TIKVAH-MAGAZINE


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
#ኢትዮጵያ
ያግኙን +251913134524

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


በAI ዘርፍ ተስፋ እና ስጋትን ይበልጥ ያጫረው Veo 3 . . . ዝግጁ ነን ?

ግዙፉ የአለማችን የቴክኖሎጂ ኩባንያ ጎግል Veo 3 የተሰኘ ቪዲዮ የሚሰራ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ከሰሞኑ ከለቀቀ በኋላ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።

የቴክኖሎጂ ኩባንያው አዲስ ያስተዋወቀው Veo-3 በራሱ ቪዲዮ ሰርቶ ድምፅን ከቪዲዮው ጋር የሚያዋህድ ሲሆን ከዚህ በፊት ከነበሩት በጥራት ከፍ ያለ ነው።

መተግበሪያው ከOPEN AI ምርት ከሆነው sora ለየት የሚያደርገው በሰዎች መካከል የሚደረጉትን ንግግሮች እውነት እስኪመስል ድረስ ድምፅና ምስልን በማቀናበር ማቅረቡ ነው።

ይህ የጎግል አዲሱ ቴክኖሎጂ የተሰሩ ቪዲዮዎች ( ከላይ እንዳለው አይነት) ከእውነተኛ ቪዲዮች ለመለየት በሚያዳግት ደረጃ የቀረቡ ሲሆን የቋንቋ አማራጩም ከዚህ ቀደም ከነበሩት እጅጉን የሚሻል ነው።

አሁን ላይ መተግበሪያውን ለመጠቀም የ249.9 ዶላር ወርሃዊ ክፍያ ያስፈልጋል ተብሏል።

በርካታ በVeo 3 የተሰሩ ቪዲዮዎች ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲለቀቁ አብዛኛው ሰው ከእውነተኛ ቪዲዮዎች ለመለየት ሲቸገር ተስተውሏል።

ቴክኖሎጂው ይፋ በሆነ በጥቂት ቀናት በአማርኛ ቋንቋ ተሰርተው የተለቀቁ ቪዲዮዎችን እንኳን ብንመለከት በቀላሉ ለመለየት አስቸጋሪ ሆኗል። ከዚህ ቀደም ድምጽ ላይ የነበሩ ክፍተቶች በአጭር ጊዜ ተሻሽለው ቀርበዋል። (ቪዲዮ ከላይ ተያይዟል)

ጎግል በተጨማሪ Flow የተሰኘ የተለያዩ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መተግበሪያዎችን ያካተተ እና ፊልም ሰሪዎች በፈለጉት መንገድ ፊልማቸውን እንዲሰሩ የሚያግዝ የፊልም መስሪያ መተግበሪያንም ይፋ ሲያደርግ በዘርፉ ስጋትንም ተስፋንም ይዞ መምጣቱ ተነግሯል።

ተጠቃሚዎች በVeo 3 መስራት የሚፈልጉትን ነገር በፅሁፍ እንደሚያስገቡ የተነገረ ሲሆን መተግበሪያው ከተሰጠው ፅሁፍ በመነሳት እውነተኛ የሚመስል ቪዲዮን ከሰራ በኋላ ትክክለኛ የሚመስሉ ድምፆችን በመጨመር ለተጠቃሚዎች ያቀርባል።

ተጠቃሚዎች የቀረበላቸውን ቪዲዮ ካዩ በኋላ FLOW የተሰኘውን ሌላ የጎግል መተግበሪያ በመጠቀም የካሜራ አንግል እና የገፀ ባህሪያትን እንቅስቃሴ መቀየር ይችላሉ ተብሏል።

ወጪን ከመቀነስ አንፃር በ500 ሺህ ዶላር ሊሰራ የሚችልን የመድሃኒት ማስታወቂያ በVEO 3 ከ500 ዶላር ባነሰ ገንዘብ በአንድ ቀን ውስጥ መሰራቱም ተነግሯል።

አንዳንድ ሰዎች ፈጠራን ይቀንሳል የሚል ሃሳባቸውን እያንፀባረቁ ሲገኙ የተመልካቹ እውነተኛ ቪዲዮ አለመሆናቸውን ለመለየት መቸገር ሌላ ፈተና ነው ተብሏል።

እናንተስ በዚህ ጉዳይ ምን ትላላችሁ ? ለዚህ ቴክኖሎጂ ዝግጁ ነን ?

Source: CNBC, AXIOS

Video Credit : Ehud Ai Studio

#AI #Google #Gemini

@TikvahethMagazine

14.1k 0 107 7 134

ኬንያ የሶማሊላንድን ቢሮ ከዝርዝሯ አስወጥታለች።

ሶማሊላንድ ባለፈው ሃሙስ በኬንያ፤ ናይሮቢ ከተማ በፕሬዚዳንቷ አማካኝነት የተልዕኮ ቢሮዋን መክፈቷ ይታወሳል።

በኬንያ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት መረጃ ላይም በሃገሪቱ ያሉ ኤምባሲዎች እና የዲፕሎማቲክ ተልዕኮዎች ውስጥ የሶማሊላንድ ስም ሰፍሮ የነበረ ቢሆንም እንዲነሳ መደረጉ ተዘግቧል።

ቢሮው በተከፈተ ዕለትም የኬንያ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ቢሮው መከፈቱን ኬንያ እንደማታውቅ በመግለፅ ዳግም ለሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ያለውን አጋርነት የገለፀበትን መግለጫ አውጥቷል።

የሶማሊላንዱ ፕሬዚዳንት አብድራህማን ኢሮ ከኬንያው አቻቸው ዊሊያም ሩቶ ጋር በጋራ ትብብር እና በቀጣናው ደህንነት ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀው በኬንያ መንግስት እና ህዝብ ለተደረገላቸው ግብዣም አመስግነዋል።

ኬንያ ፕሬዚዳንቱ ለጉብኝት ከመምጣታቸው በፊት ከሶማሊላንድ ጋር የምታደርገው ግንኙነት በሶማሊያ ፌደራል መንግስት ፈቃድ ላይ የተመሰረተ እንደሚሆን መግለጿ ይታወሳል።

Source: Garowe Online

@TikvahethMagazine


"የገቢ ግብር ቢቀንስ አሰሪዎችም በነጻነት ሰራተኛ እንዲቀጥሩ ያበረታታል ይህም የስራ እድል ፈጠራን ያሳድጋል" -አቶ መርዕድ ፍቅረዮሃንስ

በኢትዮጵያ ሰራተኞች በተደጋጋሚ የሚነሱት ጥያቄዎች ዋነኛው የገቢ ግብር ጉዳይ ነው። የገቢ ግብር በሰራተኛው ላይ ብቻ ሳይሆን በቀጣሪ ድርጅቶች ላይም ከፍተኛ ጫና የሚያደርስ እንደሆነ ባለሞያዎች ይናገራሉ።

መንግስት በአንፃሩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና በሰራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ጭምር በተደጋጋሚ የተጠየቀው የተቀጣሪ ሰራተኛ ገቢ ግብር ቅነሳ ላይ ይኼ ነው የሚባል ምላሽ እስካሁን አልሰጠም።

በዚሁ ጉዳይ ሸገር ኤፍ ኤም የጠየቃቸው የፋይናንስ እና ኢንቨስትመንት ባለሙያው አቶ መርዕድ ፍቅረዮሃንስ የገቢ ግብሩ እርከን ቢስተካከል የሰራተኛ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ባይችል እንኳን የተወሰነ አፎይታ እንደሚሰጥ ያነሳሉ።

ባለሞያው በዝርዝር ምን አሉ ?

"መንግስት ለመጠናቀቅ 38 ቀናት በቀረው በጀት ዓመት ወደ 900 ቢሊዮን ብር ከቀረጥ እና ቀጥታ ካልሆነ ታክስ እንዲሁም 50 ቢሊዮን ብር ከመንግስት እና ከግል ተቀጣሪ ሰራተኞች ለመሰብስብ አቅዶ እየሰራ ነው።

50  ቢሊዮን ብሩን መንግስት የሚሰበስበው ከግል እና ከመንግስት የጡረታ ፈንዶች ነው። በአገር አቀፍ በግል እና በመንግስት የተቀጠሩ 4.4 ሚሊየን ሰራተኞች አሉ። 50 ቢሊዮን ብር የሚሰበሰበውም በሀቅ ከሚከፍሉት ከእነዚሁ ሰራተኞች ነው።

የተቀጣሪ ሰራተኛ ገቢ ግብሩ ቢቀነስ ምን ለውጥ ይመጣል?

የገቢ ግብሩ እርከን ቢስተካከል የ4.4 ሚሊዮን ሰራተኛ የኑሮ ሁኔታ ማሻሻል ባይችል እንኳን የተወሰነ አፎይታ ይሰጣቸዋል።

በተጨማሪም አሰሪዎችም በነጻነት ሰራተኛ እንዲቀጥሩ ያበረታታል ይህም የስራ እድል ፈጠራን ያሳድጋል።

መንግስት ግብሩን ቢቀንስ ምንም አያጣም። ሰራተኛው በተዘዋዋሪ መልሶ በአንድም በሌላም መንገድ ለመንግስት ገቢ ማድረጉ አይቀርም።

የጎረቤት አገራትን ተሞክሮ በምሳሌነት ብናነሳ የኢትዮጵያ ሰራተኞች ዝቅተኛ ክፍያ እየተከፈላቸው ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ናቸው።

ለማሳያም ኬንያ [እናንሳ] የሚቆርጡትን ግብር ከማየታችን በፊት የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ማስተካከያ መደረጉን ተከትሎ የኢትዮጵያና የኬኒያ የመገበያያ ገንዘብ ከዶላር አንፃር አቻ መሆናቸው ልብ ማለት ይገባል፡፡

ከግብር አንፃር ስናይ ኬንያ 800 ሺህ ብር ከሚያገኝ ተቀጣሪ ላይ 35 በመቶ ግብር ስትቆርጥ ኢትዮጵያ ከ10 ሺህ 900 ብር ጀምሮ ተመሳሳይ ግብር ትቆርጣለች።

በኢትዮጵያ 600 ብር ከሚያገኝ ጀምሮ የገቢ ግብር ሲቆርጥበት በኬኒያ ግብር የሚቆረጠው 4 ሺህ ብር ከሚያገኝ ደሞዝተኛ ነው።"
ሲሉ አስረድተዋል።

ከሰራተኛው ላይ የገቢ ግብር መቀነስ ለምን እንዳልተቻለ ባለፈው የምክርቤት አባላት የገቢዎች ሚኒስቴርን ጠይቆ ገቢዎች ሚኒስቴር በሰጠው ምላሽ የተሰጠውን ሃላፊነት ማስፈፀም እንጂ ይቀነስ፣ ይጨመር የሚልበት ስልጣን እንደሌለው አስረድቷል።

ሰራተኛው እያነሳ ያለው የገቢ ግብር ቅነሳ ጥያቄ ተገቢ ነው ያሉት አቶ መርዕድ ፍቅረዮሃንስ እንዴት ይቀነስ በሚለው ላይ ግን በስፋት መወያየት እና በጥንቃቄ ማየት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

Credit : Sheger FM 102.1

@TikvahethMagazine


ብዙ ብሔሮች ባሉባት ናይጄሪያ የፕረዚዳንቱ የስልጣን ድልድል ጥያቄ አስነስቷል ... ለምን?

በናይጄሪያ ፖለቲካ ውስጥ አንዱ በጉልህ ከሚነሱት ነገሮች ተመራጩ ፕሬዚዳንት በሃገሪቱ ያሉትን ብዙ ብሔሮችን እና ሃይማኖቶችን ሚዛን ጠብቆ መምራት ነው።

የአሁኑ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ ባለፉት ሁለት አመታት የአፍሪካ ባለ ብዙ ህዝብ ሃገሯን እየመሩ ሲሆን አንዳንዶች ፕሬዚዳንቱ የሚሰጧቸው ሹመቶች ለእሳቸው የዮሩባ ዘር ያደላ ነው ብለው ይከሷቸዋል።

በናይጄሪያ ከ250 በላይ ብሔሮች ያሉ ሲሆን ሃውሳ-ፉላኒ፣ ኢግቦ እና ዮሩባ ሶስቱ ትላልቅ ብሔሮች ናቸው።

ሃገሪቷ ውስጥ የእስልምና እና ክርስትና እምነት ተከታዮች በብዛት ያሉ ሲሆን አሸናፊ ፓርቲዎች የሁለቱን ሃይማኖቶች ሚዛን ለመጠበቅ ሲጥሩም ይታያል።

