ዩናይትድ ከኤፌ ካፕ ውድድር ተሰናበተ !
ፉልሀም ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ያደረገውን የኤፌ ካፕ አምስተኛ ዙር ጨዋታ በመለያ ምት 4ለ3 በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን መቀላቀል ችለዋል።
ሁለቱ ክለቦች መደበኛውን የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 1ለ1 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቀዋል።
ግቦችን ለማንችስተር ዩናይትድ ብሩኖ ፈርናንዴዝ እንዲሁም ለፉልሀም ካልቪን ባሴይ ማስቆጠር ችለዋል።
በመለያ ምት በማንችስተር ዩናይትድ በኩል ቪክቶር ሊንድሎፍ እና ዚርኪዜ ሳይጠቀሙ ቀርተዋል።
ብሩኖ ፈርናንዴዝ በውድድር ዘመኑ ከየትኛውም የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋች በበለጠ ሀያ አራት የግብ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል።
የኤፌ ካፕ ሩብ ፍፃሜ ተጋጣሚዎች ከደቂቃዎች በኋላ በሚደረግ የእጣ ማውጣት ስነስርዓት የሚለዩ ይሆናል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe