TIKVAH-SPORT


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Sport


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Sport
Statistics
Posts filter


ዋልያዎቹ የፊፋ ደረጃቸው ዝቅ አለ !

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን " ዋልያዎቹ " በፊፋ ወርሀዊ የብሔራዊ ቡድኖች ደረጃ ሰንጠረዥ ከባለፈው ወር በሶስት ደረጃዎች ዝቅ ብለዋል።

ዋልያዎቹ ባለፈው ወር ከነበሩበት 145ኛ ደረጃ በሶስት ደረጃዎች ዝቅ ብለው 148ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በቅርቡ ያደረጋቸውን ሁለት የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች መሸነፉ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከስድስት አመታት በኋላ ዝቅተኛ የተባለው የፊፋ ወርሀዊ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ ተገዷል።

የወቅቱ የአለም ሻምፒዮን አርጀንቲና በፊፋ ወርሀዊ ደረጃ አንደኝነት ደረጃዋን አስጠብቃለች።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


Forward from: WANAW SPORT WEAR
🔔 #ይህን_እናጋራችሁ

🇪🇹 የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ለፊፋው ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ያበረከቱት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያን በተመለከተ መረጃ አለዎት?

🇪🇹 ይህ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያ በዲዛይነሮች ልዩ ውድድር ኢትዮጵያን የሚመጥን እንዲሆን ተደርጎ በዋናው ስፖርት የተመረተ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ማልያ በሀገራችን የስፖርት ትጥቅን ፋይዳ ከሜዳ ያስወጣ ነው።

🇪🇹 ባለብዙ ታሪክ እና ባህል ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያን የሚወክሉት ተጫዋቾች የሚለብሷቸዉ ልብሶች ልዩ ትርጉም እንዲኖራቸው ዋናው ስፖርት አድርጓል።

🔎 ተጨማሪ በምስሉ ላይ ይመልከቱ።

🌍 Made in Africa 🌍

Contact us!
📞 8289


Instagram | Facebook | TikTok  | X  |@wanawsportswear?si=TSJ9HZINs4MzMPj2' rel='nofollow'> @wanawsportswear?si=TSJ9HZINs4MzMPj2' rel='nofollow'>Youtube

🏅 ዋናው ወደፊት...

@wanawsportwear


ሮድሪጎ ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ ይርቃል ?

ብራዚላዊው የሪያል ማድሪድ የፊት መስመር ተጨዋች ሮድሪጎ የጡንቻ ጉዳት እንዳጋጠመው ይፋ ተደርጓል።

ሮድሪጎ ከጉዳቱ አገግሞ ወደ ሜዳ ለመመለስ እስከ ሀያ ቀናት ጊዜ ሊወስድበት እንደሚችል ተገልጿል።

ይህንንም ተከትሎ ሮድሪጎ ቅዳሜ የሚደረገውን የባርሴሎና ጨዋታ ጨምሮ ሪያል ማድሪድ በቀጣይ

- ከ ቫሌንሽያ
- ኤሲ ሚላን እና
- ኦሳሱና ጋር የሚያደርጋቸው ጨዋታዎች የሚያመልጡት ይሆናል።

ሮድሪጎ በቀጣይ የብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ እረፍት የብራዚል ብሔራዊ ቡድንን ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


የስፔን ፖሊስ አራት ደጋፊዎችን ማሰሩ ተገለፀ !

የስፔን ፖሊስ ከዘረኝነት ጥቃት ጋር በተያያዘ አራት የአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎችን ማሰሩ ተገልጿል።

ደጋፊዎቹ ከማድሪድ ደርቢ ጨዋታ በፊት በቪንሰስ ጁኒየር ላይ የዘረኝነት ጥቃት ለማድረስ በማህበራዊ ሚዲያዎች ዘመቻ አድርገዋል በሚል መጠርጠራቸው ተነግሯል።

ከጨዋታው በፊት የአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች በጨዋታው ወቅት ደጋፊዎች እንዳይለዩ ፊታቸውን ሸፍነው እንዲመጡ በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲጠይቁ ተስተውለው ነበር።

@Tikvahethsport          @Kidusyoftahe


“ በዩሮፓ ሊጉ ስኬታማ መሆን እንፈልጋለን “ ቴንሀግ

የማንችስተር ዩናይትዱ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ቡድናቸው ዛሬ ምሽት ከፌነርባቼ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን ገልፀዋል።