የፖለቲካ ተንታኞች የአንድ አስተዳደር ቁልፍ ብለው የሚጠሯቸው ቦታዎች የፋይናንስ ቦታዎችን እና የደህንነት ስፍራዎችን ነው።

የወቅቱ የናይጄሪያ ፕሬዚዳንት ቦላ ቲኑቡ የማዕከላዊ ባንክ፣ የነዳጅ ድርጅት፣ የጦር መሪ ፣ የደህንነት መስሪያ ቤቱን ጨምሮ ቁልፍ የሚባሉ 8 ቦታዎችን በራሳቸው የዮሩባ ብሔር ሰዎች እንዲመሩ አድርገዋል።

ከቲኑቡ በፊት በነበሩት የጉድላክ ጆናታን እና መሐመዱ ቡሃሪ ጊዜ እነዚህ 8 ቦታዎች በአንድ የብሔር የበላይነት የተያዙ እንዳልነበረ ተገልጿል።

የፕሬዝዳንቱ ቁልፍ ቦታዎችን በራሳቸው ብሔር ሰዎች መምራት አንዳንድ ምሁራን የሃገሪቱን መፃኢ ስጋት ውስጥ ይከታል እያሉ ይገኛል።

ቀጣዩ ፕሬዚዳንትም ሲመጣ ተመሳሳዩን ነገር ካደረገ ዲሞክራሲን በመሸርሸር አንድነትን ይቀንሳል የሚል ስጋትንም ፈጥሯል።

የፕሬዚዳንቱ ቃለ አቀባይ ግን ፕሬዚዳንቱ የሚሰጧቸው ሹመቶች ሚዛናዊ ናቸው ያሉ ሲሆን በፕሬዚዳንቱ 71 ሰዎች ከሰሜን፤ 63 ሰዎች ከደቡብ ተሹመዋል ብለው የለጠፉትን ፅሑፍም ሰዎች ስህተት ነው ካሉ በኋላ አንስተውታል።

የቲኑቡ ደጋፊዎች ህገመንግስቱ ሹመትን በተመለከተ መብቱን የሰጠው ለፕሬዚዳንቱ ነው ሲሉ ምርጥ 5 ወይም አስሩን እንዲህ አድርግ የሚል ህግ የለም ሲሉ ይከራከራሉ።

የመንግስት ፅህፈት ቤቱ ባወጣው መግለጫም መንግስት ሁሉም ብሔሮች እና ክልሎች በእኩልነት በመንግስት ተቋማት እንዲወከሉ ይሰራል ብሏል።

ሌሎች የፖለቲካ ተንታኞች በአንጻሩ ፕሬዚዳንቱ ሰዎችን ሲሾሙ በችሎታቸው እንጂ የመጡበትን ዘር በማየት መሆን የለበትም የሚልም መከራከሪያ ያነሳሉ።

Source : BBC

@TikvahethMagazine


"ዜጎች በግብርናው ዘርፍ ለመስራት ከመንግስት የሚበደሩትን ብር ወደ ውጪ አገሮች ለመሄጃነት እየተጠቀሙበት ነው" የዘርፉ ባለሞያ

በግብርናው ዘርፍ ለሚሰሩ ወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር የገንዘብ ብድር ቢሰጥም ሰዎች በግብርናው ዘርፍ ከመስራት ይልቅ ወደ ውጪ አገሮች ለመሄጃነት እያዋሉት ስለመሆኑ ተነግሯል።

ይህ የተገለፀው YWCA ኢትዮጵያ በአግሮ ኢኮሎጂ ፖሊሲ እና በወጣቶችን ያማከለ አረንጓዴ የስራ እድል ፈጠራ ላይ ባዘጋጀው ውይይት ወቅት ነው።

በመድረኩ የግብርና ሚኒስቴርን ወክለው የተገኙት በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሴቶች እና ወጣቶች አካቶ ተግባራዊ ስራ ክፍል ውስጥ ከፍተኛ የማህበራዊ ጉዳይ ባለሙያ አቶ አብዱ ጀሊል ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል።

ባለሙያው በግብርና ዘርፍ የስራ እድል የሚፈጠርላቸው ዜጎች በየአመቱ 1.3 ሚሊየን መሆኑን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ አንዳንድ ዜጎች ግን ገንዘቡን ሌላ ነገር እያዋሉት መሆኑን በመስክ ምልከታ መገኘቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።

" መንግስት በ10 አመት 13 ሚሊየን ለሚሆኑ አርሶ አደር ዜጎች የስራ እድል ለመፍጠር ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ አቅዶ እየሰራ ነው" ሲሉም አንስተዋል።

በየአመቱ የስራ እድል ከሚፈጠርላቸው 1.3 ሚሊየን ዜጎች ውስጥ 500 ሺህ የሚሆኑት ሴቶች እና ወጣቶች መሆናቸውንም ነው የገለጹት።

በኢትዮጵያ የሥራ አጥነት ቁጥር እድሜያቸው ከ18-29 የሆናቸው ወጣቶች ሲታይ በ2023 5.6 በመቶ እንደነበር እና አሁን ላይ እየጨመረ መምጣቱን ገልፀዋል።

አሁንም ኢትዮጵያ ከድህነት ወለል በታች ( under poverty ) 20 በመቶ የሚሆኑ ዜጎች አሏት፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ አረጋዊያን እና አካል ጉዳተኞች ናቸው ብለዋል።

በግብርናው ዘርፍ ወጣቱ በበቂ ሁኔታ እንዳይሳተፍ ያደረገው ችግር ወጣቱ የራሱ መሬት አለመኖሩ ነው ሲሉ ባለሞያው ይጠቅሳሉ።

በተጨማሪም " በወጣቶች ላይ በሚስተዋለው በክህሎት ችግር አብዛኛው ወጣት ገንዘብ ተበድሮ ወደ አረብ ሀገር ነው የሚሄደው " ሲሉ ሌላኛውን መልክም ያነሳሉ።

ይህ ደግሞ በግብርናው ዘርፍ ላይ ለመስራት ያላቸው የግንዛቤ እጥረት እና በቂ ስልጠና አለመኖሩ እንደምክንያት እንደሚወሰድ ነው ያስረዱት።

የሥራ እድል ፈጠራው በቂ ነው ተብሎ ባይወሰድም በግብርናው ዘርፍ ወጣቶች እንድሰሩ የሚያስችሉ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ ስለመሆኑ ባለሞያው ጠቁመዋል።

#TikvahEthiopia

@TikvahethMagazine


በምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ ሽብርተኛ ቡድኖች የሚያስፈልጋቸውን ገንዘብ እንዴት ያገኛሉ ?

