#UCL
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መርሐ ግብር ባርሴሎና ባየር ሙኒክን 4ለ1 ፣ ማንችስተር ሲቲ ስፓርታ ፕራግን 5ለ0 እንዲሁም ሊቨርፑል ሌፕዚግን 1ለ0 ማሸነፍ ችለዋል።
የባርሴሎናን የማሸነፊያ ግቦች ራፊንሀ 3x እና ሌዋንዶውስኪ ሲያስቆጥሩ ለባየር ሙኒክ ሀሪ ኬን ከመረብ አሳርፏል።
ኤርሊንግ ሀላንድ 2x ፣ ጆን ስቶንስ ፣ ፊል ፎደን እና ማቲውስ ኑኔስ የማንችስተር ሲቲን ግቦች ያስቆጠሩ ተጨዋቾች ናቸው።
ለሊቨርፑል የማሸነፊያ ግቧን ዳርዊን ኑኔዝ አስቆጥሯል።
ሀሪ ኬን በዘንድሮው የውድድር ዘመን ባደረጋቸው አስራ አንድ ጨዋታዎች አስራ አራት ግቦችን አስቆጥሮ ስድስት አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።
ኤርሊንግ ሀላንድ በአርባ ሁለት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች አርባ አራተኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።
ራፊንሀ ከሮናልዶ ፣ አጉዌሮ እና ሮይ ማካይ በመቀጠል በሻምፒየንስ ሊጉ ባየር ሙኒክ ላይ ሀትሪክ የሰራ አራተኛው ተጨዋች መሆን ችሏል።
ማንችስተር ሲቲ ሀያ ስድስት ተከታታይ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ባለመሸነፍ በማንችስተር ዩናይትድ ተይዞ የነበረውን ሪከርድ መስበር ችለዋል።
በሌሎች ጨዋታዎች
- ኢንተር ሚላን ያንግ ቦይስን 1ለ0
- ሊል አትሌቲኮ ማድሪድን 3ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
*የሻምፒየንስ ሊግ የዛሬ ምሽት ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዡ በምስሉ ላይ ተያይዟል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe