TIKVAH-MAGAZINE


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524


Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


የደብረምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል እና ህንፃ ቤተክርስቲያን ምርቃት ዛሬ ተከብሮ ውሏል።

በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ የምትገኘው የደብረምጥማቅ ፃድቃኔ ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል እና አስር አመታት የግንባታ ሂደትን የወሰደው ህንፃ ቤተክርስቲያን ምርቃት በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን ወረዳው አስታውቋል።

ከእስከዛሬዉ ለየት ባለ መልኩ ሰፊ ቁጥር ያለዉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መታደማቸውን የገለጹት የወረዳዉ ሠላምና ድህነት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሸዋፈረዉ ግርማ በዓሉ በድምቀት አክብረዉ ዉለዋል ሲሉ ገልጸዋል።

ኃላፊው ክብረ በዓሉም በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ምዕመናኑ ወደ ቤታቸዉ የመሸኘቱ ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።

t.me/tikvahethmagazine

21.5k 0 20 30 422

በሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይ ሲ ቲ ፍጻሜ ውድድር የተሳተፉት ኢትዮጵያን ተማሪዎች 3ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ።

ኢትዮጵያን ወክለው በ7ኛው የሁዋዌ ዓለም አቀፍ የአይ ሲ ቲ ፍጻሜ ውድድር የተሳተፉት ተማሪዎች የሶስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀቁ። ውድድሩ ከግንቦት 16 እስከ 20 ቀን 2015 ዓ.ም በቻይና ሼንዘን ከተማ ሲካሄድ ቆይቷል። ተሳታፊዎቹም ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ተገልጿል። (FBC)

t.me/tikvahethmagazine

23.9k 0 20 12 230

ወንድማችንን እናሳክም🙏

ደግነት ዳንኤል ባሳ ይባላል፤ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 5ኛ ዓመት (Clinical ll) የሕክምና ተማሪ ነው። በአሁኑ ሰዓት  ባጋጠመዉ የአንገት አከባቢ ህብለ ሰረሰር እጢ በሽታ (C2 –C3 intramedullary spinal cord tumor) ክፉኛ እየታመመ ይገኛል።

ለዚህም በአስቸኳይ ሕክምናን የማያገኝ ከሆነ በሽታዉ የመተንፈሻ ጡንቻዎችን በመጉዳት ሕይወቱን አደጋ ላይ ይጥላል፡፡ ሕክምናዉም ሀገር ዉስጥ ስለሌለ በአስቸኳይ ወደ ዉጪ ሀገር ሄዶ እንዲታከም የሐዋሳ ዩኒቨርስቲ ስፔሻላይዝድ እና ኮምብርሄንሲቨ ሆስፒታል ሕክምና ቦርድ ወስኗል።

ለህክምናው ቢያንስ 1.5 ሚሊዬን ብር እንደሚያስፈልገዉ ተነግሮታል፡፡ ይህም ከቤተሰቡ አቅም በላይ ስለሆነ ሁላችውም የአቅማችሁን ትብብር እንድታደርጉ ይጠይቃል።

CBE፡ 1000205065478
Deginet Daniel Bassa

Dashen Bank፡ 5049110500011
Deginet Daniel Bassa

gofundme-👇👇👇👇👇
https://gofund.me/69abf8d1

+251949613179 ደግነት ዳንኤል

በተጨማሪም፦
0941047406 ሳምሶን መስቀሌ
0904761931 ናፓሊዮን ፈ/ሥላሴ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

t.me/tikvahethmagazine


የልማት አርበኛው የማሩ አበበ የህይወት ታሪክ  መጽሀፍ ተመረቀ።

በጋዜጠኛ ዓይናለም ሀድራ እና በጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ የተዘጋጀው የአቶ ማሩ አበበን የህይወት ታሪክ የሚዳስስ መጽሐፍ እሁድ ግንቦት 20 2015 ዓ.ም 5 ኪሎ በሚገኘው በቅርስ  ባለስልጣን አዳራሽ ተመርቋል።

ታሪካቸው በመጽሀፍ የተሰነደላቸው የደን ልማት ባለሙያው አቶ ማሩ ኮተቤ ኪዳነምህረትን እንዲሁም አሁን እንጦጦ ፓርክ የተሰራበትን ስፍራ በማልማት ለሀገር ጠቃሚ ተግባር ያከናወኑ ናቸው፡፡

ከደን ልማቱም ባሻገር በመንገድ ቅየሳ የጎላ ሚና አበርክተዋል፡፡ አቶ ማሩ አበበ ለሀገር ትልቅ ስራ በማበርከታቸው  መታሰቢያ ይሆን ዘንድም በስማቸው በደቡብ ወሎ ዞን ት/ቤት ተሰይሞላቸዋል፡፡

በምረቃ መርሀ-ግብሩ ላይ  በኢትዮጵያ ደን ልማት የብሄራዊ ደን ልቀት ፕሮግራም አስተባባሪ ዶክተር ይተብቱ ሞገስ በክብር እንግድነት የታደሙ ሲሆን ወጣት የደን ባለሀብቶች ከአቶ ማሩ የሥራ ትጋት  ብዙ ሊማሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል፡፡ 

የአቶ ማሩ የህይወት ታሪክ መጽሀፍ ምረቃ ላይ የአቶ ማሩ ቤተሰቦች እና ወዳጆች የታደሙ ሲሆን ወንድማቸው አቶ ዳኘው አበበ መጽሀፉን ሙሉውን በመግዛት ገቢውን በአቶ ማሩ ስም ለተሰየመው ት/ቤት ማደረጃ እንዲሆን አውለዋል፡፡ 

via ጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ

t.me/tikvahethmagazine


ሽመልስ በቀለ 1⃣8⃣ ገስት ሀውስ

በውቢቷ ሀዋሳ ቆይታዎ የት ለማረፍ አስበዋል ? ንፁህ እና በደንበኞቻችን ተወዳጅ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን መጥተው የእረፍት ጊዜውን ያሳልፉ።

እንግዶቻችንን ተቀበልን ለእይታ ሳቢ በሆነው የእንግዳ ማረፊያችን ማስተናገድ ከጀመርን አመታትን አስቆጥረናል።

አድራሻችን :- ሀዋሳ አርቴፍሻል ስታዲየም መንገድ ላይ ያገኙናል።

ለተጨማሪ መረጃ እና ለትዕዛዝዎ ይደውሉልን :- 0928684848

#ShemelesBekele18


ለኪራይ ዝግጁ የሆኑ የሱቅ እና ዲስፕሌይ ቦታዎች በአምባሳደር ሞል!

አድራሻ፡ አራት ኪሎ፣ በትምህርት ሚኒስቴር እና በአብርሆት ቤተ መጻሕፍት መካከል

ለበለጠ መረጃ፡ +251 911 74 5899 ወይም +251 923 28 4587

https://goo.gl/maps/dcpQ8MMtvCi5jDRcA

https://ambassadormall.et


አምስት መቶ አስራ አንድ ማህተሞችን  በመጠቀም የሀስት ሰነዶች ሲያዘጋጁ የነበሩ ተጠርጣሪዎች ተያዙ።

አምስት መቶ አስራ አንድ (511) ማህተሞችን  በመጠቀም የሃስት ሰነዶች ሲያዘጋጁ  የነበሩ ወንጀል ፈጻሚዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ አስታውቋል።

አቶ አሻግሬ በለጠ አለሙ የተባለው  ግለሰብ  እና ግብረአበሮቹ በአራዳ ክፍለ ከተማ ከ1500 እስከ 4500 ብር በማስከፈል የሃስት ሰነዶችን በማዘጋጀት የወንጀል ተግባር ሲፈፅሙ እንደነበር ነው የተገለጸው።