የምዕራብ አፍሪካ የሚገኙ አደገኛ የሽብር ቡድኖች እራሳቸውን ለማጠናከር የሚያስችላቸውን ገንዘብ ከየት ያገኛሉ በሚል The conversation ሰፊ ሃተታ አውጥቷል።

የምዕራብ አፍሪካ የሳህል ቀጠና ከ1990ዎቹ ጀምሮ በታጠቁ ቡድኖች ቀውስ ውስጥ የገባ አካባቢ ነው።

በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱት ቡድኖች መካከል አንዱ በ2017 በአልጄሪያ እና ማሊ የተመሰረተው እና በ2018 በተመድ የአልቃይዳ ክንፍ በመባል የተሰየመው ጃማህት ኑስራት አል ኢስላም ወል ሙስሊሚኒ( ለእስላም እና ለሙስሊም የድጋፍ ቡድን) ነው።

ቡድኑ በ2024ቱ የGlobal Terrorism Index በአለም ላይ ካሉ አደገኛ የሽብር ቡድኖች ውስጥ አንዱ የተባለ ሲሆን ቡድኑ ዲፕሎማሲ እና ግጭትን አንድ ላይ በመጠቀም ለአካባቢው ፈተና ሆኗል።

ቡድኑ የተከፈቱበትን ወታደራዊ ዘመቻዎች በመቋቋም በአንዳንድ ቦታዎች ኬላዎችን በመቆጣጠር ታክስ ያስከፍላል።

የThe conversation ፀሐፊዎች የቡድኑ የገቢ ምንጭ የሆኑ ነገሮችን ያጠኑ ሲሆን በዚህም መሰረ በዋነኝነት ቡድኑ፦

- ከማዕድን ማውጣት፣

- ሰዎችን ከማገት፣

- ከብቶችን በመዝረፍ እና

- በገንዘብ ማጭበርበር ተግባራት ገቢ እንደሚያገኝ አመላክተዋል።

በጥናቱ የወርቅ ማውጣት እና ሽያጭ ለቡደኑ መጠናከር ወሳኝ ሚና አለው ሲባል ቡድኑ ተፅዕኖውን ባሳደረባቸው አካባቢዎች ከወርቅ በአመት ከ30 ቢሊየን ዶላር በላይ ገቢ እንደሚመነጭ ተገልጿል። የእነዚህ ወርቆች መዳረሻም የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ቱርክ እና ስዊዘርላንድ ናቸው።

ቡድኑ የወርቅ ማውጫ ቦታዎቸን ከመያዝ አልፎ ወደ ቦታው የሚወስዱ መንገዶችን የተቆጣጠር ሲሆን ወደ ቦታው ከሚሄዱ ሰዎች ክፍያም ይቀበላል። ቡድኑ ከያዘው የወርቅ ማውጫ በአመት 725 ኪሎ ግራም ወርቅ ወይም ከ34 ሚሊየን ዶላር በላይ ገንዘብ ይገኛል ተብሎ ይገመታል።

ሌላኛው የቡድኑ የገቢ ምንጭ ሰዎችን በማገት ለመልቀቅ ገንዘብ መጠየቅ ሲሆን በ2020 1 ፈረንሳዊ እና ሁለት ጣልያናውያንን ለመልቀቅ 30 ሚሊየን ዩሮ ተቀብሏል።

ቡድኑ ከ2017-2023 በቡርኪናፋሶ ፣ ማሊ እና ኒጀር ከተፈፀሙ 1100 እገታዎች በ845ቱ የተሳተፈ ሲሆን ለመልቀቅ ከፍተኛ ገንዘብ ይጠይቃል።

ቡድኑ የእሱን አስተሳሰብ ከማይቀበሉ ሰዎች ከብቶችን በመዝረፍ ወደ ማሊ ፣ ሞሪታኒያ እና ሴኔጋል በመውሰድም ይሸጣል።

በተጨማሪ ቡድኑ ለሰዎች ገንዘብ በማበደር፣ በባንኮች ኢንቨስት በማድረግ እና በሌሎችም መንገዶችም ያልተቋረጠ ትርፍ በማግኘት እራሱን አጠናክሯል።

ከዚህ ሁሉ ለመውጣት የቡድኑ የገቢ ምንጭ የሆኑትን የወርቅ ማውጫ ቦታዎችን መቆጣጠር፣ ቡድኑ ገንዘብ የሚሰጣቸውን ነጋዴዎች በመቆጣጠር የገቢ ምንጩን ማዳከም እና ወታደራዊ አቅምን ማሳደግ በአማራጭነት ተቀምጠዋል።

@TikvahethMagazine


አዲስ ብሎክ ለሽያጭ ቀርቧል!

ከተወዳጁ የሂል ሳይድ መንደር ውስጥ ለሽያጭ የመጨረሻ በሆነው የዲያስፓራ ብሎክ ቁጥር 3 ላይ ከስቱድዮ እስከ ባለ አራት መኝታ ከተጨማሪ የሰራተኛ፣ ላውንደሪ ክፍል እና የዕቃ ክፍል ያካተቱ ቤቶች በ 8% ቅድመ ክፍያ ብቻ ያግኙ።

የቤቱን 60% እየኖሩበት ወይም አከራይተውት በ20 አመት ቀስ ብለው መክፈል ይችላሉ።

🏫 ከስቱድዮ እስከ ባለ 4 መኝታ ፦
💎 ባለ 1 መኝታ በ 431 ሺ ብር
💎ባለ 2 መኝታ በ 619 ሺ ብር
💎ባለ 3 መኝታ በ 751 ሺ ብር
💎ባለ 4 መኝታ በ 1,051,626 ብር
ቅድመ ክፍያ ጀምሮ

🛍️🛒 ሱቆች ከ 20 ካሬ ጀምሮ ይምጡ የግሎ ያድርጉ። ባሉት ውስን ቀናቶች ለሚመጡ ደንበኞች እስከ 2 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ታላቅ ቅናሽ አቅርበን እየጠበቅኖት ነው።

ይደውሉልን ☎️0900025097
የዘመናዊ መንደራችን አካል ይሁኑ!

#telegram (@SamuelDMCRealtor)
#whatsapp


#Nigeria

በናይጄሪያ በጣለው ከባድ ዝናብ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ117 ሰዎች ህይወት አልፏል።

በማዕከላዊ ናይጄሪያ በተከሰተው የጎርፍ አደጋ የ117 ሰዎች አስክሬን ሲገኝ የሟቾች ቁጥር ከዚህም ሊያሻቅብ እንደሚችል የአካባቢው አመራሮች ተናግረዋል።

በጎርፍ አደጋው በርከት ያሉ ቤቶች የወደሙ ሲሆን በአካባቢው ያለ የውሃ ግድብ መፍረሱ ሁኔታውን እንዳባባሰው ተነግሯል።

በተደጋጋሚ በጎርፍ አደጋ ዜጓቿን በምታጣው ናይጄሪያ ብሔራዊ የሜትሮዎሎጂ ተቋሟ ካሏት 36 ግዛቶች በ15ቱ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቅቋል።

ባለፈው አመት ከ36ቱ ግዛቶች ውስጥ በ31 ግዛቶች በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከ1200 በላይ ሰዎች ሲሞቱ ከ1.2 ሚሊየን በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው ይታወሳል።

Source: Al Jazeera, Reuters

@TikvahethMagazine


#SchengenVisa

የሸንገን ቪዛ ጥያቄያቸው ውድቅ የሆነባቸው አፍሪካውያን ከ67.5 ሚሊየን ዶላር በላይ አውጥተዋል።

ኢትዮጵያ በ36.1 በመቶ  የቀረቡ የቪዛ ጥያቄዎች ውድቅ ሆነውባት 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።

አፍሪካውያን መንገዶች ወደ 29 የአውሮፓ ሃገራት  ለመግባት የሚያስችለውን የሸንገን ቪዛ ለማግኘት እንደተቸገሩ መሆኑ ተገልጿል።

ወደ አውሮፓ ለጉብኝት፣ ለትምህርት እና ስብሰባ ለማምራት የሚፈልጉ አፍሪካውያን የሸንገን ቪዛ ጥያቄያቸው ውድቅ የመደረጉ ንፃሬ ከፍተኛ መሆኑ ነው የተነገረው።

29ኙ የሸንገን ዞን የአውሮፓ ሃገራት በዚህ አመት ብቻ ከ11.7 ሚሊየን በላይ የቪዛ ጥያቄዎች የቀረቡላቸው ሲሆን  እያንዳንዱ የሸንገን ቪዛ ጥያቄ 100 ዶላር ያስከፍላልም ነበር ተብሏል።

ይህ ክፍያ የቪዛው ጥያቄ ተቀባይነት ባያገኝም የማይመለስ ሲሆን በዚህ መንገድ ብቻ ጥያቄያቸው ተቀባይነት ያላገኙ አፍሪካውያን ከ67.5 ሚሊየን ዶላር በላይ ገንዘብ አውጥተዋል ተብሏል።

ከአፍሪካ ሃገራት ኮሞሮስ የቪዛ ጥያቄዋ ውድቅ በመደረግ መሪ ስትሆን 62.8 በመቶ ጥያቄዎች ውድቅ ይደረጋሉ ተብሏል።

ጊኒ ቢሳው እና ናይጄሪያ ተከታዩን ስፍራ ሲይዙ ኢትዮጵያ በ36.1 በመቶ ውድቅ የመደረግ ንፃሬ 10ኛ ላይ ተቀምጣለች።

ቪዛውን ለማግኘት የጉዞ ምክንያት፣ የገንዘብ አቅም እና ወደ ሃገር የመመለስ ፍላጎት የሚታይ ነው ቢባልም አብዛኞቹ ሰዎች የተባለውን በሙሉ ቢያሟሉም ቪዛውን እንዳላገኙ በመግለፅ መድሎ እንዳለ ተናግረዋል።

Source: Africa News, Business Insider Africa

@TikvahethMagazine


የቱሪስት ፍሰት ጨምሯል ቢባልም የባህላዊ ምግብ ቤቶች ድባብ ግን ተቀዛቅዟል ... ለምን?

በአዲስ አበባ የቱሪስቶች ቁጥር ስለመጨመሩ በተደጋጋሚ ቢነገርም ለወትሮ በሰዎች የሚሞሉት የባህላዊ ምግብ ቤቶች በደንበኞች ቁጥር ማነስ ከፍተኛ ፈተናዎች እያጋጠሟቸው እንደሆኑ አዲስ ፎርቹን ያነጋገራቸው የዘርፉ ተዋናዮች ይናገራሉ።

የዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤት የምግብ እና መጠጥ ማናጀር የሆኑት ዳንኤል ፍቃዱ ለፎርቹን እንደገለጹት በ2022 በቀን 1000 ሰዎችን እንደሚያስተናግዱ እንደነበር፤ ይህ ቁጥር ግን በ2023 ወደ 500፤ በ2024 ደግሞ ወደ 250 መቀነሱን ያስረዳሉ።

በደንበኞቹ ቁጥር መቀነስም ምግብ ቤቱ የሥራ ሰዓቱን መቀነሱን ገልጸዋል።

የምግብ ቤቱ እህት ኩባንያ የሆነው የዮድ አቢሲኒያ ቱር እና ትራቭል ማናጀር የሆኑት ሶስና ገብረማርያም በበኩላቸው የፍላጎት ለውጥ በመኖሩ አሁን ላይ አብዛኛው ሥራው ከኢትዮጵያ ውጪ በተለይ ወደ እየሩሳሌም ለጉብኝት ለሚያመሩ ሰዎች አገልግሎት ወደ መስጠት መዞሩን ገልጸዋል።

ሌሌኛው በሚዲያው ቃለ-መጠይቅ የሰጠው የጳጉሜን ቱር እና ትራቭል ድርጅት ከዚህ በፊት በዓመት 20 ሰዎችን የያዘ 20 ቡድን በአመት እንደሚያስተናግድ በመግለፅ እነዚህ ቱሪስቶች በአማካይ ለ8 ቀናት እንደሚቆዩና ከፍተኛ የውጪ ምንዛሬ ይገኝ እንደነበር አንስቷል።

አሁን ላይ ግን ዘርፉ በመቀዛቀዙ ስራውን ላለማቋረጥ በመኪና ኪራይና ሌሎች ዘርፎች ላይ መሰማራቱን ገልጿል።

ሌላኛው በዘርፉ የተሰማራው በካፒታል ሆቴል ስር ያለው የካፒታል ባህላዊ ሬስቶራንት ድሮ በቀን ከ150-230 እንግዶችን እንደሚያስተናግድ ገልፆ አሁን በጣም ጥሩ ሆነ ከተባለ ከ20-30 ሰዎችን እንደሚያስተናግድ ገልጿል።

ኢትዮጵያ በርካታ ዓለም አቀፍ ኮንፍረንሶችን እያስተናገደች ሲሆን ብዛት ያላቸው የውጭ ሀገራት ጎብኚዎችም በእነዚህ ስብሰባዎች ለመታደም መጥተዋል።

ለስብሰባ የሚመጡ ጎብኚዎች ደግሞ ከባህላዊ ምግብ ቤቶች በላይ ሆቴሎችን የሚመርጡ በመሆናቸው ይህ ለባህላዊ ምግብ ቤቶች ፈተና እንደሆነባቸው ተጠቅሷል።

አሁንም ቢሆን ግን በቱሪዝም ዘርፉ የመረጃ ምዝገባ ላይ ችግሮች መኖራቸው ይታመናል። ይህንንም ለመቅረፍም በቅርቡ የቱሪስት ሳተላይት አካውንት ስርዓት ይተገበራል ተብሏል።

Source: Addis Fortune

@TikvahethMagazine

22.1k 0 15 16 100

#SouthAfrica

"ከደቡብ አፍሪካ ቤተሰቦች ሩብ ያህሉ የሚሆኑት የሚበሉት በቂ ምግብ የላቸውም"

"ብዙ አባወራዎች የውሃ እና ኤሌክትሪክ እንዲኖራቸው ማድረግ ተችሏል" - የሀገሪቱ ስታስቲክስ ቢሮ

የሀገሪቱ ስታስቲክስ ቢሮ ባወጣው ሪፖርት በደቡብ አፍሪካ ከሚኖሩ 63 ሚሊየን ሰዎች ውስጥ 14 ሚሊየኑ ባለፈው አመት የሚበሉት በቂ ምግብ አልነበራቸውም ሲል ገልጿል።

ከ22.2 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝቧ በቂ ምግብ አያገኙም ሲባል ከመንግስት ድጋፍ የሚጠብቁ ሰዎች ቁጥርም በ2003 ከነበረበት 12.8 በመቶ ወደ 40.1 በመቶ መጨመሩ ተዘግቧል።

በደቡብ አፍሪካ 42.2 በመቶ ያህሉ ቤተሰቦች በሴቶች ራስነት የሚመሩ መሆናቸውን የሀገሪቱ  ስታስቲክስ ቢሮ ሪፖርት ያመለክታል። ይህ ደግሞ በገጠራማ አካባቢዎች ቁጥሩ እስከ 47 በመቶ ይደርሳል።

18 በመቶ የሚሆኑ የደቡብ አፍሪካ ህፃናት ከወላጅ ቤተሰቦቻቸው ጋር እንደማይኖሩ ሪፖርቱ አክሎ ገልጿል። በተጨማሪም 11 በመቶ የሚሆኑት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ህጻናት ወላጅ አልባ መሆናቸውም ተጠቅሷል።

በአንጻሩ፦

በጥናቱ እንደተጠቀሰው መደበኛ መኖሪያ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች ቁጥር በ2002 ከነበረው 73.5 በመቶ በ2024 ወደ 84.1 በመቶ ከፍ ብሏል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ 60.1 በመቶ የሚሆኑት የሚኖሩበት ቤት የራሳቸው ሲሆን 25.1 በመቶ ደግሞ ተከራይተው የሚኖሩ ናቸው።

የንጹህ መጨጥ ውኃ ተጠቃሚዎች ቁጥር 87.7 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን ውሃ በቤታቸው የሚያገኙ (ቧንቧ ያላቸው) ቁጥር ደግሞ ወደ 46.4 በመቶ ከፍ ብሏል።

የተሻሻለ የንፅህና አጠባበቅ አጠቃቀም ያላቸው መጸዳጃ ቤቶች ወይም የጉድጓድ መጸዳጃ ቤቶች ሆነው በቂ አየር ማናፈሻ ቱቦዎች ያላቸው መጻዳጃ ቤቶች በ 2002 ከነበረበት 61.7% በ 2024 ወደ 83.1% አድጓል።

ከ1% ያነሱ አባወራዎች በጊዜው ምንም አይነት ሽንት ቤት አልነበራቸውም። በተጨማሪም 46.2% የመፀዳጃ ቤቶች የሚገኙት በመኖሪያ ቤት ውስጥ ሲሆን 49.9% በጓሮ ወይም ከቤት አቅራቢያ የሚገኙ ናቸው።

የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን በተመለከተ 2002 ከነበረው 76.7 በመቶ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተደራሽነት ወደ 90.2 በመቶ ከፍ ብሏል።

ቢያንስ አንድ የሞባይል ስልክ የሚኖርበት መኖሪያ ቤቶች ቁጥር ወደ 96.1 ከፍ ሲል፤ የኢንተርኔት አገልግሎት ማንኛውም መንገድ የሚያገኙ መኖሪያ ቤቶች ቁጥር ደግሞ ወደ  82.1 በመቶ ከፍ ብሏል።

በደቡብ አፍሪካ የሬዲዮ ተጠቃሚዎች በ2002 ከነበረበት 79 በመቶ ወደ 31 በመቶ ሲቀንስ የቴሌቪዥን ተጠቃሚዎች በእጅጉ ጨምረዋል።

ይህ የሀገሪቱ ስታስቲክስ ቢሮ ያወጣው መረጃ ነው።

@TikvahethMagazine


#ጥቆማ

የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት የAI Summer Camp አዘጋጅቷል።

በሰመር ካምፑ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ላይ ፍላጎት ያላቸው ከ1-12ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች መሳተፍ ይችላሉ ተብሏል።

የሰመር ካምፑ ከሐምሌ 1 ጀምሮ ለሁለት ወራት የሚሰጥ ሲሆን ከግንቦት 21 ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት መመዝገብ ይቻላል።

ለመመዝገብ https://forms.gle/yFThcRq3bSMcFEKU6

መረጃ ለማግኘትና እገዛ ለማግኘት eaiisummercamp@gmail.com ይጠቀሙ።

@TikvahethMagazine


#EthiopiaAirlines 🛫

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለናይጄሪያውያን መንገደኞች ተጨማሪ ጭነት ፈቀደ።

