሪክ ለማጥናት እና በዘመናዊ መንገድ ከሚመረቱ  ሌሎች የቡና ተክሎች ጋር ያለውን ግንኙነት ለመለየት ጥናት ማድረጋቸው ተገልጿል።

በዚህም የአረቢካ ቡና ከ "Coffea canephora" እና " Coffea eugenioides "  ከተባሉ የቡና ዝርያዎች ከእያንዳንዳቸው ሁለት ክሮሞዞሞችን በመውሰድ ከ600ሺ አመታት በፊት ስለመፈጠሩ የሳይንስ ተመራማሪዎቹ በተጠቀሙት የጊዜ ስሌት ቀመር ማረጋገጣቸውን ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine


በወር 15,000 ብር 💸💵💰💰 ማግኘት ይፈልጋሉ?

እንግዲያውስ
🚴‍♀️ ብስክሌት
🏍 ሞተር
🛵 E-bike ካልዎት ምን ይጠብቃሉ ከ ቢዩ ዴሊቨሪይ ጋር መስራት ይችላሉ።

💰ቢዩ ዴሊቨሪይ የምግብ አድራሽ ድርጅት ሲሆን ብስክሌት ፥ ሞተረ እና E-bike ካለው ግለሰብ ጋር አብሮ መስራት ይፈልጋል።

የስራ አድራሻ ፥ አዲስ አበባ

ለመመዝገብ:-


ከታች ባለ
ው ( Telegram Bot ) በመጠቀም የቀረባልችሁን ጥያቄ በመሙላት

✴️https://t.me/DriversRegistration_bot

ወይም

☎️ 9533 ላይ በመደወል መመዝገብ ይችላሉ።


በግብርና ምርቶች ብክነት በዓመት ከ474 ቢሊዮን ብር በላይ እየታጣ መሆኑ ተነገረ

የግብርና ሚኒስቴር አዲስ ያስተዋወቀው የግብርና ምርቶች አስተዳደርና አመራር ስትራቴጂ፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ 474.67 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የምርቶች ብክነት መኖሩን አመልክቷል በማለት ሪፖርተር አስነብቧል።

እያጋጠመ ያለው ብክነት የምርት ሒደት የሚያቀላጥፉ ምርጥ ዘር፣ ውኃ፣ የአፈር ማዳበሪያ፣ የግብርና ኬሚካሎች፣ መሬት፣ የእንስሳት መኖ፣ እንዲሁም የእንስሳት መድኃኒቶችን በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል ካለመቻል እንደሆነ ተጠቅሷል። 

በመሆኑም በየዓመቱ 161.74 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ የሥጋና ወተት ምርቶች እንዲሁም 312.93 ቢሊዮን ብር የሚያወጡ የቅባት እህሎች፣ ጥራጥሬዎች፣ ፍራፍሬዎችና አትክልቶች እየባከኑ መሆኑም ነው የተገለፀው።

@TikvahethMagazine


በኦሮሚያ ክልል እየተካሄደ ባለ የቁጠባ ዘመቻ በርካታ ጥሬ ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው።

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አከባቢዎች ቁጠባን ለማበረታታት በተደረጉ ዘመቻዎች ነዋሪዎች በርካታ ጥሬ ገንዘብ በስንቄ ባንክ በኩል በቁጠባ መልክ ማስቀመጥ መቻላቸው ተገልጿል።

ለአብነትም በጅማ ዞን ሊሙ ወረዳ በነበረ የአንድ ቀን ዘመቻ ብቻ 252 ሚሊዮን ብር በስንቄ ባንክ በኩል ገቢ መሆን ችሏል። የወረዳው አስተዳዳሪ አንደገለጹት በዚህ ዓመት 2.4 ቢሊዮን ብር በቁጠባ መልክ ወደ ባንኩ እንዲገባ እየሰሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተመሳሳይ በአጋሮ ከተማ በአንድ ቀን በተደረገ የቁጠባ ዘመቻ 21.8 ሚሊየን ብር በስንቄ ባንክ በቁጠባ ሂሳብ ገቢ ሆኗል ተብሏል።