“ ፌነርባቼን ለመግጠም ዝግጁ ነን “ ያሉት ኤሪክ ቴንሀግ በስታዲየማቸው ያለውን ድባብ ለመጋፋጥም ተዘጋጅተናል ብለዋል።

“ ማንችስተር ዩናይትድ ጆዜ ሞሪንሆ ከለቀቁ ወዲህ የሀገር ውስጥ ዋንጫዎችን አሸንፏል ነገርግን በአውሮፓ መድረክ ማሸነፍ አልቻለም።“ ቴንሀግ

“ እኔና ሞሪንሆ በቅርብ አመታት ብዙ ዋንጫዎችን አሸንፈናል “ ሲሉ ያስታወሱት አሰልጣኙ ነገርግን ትችቶች እንዳይቀርቡብህ በየአመቱ ራስህን ማስመስከር አለብህ ብለዋል።

አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ አክለውም በዚህ አመት በዩሮፓ ሊጉ ስኬታማ መሆን እንፈልጋለን በማለት ተናግረዋል።

@Tikvahethsport          @Kidusyoftahe


አቡበከር ናስር በይፋ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድን ተቀላቀለ !

ኢትዮጵያዊው የፊት መስመር አጥቂ አቡበከር ናስር የደቡብ አፍሪካውን ክለብ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ መቀላቀሉን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

አቡበከር ናስር ከቀድሞ ክለቡ ማሜሎዲ ሰንዳውንስ ጋር መለያየቱን በቅርቡ የክለቡ ዋና አሰልጣኝ ማንቆባ ማንጊቲ መግለፃቸው አይዘነጋም።

ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ አሁን ላይ አቡበከር ናስርን ለአንድ የውድድር አመት ማስፈረሙን በይፋ አስታውቋል።

የአቡበከር ናስሩ ክለብ ሱፐር ስፖርት ዩናይትድ በሊጉ በአራት ነጥቦች አስራ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ግልጽ ሽንፈት ነው ሰበብ አያስፈልግም “ ኮምፓኒ

የባየር ሙኒክ ዋና አሰልጣኝ ቪንሴንት ኮምፓኒ ምሽት የደረሰባቸውን ሽንፈት “ ግልጽ የሆነ ሽንፈት “ ሲሉ ገልፀውታል።

ባርሴሎና ከአውሮፓ ምርጥ ክለቦች አንዱ መሆኑን ያስረዱት ኮምፒኒ “ ስለዚህ ውጤቱ ያልተጠበቀ አይደለም ለባርሴሎና እንኳን ደስ አላችሁ “ ብለዋል።

ለሽንፈቱ “ ምንም ስበብ አያስፈልግም “ ያሉት አሰልጣኙ “ ተሸንፈናል ግልጽ ሽንፈት ነው “ ሲሉ በቀጣይ ከዚህ መማር አለብን በማለት ተናግረዋል።

ቶማስ ሙለር በበኩሉ “ ለባርሴሎና የሚገባው ድል ነው እንኳን ደስ አላችሁ ለሀንሲ ፍሊክ ተደስቻለሁ ለእኛ ግን በጣም አዝኛለሁ “ ሲል ተደምጧል።

@Tikvahethsport          @Kidusyoftahe


“ የምሽቱ ጨዋታ በቀል ነው “ ራፊንሀ

ባየር ሙኒክ ላይ ሀትሪክ መስራት የቻለው ራፊንሀ ውጤቱ ባርሴሎና ከባየር ሙኒክ ጋር ለነበረው መጥፎ ውጤት በቀል ነው በማለት ተናግሯል።

“ ጨዋታው ከእነሱ ጋር ለነበረን መጥፎ ውጤት በቀል ነበር “ ያለው ራፊንሀ በሰዓቱ እዚህ ባልሆንም እንደ ደጋፊ ይሰማኛል በማለት ተናግሯል።

“ ጥሩ ጨዋታ ተጫውተናል የምንፈልገውን ነገር አሳክተን ወጥተናል አሁን ሙሉ ትኩረታችን የቅዳሜው ኤል ክላሲኮ ላይ ነው።" ራፊንሀ

“ ምርጡ አቋሜን ገና አላሳየሁም እንደ ቡድን ለማያምኑን ሁሉ ማንነታችንን ለማሳየት እየሰራን እንገኛለን “ ሲል ራፊንሀ ተናግሯል።

@Tikvahethsport          @Kidusyoftahe


“ ሀላንድ ከሌለ ስቶንስ አጥቂ ይሆናል “ ጋርዲዮላ

የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ቡድናቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተጫወተ ያለበትን መንገድ “ ወድጄዋለሁ “ ብለዋል።