አየር መንገዱ ከሌጎስ የሚያደርገውን በረራ ከሰኔ 24 ጀምሮ ሳምንታዊ በረራውን ወደ 14 ከፍ ይላል ብሏል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለናይጄሪያውያን መንገደኞች ተጨማሪ ጭነት መያዝ እንዲችሉ መፍቀዱን እንዲሁም የደብል ማይልስ ሽልማት ማዘጋጀቱን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ ከሌጎስ ተጨማሪ 7 በረራዎችን ማድረግ የጀመረ ሲሆን ለተሳፋሪዎቹ ተጨማሪ ጭነት እንዲጭኑ ማስቻሉንና በአየር መንገዱ ሲበሩ የደብል ማይልስ ሽልማት ማዘጋጀቱን የአካባቢው የአየር መንገዱ ኃላፊ ፍሬህይወት መኮንን ገልፃለች።

ተጨማሪ ጭነት የተፈቀደላቸው ተሳፋሪዎች ወደ ሙምባይ፣ ዴሊህ፣ ሃይደርባድ፣ ማድራስ እና ዱባይ የሚበሩ መንገደኞች ናቸው።

ኃላፊዋ ፍሬህይወት መኮንን "እነዚህ ተጨማሪ ጥቅሞች የተዘጋጁት ታማኝ ደንበኞችን ለማበረታት" ነው ሲሉ የተጨመሩ አዳዲስ በረራዎች የመንገደኞችን ወጪ በመቀነስ የአየር መንገዱን የአገልግሎት አሰጣጥ እንደሚያሻሽል አንስተዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ናይጄሪያ ከ1960 ጀምሮ መብረር የጀመረ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የሌጎስ ከተማን ከ140 አለም አቀፍ መዳረሻዎች ጋር ያስተሳስራል።

Source: Afritraveller

@TikvahethMagazine


አዲስ ብሎክ ለሽያጭ ቀርቧል!

ከተወዳጁ የሂል ሳይድ መንደር ውስጥ ለሽያጭ የመጨረሻ በሆነው የዲያስፓራ ብሎክ ቁጥር 3 ላይ ከስቱድዮ እስከ ባለ አራት መኝታ ከተጨማሪ የሰራተኛ፣ ላውንደሪ ክፍል እና የዕቃ ክፍል ያካተቱ ቤቶች በ 8% ቅድመ ክፍያ ብቻ ያግኙ።

የቤቱን 60% እየኖሩበት ወይም አከራይተውት በ20 አመት ቀስ ብለው መክፈል ይችላሉ።

🏫 ከስቱድዮ እስከ ባለ 4 መኝታ ፦
💎 ባለ 1 መኝታ በ 431 ሺ ብር
💎ባለ 2 መኝታ በ 619 ሺ ብር
💎ባለ 3 መኝታ በ 751 ሺ ብር
💎ባለ 4 መኝታ በ 1,051,626 ብር
ቅድመ ክፍያ ጀምሮ

🛍️🛒 ሱቆች ከ 20 ካሬ ጀምሮ ይምጡ የግሎ ያድርጉ። ባሉት ውስን ቀናቶች ለሚመጡ ደንበኞች እስከ 2 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ታላቅ ቅናሽ አቅርበን እየጠበቅኖት ነው።

ይደውሉልን ☎️0900025097
የዘመናዊ መንደራችን አካል ይሁኑ!

#telegram (@SamuelDMCRealtor)
#whatsapp


የእንግሊዝ ዶክተሮች የ4% የክፍያ ጭማሪ ቢያገኙም አነሰ በሚል ለተቃውሞ ድምፅ እያሰባሰቡ ነው።

ባለፈው ሳምንት እንግሊዝ ለአስተማሪዎች እና ዶክተሮች ጭማሪ መደረጉን ብትገልፅም የብሪትሽ የሃኪሞች ማህበር በቂ ባለመሆኑ ሃኪሞች እንዲያምፁ እየጠየቀ ነው።

ማህበሩ የክፍያ ጭማሪው በቂ ባለመሆኑ የተነሳ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ ለመወሰን እንዲያስችል እስከ መጪው ሐምሌ 7 ድምፅ ይስጡ ብሏል።

በአዲሱ ጭማሪ መሰረት ለሪዝደንት ሃኪሞች 750 ፓውንድ ክፍያ ሲጨመርላቸው የሃኪሞቹ ማህበር ግን ትክክለኛ ገቢያችን ከ2008 ጀምሮ በ23 በመቶ በመቀነሱ የተደረገው ጭማሪ በቂ አይደለም ብሏል።

ማህበሩ ሃኪሞች በአድማው ላይ የይሁንታ ድምፅ ይስጡ ሲል መንግስት ክፍያዎችን ማስተካከል ያለበት ዛሬ ነው ብሏል።

በእንግሊዝ የሬዚደንት ሃኪም ከደሞዙ በተጨማሪ 37 በመቶ የክፍያ ጭማሪ ለምሽት ስራዎች እና ሌሎችም ጥቅማጥቅሞችን ያገኛል።

በፋውንዴሽን ትሬኒንግ(F1) ያሉ ዶክተሮች መሰረታዊ የሚባል ከ36,616 እስከ 42,008 ፓውንድ በአመት ሲያገኙ የስፔሻሊስት ስልጠና የጀመሩ ደግሞ ከ49,909 እክከ 70,425 ፓውንድ ያገኛሉ።

የስፔሻሊቲ ዶክተር ከ59,175 ፓውንድ እስከ 95,400 ፓውንድ ሲያገኝ ሃኪሞቹ የስራ ጫናችን ባልቀነሰበት ሁኔታ ትክክለኛው ገቢያችን መቀነሱ አሳስቦናል ብለዋል።

በ2023 እና 2024 ዶክተሮቹ ተመሳሳይ ውሳኔ ውስጥ ገብተው የነበረ ቢሆንም በሁለት አመታት ውስጥ ክፍያቸው በ22 በመቶ ይጨምራል ከተባለ በኋላ ውሳኔያቸውን ቀልብሰው ነበር።

በአዲሱ ማሻሻያ የአንድ የሙሉ ሬዚደንት ዶክተር ክፍያ ከ38,800 ፓውንድ የሚጀምር ሲሆን ከ2023 አንፃር የ9500 ፓውንድ ጭማሪ አለው።

ማህበሩ ዶክተሮቹ በቂ ክፍያ ካልተከፈላቸው ከሃገር ወጥተው ይሰራሉ ያለ ሲሆን በ2023 ከ4000 በላይ ዶክተሮች ከሃገር ወጥተው ለመስራት ወስነዋል ወይም ደግሞ ስራቸውን አቋርጠዋል ብሏል።

Source: BBC , Yahoo news

@TikvahethMagazine

51.3k 0 116 26 305

በኢትዮጵያ ከጥር እስከ ሚያዚያ ወር (2025) ድረስ ባለው ፦

ከ1.9 ሚሊየን በላይ ዜጎች በወባ ተጠቅተው፤ የ77 ሰዎች ህይወት አልፏል።

4056 ሰዎች በኮሌራ በሽታ ተይዘው፤ የ42 ሰዎች ህይወት አልፏል።

3908 የኩፍኝ በሽታ ተጠቅተው፤ የ22 ሰዎች ህይወት አልፏል።

በኢትዮጵያ ከጥር እስከ ሚያዚያ ወር ድረስ ከ1.9 ሚሊየን በላይ የወባ በሽታ ተጠቂዎች መገኘታቸውን እና 77 ሰዎች እንደሞቱ የዓለም ጤና ድርጅት ሪፖርት አመላክቷል።

ዓለም ጤና ድርጅት የኢትዮጵያ የጤና ክላስተር የሚያዚያ 2025 ሪፖርት መሰረት ከጥር እስከ ሚያዚያ ባለው ጊዜ 1,978,505 የወባ በሽታ ተጠቂዎች ሲመዘገቡ 77 ያህሉ ህይወታቸው ማለፉን ይጠቅሳል።

በመላ ሀገሪቱም 1147 ወረዳዎች ቢያንስ በወባ በሽታ የተያዘ አንድ ሰው ሪፖርት ማድረጋቸው ተመላክቷል።

ከጥር ወር ጀምሮ በኦሮሚያ ምዕራብ ወለጋ ዞን ከ168 ሺህ በላይ የወባ ተጠቂዎች የተመዘገቡ ሲሆን ይህም ከፍተኛው ነው። ጅማ፣ ምስራቅ ወለጋ እና አዊ ዞኖች ተከታዩን ከፍተኛ የወባ ተጠቂ ያስመዘገቡ ናቸው።

በክልል ደረጃ የኦሮሚያ ክልል ከ700 ሺህ በላይ፤ አማራ ክልል ደግሞ ከ400 ሺህ በላይ ተጠቂዎችን በማስመዝገብ ከፍተኛውን ቁጥር ይዘዋል።

ኮሌራን በተመለከተ ሪፐፖርቱ ምን አለ ?

ከጥር እስከ ሚያዚያ 2025 ባሉት ጊዜያት ከሁለት ክልሎች 4056 ሰዎች በኮሌራ በሽታ መያዛቸውን እና 42 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።

በክልል ደረጃ የጋምቤላ እና የአማራ ክልል ከፍተኛውን የኮሌራ ተጠቂ ያስመዘገቡ ሲሆን በጋምቤላ 2016 ሰዎች ተይዘው 32ቱ ሲሞቱ በአማራ 2040 ሰዎች ተይዘው 10 ሰዎች እንደሞቱ ተገልጿል።

የኮሌራ በሽታ አሁንም በሁለቱ ክልሎች በሚገኙ 32 ወረዳዎች እንዳለ ሲዘገብ ከዚህ ውስጥ 27ቱ በአማራ ክልል ይገኛል።

በአማራ ክልል በሽታው ካለባቸው ወረዳዎች ውስጥ 89.9 በመቶ ያህሉ ከአራት ወረዳዎች ብቻ ሪፖርት የተደረገ ነው።

ሪፖርቱ ኩፍኝን በተመለከተ ምን አለ ?

ከጥር እስከ ሚያዚያ 2025 ባለው ጊዜ 3908 የኩፍኝ በሽታ ተጠቂዎች ሲገኙ 22ቱ መሞታቸው በሪፖርቱ ተገልጿል።

የኩፍኝ በሽታ 7 ክልሎችን ጨምሮ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እና በአጠቃላይ በ25 ወረዳዎች ስለመከሰቱ ተመላክቷል።

#Report

@TikvahethMagazine


"በቀጣዮቹ 3 ዓመታት በAI ላይ 500 ሚሊየን ዶላር ፈሰስ አደርጋለሁ" - ሳፋሪኮም

ሳፋሪኮም በሚቀጥሉት ሶስት አመታት በምስራቅ አፍሪካ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሰረተ ልማቶች ላይ 500 ሚሊየን ዶላር ፈሰስ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ።

ኢንቨስትመንቱ በአካባቢው ምቹ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሥነ-ምህዳርን በመፍጠር የዲጂታል አገልግሎቶችን በማቀላጠፍ ፈጠራን ያበረታታል ተብሏል።

በተጨማሪ ሳፋሪኮም 5000 ሰራተኞችን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዙሪያ ማሰልጠኑን በመግለፅ አካባቢው የራሱን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕቀፍ በመፍጠር በንቃት የሚሳተፍበት ጊዜ ነው ብሏል።

Source: The star

#Safaricom
#AI

@TikvahethMagazine


ቴሌግራም ከኤለን መስክ የ300 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አገኘ።

የቴሌግራሙ መስራች ፓቨል ዱሮቭ ከኤለን መስክ ጋር በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዙሪያ ለመስራት መስማማታቸውን ገልጿል።

በዚህም የቴሌግራም ተጠቃሚዎች በገበያው ላይ ያለውን ምርጡን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ መጠቀም ይጀምራሉ ብሏል።

ዱሮቭ የxAI ቻትቦት የሆነው GROK ከቢሊየን በላይ ለሆኑ ተጠቃሚዎቻችን ለማድረስ ተስማምተናል ብሏል።

በተጨማሪ ከኤለን መስክ የ300 ሚሊየን ዶላር የካሽ ድጋፍ ለቴሌግራም እንደሚኖር እና በቴሌግራም በኩል ከሚሸጡት የxAI ደንበኝነት ግማሽ ያህሉን ቴሌግራም ያገኛል ብሏል።

GROK የተሰኘው አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ከወራት በፊት በኤለን መስክ የተለቀቀ ሲሆን ወደ ቴሌግራም ከመጣ በኋላ አሁን ላይ የቴሌግራም ፕሪሚየም ተጠቃሚዎች ብቻ አገልግሎቱን እያገኙ ይገኛሉ።

በመጪዎቹ ወራት ሁሉም የቴሌግራም ተጠቃሚ አገልግሎቱን እንደሚያገኝ ይጠበቃል።

#Telegram #AI

@Tikvahethmagazine

18 last posts shown.