ከተጠርጣሪዎቹ ጋር ሀስተኛ የሆኑ የመከላኪያ ሠራዊት የስንብት ወረቀት፣ የመከላከያ የፍቃድ ወረቀት፥  የብሔራዊ መረጃ መታወቂያ፣ የመከላከያ ልዩ ዘመቻ ም/አዛዥ ሻ/ቃ፣ የመከላከያ ሠራዊት መታወቂያ በፍተሻ ወቅት ተይዟል።

በተጨማሪም የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የፌደራል አሰተዳደር  ፓሊስ ኮሚሽን የወንጀል መከላከል  ዳርክቶሬት፣ የፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ፥ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ የሀገር መከላከያ ሚኒስትር  ማዕከላዊ፣ 31ኛ ክፍለ ጦር መምሪያ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሉ የሀሰት ሰነዶች በኤግዚቢትነት መያዙን ፖሊስ አስታውቋል።

t.me/tikvahethmagazine


የቁማር ሱስ የብዙዎችን ህይወት እያበላሸ ነው። እርሶ ውይም በአጠገቦ የቅርቤ የሚሉት ሰው በቁማር ሱስ ምክንያት ይጎዳሉ ብለው ይሰጋሉ?
Poll
  •   ቁማር ሱስ ሆኖብኛል፤ አዎ እሰጋለው
  •   የቅርቤ የምለው ሰው የቁማር ሱስ አለበት፤ አዎ እሰጋለው
  •   በአጠገቤ የቁማር ሱስ ያለበት ሰው የለም ግን ያሳስበኛል።
  •   በዚህ ዙሪያ ብዙም የማውቀው ነገር የለም
5145 votes

31.4k 0 41 43 170

#WolaitaSodo

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባለፉት 9 ወራት ከ900 ለሚበልጡ ሰዎች አጠቃላይ የኩላሊት እጥበት (ዲያሊሲስ) ሕክምና መስጠቱን አስታውቋል።

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኩላሊት እጥበት (ዲያሊሲስ) ሕክምና ማዕከሉ፦

- የኩላሊት ናሙና ምርመራ፤

- የተሟላ የኩላሊት እጥበት፤

- ለእጥበት የደምስር ቱቦ የማስገባት፤

- የኩላሊት፥ የሽንት ቧንቧና የፊኛ ጠጠር ህክምና፤

- የፕሮስቴት እድገትና ፕሮስቴት ካንሰር ህክምና፤

- የኩላሊት፥ የፊኛና ቴስቲኩላር ካንሰር ሕክምና፤

- በጠባሳ ምክንያት ለሚከሰት የሽንት ቧንቧ መጥበብ ሕክምና፤

- የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ሕክምና እና ሌሎች አገልግሎቶችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውቋል።

t.me/tikvahethmagazine


አምስት ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን የነጻ ትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ሊያደርጉ ነው።

ሊሴ ገ/ማርያም ፣ ጣሊያን ት/ቤት፣ ቤንግሀም አካዳሚ፣ ሳንፎርድአለም አቀፍ ት/ቤትና አሜሪካን ማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች የመክፈል አቅም የሌላቸው ተማረዎችን ነጻ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

ከማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደረጉት የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ የማኅበረሰብ ትምህርት ቤቶች 10 በመቶ ተማሪዎችን ተቀብለው እንዲያስተምሩ ከስምምነት ደርሰዋል ብለዋል።

t.me/tikvahethmagazine

30.1k 0 29 15 170

#Update: ሪድም ዘጀኔሬሽን USAID ጋር በመተባበር ዕድሜያቸው ከ18 -29 ለሆኑ ወጣቶች በቡድን ሆነው የሚሳተፉበት የስዕል ውድድር ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቃል። በውድድሩ የሚሳተፉ ወጣቶች ከ60 ሺ ብር ጀምሮ ሽልማት የሚያገኙ ይሆናል።

ለዝርዝሩ https://t.me/tikvahethmagazine/19692


በተቆፈረ ገድጓድ ውስጥ ለመዋኘት የገባው ወጣት ህይወቱ አለፈ

ዛሬ ግንቦት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በሸገር ከተማ አንፎ አደባባይ አካባቢ ተቆፍሮ ክፍቱን በተተወ ጉድጓድ ዉስጥ እድሜዉ 19 ዓመት የሆነ ወጣት ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል።

ወጣቱ ህይወቱ ያለፈዉ ምንም ዓይነት የዋና ችሎታ ሳይኖረዉ ዋና ለመዋኘት በመግባቱ መሆኑ ተነግሯል። የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጠላቂ ዋናተኞች የወጣቱን አስከሬን አዉጥተዉ ለፖሊስ ማስረከባቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል።

t.me/tikvahethmagazine


በሰው አንጎል ውስጥ ‘ቺፕ’ የሚቀብረው የኢላን መስክ ኩባንያ በሰው ላይ ሙከራ ሊያደርግ ነው።

ኒውራሊንክ የተባለው በሰው አንጎል ውስጥ ‘ቺፕ’ የሚቀብረው የኢላን መስክ ድርጅት በሰው ልጅ ላይ ሙከራ እንዲያደርግ ከአሜሪካ የምግብ እና መድኃኒት አስተዳዳር ባለሥልጣን (ኤፍዲኤ) ፈቃድ አግኝቷል።

የኒውራሊንክ ፈቃድ ማግኘት ዜና የመጣው የስዊትዘርላንድ አጥኚዎች አእምሮ ላይ በተሳካ ሁኔታ ኮምፒውተር ከቀበሩ በኋላ ነው። በዚህም ሰውነቱ የማይታዘዝለት አንድ የኔዘርላንድስ ዜጋ ጭንቅላቱ ውስጥ በተቀበረለት ቴክኖሎጂ አማካይነት ስለመራመድ በማሰብ ብቻ መራመድ መቻሉ ተነግሯል።

ኒውራሊንክ፤ ‘ማይክሮቺፕ’ ተጠቅሞ ሰውነታቸው የማይታዘዛቸውን (ፓራላይዝ) እና ዐይነ-ስውራንን መርዳት ያልማል። አልፎም አንዳንድ የአካል ጉዳት ያለባቸው ሰዎች ኮምፒውተር እና ተንቀሳቃሽ ስልክ እንዲጠቀሙ ለማድረግ አመቺ ሆኑታን ይፈጥራል ተብሏል።

መስክ፤ ሐሙስ ዕለት በትዊትር ገጹ ኒውራሊንክ “የሰው ልጅን ለማገዝ አንድ እርምጃ ወደፊት ተጉዘናል” ብሏል። ተቋሙ በቅርቡ የሰው ልጅ ላይ ሙከራ ለማድረግ “ተሳታፊዎችን” መመዝገብ እንደሚጀምር አሰውቋል።

የኒውራሊንክ ድረ-ገጽ “ደኅንነት፣ ተደራሽነት እና አስተማማኝ” የሆነ ሥራ እንደሚሠራ ቃል ገብቶ ጥናቱን በጥንቃቄ እንደሚያካሂድ ይገልጻል።

የዘርፉ ባለሙያዎች ግን አእምሮ ውስጥ ቺፕ መቅበር በጣም ጥንቃቄ የሚፈልግ እና ከባድ ጥናት የሚጠይቅ ነው ሲሉ ያስጠነቅቃሉ። አልፎም ቴክኖሎጂው በሰፊው ከመሠራጨቱ በፊት ቴክኒካዊ እና ሥነ-ምግባራዊ ጎኑ መቃኘት አለበት ይላሉ። (BBC)

t.me/tikvahethmagazine

23.4k 1 94 17 268

ትላንትና ዛሬ በተከሰቱ አደጋዎች የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ

ዛሬ ግንቦት 17 ቀን ከቀኑ 5:49 ደቂቃ ላይ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5  የቦሌ ለሚ እንደስትሪ ፓርክ ዕድሜዉ 35 ዓመት የተገመተ በፓርኩ የኤሌክትሪክ ባለሙያ የሆነው ግለሰብ በፋብሪካዉ ቤዝመንት በስራ ላይ እያለ በኤሌክትሪክ ተይዞ ህይወቱ አልፏል።