በግብ አስቆጣሪነቱ ስለቀጠለው ተከላካዩ ጆን ስቶንስ ያነሱት ፔፕ ጋርዲዮላ “ ቀጣይ ሀላንድ ከሌለ ስቶንስን ዘጠኝ ቁጥር አጫውተዋለሁ “ ብለዋል።

“ እንደ ኤርሊንግ ሀላንድ አይነት ተጨዋች ማግኘት ለእኔ ክብር ነው እሱ የማይታመን ተጨዋች ነው “ ፔፕ ጋርዲዮላ።

በቀጣይ ሰኞ ባሎን ዶሩን ማን ሊያሸንፍ ይችላል የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ፔፕ ጋርዲዮላ “ ምንም ግድ የለኝም “ ሲሉ መልሰዋል።

@Tikvahethsport          @Kidusyoftahe


“ አርሰናልን ለማሸነፍ ሁሉንም እንሰጣለን “ አርኔ ስሎት

የሊቨርፑሉ ዋና አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ቡድናቸው በምሽቱ ጨዋታ በጣም አስፈላጊ ሶስት ነጥቦችን ማሳካቱን ገልጸዋል።

“ አስቸጋሪ ጨዋታ ነበር “ ያሉት አርኔ ስሎት “ ሌፕዚግ ጠንካራ ቡድን ነው በጣም አስፈላጊ የሆነ ሶስት ነጥብ ነው ያሳካነው በማለት ተናግረዋል።

“ በቀጣይ ከአርሰናል ጋር የምናደርገውን ጨዋታ ለማሸነፍ ያለንን ሁሉ እንሰጣለን “ ሲሉ አሰልጣኝ አርኔ ስሎት ገልጸዋል።

" ኤምሬትስ ላይ መጫወት ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሆነ እናውቃለን ነገርግን ቼልሲ ፣ ዩናይትድ እና ሚላን ላይ እንዳደረግነው እናደርጋለን።" አርኔ ስሎት

ሊቨርፑል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሜዳው ውጪ ያደረጋቸውን የውድድር አመቱ የመጀመሪያ ስድስት ጨዋታዎች አሸንፏል።

በአሰልጣኝ አርኔ ስሎት የሚመራው ሊቨርፑል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከመጀመሪያ አስራ ሁለት ጨዋታዎች አስራ አንዱን በአሸናፊነት መወጣት ችሏል።

@Tikvahethsport          @Kidusyoftahe


የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ማን ይሆናል ?

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሶስተኛ ጨዋታዎች ባለፉት ሁለት ቀናት ተካሂደው መጠናቀቃቸውን ተከትሎ የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች አራት እጩዎች ይፋ ተደርገዋል።

በዚህም መሰረት :-

⏩ ቪንሰስ ጁኒየር

⏩ ራፊንሀ

⏩ ሚናሚኖ ( ሞናኮ )

⏩ ሬንደርስ ( ኤሲ ሚላን ) በእጩነት መቅረብ ችለዋል።

የሳምንቱ ምርጥ ተጨዋች ማን ነው ?

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


Forward from: HEY Online Market
•iMac (M1 Chip)

2022 Year
24’ Retina Display
512 GB Storage
8GB RAM

290,000 birr

0953964175 @heymobile

@heyonlinemarket


#UCL

በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ መርሐ ግብር ባርሴሎና ባየር ሙኒክን 4ለ1 ፣ ማንችስተር ሲቲ ስፓርታ ፕራግን 5ለ0 እንዲሁም ሊቨርፑል ሌፕዚግን 1ለ0 ማሸነፍ ችለዋል።

የባርሴሎናን የማሸነፊያ ግቦች ራፊንሀ 3x እና ሌዋንዶውስኪ ሲያስቆጥሩ ለባየር ሙኒክ ሀሪ ኬን ከመረብ አሳርፏል።

ኤርሊንግ ሀላንድ 2x ፣ ጆን ስቶንስ ፣ ፊል ፎደን እና ማቲውስ ኑኔስ የማንችስተር ሲቲን ግቦች ያስቆጠሩ ተጨዋቾች ናቸው።

ለሊቨርፑል የማሸነፊያ ግቧን ዳርዊን ኑኔዝ አስቆጥሯል።

ሀሪ ኬን በዘንድሮው የውድድር ዘመን ባደረጋቸው አስራ አንድ ጨዋታዎች አስራ አራት ግቦችን አስቆጥሮ ስድስት አመቻችቶ ማቀበል ችሏል።

ኤርሊንግ ሀላንድ በአርባ ሁለት የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች አርባ አራተኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

ራፊንሀ ከሮናልዶ ፣ አጉዌሮ እና ሮይ ማካይ በመቀጠል በሻምፒየንስ ሊጉ ባየር ሙኒክ ላይ ሀትሪክ የሰራ አራተኛው ተጨዋች መሆን ችሏል።

ማንችስተር ሲቲ ሀያ ስድስት ተከታታይ የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች ባለመሸነፍ በማንችስተር ዩናይትድ ተይዞ የነበረውን ሪከርድ መስበር ችለዋል።

በሌሎች ጨዋታዎች

- ኢንተር ሚላን ያንግ ቦይስን 1ለ0

- ሊል አትሌቲኮ ማድሪድን 3ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

*የሻምፒየንስ ሊግ የዛሬ ምሽት ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዡ በምስሉ ላይ ተያይዟል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


88 ’

ማንችስተር ሲቲ 5-0 ስፓርታ ፕራግ

⚽ ፎደን
⚽⚽ ሀላንድ
⚽ ስቶንስ
⚽ ኑኔስ

ባርሴሎና 4 - 1 ባየር ሙኒክ

⚽⚽⚽ ራፊንሀ         ⚽ ሀሪ ኬን
⚽ ሌዋንዶውስኪ

ሌፕዚግ 0-1 ሊቨርፑል

             ⚽ ኑኔዝ

አትሌቲኮ ማድሪድ 1-2 ሊል

⚽ አልቫሬዝ        ⚽ ዜግሮቫ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


70 ’

ማንችስተር ሲቲ 4-0 ስፓርታ ፕራግ

⚽ ፎደን
⚽⚽ ሀላንድ
⚽ ስቶንስ

ባርሴሎና 4 - 1 ባየር ሙኒክ

⚽⚽⚽ ራፊንሀ         ⚽ ሀሪ ኬን
⚽ ሌዋንዶውስኪ

ሌፕዚግ 0-1 ሊቨርፑል

             ⚽ ኑኔዝ

አትሌቲኮ ማድሪድ 1-1 ሊል

⚽ አልቫሬዝ        ⚽ ዜግሮቫ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


65 ’

ማንችስተር ሲቲ 3-0 ስፓርታ ፕራግ

⚽ ፎደን
⚽ ሀላንድ
⚽ ስቶንስ

ባርሴሎና 4 - 1 ባየር ሙኒክ

⚽⚽⚽ ራፊንሀ         ⚽ ሀሪ ኬን
⚽ ሌዋንዶውስኪ

ሌፕዚግ 0-1 ሊቨርፑል

             ⚽ ኑኔዝ

አትሌቲኮ ማድሪድ 1-1 ሊል

⚽ አልቫሬዝ ⚽ ዜግሮቫ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


59 ’

ባርሴሎና 4 - 1 ባየር ሙኒክ

⚽⚽⚽ ራፊንሀ         ⚽ ሀሪ ኬን
⚽ ሌዋንዶውስኪ

ሌፕዚግ 0-1 ሊቨርፑል

             ⚽ ኑኔዝ

ማንችስተር ሲቲ 2-0 ስፓርታ ፕራግ

⚽ ፎደን
⚽ ሀላንድ

አትሌቲኮ ማድሪድ 1-0 ሊል

⚽ አልቫሬዝ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


#TikvahGoal

በአሁን ሰዓት እየተካሄዱ የሚገኙ ጨዋታዎች አጫጭር ቪዲዮች እና ግቦችን በጎል ቻናላችን መከታተል ይችላሉ።

የጎል ቻናላችን 👉 https://t.me/+rbdEU4UaEdQxYWFk

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


#እረፍት

ባርሴሎና 3 - 1 ባየር ሙኒክ

⚽ ራፊንሀ         ⚽ ሀሪ ኬን
⚽ ሌዋንዶውስኪ
⚽ ራፊንሀ

ሌፕዚግ 0-1 ሊቨርፑል

             ⚽ ኑኔዝ

ማንችስተር ሲቲ 1-0 ስፓርታ ፕራግ

⚽ ፎደን

አትሌቲኮ ማድሪድ 1-0 ሊል

⚽ አልቫሬዝ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


38 '

ባርሴሎና 2 - 1 ባየር ሙኒክ

⚽ ራፊንሀ         ⚽ ሀሪ ኬን
⚽ ሌዋንዶውስኪ

ሌፕዚግ 0-1 ሊቨርፑል

             ⚽ ኑኔዝ

ማንችስተር ሲቲ 1-0 ስፓርታ ፕራግ

⚽ ፎደን

አትሌቲኮ ማድሪድ 1-0 ሊል

⚽ አልቫሬዝ

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe

20 last posts shown.