TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
  • flag English
    Site language
    flag Russian flag English flag Uzbek
  • Sign In
  • Catalog
    Channels and groups catalog Search for channels
    Add a channel/group
  • Ratings
    Rating of channels Rating of groups Posts rating
    Ratings of brands and people
  • Analytics
  • Search by posts
  • Telegram monitoring
TIKVAH-MAGAZINE

13 May, 12:22

Open in Telegram Share Report

ወደ ውጪ መላክ የነበረበት 235 ሺ በላይ ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ እና የቅባት እህል በክምችት መኖሩ ተረጋገጠ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በአራት ከተሞች በክምችት ተይዘው ያሉ የቅባትና ጥራጥሬ ሰብሎች በአይነትና በመጠን ለማጣራት ዳሰሳዊ ጥናት አካሂዷል።

በተደረገው የዳሰሳ ጥናትም፦

- በአዳማ ከተማ 6,610.18 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል፣ 55,485.75 ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ ሰብል፤

- በአቃቂ ቃሊቲ 3,325.95 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል፣2,400.22 የጥራጥሬ ሰብል፤

- በቡራዩ ከተማ 43,569.25 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል ፣116,844.99 ሜትሪክቶን የጥራጥሬ እህል፣

- በገላን 57,274.13 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል 177,514.82 ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ እህል እንዲሁም 502.06 ሜትሪክቶን ሌሎች ምርቶች በድምሩ 235,291.02 ቶን በክምችት መገኘቱ ተገልጿል።

በሚኒስትር መ/ቤቱ የግብርና ምርቶች መሠረት ልማት ቡድን መሪ አቶ ታረቀኝ ሽበሺ ወደፊት የምርቶቹ ዋጋ ይጨምራል በማለት ምርትን በወቅቱ ወደ ውጪ ገበያ ከመላክ ይልቅ በክምችት ይዞ ማቆየት የሀገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙ አካላት ከዚህ ህገ ወጥ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አሳስበው ከዚህ ድርጊታቸው የማይታቀቡ ከሆነ ሚኒስቴር መ/ቤቱ እርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን ሲሉ መግለጻቸውን ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethmagazine

29.3k 0 48 57
Catalog
Channels and groups catalog Search for channels Add a channel/group
Researches
Telegram Research 2019 Telegram Research 2021
Ratings
Rating of Telegram channels Rating of Telegram groups Posts rating Ratings of brands and people
Contacts
Support Email
API
API statistics Search API of posts API Callback
Miscellaneous
Terms and conditions Privacy policy Public offer
Our channels
@TGStat @TGStat_Chat @telepulse
Our bots
@TGStat_Bot @SearcheeBot @TGAlertsBot