በሌላ በኩል ትላንት ምሽት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ቡልቡላ አካባቢ በሚገኝ ድልድይ ላይ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2 -47681 የሆነ ተሽከርካሪ በእግረኞች ላይ ባደረሰዉ ግጭት ሁለት ሰዎች ከባድ ጉዳት የደረሰባቸዉ ሲሆን የአንድ ሰዉ ህይወት አልፏል ተብሏል።

ህይወቱ ያለፈዉ የ35 ዓመት ሰዉ በተሽከርካሪዉ ተገጭቶ 20 ሜትር ጥልቀት ባለዉ ገደልና ወንዝ ዉስጥ በመግባቱ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጠላቂ ዋናተኞች ፍለጋ ሲያካሄዱ ቆይተዉ ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ረፋድ አስከሬኑን አግኝተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።

መረጃው፦ እሳትና አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን ነው

t.me/tikvahethmagazine


የአሰብ ኮሪደር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመጪው ሐምሌ ወር ይጠናቀቃል ተባለ።

ኢትዮጵያን በአሰብ በኩል ከኤርትራ ጋር የሚያገናኘው 71 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመጪው ሐምሌ ወር  2016 በጀት ዓመት ይጠናቀቃል ሲልየኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አስታውቋል።

በመንግስት በተመደበ ሁለት ቢሊዮን ብር በጀት የሚሰራው ግንባታው በገጠር 10 ሜትር እና በቀበሌ ከተሞች ደግሞ 21 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል።

የአሰብ ኮሪደር የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የሚካሄደው ሻንዶንግ ሉሽያዎ ግሩፕ ካምፓኒ ሊሚትድ በተባለ የውጭ ሀገር የሥራ ተቋራጭ ሲሆን ከአዲስ አበባ 787 ኪሜ ርቀት ላይ ከኤሊ ዳር ከተማ 16 ኪሜ በኃላ ጀምሮ ኢትዮ ኤርትራ ድንበር ላይ ያበቃል።

እንደሀገር የተከሰተው ከፍተኛ የሲሚንቶ እጥረት፤ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት፤ እና በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ተቀብረው ያልመከኑ ፈንጂዎች መኖር በግንባታ ሂደቱ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደሩን አስተዳደሩ ገልጿል።

t.me/tikvahethmagazine


ኮካ-ኮላ 50 መስማት የተሳናቸው ወጣቶችና እና ሴቶችን በቀርከሃ ሙያ አሰልጥኖ አስመረቀ።

ኮካ ኮላ ቤቭሬጅስ አፍሪካ-ኢትዮጵያ የወጣት ሴቶች ማቋቋሚያ ማህበር ከተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር 50 መስማት የተሳናቸው ወጣቶችና እና ሴቶችን ለሶስት ወራት በቀርከሃ እደጥበብ ሙያ አሰልጥኖ አስመርቋል።

“Signs of Success” በሚል የተዘጋጀው የሶስት ወራት የሥልጠና መርሃግብር ሲሲቤኤ-ኢትዮጵያ ወጣቶችን፣ አካል ጉዳተኞች እና ሴቶች በኢኮኖሚ የተካተቱ እንዲሆኑ ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ መሆኑን ተቋሙ በላከልን መግለጫ ጠቅሷል።