@TikvahethMagazine


#Update: በጄኔቫ ለኢትዮጵያ ድጋፍ ለማሰባሰብ በተደረገው ስነ ስርዓት ሀገራት ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደሚሰጡ አስታወቁ

በኢትዮጵያ ለተከሰተው የሰብዓዊ ቀውስ አስቸኳይ 1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ለማሰባሰብ በስዊትዘርላንድ ጄኔቫ በተካሄደው ሥነ ሥርዓት ሀገራት 630 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለኢትዮጵያ እንደሚሰጡ አስታወቁ።

በዚህም አሜሪካ 253 ሚሊዮን ዶላር እንደምትሰት ቃል ስትገባ ዩናይትድ ኪንግደም 125 ሚሊዮን ዶላር እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት በድምሩ ከ139 ሚሊየን ዶላር በላይ ለመስጠት ቃል ገብተዋል።

የመንግስታቱ ድርጅት በሚቀጥሉት 3 ወራት ብቻ ለኢትዮጵያ እርዳታ ለማቅረብ 1 ቢሊዮን ዶላር  እንዲሁም በሀገሪቱ በ2024 እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች ድጋፍ ለማድረግ 3.24 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገኛል ማለቱ ይታወሳል።

@TikvahethMagazine


👉👉MESTURAH STORE 👈👈

ማንኛውንም አይነት እቃ ከ SHEIN እና ከ ALI EXPRESS ትእዛዝ መቀበል ጀምረናል ከታች ባሉት Website የፈለጋቹትን መርጣቹ በቴሌግራም ሊንካችን ይላኩልን

የቴሌግራም ሊንካችን https://t.me/mesturahstore

የቲክቶክ ገፃችን @mesturahstore?_t=8lYRHxeLhfp&_r=1' rel='nofollow'>https://www.tiktok.com/@mesturahstore?_t=8lYRHxeLhfp&_r=1

በተጨማሪም 0911267699

የ SHEIN website: https://www.shein.com/

የ ALI EXPRESS website: https://www.aliexpress.com/


#cloudbridge. #traininginstitute

ክላውድ በሪጂ ማሰልጠኛ ተቋም ፤ለስልጠና ፍላጊዎች በሙሉ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽ እውቀት አቅም ግንባታ ነፃ ስልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቆ እናንተን በጉጉት  ይጠብቃል::

ስልጠና ሚሰጥባችው ዘረፎች መካከል፡
1, Digital marketing
2,Web development
3, Interior design
4, Graphic design

የስልጠና ቦታ
ሲቲ ሞል 6ኛ ፎቅ, መገናኛ ድልድይ,wow burger ያለበት፣Megenagna siti Mall 6th, Addis Ababa, Ethiopia

ለተጨማሪ መረጃ
094-228-0000
092-083-8483
ያሉን ቦታዎች ውስን ናቸው ፈጥነው በአካል መተው ይመዝገቡ።
         ለአንድ ቀን ሚቆይ ነፃ ስልጠና!
Register online
https://cloudbridgeacademy.com/registration


#Update: በኢትዮጵያ ለተከሰተው የሰብዓዊ ቀውስ አስቸኳይ 1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ የማሰባሰብ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ

በስዊትዘርላንድ ጄኔቫ ዛሬ ሚያዚያ 8/2016 ዓ.ም በኢትዮጵያ ለተከሰተው የሰብዓዊ ቀውስ የ1 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ  የማሰባሰብ ሥነ ሥርዓት ተካሄደ። በስርዓትቱም ዩናይትድ ኪንግደም 100 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ ለኢትዮጵያ እንደምታደርግ አስታውቃለች።

የገንዘብ ድጋፉን ሥነ ሥርዓት ያዘጋጁት የኢትዮጵያ፣ የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተባባሪ አካላት ለቀረበው የገንዘብ ድጋፍ ጥሪ አዎንታዊ ምላሽ የሚጠብቁ መሆኑን ገልፀዋል።

በሀገቱ በድርቅ፣ ጎርፍ እና ግጭት ሚሊዮኖችን ከቀያቸው ያፈናቀለ ሲሆን፣ በመጪዎቹ ከሐምሌ 2016 እስከ መስከረም 2017 መካከል የምግብ እጥረት የሚገጥማቸው ሰዎች ቁጥር 10.8 ሚሊዮን እንደሚደርስ ተገምቷል።

@TikvahethMagazine


"በ6 ወሩ ፌስቡክና ቴሌግራም የጥላቻ ንግግርና ሀሰተኛ መረጃዎች ማስተላለፊያ ዋነኛ መድረኮች ነበሩ" - ኢመብባ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በዛሬው ዕለት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያለ የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃ ሀገራዊ ሪፖርት ይፋ አድርጓል። ባለሥልጣኑ ሪፖርቱን ይፋ ሲያደርግ ይህ ለ2ኛ ጊዜ ነው።

ሪፖርቱ ከሀምሌ 2015 - ጥር 2016 ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ሲሆን 5 የማኅበራዊ ትስስር መድረኮች (ፌስቡክ፣ ቴሌግራም፣ ቲክቶክ፣ ዩቲዩብ እና ኤክስ) ላይ ያተኮረ ነው።

ℹ️ መረጃ የተሰበሰበው እንዴት ነው?

ባለሥልጣኑ ሪፖርቱን ለማውጣት በ9192 ነጻ የስልክ መስመር የተሰበሰቡና የተመረጡ 1400 ጥቆማዎችን እንዲሁም በአዲስ አበባና በአምስት ክልሎች 2 ሺ መጠይቆችን በመበተን የተሰበሰቡ 1776 የማኅበረሰብ ምላሾች ላይ ያደረገ ነው።

📌 የሪፖርቱ ያካተታቸው ዋና ዋና ነጥቦች

- ሪፖርቱ ባካተተው 6 ወራት የብሔር ማንነት ላይ ካተኮረ የጥላቻ ንግግር ይልቅ #ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ የጥላቻ ነግግሮች ጎልተው ወጥተዋል ይላል።

- በዚህ 6 ወር ሃይማኖታዊና ጾታዊ ማንነቶች ላይ የሚደርሱ የጥላቻ ይዘቶች #ዝቅተኛ ሆነው መመዝገባቸውን ጠቅሷል።

- የጥላቻ ንግግር ስጋት ደረጃ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል የሚለው ሪፖርቱ የጥላቻ መልዕክቶችን ከማስተላለፍ ለጥቃትና #ለአመጽ ወደ ማነሳሳት መሻገሩን ጠቁሟል።

- በ6 ወሩ የዳሰሳ ጥናት መሰረት የጭካኔ አገላለጽ በከፍተኛ ደረጃ ተሰራጭቶ የታየ ሲሆን ይህ ስርጭት #በቴሌግራም በ65% እንደተሰራጨ ይገልጻል።

- የተጠቃሚዎች ገጽ ስያሜ በአመዛኙ ትክክለኛ ማንነታቸውን በመደበቅ በሌላ ሥያሜ የሚጠቀሙ ናቸው።

- በአስተያየት መስጫ ከሚሰጡ አስተያየቶች 86.33 % የሚሆነው የጥላቻ መልዕክቱን የሚደግፍ ሲሆን፤ 11.57 % የሚቃረኑ ግን የጥላቻ ንግግሮች እንዲሁም 2.1% ገለልተኛ አስተያየቶች ናቸው።

- ሐሰተኛ መረጃን በሚመለከት ጥናቱ በከፍተኛ ሁኔታ ተስተውሏል ያለው የተሳሳተ መረጃ እና በተሳሳተ አውድ የቀረቡ ይዘቶችን ሲሆን የተቀነባበረ ይዘት በመጠኑ መስተዋሉን ጠቅሷል።

- መጠይቁን ከመለሱትና የጥላቻና ሀሰተኛ መረጃን ሪፖርት ካደረጉ 70 በመቶዎቹ ሪፖርቱ እንዳልወረደ ገልጸዋል፤ የክትትል ቡድኑም ሪፖርት ካደረጋቸው ውስጥ 2 በመቶው ብቻ መውረዳቸውን ጠቅሷል።

⛔️ የሪፖርቱ ውስንነቶች ምንድን ናቸው?

በሪፖርቱ እንደተጠቀሰው አሰራሩ #በቴክኖሎጂ ባለመታገዙና መረጃ የማሰባሰቡ ሂደት በሰው ኃይል በመሰራቱ በውስንነት ያስቀመጠ ሲሆን፤ የተለያዩ ሀገራዊ ቋንቋዎችን መሸፈን አለመቻሉን አንስቷል።

ሪፖርቱ ይህንን ይበል እንጂ ሀገራዊ የችግሩን ጥልቀት ከማሳየት አንጻር ሪፖርቱ የተጠናቀረበት መንገድና የተጠቀመው የመረጃ ምንጭ ላይ ውስንነት መኖሩን ከመድረክ በተሰጡ ሀሳቦች ተመላክቷል።

የባለሥሥልጣኑ ምክትል ዳይሬክተር ዮናታን ተስፋዬ፥ "ሪፖርቱ ብዙ ጉድለቶች ሊኖሩበት ይችላል . . . የመረጃ አሰባሰብና ትንተናው አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ያሳያል" ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም በአዋጁ የተሰጣቸው ኃላፊነት ውስን መሆኑን በመጥቀስ፥ "አዋጁ በራሱ ክፍተት አለበት  . . . ማስፈጸሚያ ደንብ አልተዘጋጀለትም" ሲሉም አንስተዋል።

በሪፖርቱ እንደተገለጸው፥ ከባለፈው ዓመት የጥላቻ ንግግር አንጻር ሲታይ መረጃዎቹ ከስድብ ወደ ስብእናን መጉዳት/ character assassination/ ከፍረጃ ወደ አግላይ ጥቅል ፍረጃ /segregation/ ከማስፈራሪያ ወደ ስጋትነት፣ ከጭካኔ አገላለጽ ወደ #ጥቃት ማነሳሳትና የግድያ ጥሪ ከፍ ብለው ታይተዋል፤ ችግሩ ሁኔታ አጣዳፊ መፍትሄ የሚፈልግ ሆኖም ታይቷል ሲል አስቀምጧል፡፡

@TikvahethMagazine


በወር 15,000 ብር 💸💵💰💰 ማግኘት ይፈልጋሉ?

እንግዲያውስ
🚴‍♀️ ብስክሌት
🏍 ሞተር
🛵 E-bike ካልዎት ምን ይጠብቃሉ ከ ቢዩ ዴሊቨሪይ ጋር መስራት ይችላሉ።

💰ቢዩ ዴሊቨሪይ የምግብ አድራሽ ድርጅት ሲሆን ብስክሌት ፥ ሞተረ እና E-bike ካለው ግለሰብ ጋር አብሮ መስራት ይፈልጋል።

የስራ አድራሻ ፥ አዲስ አበባ

ለመመዝገብ:-


ከታች ባለ
ው ( Telegram Bot ) በመጠቀም የቀረባልችሁን ጥያቄ በመሙላት

✴️https://t.me/DriversRegistration_bot

ወይም

☎️ 9533 ላይ በመደወል መመዝገብ ይችላሉ።


ከ7 እስከ 18 ለሆኑ ልጆች የኦንላይን  ኮዲንግ  ስልጠና

ስልጠና April 20 , 2024 ቅዳሜ ይጀምራል።

ከ7 እስከ 13 ለሆኑ ህጻናት የ6 ሳምንታት የscratch ስልጠና( ጌም እና አኒሜሽን እየሰሩ ነው ሚማሩት)።

ከ14 እስከ 18 ለሆኑት የ website ስልጠና ለ 2 ወር።

የምስክር ወረቀት ያገኛሉ

ክፍያ ለ6 ሳምንት ፕሮግራም 2500 ብር ነው።
ክፍያ ለ 2 ወር ፕሮግራም 3500 ብር ነው።

በቴሌግራም መረጃ ለማግኘት ያግኙን
@koderlabtrainingcenter ወይም በ 0940121072 ይደውሉ።

ይህንን ሊንክ በመጠቀም ሬጅስተር ያርጉ።
https://forms.gle/J3CeN5XE4vQW3MF49

20 last posts shown.