ኮካ ኮላ ቤቭሬጅስ አፍሪካ በቅርቡ የፕላስቲክ ቆሻሻን መልሶ ጥቅም ላይ ለሚያውሉ በአዲስ አበባ ለሚገኙ  30 ማህበራትን 10 ሚሊየን ብር ድረስ ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በባህርዳርና ድሬዳዋ በሚገኙንት ፋብሪካዎቹ በኩልም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ የንፁህ ውሃ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ አስረክቧል።

t.me/tikvahethmagazine


#GaamoTv : የጋሞ ቴሌቪዥን የሙከራ ስርጭት ጀመረ።

የጋሞን ህዝብ የማህብረሰብ ቴሌቪዥን ጣቢያ ለማቋቋም በቅርቡ ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን የቴሌቪዥን አገልግሎት ህጋዊ ፍቃድ ያገኘው ጋሞ ቲቪ ባሁኑ ሰዓት የሙከራ ስርጭት በHD ላይ በጥራት ማስተላለፍ መጀመሩ ተገልጿል።

የሙከራ ስርጭቱን በEthiosat ላይ በማድረግ Frequency 11605
NSS 12 Polarization H  Symbolrate 45000 ላይ መከታተል እንደሚቻል ተነግሯል።

t.me/tikvahethmagazine


#Adama

የአዳማ ከተማን በዲጂታላይዜሽን አገልግሎትና ቴክኖሎጂ ለማዘመን 12 ግቦችን የያዘና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች የተካተቱበት የከተማዋ የቀጣይ አስር ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ ይፋ የሆነ ሲሆን የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ በስማርት አዳማ ፕሮጄክት ውጤታማነት ዙሪያ ያስጠናውን ጥናት ለአዳማ ከተማ አስተዳደር አስረክቧል።

የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ የታገዘ ለማድረግ እየተሰራ ነው ያሉት የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሃይሉ ጀልዴ ለአብነትም በ175 ሄክታር መሬት ላይ ተግባራዊ የሚሆን የስማርት አዳማ ፕሮጄክት ተቀርጾ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም፣ በገቢዎች፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ ንግድና ገበያ ልማትን ጨምሮ የህብረተሰቡን የዕለት ተዕለት አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት አገልግሎታቸውን ወደ ዲጂታል እየቀየሩ መሆኑን ነው ያነሱት።

በቀጣይም በከተማዋ የሚሰጡ አገልግሎቶችን 80 በመቶ የሚሆነውን ከወረቀት ምልልስና ከሰው ንክኪ ነፃ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ከንቲባው ጠቁመዋል።

የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ፕረዚዳንት ዶክተር ገረመው ሁሉቃ በስማርት አዳማ ፕሮጄክት አተገባበርና ቀጣይ ትኩረት ላይ ባለፉት 10 ወራት ጥናቱን ማካሄዱን ገልጸው ጥናቱ ለከተማዋ ህብረተሰብ የዕለት ተዕለት አገልግሎት የሚሰጡ 13 ተቋማትን ተደራሽ ያደረገ መሆኑን አንስተዋል።

አስተዳደሩ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር ስማርት አዳማ ፕሮጄክትን ውጤታማ ለማድረግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነትም የተፈራረመ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው አርክቴክቸሮችና መሃንዲሶችን ያካተተ ቡድን በማደራጀት ወደ ስራ ማስገባቱን ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ለሚ ጉታ ገልጸዋል። (ENA)

t.me/tikvahethmagazine

29k 0 13 12 152

የናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በአዲስ አበባ ከተማ ሁለት ማከፋፈያ መጋዘኖችን ከፈተ።

የናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በአዲስ አበባ የሚታየውን የሲሚንቶ ገበያ ለማረጋጋት በለቡ መብራትና ጎሮ አከባቢ ሁለት የሲሚንቶ ማከፋፈያ መጋዘኖችን መክፈቱን ገልጿል። በእነዚህ ጣቢያዎች ለተጠቃሚው የሚቀርበው ሲሚንቶ በኩንታል 1320 ብር መሆኑም ተገልጿል።

ማንኛውም ሰው የግንባታ ፍቃዱን በማሳየት እስከ 35 ኩንታል ድረስ መግዛት የሚችል ሲሆን ከዚህ ቀደም ደርባ፣ ሀበሻ እና ዳንጎቴ የራሳቸውን ዴፖ በመክፍት አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

t.me/tikvahethmagazine

29k 0 58 7 75
19 last posts shown.